የግብርና የምርምር ማእከላት አመታዊ ግብር እንዲከፍሉ ተጠየቁ።
በሀገሪቱ የሚገኙ የግብርና ምርምር ተቋማት ግብርናን በምርምር ለመደገፍ የተቋቋሙ ቢሆንም ትኩረት እንዳልተሰጣቸዉ ይነሳል።
የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኘሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ፤ በአንዳንድ የምርምር ማእከላት ለትርፍ እንደተቋቋመ ተቋሙ ታይተዉ ግብር እንዲከፍሉ ተጠይቀዉ እንደነበር አንስተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ በምሳሌነትም በሰበታ የአሳ ምርምር ማእከል 1.3 ሚሊየን ብር ለአመታዊ ግብር ክፈሉ መባሉን ለጣቢያችን ገልፀዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች ይገኛሉ በተባሉ የምርምር ማእከላት ላይ የዚህ የግብር ክፈሉ አዝማሚያዎች መታየታቸውን ተናግረዋል።
የግብር ክፈሉ ጥያቄዎቹ ከህገመንግስታዊ ድንጋጌ ዉጪ ነዉ የሚሉት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር የግብርና ምርምር ማእከላቱ ላይ የተጣለባቸዉን አመታዊ ግብር አግባብነት የማይኖረዉ ነዉ ብለዋል።
ይህንን ለማስቆም ከክልል መስተዳድሮች ጋር ንግግሮች መደረጋቸዉን አንስተዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
በሀገሪቱ የሚገኙ የግብርና ምርምር ተቋማት ግብርናን በምርምር ለመደገፍ የተቋቋሙ ቢሆንም ትኩረት እንዳልተሰጣቸዉ ይነሳል።
የኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ኘሮፌሰር ንጉሴ ደቻሳ፤ በአንዳንድ የምርምር ማእከላት ለትርፍ እንደተቋቋመ ተቋሙ ታይተዉ ግብር እንዲከፍሉ ተጠይቀዉ እንደነበር አንስተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ በምሳሌነትም በሰበታ የአሳ ምርምር ማእከል 1.3 ሚሊየን ብር ለአመታዊ ግብር ክፈሉ መባሉን ለጣቢያችን ገልፀዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች ይገኛሉ በተባሉ የምርምር ማእከላት ላይ የዚህ የግብር ክፈሉ አዝማሚያዎች መታየታቸውን ተናግረዋል።
የግብር ክፈሉ ጥያቄዎቹ ከህገመንግስታዊ ድንጋጌ ዉጪ ነዉ የሚሉት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር የግብርና ምርምር ማእከላቱ ላይ የተጣለባቸዉን አመታዊ ግብር አግባብነት የማይኖረዉ ነዉ ብለዋል።
ይህንን ለማስቆም ከክልል መስተዳድሮች ጋር ንግግሮች መደረጋቸዉን አንስተዋል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1