ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፮

✞በዓለ ቅዱሳን፦

✿አቡሊዲስ ዘሮሜ (መምህረ ኲሉ ዓለም)
❀ማርያም ቅድስት (እንተ ዕፍረት)
❀አቡቂር ወዮሐንስ (ሰማዕታት)
❀ቴዎድራ፥ ቴዎፍና፥ ወቴዎዶክስያ (ደናግል)
❀አትናስያ ቡርክት (እሞን)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn


"" ዝክረ ቅዱሳን - የካቲት ፭ ""
ስንክሳር የካቲት 6

በቅዱሳን ስም መዘከር ማለት

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት


በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn


✝✞✝ እንኳን አደረሳችሁ ✝✞¥

""ሰላም #ለአብራኪከ እለ አውተራ ስግደተ፡፡
እንዘ የዓርጋ ላዕለ ፡ ወእንዘ ይወርዳ ታሕተ፡፡
ጊዜ ተቀባዕከ #ክርስቶስ #ዘአልባስጥሮስ ዕፍረተ፡፡
ገብርከሰ እምፈተውኩ አሜሃ ዕለተ፡፡
#ማርያም ትኩነኒ እህተ፡፡"" (መልክዐ ኢየሱስ)

"" በኀበ ተሠብከ ወንጌልየ ለዓለም በመክብቡ፡፡
ዛቲ ብእሲት ዘገብረት ያንብቡ፡፡ "" (ወንጌለ ማቴዎስ - አርኬ)

✿ከቅድስት እናታችን #ማርያም_እንተ_ዕፍረት በረከት ያሳትፈን፡፡✿
ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር

በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn






✞✞✞ May the God of the Saints grant us repentance like St. Mary and the mystery of being holy from Abba Apolidus (Hippolytus).✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 6th of Yekatit
1. St. Mary the Perfume Bearer (Mary the Repentant)
2. St. Apolidus (Hippolytus) the Teacher of the World (Writer of many spiritual works, an archbishop and a martyr)
3. St. Abakir and John (Martyrs)
4. St. Athanasia and her 3 martyr children (Theodora, Theopisti (Theophana) and Theodosia)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. Holy Debre Quosquam
2. Our Father Adam and our Mother Eve
3. Our Father Noah and our Mother Haikel
4. St. Elijah Prophet
5. St. Basil of Caesarea
6. St. Joseph the Carpenter
7. St. Salome
8. Abba Arke Selus
9. Abba Tsige Dingel
10. St. Arsema (Hripsime), Virgin

✞✞✞ “My head with oil thou didst not anoint: but this woman hath anointed my feet with ointment. Wherefore I say unto thee, Her sins, which are many, are forgiven; for she loved much: but to whom little is forgiven, the same loveth little. And he said unto her, Thy sins are forgiven. And they that sat at meat with him began to say within themselves, Who is this that forgiveth sins also? And he said to the woman, Thy faith hath saved thee; go in peace.”✞✞✞
Luke 7:46-50

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


Memhir Esuendale:
#Feasts of #Yekatit_6

✞✞✞On this day we commemorate our mother Saint Mary the Perfume Bearer and Saint Apolidus (Hippolytus) of Rome✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Mary the Perfume Bearer (Mary the Repentant)✞✞✞
=>Saint Mary the Perfume Bearer, as the Holy Bible tells us, washed the feet of the Holy Savior in the house of Simeon with her tears. And our Lord Jesus Christ forgave her and added her to the 36 Holy Women. (Luke 7:36-50)

✞To have the full story of this Saint one can read
1. The Commentary of the Gospel
2. The Miracles of Jesus
3. The Synaxarium and
4. The Book of the Funeral Ritual (Metsehafe Genzet)

✞Mary, the Perfume Bearer, lived during the time of the ministry of our Lord Jesus Christ and was very beautiful. However, beauty becoming the source of goodness has not been seen.

✞Our world has had many women who lapsed and made others lapse because of their good looks. It is very sad to see and hear, from Cleopatra to the self-titled “Models” of our days, making the gift of God a delight for Satan and a road to Gehenna.

✞And on the other side, when we think of the saints like Arsema (Hripsime), Thecla, Tecla, Marina, Tatus (Tatia), Irene, Eirene, Athanasia, Sophia, Hilaria . . ., who chose to be heavenly brides by shunning their acclaimed beauty, we are delighted. In like manner, we know today of many of our mothers (sisters) who chose and are moving in a similar good path whom God knows.

✞St. Mary when Satan compelled her to do evil by the beauty she was given, she agreed and strode to become his trap. And for years she took men who were of lustful eyes and of weak hearts captive to the way of sin.

✞And from her high regard for her beauty she used to look time and time again at her countenance in the mirror. And God Who has a day to call everyone to salvation (if anyone notices), sent His call to Mary. However, His call was not through a sermon, a hymn or a book.

✞St. Mary as usual stood before a mirror and looking at her hair, forehead, eyes, nose, teeth … started admiring herself. But immediately the Holy Spirit gave her a thought that said this body would rot in the soil and corrupt and she became very sad. And not to lose hope, she heard the news of our Lord Jesus Christ.
 
✞And because she had to choose, she decided to go from death to life and from darkness to light. And she prepared 3 gifts that she would offer before her God. And because Satan did not want to lose her, he created many obstacles on her way so that she would not reach to Christ. But as her decision was true, she went forth to her Creator shaming Satan.

✞And the gate keepers of Simeon the leper could not keep her back as well. She entered and sacrificed all that she had to our Savior. She offered,
1. Her tears from within
2. Her hair from her body and
3. An expensive perfume from her property.

✞And because she loved much, her sin was forgiven and she became our holy mother. And after serving with the Apostles for many years, she passed away on this day.

✞✞✞Saint Apolidus (Hippolytus) the Teacher of the Whole World✞✞✞
=>The teacher of the world
*wrote many works and homilies
*is a pillar of the Church
*wrote 38 statutes
*was one who struggled for the Upright Faith
*accepted bitter death in gladness
*was the Archbishop of Old Rome
*and was a father who was like the Apostles.

✞This star who lived at the end of the 2nd century was renounced by [Roman] Catholics (as they considered him as the first antipope or a priest in Rome or as a Bishop of Porto). Though they say, “There was no bishop called Apolidus”, their reason is of Satan. The world knows that they said this because 250 years before they changed their faith, he taught of the one nature [of Christ].

✞Our father St. Apolidus (Hippolytus) was killed (martyred) on Yekatit 5 (February 12), and his body was found on Yekatit 6 (February 13), on this day.




†✝† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †✝†

††† እንኩዋን ለእናታችን "ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት" እና "ቅዱስ አቡሊዲስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

+*" ቅድስት ማርያም "*+

=>ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚለን በስምዖን ቤት የመድኃኔ ዓለምን እግር በእንባዋ አጥባለች:: በፀጉሯም አብሳ የ300 ብር ሽቱ ቀብታዋለች:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የቀደመ ኀጢአቷን ይቅር ብሎ ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት ደምሯታል:: (ሉቃ. 7:36-50)

+ስለዚህች ቅድስት ሙሉ ታሪክ:-
1.ትርጉዋሜ ወንጌልን
2.ተአምረ ኢየሱስን
3.ስንክሳርን እና
4.መጽሐፈ ግንዘትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል::

+እንት ዕፍረት (ባለ ሽቱዋ ማለት ነው) ማርያም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን (በዘመነ ስብከቱ) የነበረችና ይህ ቀረሽ የማይሏት ቆንጆ ሴት ነበረች:: ግን መልክ የመልካም ነገሮች ምንጭ ሲሆን አይታይም::

+በመልካቸው ማማር የጠፉና ያጠፉ ብዙ ሴቶችን ዓለማችን አስተናግዳለች:: ከክሊዎፓትራ እስከ ዘመናችን "ሞዴል" ነን ባዮች : እግዚአብሔር የሰጣቸውን ጸጋ የሰይጣን መደሰቻ : የገሃነም መንገድ አድርገውት ማየት (መስማት) እጅግ ያሳዝናል::

+በአንጻሩ ደግሞ ብዙዎችን ያስደመመ መልካቸውን ንቀው : ሰማያዊ ሙሽርነትን የመረጡትን ቅዱሳቱን:- አርሴማን : ቴክላን : ጤቅላን : መሪናን : ጣጡስን : ሔራኒን : ኢራኒን : አትናስያን : ሶፍያን : ኢላርያን . . . ስናስብ ደስ ይለናል:: ዛሬም ጌታ በሚያውቀው ብዙ እናቶቻችን (እህቶቻችንም) ተመሳሳዩን በጐ ጐዳና መርጠው እየተጉዋዙ መሆኑን እናውቃለን::

+ቅድስት ማርያምም ከፈጣሪዋ በተሰጣት ቁንጅና ክፋትን ትሠራ ዘንድ ሰይጣን ሲያገብራት "እሺ" ብላ የእሱ ወጥመድ ልትሆን ተራመደች:: ለዘመናትም ዓይነ-ዘማ : ልበ-ስስ የሆኑ ወንዶችን ወደ ኃጢአት ጐዳና ማረከች::

+ለመልኩዋ ከነበራች ስስት የተነሳም ቶሎ ቶሎ ራሷን በመጽሔት (መስታውት ማለት ነው) ትመለከት ነበር:: መቼም አምላካችን ለሁሉም የመዳን ቀን ጥሪ አለውና (የሚያስተውለው ቢገኝ) ለማርያም ጥሪውን ላከላት:: ጥሪው ግን በስብከት : በመዝሙር : በመጽሐፍ . . . አልነበረም::

+እንዳስለመደች ውበቷን ለመመልከት መስታውት ፊት ቆማ የራሷን ጸጉር : ግንባር : ዐይን : አፍንጫ : ጥርስ . . . እየተመለከተች ተደመመች:: ወዲያው ግን ይህ አካል አፈር እንደሚበላው የሚያስብ ልቡና መንፈስ ቅዱስ አምጥቶባት በጣም አዘነች:: የመኖር ተስፋዋ እንዳይቆረጥ ደግሞ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ዜና ሰማች::

+መወሰን ነበረባትና ከሞት ወደ ሕይወት : ከጨለማ ወደ ብርሃን ልትሔድ ቆረጠች:: በአምላኩዋ ፊት የሚቀርቡም 3 ስጦታዎችን አዘጋጀች:: ሰይጣን ሊያጣት አልፈለገምና ወደ ክርስቶስ እንዳትደርስስ ብዙ መሰናክልን ፈጠረባት:: ግን ውሳኔዋ የእውነት ነበርና እያሳፈረችው ወደ አምላኩዋ ገሰገሰች::

+የስምዖን ዘለምጽ በረኞችም ሊያስቀሰሯት አልተቻላቸውም:: ወደ ውስጥ ዘልቃ የያዘችውን ሁሉ ለመድኃኒታችን ሰዋች::
1.ከውስጧ እንባዋን:
2.ከአካሏ ጸጉሯን:
3.ከንብረቷ ውድ የሆነውን ሽቱ አቀረበች::

+ብዙ ወዳለችና ብዙ ኃጢአቷ ተሠርዮ ቅድስት እናታችን ሆነች:: ብዙ አዝማናትን ከሐዋርያት ጋር አገልግላም በዚህች ቀን ዐርፋለች::

+*" ቅዱስ አቡሊዲስ መምህረ ኩሉ ዓለም "*+

=>የዓለም ሁሉ መምህር:
¤ባለ ብዙ ድርሳንና ተግሣጽ:
¤የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ:
¤38 ሕግጋትን የደነገገ:
¤ስለ ቀናች እምነት የተጋደለ:
¤መራራ ሞትን በደስታ የተቀበለ:
¤የቀደመችዋ ሮም ሊቀ ዻዻሳት የነበረና:
¤ሐዋርያትን የመሰለ አባት ነው::

+በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ያበራው ይሀን ኮከብ ካቶሊካውያን ክደውታል:: እነርሱ "አቡሊዲስ የሚባል ዻዻስ አልነበረም" ቢሉም ምክንያታቸው ግን ከሰይጣን ነው:: ሃይማኖታቸውን ከመለወጣቸው 250 ዓመታት በፊት ስለተናገረባቸውና አንድ ባሕርይን ስላስተማረ መሆኑን ዓለም ያውቃል::

+አባታችን ቅዱስ አቡሊዲስ የተገደለ የካቲት 5 ሲሆን የካቲት 6 ሥጋው የተገኘበት ነው::

=>አምላከ ቅዱሳን ከቅድስት ማርያም ንስሃዋን : ከአባ አቡሊዲስ ምሥጢረ ቅድስናውን ያድለን::

=>የካቲት 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ማርያም እንተ ዕፍረት
2.የዓለም ኁሉ መምሕር ቅዱስ አቡሊዲስ (ብዙ መንፈሳዊ ድርሳናትን የደረሰ ሊቀ ዻዻስና ሰማዕት)
3.ቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ (ሰማዕታት)
4.ቅድስት አትናስያና 3ቱ ሰማዕታት ልጆቿ (ቴዎድራ : ቴዎፍናና ቴዎዶክስያ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም
2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን
3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል
4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ
5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ
7.ቅድስት ሰሎሜ
8.አባ አርከ ሥሉስ
9.አባ ጽጌ ድንግል
10.ቅድስት አርሴማ ድንግል

=>ከበረከተ ቅዱሳን ይክፈለን::

=>+"+ . . . አንተ ራሴን ዘይት አልቀባኸኝም:: እርሷ ግን እግሬን ሽቱ ቀባች:: ስለዚህ እልሃለሁ : እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ኃጢአቷ ተሰርዮላታል:: ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል:: እርስዋንም:- 'ኃጢአትሽ ተሰርዮልሻል' አላት:: ከእርሱም ጋር በማዕድ ተቀምጠው የነበሩት በልባቸው:- 'ኃጢአትን እንኩዋ የሚያስተሰርይ ይህ ማነው' ይሉ ጀመር:: ሴቲቱንም:- 'እምነትሽ አድኖሻል: በሰላም ሒጂ' አላት:: +"+ (ሉቃ. 7:46)

>


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፭

✝ቅድስት ጾመ ነነዌ

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ዕብሎይ ገዳማዊ (ኖላዌ አባግዕ)
✿ብሶይ ጴጥሮስ (ዘሀገረ አክሚም)
✿፵ወ፱ቱ አዕሩገ ገዳም (ዘአስቄጥስ)
✿ኖብ ጻድቅ (መነሳንሱ ዘወርቅ)
✿አቡሊዲስ ዘሮሜ
✿ቡላ ወአሞኒ
✿ሙስያ/አበያ (እመ አባ ዕብሎይ)
✿አክርጵዮስ ሊቀ ጳጳሳት
✿ዮናስ ነቢይ (ወልደ አማቴ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn








✞God heard and healed him quickly. And Abba Bishoy according to his word repented fully in his heart and took up asceticism. And in the Monastery of Scetes (Egypt) when he lived for 38 years, he did not eat prepared meal or slept on a comfortable bed or bedding.

✞And to penalize his body he did not eat nor drink for 30 days. And in his days, he did not also see the appearance of a woman. And the Lord, Who loves repentance, increased His grace upon him and he wrote many works.  And what was astounding was that because of his humility and holiness, he used to see the sin of each man.

✞Our holy father Bishoy-Peter lived in repentance and holiness in such a manner and passed away on this day and was buried in his monastery. And he received the wages for his labors from the true judge our Savior Jesus Christ, Who knows no bias.

✞✞✞ May the God of the Saints not deprive us of a time for repentance and an age for gladness. And may He grant us from the glory of the Saints. Amen!

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 5th of Yekatit
1. Abba Apollo the Ascetic
2. St. Abba Bishoy the Righteous
3. Abba Agrippinus the Archbishop
4. The “49” Elder Martyrs (Translocation of their relics)
5. St. Amani (Hamai) and his wife St. Eyse (Isa)/Musia (Parents of the Great Abba Apollo)
6. Abba Abanoub the Righteous (who had a golden hand fan)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Peter the Arch-Apostle
2. St. Paul the Apostle
3. Abune Gebre Menfes Qidus
4. St. Yohani the Ethiopian
5. St. Amoni of Nah(i)so

✞✞✞May God bless us with their blessings.

✞✞✞ “What man of you, having an hundred sheep, if he lose one of them, doth not leave the ninety and nine in the wilderness, and go after that which is lost, until he find it? And when he hath found it, he layeth it on his shoulders, rejoicing. And when he cometh home, he calleth together his friends and neighbours, saying unto them, Rejoice with me; for I have found my sheep which was lost. I say unto you, that likewise joy shall be in heaven over one sinner that repenteth, more than over ninety and nine just persons, which need no repentance.”
Luke 15:4-7

✞✞✞ Praise be to God, to His Virgin Mother and to the honorable Cross. Amen✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)


ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ):
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Yekatit_5

✞✞✞On this day we commemorate Saint Agrippinus, Abba Pishoi/Bishoy (Peter) and Saint Apollo✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Agrippinus✞✞✞
=>On this day departed the Archbishop of Alexandria the honorable father St. Agrippinus. He was the tenth Archbishop of Alexandria. This father feared God and was pure.

✞He served in Alexandria as a priest. And when his predecessor Archbishop Cladianus passed away, the people of Alexandria and the Episcopes chose and appointed him as Archbishop on the See of the Evangelist St. Mark.

✞Thereafter, he went on a righteous path as the Apostles did. He taught the Faith of God, His law which is life, read and exegeted to the people the Scriptures and kept his flock. And he always looked for them. Except from his daily meal, and the cloth he had on to keep him from the sun’s heat and the cold, he did not accumulate even half of or one gold Dinar.

✞He departed in peace after living in such a strife serving our Lord for 12 years.

✞✞✞Saint Apollo✞✞✞
=>Abba Apollo lived for 40 years, in his earlier life, in sin and when God called him for repentance, he said “okay” and lived for 40 years more in compunction. He struggled in the desert. His tears used to fall like a torrent. And he was a Holy Father that was victorious over the demons and was able to bear fruits of virtue. And God gave him many assurances [to those who plea in his name].

✞”Forgive me, as there is no servant without sin and as there is no Lord without mercy!” was Abba Apollo’s prayer of repentance.

✞✞✞ Abba Pishoi/Bishoy (Peter)✞✞✞
=>Pishoi (Bishoy) is a frequented name for Saints in Church history. Particularly, in the land of Egypt, martyrs and the righteous were called by this name.  And one of these Saints, Abba Bishoy (sometimes called Abba Peter), was the fruit of the Era of the Righteous.

✞The Church is the abode of the Saints. Which means those who have separated themselves for Christ abide in Her. These people might come from different paths and identities. But at least because they are cleansed by repentance, that becomes a huge basis for them to enter into the holy communion/unity.

✞The Saints are seen as some being chosen from their mothers’ wombs and others as those who have returned from sin. And what is delightful is that after they have repented, because they have struggled with all their heart, they are topped in mystical crowns.

✞Abba Bishoy-Peter is also one of the fathers who have returned from sin and became saints. In the land of Egypt, the Saint was a recognized bandit, adulterer and his wickedness was known. And when he was not able for many years to detach himself from his evil deeds, God sent him His call [to repentance]. 
  
✞As God’s call comes in various ways, He sent the Saint an illness. Though we like it or not, sickness is a good means which makes one closer to God. Today also, after we play around and get broken, get sick and find no solution from the doctors, we come to God (the holy healing springs). May God be praised for this, His wisdom.

✞And so St. Abba Bishoy after he lived as a bandit and in sin, he became bedridden as he had an illness which could have taken his life. His strength weakened. And while he was like this, what he saw in a revelation frightened him. He wept after the angels took his soul and showed it the place of judgment/torment.

✞Especially, because he saw thieves and adulterers being sawn into 4, he was completely distraught. And he was regretful. And he pleaded his Creator to give him years for repentance. He beseeched saying, “My God! If You heal me from my sickness, I will not trespass against You ever again. And I will serve You by renouncing the world”.




†✝† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †✝†

††† እንኩዋን ለአባታችን "አባ ብሶይ ዼጥሮስ" እና "ቅዱስ ዕብሎይ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

††† አክርጵዮስ †††

በዚች ቀን የእስክንድሪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አክርጵዮስ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አስረኛ ነው። ይህም አባት እግዚአብሄርን የሚፈራ ንፁህ ቅዱስ ነው ።

በእስክንድርያ አገርም ቄስ ሆኖ የሚያገለግል ነበር ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ከላድያኖስ በአረፈ ጊዜ የእስክንድር አገር ህዝብና ኤጲስቆጶሳቱ መረጡት በወንጌላዊው ማርቆስ ወንበር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።

ከዚህም በኃላ እንደ ሀዋሪያት መልካም ጉዞን ተጓዘ የእግዚአብሄርን ሀይማኖት ህይወት የሆነ ህጉንም እያስተማረ ቅዱሳት መፅህፍትንም እያነበበላቸውና እያስተማራቸው መንጋዎቹን ይጠብቃቸው ነበር ሁል ጊዜም ይመለከታቸዋል አንድ የብር አላድን ወይም አንድ የወርቅ ዲናርን ጥሪት አላኖረም ከእለት ምግቡ ከቁርና ከሀሩር ስጋውን ከሚሸፈንበት ልብስ በቀር ምንም አላከማቸም።

በዚህም ተጋድሎ አስራ ሁለት አመት ኑሮ ጌታችንንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

+*" ቅዱስ ዕብሎይ "*+

=>አባ ዕብሎይ በቀደመ ሕይወቱ ለ40 ዓመታት በኀጢአት የኖረ: እግዚአብሔር ለንስሃ ሲጠራው "እሺ" ብሎ : ለ40 ዓመታት በንስሃ ሕይወት ተመላልሶ በበርሃ የተጋደለ: እንባው እንደጐርፍ ይፈስ የነበረ: አጋንንትንም ድል የነሳና ለፍሬ: ለትሩፋት የበቃ ቅዱስ አባት ነው:: እግዚአብሔርም ብዙ ቃል ኪዳን ገብቶለታል::

> (የአባ ዕብሎይ የንስሃ ጸሎት)

+*" አባ ብሶይ (ዼጥሮስ) "*+

=>ብሶይ (ቢሾይ) በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተለመደ
የቅዱሳን ስም ነው:: በተለይ በምድረ ግብ በዚህ ስም
ሰማዕታትም : ጻድቃንም ተጠርተውበታል:: ከእነዚህ
ቅዱሳን (ከገዳማውያኑ) አንዱ የሆነው አባ ብሶይም
(አንዳንዴ አባ ዼጥሮስም ይባላል) የዘመነ ጻድቃን ፍሬ
ነው::

+ቤተ ክርስቲያን የቅዱሳን ቤት ናት:: ያ ማለት ራሳቸውን
ለክርስቶስ የለዩ ሰዎች ይኖሩባታል:: እነዚህ ሰዎች
ከተለያየ ጐዳና እና ማንነት ሊመጡ ይችላሉ:: ቢያንስ ግን
በንስሃ የታጠቡ መሆናቸው ወደ ተቀደሰው አንድነት
እንዲገቡ ትልቅ መሠረት ይሆናቸዋል::

+ቅዱሳንም አንዳንዶቹ ከእናታቸው ማኅጸን ሲመረጡ :
ሌሎቹ ደግሞ ከኃጢአት ሕይወት የተመለሱ ሆነው
ይታያሉ:: ደስ የሚለው ደግሞ በንስሃ ከታጠቡ በሁዋላ
በፍጹም ልባቸው በመጋደላቸው እነሆ በሰማያዊ አክሊል
ተከልለዋል::

+አባ ብሶይ ዼጥሮስም ከኃጢአት ተመልሰው ለቅድስና
ከበቁ ቀደምት አበው አንዱ ነው:: ቅዱሱ ተወልዶ
ባደገባት ምድረ ግብጽ የታወቀ ሽፍታ : ዝሙተኛና ክፋቱ
የተገለጠ ሰው ነበር:: ለብዙ ዘመናት በእንዲህ ካለ ግብሩ
መላቀቅ ባይችል እግዚአብሔር ጥሪውን ላከለት::

+የአምላካችን የጥሪ መንገዱ ብዙ ነውና ለእርሱ ደዌን
ላከለት:: መቼም ወደድንም ጠላንም በሽታ ወደ
እግዚአብሔር የሚያቀርብ ጥሩ ፈሊጥ (አጋጣሚ) ነው::
ዛሬም ቢሆን ዘለን : ዘለን ስንሰበርና የሐኪም መፍትሔ
ሲጠፋ የግዳችን ወደ እግዚአብሔር ቤት (ወደ ጸበሉ)
እንቀርባለንና:: አምላካችን ስለዚህ ጥበቡ ይክበር
ይመስገን::

+ቅዱስ አባት ብሶይም በሽፍትነትና በኃጢአት ኑሮ ሳለ
ለሞት የሚያበቃ ደዌ ደርሶበት የአልጋ ቁራኛ ሆነ::
ኃይሉም ደከመ:: በእንዲህ እያለም በራዕዩ ያየው ነገር
ፍጹም አስደነገጠው::

መላእክት ነፍሱን ወስደው መካነ ኩነኔን ካሳዩት በሁዋላ
አለቀሰ::

+ይልቁን ሌቦችና ዝሙተኞችን ከ4 ሲቆራርጣቸው ስላየ
ፈጽሞ አዘነ : ተጸጸተ:: ፈጣሪውንም ዕድሜ ለንስሃ
እንዲሰጠው ተማጸነ:: ጌታንም "አምላኬ ሆይ! ከበሽታየ
ብታድነኝ : ዳግመኛ አልበድልህም:: ዓለምን ሁሉም ንቄ
አገለግልሃለሁ" ሲል ተማጸነው::

+እግዚአብሔርም ሰምቶት ፈጥኖ ፈወሰው:: አባ ብሶይም
እንደ ቃሉ በፍጹም ልቡ ንስሃ ገብቶ መነነ:: በገዳመ
አስቄጥስ (ግብጽ) ለ38 ዓመታት ሲኖር የላመ የጣመ
በልቶ : ከሞቀ መኝታ ተኝቶ አያውቅም::

+ሰውነቱን ይቀጣት ዘንድም እስከ 30 ቀን ያለ እህል ውሃ
ይጾም ነበር:: በዘመኑ ሁሉም የሴት መልክን አላየም::
ንስሃን የሚወድ ጌታም ጸጋውን አብዝቶለት ብዙ ድርሳናትን
ጽፏል:: የሚገርመው ደግሞ ከትህትናውና ቅድስናው
የተነሳ የእያንዳንዱ ሰው ኃጢአት ተገልጦ ይታየው ነበር::

+ቅዱሱ አባታችን ብሶይ ዼጥሮስ በንስሃና በቅድስና
ሕይወት እንዲህ ተመላልሶ በዚህች ቀን ዐርፎ በገዳሙ
ተቀብሯል:: የድካሙን ዋጋም አድልዎ ከሌለበት :
ከእውነተኛው ፈራጅ ከመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ተቀብሏል::

=>አምላከ ቅዱሳን ዕድሜ ለንስሃ : ዘመን ለፍስሐ
አይንሳን:: ከክብረ ቅዱሳንም ያካፍለን . . . አሜን !!

=>የካቲት 5 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አባ ዕብሎይ ገዳማዊ
2.ቅዱስ አባ ብሶይ ጻድቅ
3.አባ አክርዽዮስ
4."49" አረጋውያን ሰማዕታት (ፍልሠታቸው)
5.ቅዱስ አሞኒና ሚስቱ ቅድስት ሙስያ (የታላቁ ዕብሎይ ወላጆች)
6.አባ ኖብ ጻድቅ : መነሳንሱ ዘወርቅ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
2.ቅዱስ ዻውሎስ ሐዋርያ
3.አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
4.ቅዱስ ዮሐኒ ኢትዮዽያዊ
5.ቅዱስ አሞኒ ዘናሒሶ

=>አምላክ በበረከታቸው ይባርከን::

=>+"+ መቶ በግ ያለው : ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋ ዘጠና ዘጠኙን በበርሃ ትቶ የጠፋውን እስኪያገኘው ድረስ ሊፈልገው የማይሔድ ከእናንተ ማን ነው? ባገኘውም ጊዜ ደስ ብሎት በጫንቃው ይሸከመዋል:: ወደ ቤትም በመጣ ጊዜ ወዳጆቹንና ጐረቤቶቹን በአንድነት ጠርቶ 'የጠፋውን በጌን አግኝቼዋለሁና ከእኔ ጋር ደስ ይበላችሁ' ይላቸዋል:: እላችሁአለሁ: እንዲሁ ንስሃ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሃ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል:: +"+ (ሉቃ. 15:3-7)

†ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
†ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር አሜን †


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፬

✝ቅድስት ጾመ ነነዌ

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿አጋቦስ ሐዋርያ ወነቢይ (እም፸ወ፪ቱ አርድእት)
✿ዘካርያስ ጻድቅ (ትሩፈ ምግባር)
✿አቃርዮስ ገዳማዊ (አቡሁ)
✿ኤስድሮስ ወሙሴ
✿ዮሐንስ አበ ምኔት (ዘደብረ ሊባኖስ)
✿ሰማዕታት ዘደብረ አሪንጎ (፹ወ፭ቱ)
✿ዮናስ ነቢይ (ወልደ አማቴ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn


"" መንፈስ ቅዱስን የሰደበ ኀጢአቱ አይሠረይለትም! "" (ማቴ. ፲፪:፴፩)

(የካቲት 1 - 2016)

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

https://t.me/zikirekdusn

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.