✞ የኢዮብ መልሱ ✞
እንደምነህ ቢሉት ዘመዶች ከድተውት
ሚስቱ ትታው ሄዳ ልጆች ሞተውበት
ዓይኖቹ በምሬት እንባ አላፈሰሱ
እግዚአብሔር ይመስገን [፪] ነበር የኢዮብ መልሱ
በሕይወት ገጥሞት የበረታ ፅልመት
በአንድ ቀን ሲነጠቅ ልጆችና ንብረት
አካሉ በቁስል ተይዞ በጠና
ኢዮብ እንዴት ቻለ ለአምላኩ ምስጋና
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በሰጠበት መንደር ሲቆም ለልመና
ሚስቱ ሙት ስትለው ጌታን እርገም እና
የስንፍናን ነገር አይሰማም ጆሮዬ
ይክሰኛል እርሱ ይችላል ጌታዬ
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ቅን ነገር መናገር ለአፌ ከቸገረኝ
አምላኬ እንዳያዝን ምነው ዝም በአልኩኝ
ልሳኔ እንዳይጠራ ሞት እና መከራ
ለምስጋና ቆሜ ነገን ዛሬ ልሥራ
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
እግዚአብሔር ይመስገን ቢጎድልም ቢሞላም
ለዓይኔ ሽፋሽፍት እንቅልፍ እንኳን ባጣም
ብዙ እንደነበረው ትናንትና ደጄ
ክፉውንም ደግሞ ይቀበላል እጄ
መዝሙር|
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
እንደምነህ ቢሉት ዘመዶች ከድተውት
ሚስቱ ትታው ሄዳ ልጆች ሞተውበት
ዓይኖቹ በምሬት እንባ አላፈሰሱ
እግዚአብሔር ይመስገን [፪] ነበር የኢዮብ መልሱ
በሕይወት ገጥሞት የበረታ ፅልመት
በአንድ ቀን ሲነጠቅ ልጆችና ንብረት
አካሉ በቁስል ተይዞ በጠና
ኢዮብ እንዴት ቻለ ለአምላኩ ምስጋና
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
በሰጠበት መንደር ሲቆም ለልመና
ሚስቱ ሙት ስትለው ጌታን እርገም እና
የስንፍናን ነገር አይሰማም ጆሮዬ
ይክሰኛል እርሱ ይችላል ጌታዬ
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
ቅን ነገር መናገር ለአፌ ከቸገረኝ
አምላኬ እንዳያዝን ምነው ዝም በአልኩኝ
ልሳኔ እንዳይጠራ ሞት እና መከራ
ለምስጋና ቆሜ ነገን ዛሬ ልሥራ
አዝ▸▸▸▸▸▸▸▸▸▸►
እግዚአብሔር ይመስገን ቢጎድልም ቢሞላም
ለዓይኔ ሽፋሽፍት እንቅልፍ እንኳን ባጣም
ብዙ እንደነበረው ትናንትና ደጄ
ክፉውንም ደግሞ ይቀበላል እጄ
መዝሙር|
ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
https://t.me/yemezmur_gexem
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥