ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


እስራኤል በኢራን ላይ የአጸፋ ጥቃት ሰነዘረች‼️

እስራኤል ኢስፋሃን በተባለ የማዕከላዊ አራን አካባቢ ባሉ ወታደራዊ ካምፖች ላይ በድሮኖች ጥቃት መሰንዘሯን አለማቀፍ ሚድያዎች እየዘገቡት ነው፡፡

ይህን ተከትሎ ኢራን የጸረ-ሚሳኤል መከላከያ ማስወንጨፏንና የተተኮሱባትን ሦስት ድሮኖች መታ መጣሏን አስታውቃለች።

ኢስፋሃን የኢራን አየር ኃይል እና የኒዩክሌር ጣቢያ የሚገኝ ከተማዋ ሲሆን በአካባቢው የተሰማው ፍንዳታ ኢራን ያስወነጨፈቻቸው የጸረ ሚሳኤል መከላከያ መሆኑን አገሪቱ ባወጣችው መረጃ ገልጻለች።

የእስራኤልን ጥቃት ተከትሎ የአየር በረራዎች ተስተጓጉለው እንደነበርና በአሁኑ ሰዓት በረራ መጀመሩን እንዲሁም አካባቢው ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሱን የአልጃዚራ ዘገባ አመላክቷል።

በፈረንጆቹ ሚያዝያ 1 ቀን እስራኤል ሶሪያ በሚገኘው የኢራን ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ላይ ባደረሰችው ጥቃት 13 ዜጎቿ መገደላቸውን ተከትሎ በእስራኤል ላይ ባሳለፍነው ቅዳሜ 300 ሚሳኤልና የድሮን ጥቃት ማድረሷ ይታወሳል።

ለኢራን ጥቃት እስራኤል አጸፋዊ እርምጃ እንደምትወስድ ዝታ እንደነበርም የሚታወስ ነው።
የሁለቱ አገራት የሰሞኑ ግጭትን ተከትሎ አገራት ዜጎቻቸውን ወደ እስራኤል እንዳይጓዙ እያስጠነቀቁ ነው።

ከስውር ጦርነት አልፎ ወደ ይፋዊና ቀጥተኛ ግጭት ውስጥ የገባው የሁለቱ አገራት የሰሞነኛ ፍጥጫ በቋፍ ላይ የነበረ የአካባቢውን ሰላምና ጸጥታ ወደለየለት ጦርነት እንዳይከተው ተሰግቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


➨ በኢትዮጵያ ትልቁን የአክሲዮን ትርፍ ክፍፍል ያስመዘገበው የአያት አክሲዮን ሽያጭ ሊጠናቀቅ  ጥቂት እጣዎች ቀሩት!!

አያት አክሲዮን ማህበር በ 2015 ዓ.ም 51.3% ትርፍ /Dividend/ ለባለክሲዮኖች አከፋፍሏል

በቀላሉ
የ 1 ሚሊዮን ብር አክሲዮን የነበራቸው ባለአክሲዮኖች 513,000 ብር ትርፍ /Dividend/ አግኝተዋል

አክሲዮኑን ከገዙ ከአንደኛው ወር ጀምሮ የትርፍ ተካፋይ መሆን ይጀምራሉ

የአንድ አክሲዮን ዋጋ 100 ብር

ዝቅተኛ የአክሲዮን መጠን 2500 ጠቅላላ ዋጋ 250,000ብር

ቅድመ ክፍያ 112,500 ብር ቀሪ ክፍያ  በ 3 ዓመት የሚከፈል በየዓመቱ 50,000ብር

ከፍ ያለ የአክሲዮን ድርሻ በመግዛት ዳጎስ ያለ የአክሲዮን ትርፍ ያግኙ

ሽያጭ ከመጠናቀቁ በፊት ዛሬውኑ እርሶም የራስዎን ድርሻ ይውሠዱ

የሽያጭ ባለሙያዎቻችንን ለማግኘት (whatsapp/ telegram/direct)
📞 ☎️  0904272788


መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

☎️ 0911248768   👈 ይደውሉልን


የዉጪ ባለሃብቶች ከማዳበሪያ እና ከነዳጅ በስተቀር በሁሉም የንግድ ኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ እንዲሳተፉ ተፈቀደ‼️

መሰረታቸውን በዉጪ ያደረጉ ባለሃብቶች በችርቻሮ እና በጅምላ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ፍቃድ መሰጠቱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሸን እና የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጋራ አስታውቀዋል።

ከጅምላ ንግድ ጋር ተያይዞ ከማዳበሪያና ከነዳጅ ጅምላ ንግድ በስተቀር በሁሉም አይነት የጅምላ ንግድ መስኮች መሰማራት ይችላሉ ተብሏል በዚህም በጥሬ ቡና፣ በቅባት እህሎች፣ ጫት፣ ጥራጥሬ፣ ቆዳ እና ሌጦ፣ የደን ውጤቶች እና የቁም እንስሳት የመላከ የወጪ ንግድ ላይ እንዲሳተፉ ነዉ የተፈቀደው ።

ከዚህ ቀደም ለአገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ተከልለው የቆዩ የወጪ፣ የገቢ፣ የጅምላ እና የችርቻሮ ንግድ ዘርፎች አሁን ደግሞ ለውጭ ባለሃብቶች ከፍት እንዲሆኑ መደረጉ ነዉ ለማወቅ የተቻለው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ አካሂዶ በሁለት ጉዳዮች ውሳኔ አሳልፏል‼️

ውሳኔ ከተላለፈበት አንዱ ጉዳይ የሽግግር ፍትሕ ረቂቅ ፖሊሲ ነው።

ምክር ቤቱ ፥ " በሀገሪቱ በተለያዩ ዘመናት የተከሰቱ እና የቀጠሉ ተደራራቢ እና ሰፊ የተጎጂና የአጥፊ ወሰን ያላቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ የእርስ በእርስ ግጭቶች፣ ያልጠሩ ትርከቶች እና በደሎችን ለመፍታት የተለያዩ ሙከራዎች ተደርገዋል " ብሏል።

" ሆኖም እነዚህ አሰራሮች ፦
- በእውኀት፣
- በዕርቅ፣
- በምህረት እና በፍትሕ ላይ የተዋቀረ እና በግልፅ ፖሊሲ የሚመራ ሁለንተናዊ የሽግግር ፍትሕ ስልትን አካታች፣ ሰብአዊ መብት ተኮር በሆነ እና በተሰናሰለ መንገድ ባለመተግበራቸው የሚፈለገውን ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አልቻሉም " ሲል ገልጿል።

በመሆኑንም የሽግግር ፍትሕ ሂደቱን በተደራጀ፣ በተቀናጀ እና ውጤታማ በሆነ መልኩ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመምራትና ለመተግበር እንዲቻል ረቂቅ ፖሊሲ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቀረቡን አስረድቷል።

ምክር ቤቱም በረቂቅ ፖሊሲው ላይ ከተወያያ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ዱባይ በጎርፍ ተጥለቀለቀች‼

በዱባይ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መጠን ነፋስ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ መዝነቡን ተከትሎ ከተማዋ በጎርፍ ተጥለቅልቃለች።

ጎርፉን ተከትሎ የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያን ጨምሮ የከተማዋ ዋና ዋና ጎዳናዎች ከባድ ጎርፍ እያስተናገዱ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይም ከዚህ ቀደም በርከታ በረራዎችን ሲያስተናግድ በነበረው የዱባይ አየር መንገድ በረራዎች ተስተጓጉለዋል።

ነፋስ የቀላቀለው ከባድ ዝናብ በኦማን ተከስቶ 18 ሰዎች ህይወታቸው ካለፈ በኋላ አሁን ደግሞ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና በባህሬን ጉዳት እያስከተለ እንደሚገኝ የአልጀዚራ ዘገባ ያመለክታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት ኢራን ላይ ማዕቀብ ለመጣል ዝግጅት ጀመሩ‼️

ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ኅብረት፤ እስራኤል ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ኢራን ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ ለመጣል እየተሰናዱ ነው።የአሜሪካ ግምጃ ቤት ኃላፊ ጃኔት የለን “በሚቀጥሉት ቀናት” እርምጃ እንወስዳለን ሲሉ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳይ ፖሊስ ኃላፊ ጆሴፍ ቦሬል ደግሞ ኅብረቱ ማዕቅብ ለመጣል እየሠራ መሆኑን ገልጠዋል።እስራኤል አጋሮቿ የኢራን የሚሳዔል ፕሮግራም ላይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ጠይቃለች።

የተባበሩት መንግሥታት የኢራን የሚሳዔል ፕሮግራም ላይ የጣለው ማዕቀብ ባለፈው ጥቅምት ጊዜው አብቅቷል።እኒህ ማዕቀቦች የሚጣሉት የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም ለመግታት ነው የሚሉ ሐሳቦች ከፖለቲካ ተንታተኖች ዘንድ ይሰማሉ።አሜሪካ፣ የአውሮፓ ኅብረት እና ዩናይትድ ኪንግደምን ጨምሮ በርካታ ሀገራት ኢራን ላይ የተለያዩ ማዕቀቦች ከዚህ ቀደም መጣላቸው አይዘነጋም።የእስራኤል ጦር ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ሌተናንት ጄኔራል ሄርዚ ሀሌቪ ባለፈው ሰኞ በሰጡት አስተያየት ኢራን ያደረሰችው ጥቃት ምላሽ ሳያገኝ አያልፍም የሚል አስተያየት ሰጥተው ነበር።

ኢራን ባለፈው ቅዳሜ ለመጀመሪያ ጊዜ እስራኤል ላይ ቀጥተኛ ጥቃት ባደረሰችበት ወቅት 300 ሚሳዔሎችና ድሮኖች ከራሷ ክልል፣ ከኢራቅ፣ ሶሪያ እና የመን አስወንጭፋለች።አብዛኛዎቹ ሚሳዔሎች እና ድሮኖች በእስራኤል እና አጋሮቿ ዒላማቸውን ሳይመቱ እንዲከሽፉ ተደርገዋል።ቴህራን እንዳለችው ጥቃቱን የሰነዘረችው እስራኤል፤ ሶሪያ በሚገኘው ቆንስላዋ ላይ ጥቃት አድርሳ 13 ሰዎችን ለገደለችበት ጥቃት አፀፋውን ለመመለስ ነው።

እስራኤል ለደረሰባት ጥቃት እስካሁን ቀጥተኛ ምላሽ አልሰጠችም። በምትኩ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ኢራንን ለማሽመድመድ እየሠራች ትገኛለች።እስራኤል 30 የሚሆኑ አጋር ሀገሮች የኢራን የሚሳዔል ፕሮገራም ላይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ጠይቃለች።አልፎም እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኢስላሚክ ሪቮሎሺናሪ ጋርድ ኮር የተባለው የኢራን ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ኃይል ሽብርተኛ ተብሎ እንዲፈረጅ ጠይቃለች። አሜሪካ ከዚህ ቀደም ቡድኑን ሽብርተኛ ብትልም ዩኬ ይህን ከማድረግ ተቆጥባለች።

ማክሰኞ ዕለት ንግግር ያደረጉት የአሜሪካ ግምጃ ቤት ሚኒስትር የለን “በሚቀጥሉት ቀናት ኢራን ላይ ማዕቀብ እንደምንጥል ይጠበቃል” ብለዋል።ሚኒስትሯ አክለው ኢራን ወደ ውጭ የምትልከው ነዳጅ “ምናልባት የምናየው ይሆናል” ካሉ በኋላ “ኢራንም አሁንም በግልፅ ነዳጅ እየሸጠች ነው፤ ስለዚህ ጉዳይ የምናደርገው ነገር ይኖራል” ሲሉ ማዕቀቡ ምን ላይ እንደሚያተኩር ጠቁመዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የተሰጠ መግለጫ‼️

የክልሉ መንግሥት ፥ " ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ መማር የተሳነው ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሓት) የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመጣስ ለአራተኛ ዙር ሕዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ከሷል።

" ህወሓት የአማራ ክልል ተማሪዎችን መማሪያ መጽሐፍ እንደ ሰበብ ተጠቅሞ በይፋ ጦርነት ማወጁና መቀስቀሱ ይታወቃል " ሲል አስታውሷል።

የአማራ ክልል መንግሥት ህወሓትን " የመላ ኢትዮጵያ ጠላትና የደኅንነት ስጋት " እንደሆነ ገልጾ " ባለፉት 3 ዙሮች ከተደረገው ደም አፋሳሽ ጦርነት ትምህርት ሊወስድ ይችል ይሆናል በሚል ጭላንጭል ተስፋ የፌዴራል መንግሥት እጅግ እልህ አስጨራሽ ትዕግስት ተላብሶ ውይይቶች እንዲካሄዱ ተደጋጋሚ ጥረት ሲያደረግ ቆይቷል " ብሏል።

" የአማራ ክልል መንግሥትም በተደጋጋሚ ከትግራይ ጊዜያዊ አሥተዳደር ጋር በፌዴራል መንግሥት አማካኝነት ውይይት ለማድረግ በርካታ ሙከራዎች የተደረጉ ቢሆንም ህወሓት ይህን የሰላም አማራጭ ወደ ጎን በመተው የማንነት ጥያቄ ያለባቸውን የራያ አላማጣ፣ ራያ ባላ፣ ኦፍላ፣ ኮረምና ዛታ አካባቢዎች ላይ ወረራ ፈፅሟል " ሲል ገልጿል።

" ህወሓት ወረራ የፈፀመባቸው ፦
- የራያ አላማጣ፣
- ራያ ባላ፣
- ኦፍላ፣
- ኮረምና ዛታ እንዲሁም የወልቃይት ጠገዴ እና ጠለምት አካባቢዎች የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት ከመፅደቁ በፊት በነበሩ አሥተዳደራዊ መዋቅርና አደረጃጀት በኀይል ጠቅልሎ ከመውሰድ ጀምሮ የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከመፈፀም ድረስ አሰቃቂ ጥፋት የፈፀመባቸው አካባቢዎች  ናቸው " ብሏል።

" ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ህወሓት በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን አሰቃቂ ጥቃት ተከትሎ ከተቀሰቀሰው ጦርነት በኃላ አካባቢዎቹ በጉልበት ተገፎባቸው የነበረውን ራሳቸውን የማሥተዳደር ነጻነት መቀዳጀት እንደቻሉ " የአማራ ክልል መንግሥት ገልጿል።

በኃላም የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መፈረሙን ፤ ህወሓት ግን ስምምነቱን በማክበር በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን የድርሻውን ከመወጣት ይልቅ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ በመጣስ የተለያዩ ጥፋቶችን ሲፈጽም እንደቆየ አመላክቷል።

" አሁንም እየፈጸመ ይገኛል " ብሏል።

የአማራ ክልል መንግሥት ፥ ህወሓት ደም አፋሳሽ የሆነ ጦርነት ለማድረግ ከመሞከር እንዲታቀብ እና የፕሪቶሪያውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ እንዲያከብር አሳስቧል።

" በአጭር ጊዜ በወረራ የያዛቸውን አካባቢዎች ለቆ እንዲወጣ " ሲል ጠይቋል።

" ይህ የማይሆን ከሆነ የአማራ ክልል መንግሥት እና ሕዝብ ከሌሎቹ ወንድምና እህት ኢትዮጵያዊያን ጋር በጋራ በመሆን ሀገርን ከማፍረስ መታደግናረ ሕዝባችንንም ከጥቃት ለመከላከል እንገደዳለን " ሲል አስጠንቅቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@Esat_tv1
@Esat_tv1




የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ 95 በመቶውን ማስመለስ መቻሉን አስታወቀ‼️

የኢትዯጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከተከሰተው የሲስተም ችግር ጋር በተገናኘ ያለአግባብ ተወስዶ ከነበረው ገንዘብ 95 በመቶ የሚሆነውን ማስመለሱን አስታውቋል።ባንኩ ከሲስተም ማሻሻያ ሥራ ጋር በተገናኘ በተጠቀሰው ዕለት በተፈጠረ ችግር ምክንያት ብር 801 ሚሊዮን 417 ሺህ 747.81 ያለአግባብ ተወስዶ እንደ ነበር መገለፁ ይታወሳል።

ከተወሰደው ገንዘብ 762 ሚሊዮን 941 ሺህ 341 ብር ማስመለስ መቻሉን ባንኩ በማኅበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።ይህም መሰብሰብ ከነበረበት ገንዘብ ውስጥ 95 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን ቀሪውን 38 ሚሊዮን 474 ሺህ 938 ብር የማስመለስ ስራ እንደሚቀጥልም ባንኩ ገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


Niya Online payment ‼️

የተለያዩ እንደ SAT እና USMLE ያሉ የውጭ ፈተናዎችን ክፍያ ለመፈጸም ለ Scholarship application fee ለመክፈል ከ Alibaba, Amazon እና የመሳሰሉ የኦንላይን ገበያዎች ላይ ክፍያ ለመፈጸም እንዲሁም ለሌሎች ማንኛውንም በ online የሚከፈሉ ክፍያዎች ለመክፈል ፈልገው ተቸግረዋል❓

እንግዲያውስ እኛ ጋር መፍትሄ አለ!

በVisa card, Mastercard ወይም በ Payoneer እንደራስዎ ሆነን ክፍያዎን እንፈጽምሎታለን!

- በ ቴሌግራም  አድራሻችን 👉@StraightouttaNazreth
-በ ስልክ ቁጥራችን 👉+251934729413 ይደውሉ

Niya online payment


በኮሪደር ልማት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ሆኑ‼️

በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰኑ አካባቢዎች እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ምክንያት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት መደረጋቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በዚህም መሰረት፡-

ከደጃች ውቤ በአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

ከባሻወልዴ ችሎት በቱሪስት ሆቴል ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

ከዳኑ ሆስፒታል እስከ ቱሪስት ሆቴል በመውጣት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

ከአራዳ መስተዳደር ወደ ዳኑ ሆስፒታል መውረጃ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አሽከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ሥራዎች ምክንያት ለአጭር ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ በጥብቅ መከልከሉንም ነው ፖሊስ ያሳሰበው፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን የተሰጠ መግለጫ‼️

ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ የማይማረው ህወሐት ለአራተኛ ዙር በህዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል። የፌዴራልና የአማራ ክልል ክልሉ መንግስታትም በህዝብ ላይ የተቃጣውን የጥፋት ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

የኢትዮጵያ ህዝብ ዘላለማዊ ጠላት የሆነው ወያኔ ህወሐት በህዝብ ትግል ተገፍትሮ ወደ ትግራይ ከተሰበሰበ በኋላ በተደጋጋሚ ወረራ በመፈፀም በህዝባችን ላይ ለጆሮ የሚከብድ ዘግናኝ ግፍ ፈፅሟል። ምንም እንኳን ህወሐት በተደጋጋሚ ጊዜ በቆሰቆሰው ጦርነት የአማራ እና የአፋር ህዝብ በቀጥታ የገፈቱ ቀማሽ ይሁኑ እንጅ ዋና ዓላማው ኢትዮጵያ ሐገራችንን መበታተን እና የፈራረሰች ሐገር መፍጠር መሆኑን በአፈ ቀላጤው በኩል በተደጋጋሚ ተናግሯል።

ይህ የእናት ጡት ነካሽ ቡድን የሐገራችን ደጀን የሆነውን የሰሜን እዝ የመከለከያ ሰራዊት በማጥቃቱ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያጋጠመውን ቁጣ መቋቋም ተስኖት ለሶስተኛ ጊዜ እየተመላለሰ ያደረገው የሐገር ማፍረስ ሙከራ ባይሳካለትም እንኳን አድፍጦ ለጦርነት ከመዘጋጀት ግን ቦዝኖ አያውቅም።

ህወሐት ከጦርነት ውጭ መኖር የማይችል፣ በጦርነት አድጎ በጦርነት ያረጀ ቡድን በመሆኑ በመላው የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ አማፂያንን ከማስታጠቅ አልፎ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በመወገን ሐገራችንን የጦር ቀጠና ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ነበር የከረመው። በቀጥታ ከሚደግፋቸው የጥፋት ኃይሎች በተጨማሪ የራሱን ኃይል በማደራጀት የሰርጎ ገብ ኃይል እየላከ ህዝባችንን ሲረብሽ መክረሙ ሳያንሰው በአሁኑ ሰዓት በራያ በኩል ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ከፍቶ ይገኛል።

ኋላ ቀርነት እና ግትርናት ዋና መገለጫው የሆነው የጥፋት ቡድን የሚሊዮኖችን ህይዎት በቀጠፈውና ከተደጋጋሚ ስህተቱ ባለመማር ዛሬም ለሌላ ዙር እልቂት ተዘጋጅቶ በህዝባችን ላይ ጦርነት ከፍቷል።

በህዝቦች እኩልነት እና በብሔረሰቦች መብት ፈፅሞ የማያምነው ህወሐት እኔ የማልገዛት ኢትዮጵያ ተረጋግታ መኖር የለባትም የሚል ያልተገራ ክፉ አመሉን በተደጋጋሚ አሳይቷል። በዚህም እንደ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እኩልነትን ፈፅሞ እንደማይሻ አረጋግጧል።

ለህዝባችን የሚከተሉትን መልዕክቶች እናስተላልፋለን

1. ምንም እንኳን አሸባሪው እና ተስፋፊው ወያኔ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጠላት ቢሆንም ፣ በተለይ የአማራ ህዝብ የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ ጦርነቱን የመመከት ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኘው ሕዝባችን ካለፈው የጥፋት ግዜ በመማር ከታሪካዊ ጠላቱ የሚሰነዘርበትን ወረራ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት እንዲመክት፣

2. ህዝባችን ከወያኔ ትጥቅ አስፈች ፕሮፖጋንዳ ራሱን እንዲጠብቅ እና ከዚህ ታሪካዊ ጠላት የሚመጣን ማንኛውንም ውዥንብር ጆሮ እንዳይሰጥ፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የወገን ኃይሎች ለወያኔ የሚያሳዩትን የተለሳለሰ የባንዳነት መንገድ ህዝባችን ፈፅሞ እንዳያዳምጥ እና እንዲህ ያሉትን ቡድኖች አጥብቆ እንዲታገል፣

3. የአማራ እና የአፋር ህዝብ የጦርነቱ ዋና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኃይሎች የሚፈልጉትን ሁሉ በማቅረብ ከሐገሩ ጎን እንዲቆም

4. ህዝባችን ይህን ታሪካዊ ጠላት በመቅጣት የተለመደ ጀግንነቱን እንዲወጣ ስንል ጥሪ እያቀረብን፤ በተለይ መንግስት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በዝምታ የሚመለከት ከሆነ፤ ህዝባችን ስርአትን አምኖ ችግሮች ሁሉ በህግ አግባብ ይፈታሉ የሚል ቀናኢነቱ ማታለያ ሆኖ ከዋለ፤ ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ እንዲሆን መንግስት የፈቀደ መሆኑን ታሪክ የሚመዘግበው ሀቅ ይሆናል።

5. በህወሐት ችግር የአማራና የትግራይ ህዝቦች እንዲሁም መላ ሀገሪቱና ቀጠናው ችግር ውስጥ እየወደቀ በመሆኑ ይህ በአስቸኳይ እንዲቆም እያሳሰብን በተለይ የፌዴራሉ መንግስትና የአማራ ክልል መንግስት በህዝባችን ላይ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

ሚያዝያ 07/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ

@Esat_tv1
@Eaat_tv1


እስራኤል “ትክክለኛው ሰዓት ላይ” ለኢራን ጥቃት የአጸፋ ምላሽ እሰጣለሁ አለች‼️

እስራኤል ልክ እንደ ኢራን ሁሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሚሳኤሎችን በመተኮስ ‘ትክክለኛው ሰዓት ላይ’ የበቀል እርምጃ እውስዳለሁ አለች።ዓለም አቀፉ ማሕብረሰብ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ውጥረት ከሚያባብስ እርምጃ እንዲቆጠቡ አገራት ቢያሳስቡም እስራኤል ግን ትክክል ሆኖ ሳገኘው የአጸፋ እርምጃ እውስዳለሁ ብላለች።

ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ በእስራኤል ላይ በፈጸመችው ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት ከ300 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ወደ እስራኤል ማስወንጨፏ ይታወሳል።ከ300 በላይ የሚሆኑት ሚሳኤሎች እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ እና ከየመን ወደ እስራኤል የተተኮሱ ቢሆንም አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ በእስራኤል፣ በአሜሪካ እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ ተደርገዋል።

ከኢራን የተወነጨፉ ሚሳኤሎችን በማምከን ድጋፍ ስታደርግ የነበረችው አሜሪካ እስራኤል የበቀል እርምጃ ብትወስድ ተሳታፊ አልሆንም ስትል አስታውቃለች።አምስት አባላት ያሉት የእስራኤል የጦር ካቢኔ እና የአገሪቱ ፓርላማ አባል ቤኒ ጋንትዝ ትክክለኛው ሰዓት ላይ ኢራን ለፈጸመችው ተግባር እስራኤል ዋጋ ታስከፍላታለች ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


እስራኤል ከኢራን የተወነጨፉባትን 300 ሰው አልባ አውሮፕላኖችና ሚሳኤሎች ማክሸፏን ገለጸች‼️

እስራኤል በራሷና አጋሮቿ በኢራን ከተወነጨፉባት ከ300 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሚሳኤሎች ውስጥ 99 በመቶውን ማክሸፍ መቻሏን አስታውቃለች።

ይሁንና በግዛቷ ላይ አነስተኛ መጠን ያለው ድብደባ እንደተፈፀመና በዚህም በደቡባዊ እስራኤል የሚገኘው የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ካምፕ መመታቱን አንዲት ሕፃንም መቁሰሏን ገልፃለች።

ኢራን በእሥራኤል ላይ ጥቃት መሠንዘር መጀመሯን ተከትሎም መረጃዎች ተከታትለው በመውጣት ላይ ይገኛሉ።
እሥራኤል እየተሰነዘረባት ካለው ጥቃት የተነሳ አየር ክልሏን መሉ በሙሉ ዝግ ማድረጓ ተሰምቷል።

የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ላልተወሰነ ጊዜ የአየር ወሰናቸውን ዝግ ያደረጉ ሲሆን፤ ሶሪያ ፣ ኢራቅ ፣ ዮርዳኖስ እና ግብፅ የአየር ክልሎቻቸውን በጊዜያዊነት በመዝጋትም ከፍተኛ ተጠንቀቅ አውጀዋል።
ኢራን በእሥራኤል ላይ ከድሮንና የሚሳዔል ጥቃቶች በተጓዳኝ፤ የሳይበር ጥቃት መፈፀሟም ተነግሯል።

ከቴህራን የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት፤ በእሥራኤል የመከላከያ ቴክኖሎጂዎች ላይ የሳይበር ጥቃት ተፈፅሟል።
ይሁንና ይህን የሳይበር ጥቃት ትክክለኝነት እስካሁን ከገለልተኛ አካል ማረጋገጥ አለመቻሉ ተመላክቷል።

መዳረሻቸውን ወደ እሥራኤል ያደረጉ የኢራን ድሮኖች እንደ ግሪሣ ወፍ ምሽቱን በኢራቅ ሰማይ ላይ በብዛት የታዩ ሲሆን፤ ከዋክብት እንጂ ድሮኖች የማይመስሉበትን ምስል የኢራኑ ታዝኒም የዜና አውታር ይዞ ወጥቷል።

የአየር እና የባሕር ኃይል ምድብ ጣብያዎች እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ መኖሪያ የኢራን ጥቃት ዒላማ ተብለው ከተገመቱት መካከል እንደሚጠቀሱም ተመላክቷል።
ኢርና የዜና ምንጭ እንደዘገበው ከሆነ፤ ኢራን ወደ እሥራኤል ባላስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፍ ጀምራለች።

ከኢራን እየተሠነዘረ ባለው ጥቃት ቅድሚያ ተጠቂ ሊሆኑ ከሚችሉ አካባቢዎች ዜጎች እንዲርቁና ፡ ጥቃትን በሚቀንሱ መከለያዎች ውስጥ እንዲቆዩ ሲል የእሥራኤል መከላከያ ሠራዊት ለዜጎች ትዕዛዝ መስጠቱም ተነግሯል።

ለኢራን ጥቃት ተጋላጭ ናቸው ከተባሉት የእሥራኤል ይዞታዎችና ግዛቶች መካከል የጎላን ኮረብታዎች ፣ ኔቫቲም ፣ ዲሞና ፣ ኤይላትና በዙሪያቸው ያሉ ነዋሪዎች መሽገው እንዲቆዩ የእሥራኤል ጦር ለሀገሪቱ ዜጎች አሳስቧል።

ትናንት ምሽቱን ጥቃት የጀመረችው ኢራን ከ300 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖችና ሚሳኤሎችን ወደ እሥራኤል አስወንጭፋለች።

ይሁንና ሰው አልባ አውሮፕላኖቹና ሚሳኤሎቹ የእሥራኤልን የአየር ክልል ከመጣሳቸው በፊት በእስራኤል በራሷና በአጋሮቿ በአሜሪካ፣ በብሪታንያ፣ በፈረንሳይ እና በዮርዳኖስ የአየር መከላከያ ኃይሎች እንዳከሸፏቸው አንድ የእሥራኤል መከላከያ ከፍተኛ ሹም ለ ዘ ታይምስ ኦቭ እሥራኤል ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች‼️

ከሰምኑ ውጥረት ውስጥ በከረሙት  ኢራንና እስራኤል መካከል ጦርነቱ ስድስት ሰአት ተኩል ላይ በይፋ ጀምሯል።

ኢራን ወደ እስራኤል በሺወች የሚቆጠሩ  ሮኬት እና ሚሳኤሎችን ተኩሳለች።

የሊባኖሱ ሄዝቦላህ በእስራኤል ቁጥጥር ስር ወደሚገኙት  የጎላን ተራሮች በደርዘን የሚቆጠሩ  ሮኬቶችን እየስወነጨፈ ነው።

አሜሪካ ተጨማሪ ሃይሏን ወደ መካከለኛው ምስራቅ አስጠግታለች።

ኢራቅና ዮርዳኖስ   የአየር ክልላቸውን  በጊዜያዊነት ዘግተዋል።

የእስራኤል የአየር ክልልም ከደቂቃዎች በኋላ ሙሉ ለሙሉ ይዘጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ድሮኖች ወይም ሰው አልባ አውሮፕላኖች ወደ እስራኤል ለመድረስ 1 ሺህ 800 ኪ.ሜ. ርቀት ያህል መጓዝ የሚኖርባቸው ሲሆን ፥ ይህም ሰዓታት ሊወስድ እንደሚችልም ነው የተገለፀው።

አልጀዚራ እያንዳንዱን ክስተት በቀጥታ ስርጭት እያስመለከተ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ‼️

ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የነበረዉን ደንብ በመሻር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ለሚሰጣቸው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታዉቋል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አዲሱ ደንብ ከመዉጣቱ በፊት ሲሰራበት የነበረዉን የሰነዶች ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያን በመሻር ማሻሻያዉ ከሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ለሚሰጣቸው የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያ ለመወሰን ባወጣዉ በዚህ ደንብ በተቀመጠው አዲሱ የክፍያ መጠን የሰነድ አይነቶቹ ቢለያይም ለሁሉም አገልግሎቶች ከ 200 ብር ጀምሮ እስከ 500 ብር ድረስ ክፍያን ይጠይቃል።

ካፒታል በተመለከተዉ በዚህ ደንብ ላይ ለሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዉል ሰነድ ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ሽያጭ ፣ ለመመስረቻ ፅሁፍ ሰነድ እና በስጦታ መልክ ለሚሰጡ ንብረቶች ዉል ሰነድ የክፍያ አገልግሎት ተመን ከወጣላቸው መካከል ዉስጥ ተካተዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮጵያን ጨምሮ በ5 የአፍሪካ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች የዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩ ተገለፀ‼️

በፈረንጆቹ 2024 ኢትዮጵያን ጨምሮ በ5 የአፍሪካ ሀገራት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ ግሽበት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው አዲስ ሪፖርት አስታውቋል።

ከፍተኛ የምግብ የሸቀጦች ዋጋ ግሽበት ከተከሰተባቸው የአፍሪካ ሀገራት መካከል ዝምባብዌ፣ ሴራሊዮን ማላዊ፣ ናይጄሪያ እና የምግብ ሸቀጦች ግሽበቱ 29.4 ደርሷል የተባለባት ኢትዮጵያ ከ1 እስከ 5 ባለው ደረጃ ሲቀመጡ ጋና፣ አንጎላ፣ ብሩንዲ፣ ጋምቢያ እና ጊኒ ከ6 እስከ 10ኛ ደረጃዎች ላይ መቀመጣቸውን ሪፖርቱ አመልክቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


​​በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም‼️

🗣 አዲስ አበባ ፓሊስ

በአዲስ አበባ ከተማ በፋኖና በፓሊስ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሲቪልና ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ፣ በሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

የ“ፋኖ” አመራርና አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ ከፀጥታ አካላት ተኩስ እንደከፈቱ፣ በ “ፋኖ” በኩል ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ አንድ በቁጥጥር ስር እንደዋለ፣ በመንግሥት በኩል ሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ በንጹሐን በኩል ደግሞ አንድ አሽከርካራ እንደተገደለ፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል፣ “ የተገደሉት የ “ፋኖ” ቡድን አመራርና አባላት ናቸው። አመራሩ ናሁሰናይ አንዳርጌ ነው። ሌላው አቤኔዘር ጋሻው የተባለው ነው፣ እዛው ቦታው ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሂወቱ አልፏል። ሀብታሙ አንዳርጌ ግን ምንም አልሆነም በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።

የ “ፋኖ” አመራርና አባላት የነበራቸውን እንቅስቃሴ ሲያስረዱም ኮማንደሩ፣ “ በከተማው ውስጥ ነው የሚንቀሳቀሱት የነበረው። በከተማው ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ጥፋቶች ለማጥፋት ነው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበረው ” ነው ያሉት።

አክለውም፣ “ እነርሱን ለመያዝ በተደረገው ሂደት ቦሌ ወረዳ 3 ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የሚባሉ ሁለት የፓሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ከእነርሱ (“ፋኖ”) በተተኮሰ ጥይት ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ እሱም ብቻ አይደለም አንድ አሽከርካሪ እንዲጭናቸው ሲያስገድዱት ‘አልተባበርም’ ስላለ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ሞቷል። የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታውት በጥይት መትተውታል። ሙሉ ለሙሉ ጉዳት ደርሶበታል። ሰውየው ግን ምንም የሆነው ነገር የለም ” ነው ያሉት።

“ ማኀበረሰቡ ከፓሊስና ከፀጥታ አካላት የሚተላለፉ መረጃዎችን በቁም ነገር ማዳመጥ፣ አካባቢውን ማዬት መቻል አለበት። በሰላምና በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም። እነዚህ ሰዎች መካከላችን አሉ። ይሄ አንዱ ማሳያ ነው። ቦሌ መሀል ከተማው ላይ እንግዲህ እየኖሩ ነው የነበረው ” ብለዋል ኮማንደር ማርቆስ።

“ እነዚህ ሰዎች መንፈስ አይደሉም። በተሽከርካሪያቸው ሲወጡ ሲገቡ ይታያሉ። ግን ፓሊስ በራሱ ነው ሲከታተተል የነበረው ” ያሉት ኮማንደር ማርቆስ፤ አሁንም ማህበረሰቡ አካባቢውን መጠበቅ አለበት ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በጽንፈኛው ኃይል አመራር እና አባል ላይ እርምጃ ተወስዷል‼️

🗣 ፖሊስ

በፅንፈኛው ኃይል አመራርና አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
በተወሰደው እምርጃም÷ የፅንፈኛው አመራርና አንድ የቡድኑ አባል መገደላቸው ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም አንደኛው በቁጥጥር ስር ውሏል ነው ያለው ፖሊስ፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.