Postlar filtri


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐረር የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኙ
**********************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሐረር የልማት ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።
በጉብኝታቸውም፤ ለክልሉ ኮሪደር ፕሮጀክቶች በሀገር ውስጥ የተሰሩ ቁሳቁሶችን የሚያመርተውን የማስ ኢንጂነሪንግ ኢንተርፕራይዝ፣ የሌማት ትሩፋት ማሳያ እና እና ለክልሉ በቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት የተገነባውን የዳቦ ፋብሪካ ተዘዋውረው መመልከታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።








ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ የጅግጅጋው ኢፍጣር መርሐ ግብር በሶማሌ እና በአፋር ሕዝቦች መካከል አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ነው ሲሉ ገለጹ
********************

በሶማሌ እና በአፋር ክልል ወንድማማች ሕዝቦች መካከል ከዚህ በፊት የነበረው ግጭት በሰላማዊ መንገድ ተፈትቶ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ መቻሉን በጅግጅጋ በተዘጋጀው “ኢፍጣር ለሰላም እና ለአብሮነት” መድረክ ላይ የተገኙት ኡስታዝ አቡበከር አሕመድ ተናግረዋል።

በሶማሌ እና በአፋር ሕዝቦች መካከል አዲስ ምዕራፍ…
@EBCNEWSNOW


በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ግራዋ ወረዳ የእርከን ግንባታ እና የአፈር እና ውኃ ጥበቃ ሥራ ጉብኝት - በምስል


ማስታወቂያ
****
ሬስ ማይክሮ ፋይናንስ እና ሁድ ሁድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በመተባበር የተመቻቸ ብድር


"ይህ ቀን ለሰላም ወዳጆች የድል ቀን ነው" – ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ
*****************

በትናንትናው ዕለት “ኢፍጣር ለሰላምና ለአብሮነት” በሚል መሪ ሐሳብ ፤ የሶማሌ እና አፋር ክልል ወንድም ህዝብ የጋራ ኢፍጣር ፕሮግራም በጅግጅጋ ከተማ ተካሂዷል፡፡

በመርሐ-ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፤ "ይህ ቀን ለሰላም እና ለልማት ወዳጆች የድል ቀን ነው" ብለዋል፡፡

እርቅ በእስልምና አስተምህሮ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ቅዱስ ተግባር መሆኑን በማንሳትም ፤ ወንድማማች በሆኑት ህዝቦች መካከል የተፈጠረው ሰላም እጅግ አስደሳች መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሎቹ መካከል ሰላም እንዲፈጠር የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የፌዴራል መንግሥት፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የሁለቱም ክልሎች አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላትም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በሜሮን ንብረት


ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለለውጡ መሰረት የሚሆኑ ሕጎችና አሰራሮችን ማሻሻል ላይ እየተሰራ መሆኑን ገለጸ
*************

በፍትህ ተቋማት እና ፍርድቤቶች የሚሰጡ አገልግሎቶች ማሻሻያ ሊደረግባቸው እንደሚገባ ተገልጋዮች ለኢቲቪ ገልጸዋል።

የዳኝነት ችግር፣ የፋይል አያያዝ፣ የቀጠሮ ቀን ያለአግባብ ማራዘም፣ በጉዳዮች ውስጥ ጉዳይ አስፈፃሚ እንዲገባ ምቹ እድል መፍጠር እና ሌሎችም መሰል ችግሮች የፍትሕ መጓደል እንዲፈጠር ምክንያት መሆናቸውን ተገልጋዮቹ ጠቅሰዋል።

የሕጎችና አሰራሮችን ማሻሻል…
@EBCNEWSNOW


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በምሥራቅ ሐረርጌ ቆላማ አካባቢዎች እየለማ የሚገኝ የበጋ ስንዴ ልማትን ተመለከቱ
***********************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በምሥራቅ ሐረርጌ ቆላማ አካባቢዎች እየለማ የሚገኝ የበጋ ስንዴ ልማትን መመልከታቸውን ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “መትጋት፣ መሥራት እና ማየት ከቻልን ኢትዮጵያ ከመረዳት አልፋ ሌሎችን መርዳት ትችላለች፤ ይህንን ሥራ አጠናክረን እንድንቀጥል አደራ እላለሁ" ብለዋል።

10 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.