ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ‼️

የኢራን ቁልፍ ወደብ በሆነው ሻሂድ ራጃኢ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ 800 የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል።

በፍንዳታው 6 ሰዎች የደረሱበት አለመታወቁም ነው የተጠቆመው።

አደጋው ከተነሳበት ስፍራ እስከ 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ድረስ ያሉ ተሽከርካሪዎች እና ህንፃዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ነው የተጠቆመው።

"ፍንዳታው ለኢራን ባሊስቲክ ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ እንዲውል የታሰበው የሶዲየም ሮኬት ነዳጅ ወይም ሶዲየም ፐርክሎሬት የሚባለው ኬሚካል በትክክል ባለመጫኑ ሳቢያ የተከሰ ነው" ሲል የዓለም የባህር ስጋት አስተዳደር ድርጅት አምበሪ ኢንተለጀንስ አስታውቋል።

አምበሪ ኢንተለጀንስ ከዚህ ቀደም በሻሂድ ራጃኢ ያለውን አግባብነት የጎደለው የኬሚካል አቀማመጥን በተመለከተ ማስጠንቀቂያን ሰጥቶ እንደነበርም አስታውሷል።

ጭነቱን በተመለከተ የፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ሁለት የሶዲየም ሮኬት ነዳጅ የጫኑ መርከቦች ከቻይና ወደ ኢራን መግባታቸውን አመላክቶ ነበር።

አደጋውን ተከትሎ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን በአደጋው ለተጎዱ እና ህይወታቸው ላለፈ ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።

በዚህም ፍንዳታው የተከሰተው የእሳት ቃጠሎ ከተነሳ በኋላ ተቀጣጣይ ቁሶችን በውስጣቸው በያዙ እና ያልተዘጉ ወደ ነበሩ ኮንቴነሮች መዛመቱን ተከትሎ መሆኑን ጠቅሷል።

አሜሪካ ኢራን የራሷን የኒኩሌር ኃይል እንዳታበለፅግ ለማድረግ ውይይቶችን እያካሄደች ባለበት ወቅት የተከሰተው አደጋው ሀገራቱን ውጥረት ውስጥ የሚያስገባ ሊሆን ይችላል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


🏪 ዓይን በሆነ ቦታ በመሀል °ፒያሳ ከአድዋ ሙዝየም ፊት ለፊት 4200ካሬ ላይ ያረፈ ግዙፍ B+G+5 የገበያ መአከል በግንባታ ላይ ነን (እዚህ ትልቅ ሞል ውስጥ 1 ሱቅ ይገባዎታል)

              
🏗️ለንግድ እና ለቢሮ ሱቆች የሚሆን ⛏️

✅ Location ከአድዋ ሙዝየም ፊት ዋና መንገድ ዳር

✅ ለሁሉም የንግድ እና ቢሮዎች የሚውሉ

✅ መመዝገብያ ቅድመ ክፍያ" 900ሺ" ብር ጀምሮ

✅ ጠቅላላ ዋጋ ከ3.9 _10 ሚልዮን

✅ ስፋት ከ20 ካሬ ጀምሮ

✅ መረከብያ 18 ወራት

✅ 100% ለሚከፍል 10% ቅናሽ(discount )

ለበለጠ መረጃ ከታች ባለው ስልክ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
በ0950044741 ወይም 0967130342(whatsapp ) ይጠቀሙ


አሜሪካ ኤምባሲ ለዜጎቹ በሰጠው የማስጠንቀቂያ መልዕክት ስር በፌደራል ፖሊስ ስም የተሰጠው አስተያየት በተቋሙ ያልተላለፈ መሆኑን ፖሊስ አስታወቀ‼️

ተቋማችንን አስመልክቶ በአንዳንድ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ  የሚዘዋወረውን የተዛባ መልዕክት ተመልክተናል። በአዲስ አበባ ከተማ አንዳች
የፀጥታ ችግር ያለ ለማስመሰል የተደረገውን ጥረትም አስተውለናል።

ይሁን እንጂ እስከአሁን ባደረግነው ማጣራት መልዕክቱ በተቋማችን እንዳልተላለፈ እና ተቋማችንን የማይወክል መሆኑን እያስታወቅን ፖሊስም ጉዳዩን የበለጠ እያጣራ እንደሚገኝ እንገልፃለን።

የተላለፈው መልዕክትም ፍፁም ከከተማችን ነባራዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር የማይገናኝ ሲሆን አሁን ላይ የከተማችን ሰላምና ደኅንነት ከምን ጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ እንዳለ እንገልፃለን።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቀርበው የነበሩት አቶ ታዬ ደንዳአ ለምስክርነት የጠሯቸው ጠ/ሚር አብይ አህመድ እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፍርድ ቤት ሳይገኙ ቀርተዋል‼️

የፍርድ ቤቱ ፖስተኛ መጥሪያውን ይዞ ሲሄድ ጥበቃዎች መጥሪያ መሆኑን ካረጋገጡ በኋላ ወደ  ፅህፈት ቤታቸው እንዳይገባ ተደርጎ መመለሱ ታውቋል።

የአቶ ታዬ ጠበቃ "ተራ ፖስተኛ አድርጋችሁ ለምን ተመለሰ ትላላችሁ? የፍርድ ቤት መጥሪያ መሆኑን ሲያውቁ ከበር እንዲመለስ የተደረገው የፍርድ ቤቱን መናቅ ነው" በማለት በቀጣይ ማንኛውም ዜጋ አልቀርብ ሲል ተገዶ እንደሚመጣው ሁሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ከንቲባዋ ተገደው እንዲመጡ ለፌደራል ፖሊስ ትዕዛዝ ይፃፍልኝ ሲል ጠይቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የሩሲያ ከፍተኛ የጦር አዛዥ በመኪና ላይ በተጠመደ የቦምብ ጥቃት ተገደሉ‼️

የሩሲያ ከፍተኛ የጦር አዛዥ የሆኑት ሜጀር ጄኔራል ያሮስላቭ በሞስኮ ከተማ አቅራቢያ በመኪና ላይ በተጠመደ የቦንብ ጥቃት ህይወታቸው ማለፉን የሩሲያ ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

ጄኔራሉ በአካባቢው እያለፉ በነበረበት ወቅት በሪሞት የሚዘወር ቦንብ የተጠመደበት መኪና ፈንድቶ ጥቃቱ እንደደረሰባቸው የሩስያው አርቲ ዘግቧል፡፡

ጥቃቱን ተከትሎ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ "ሞስኮ የዩክሬንን ጦርነት ለማስቆም ከአሜሪካ ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ ነበረች፤ ሆኖም ግን ቆም ብሎ ማሰብ ያስፈልጋል" ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ጥቃቱ ከዚህ ቀደም ዩክሬን በሩሲያ አመራሮች ላይ ከሰነዘረቻቸው ጥቃቶች ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን ዘ ጋርዲያን በዘገባው አመላክቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሲም ካርድ በመጠቀም ፈንጂዎችን ለማፈንዳት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን ይዣለሁ ሲል የጎንደር ከተማ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አስታወቀ‼️

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ “ሲም ካርድ በመጠቀም ፈንጂዎችን በማፈንዳት የህብረተሰቡን ሰላም ለማደፍረስ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ ሶስት ተጠርጣሪዎች” ይዣለሁ ሲል ገለጸ።

"ተጠርጣሪዎች ገበያ ስፍራዎች በትምህርት ቤቶችና እንዲሁም ህዝብ በሚሰበሰብባቸው ስፍራዎች ፈንጂዎችን በማጥመድ የሽብር ተግባር ለመፈጸም ዝግጅት እንደነበራቸው" ባካሄድነው ምርመራ አረጋግጠናል ሲሉ የመምሪያው ኃላፊ አቶ አለልኝ ዓለም ትላንት ሚያዚያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

"ፍንዳታውን የሚያካሂደው በፈንጂው ላይ በሚታሰር የሞባይል ቀፎና ሲም ካርድ በመታገዝ ወደ ሲም ካርዱ በመደወል ፍንዳታውን በርቀት ሆነው እንደሚያካሂዱ" ተደርሶበታል ብለዋል፡፡

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አለልኝ ዓለም በመግለጫቸው "ተጠርጣሪዎቹ ከቀናት በፊት ምሽት ላይ በከተማው አንድ ፖሊስ ጣቢያና በክፍለ ከተማ ጽህፈት ቤት ላይ ፈንጂ በማፈንዳት ተሰውረው የቆዩ ናቸው" ማለታቸውን ከከተማዋ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

"የፀጥታ መዋቅሩ ባደረገው ጥብቅ ክትትልና ስምሪት ተጠርጣሪዎቹ ሌላ የሽብር ተልእኮ ለመፈጸም በአንድ የግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ በድብቅ ካዘጋጁዋቸው የፈንጂ መሳሪያዎች ጋር በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል" ማለታቸውንም መረጃው አካቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አልሸባብ በሶማሊያ ቁልፍ ነው የተባለ ወታደራዊ ማዘዣ ላይ ጥቃት ፈፀመ‼️

አልሸባብ በዋርጋዲ በሚገኘው የሶማሊያ ጦር ማዘዣ ላይ ጥቃት መፈፀሙ ሲዘገብ ከሁለቱም ኃይሎች በኩል ጉዳት ስለመድረሱ ተሰምቷል።

አልሸባብ ማዘዣውን እና መንደሩን መቆጣጠሩን ሲገልፅ የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስትር አሁንም የጦር ማዘዣው በእኛ ቁጥጥር ስር ነው ብሏል።

ዋርጋዲ ባለፈው ሳምንት አልሸባብ ከተቆጣጠረው አደን ያባል ቀጥሎ በማዕከላዊ ሸበሌ የሚገኝ ሁለተኛው ትልቁ ወታደራዊ ማዘዣ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሚስቱን ገድሎ ሊሰወር የሞከረዉ ግለሰብ በፖሊስና በሕብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ሊዉል ችሏል‼️

🗣 የጋሞ ዞን ፖሊስ

በአርባ ምንጭ ከተማ ባለቤቱ ገድሎ ሊሰወር የነበረ ግለሰብ መያዙን ፖሊስ ገልጿል።

ኮማንደር ሬታ ፤ የገዛ ባለቤቱን በመሳሪያ ተኩሶ በመግደል ሊሰወር የሞከረዉ ተጠርጣሪ በሕዝቡና በፖሊስ ትብብር በቁጥጥር ስር መዋሉን ተናግረዋል።

ተጠርጣሪው አቶ ነብዩ ጌታቸው ኤፍሬም እንደሚባልና ከሟች ጋር በትዳር ዓለም አብረዉ እንደነበሩ በመካከላቸዉ በነበረው አለመግባባት ሟች ወላጆቿ ጋር በመሄድ ላለፉት 5 ወራት ከቤተሰቦቿ ጋር ትኖር እንደነበር ገልፀዋል።

በትናትናዉ ዕለት ተጠሪጣርዉ አስቦና አቅዶ ጧት 4 ሰዓት ገደማ " ላናግርሽ እፈልጋለሁ " በማለት ካስጠራት በኋላ ሰዉ የማያይበትን ሁኔታ በማመቻቸት በሽጉጥ አንገቷ ስር ደቅኖ ተኩሶ እንደ ገደላት አስረድተዋል።

በኃላም ለመሸሸግና ለመሰወር ሲሞክር በፖሊስ ክትትልና በሕብረተሰቡ ትብብር በቁጥጥር ስር ዉሎ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዉና ሟች በትዳር አብረዉ በነበሩበት ወቅት አንድ ልጅ አፍርተዉ እንደነበርም የፖሊስ መረጃ ያመለክታል።

ተጠርጣሪዉ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀመበትን ሽጉጥ ወንዝ ዉስጥ እንደጣለ ቢገልፅም ፖሊስ ባደረገዉ ማጣራት ከደበቀበት በኤግዚቢትነት ይዞታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ሐሙስ ሚያዝያ 9/2017 ዓ.ም. በትምህርት ቤት ዙሪያ በደረሰ የድሮን ጥቃት ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ‼️

በዞኑ እናርጅ እናውጋ ወረዳ ገደብ በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ የትምህርት ቤት አጥር ለማጠር እና ቤት ለመሥራት 'ለልማት ሥራ' የወጡ "ሰላማዊ ሰዎች" በጥቃቱ መገደላቸውን ገልፀዋል።

የአካባቢው አስተዳደር ግን ጥቃቱ በአካባቢው ተሰብስበው በነበሩ የፋኖ ታጣቂዎች ላይ እንጂ በንፁሃን ነዋሪዎች ላይ አለመፈጸሙን ለቢቢሲ ገልጸዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ተራ አስከባሪ ግብር እንዲከፍሉ ተወሰነ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የታክሲ ተራ አስከባሪ ማኅበራት ከገቢያቸው 20 በመቶውን ለመንግሥት እንዲሰጡ የሚያስገድድ ደንብ አጽድቋል።

ደንቡ ማኅበራቱ “ዝግ እና መደበኛ የባንክ አካውንት" እንዲከፍቱና ከሁለት ዓመት በኋላ “ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ እንዲሸጋገሩ” ግዴታ ይጥላል።

“የተርሚናል አገልግሎት አሠራርና ቁጥጥር” የተሰኘው ደንብ፣ ኢንተርፕራይዝ በማለት የሠየማቸው ማኅበራት የሚደራጁት በከተማዋ የሥራና ክህሎት ቢሮ መስፈርት መኾኑን ታውቋል።

ኢንተርፕራይዞቹ 30 በመቶ  “የግዴታ ቁጠባ” መቆጠብ፣ 50 በመቶውን በተንቀሳቃሽ የባንክ ሒሳብ ማስቀመጥና ያንድ ዓመት ውል መፈረም እንዳለባቸውም ይደነግጋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ‼️

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ፖሊስ በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታወቀ‼️

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በርካታ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ከ146 ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውርን ለመከላከል በተደረገ ኦፕሬሽን፤ 121 የጦር መሣሪያዎችን ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች እና 36 የጦር መሣሪያዎችን በኬላዎች ላይ መያዙን ገልጿል፡፡

በተጨማሪም 6 ሺህ 351 የተለያዩ የጦር መሣሪያ ጥይቶች ከመኖሪያ ቤቶች፣ 8 ሺህ 989 ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 51 ሺህ 846 በኬላዎች ተይዘዋል መባሉን የፌደራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

እንዲሁም 236 የተለያዩ የጦር መሣሪያ ካዝናዎች በመኖሪያ ቤቶች እና 148 በኬላዎች ላይ መያዛቸው ተጠቁሟል፡፡

በተመሳሳይ 1 ብሬን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 2 ብሬን በኬላዎች የተያዘ ሲሆን፤ 31 የተለያዩ ቦምቦች ከመኖሪያ ቤቶች፣ 25 ቦምቦችን ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 122 ቦምቦችን በኬላዎች መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

32 የተለያዩ ሕገ-ወጥ ሽጉጦች ከመኖሪያ ቤቶች፣128 ሽጉጦች ከፀረ-ሰላም ኃይሎች፣ 102 በኬላዎች መያዝ መቻሉንም ጠቅሷል፡፡

1 ስናይፐር ከመኖሪያ ቤቶች እንዲሁም 1 ስናይፐር ከፀረ-ሰላም ኃይሎች በኤግዚቢትነት መያዙን እና 146 ተጠርጣሪዎችም በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስረድቷል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከ14 ዓመት መለያየት በኃላ አርቲስት ገነት ንጋቱ እና አርቲስት ሙሉጌታ ጀዋሬ በድጋሚ ተሞሸሩ‼️

ሁሉቱም በማልቀስ ደስታቸውን የገለፁ ሲሆን ሁሉንም ነገር ለፈጣሪ ሰጥተን ድጋሚ ትዳርን አንድ ብለን ጀምረናል ያሉት ጥንዶች መልካም ምኞታችሁን ተመኙልን ብለዋል::

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የ12ኛ ክፍል ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው‼️

🗣 ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር)

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንደሚሰጥ ጠቁመው " ይሄ አራተኛው ነው በአዲሱ የፈተና አሰጣጥ ፈተና የሚሰጥበት " ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ባለፉት ዓመታት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከትምህርት ቤቶች ወጥቶ ተማሪዎችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አስገብቶ ፈተና እንዲሰጥ እያደረገ መሆኑ አስታውቀው ትምህርት ሚኒስትሩ ስለዘንድሮው የ2017 ዓ/ም ፈተና 150 ሺህ ተማሪዎች ፈተናቸውን በኦንላይ እንዲወስዱ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ፥ " እንደ ከዚህ ቀደሙ አድካሚ በሆነ ከቦታ ቦታ ልጆችን እያዘዋወሩ ከመሄድ ባለፈው ዓመት 29 ሺህ ተማሪ ነበር ኦንላይን ፈተና የሰጠነው ዘንድሮ ደግሞ 150 ሺህ ተማሪ ኦንላይን ፈተና ለመስጠት እየተዘጋጀን ነው " ያሉ ሲሆን ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን ቀን ቆርጠው ባይናገሩም ፈተናው ከአንድ ወር / ከአንድ ወር ተኩል በኃላ እንዲሰጥ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የለማ መገርሳ ቤተሰቦች ታሰሩ‼️

🗣ጀዋር ማህመድ

የለማ መገርሳ ቤተሰብ አባላት መታሰራቸውን ፖለቲከኛው ጃዋር አረጋግጬአለሁ አለ። ከፖለቲካ ውጭ የሆኑ ቤተሰቡ መታሰራቸው ነውር ነው። ለማ ለምን ዝም አለን ተብሎ እንዴት ቤተሰቡ ይታሰራሉ በማለት መልዕክቱን በፌስቡክ ገፁ ላይ አጋርቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብሩን ዛሬ ጠዋት ማከናወናቸውን የጽሕፈት ቤቱ መረጃ ያመላክታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ የችሎት ሂደትን ጋዜጠኞች እንዳይታደሙ በፍርድ ቤት ታገዱ‼️

ዛሬ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በፍቅረኛው ወጣት ሞዴል ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ተጠርጥሮ በምርመራ ሂደት ላይ የሚገኘው የአርቲስት አንዱዓለም ጎሳ ጉዳይ በታየበት ችሎት ነው ፍርድ ቤቱ መገናኛ ብዙሃን ችሎቱን እንዳይታደሙ ያገደው፡፡

በዛሬው ችሎት ፖሊስ የመገናኛ ብዙሃን በተለያዩ ጊዜያት “ የችሎቱን ውሎ በተደጋጋሚ አዛብተው ዘግበውታል ” በሚል የምርመራ ሂደቱ ላይ እክል በመፍጠራቸው በችሎቱ እንዳይታደሙ ጠይቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ በችሎቱ የተጠየቁት የተከሳሽ ጠበቃ በፊናቸው ፖሊስ ያቀረበውን አቤቱታ እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡

ችሎቱም ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ " መገናኛ ብዙሃን ካሁን በፊት አንድ ጊዜ ተከሳሽ ለፋሲካ በዓል ወጥቶ ኮንሰርት ለማዘጋጀት ጠይቋል፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሟች የግል ማህደር (ዳይሪ) በተከሳሽ ጠበቃ እጅ ነው የሚገኘው የሚሉ የተዛቡና ሀሰተኛ ዘገባዎች ማቅረባቸው በችሎቱና በምርመራ ሂደቱ ላይ እክል እንደሚፈጥር በመታመኑ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች (ጋዜጠኞች) ችሎቱን እንዳይታደሙ " በሚል ብይን ሰጥቷል።

በዛሬው ችሎት የታደሙትን ጋዜጠኞችን በዳኛ ትዕዛዝ እንዲወጡ ተደርገዋል።

መጋቢት 01 ቀን ሌሊት ለመጋቢት 02 ቀን 2017 ዓ.ም. አጥቢያ የመኖሪያ ቤቷ ከሚገኝበት ህንጻ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ በተሰማው በወጣት ቀነኒ አዱኛ ህልፈት በፖሊስ የተጠረጠረው ፍቅረኛዋ ድምጻሚ አንዱዓለም ጎሳ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ምክር ቤቱ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል‼️

6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 25ኛ መደበኛ ስብሰባ ነገ ይካሄዳል።

ምክር ቤቱ በ25ኛ መደበኛ ስብሰባው የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

በተጨማሪም የተቀናጀ የውኃ ሀብት አስተዳደር ማስፈጸሚያ የተፋሰሶች ከፍተኛ ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የውኃ፣ መስኖ እና ቆላማ አካባቢዎች እና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጁን ያፀድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ትምህርት ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ መሆን አለበት‼️

🗣ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ዘርፉ ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ ሆኖ ለትምህርት ዓላማ ብቻ መዋል እንዳለበት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ሚኒስትሩ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት የዘጠኝ ወራት የትምህርት ዘርፍ አፈጻጸም 5 ሺህ ትምህርት ቤቶች ከሥራ ውጭ መሆናቸውን እና በዚህም ምክንያት 7.2 ሚሊዮን ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት አለመቻላቸውን አስታውቀዋል፡፡

ለመምራን እና የትምህርት አመራሩ መንገላታት እና ለትምህርት ቤቶቹ መዘጋት ምክንያት በየአካባቢዎቹ የሚፈጠሩ ግጭቶች መሆኑን አውስተው፣ ይህ ደግሞ እንደ ሕዝብ ትልቅ ኪሳራ ነው ብለዋል፡፡

ትምህርት ከፖለቲካ ማራመጃነት ነጻ ቢሆን አሁን የተከሰተው ችግር ባልተከሰተ ነበር ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ አካላት ሁሉ የትምህርት ዘርፉን ከጥቃት መጠበቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

እንደ ኅበረተሰብ አይነኬ የሚባሉ ነገሮች መኖር አለባቸው ያሉት ሚኒስትሩ፣ የፖለቲካ ግጭቶች በሚኖሩባቸው አካባቢዎች መምህራንን ማገት እና መግደል እንዲሁም ትምህርት ቤቶችን መዝጋት ሊቆም እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ስለ መምህራን ደመወዝ እና ማበረታቻ በምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ የተነሳላቸው ፕሮፌሰር ብርሃኑ፣ የመምህራንን ደመወዝ ማሻሻል ያልተቻለው አጠቃላይ ባለው በሲቪል ሰርቪስ አሠራር ምክንያት እንደሆነ እና ይህም ሆኖ በተቻለ መጠን መምህራን ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ዘዴ ለመፍጠር እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡

መምህርነትን የተከበረ ሙያ ማድረግ ምንም አጠያያቂ እንደማይሆን አውስተው፣ ለዚህ ደግሞ መምህራን ልጆቻቸውን ምን እንደሚያበሉ የሚጨነቁበት ደረጃ ላይ እንዳይወድቁ የተለያዩ የማትጊያ ሥርዓቶችን ለመዘርጋት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

አሁን ወደ ፍጻሜው እየደረሰ ያለውን የመምህራን ባንክን ለመመሥረት የተፈለገውም መምህራን ቢያንስ መሰረታዊ የሆነውን የመኖሪያ ቤት እንዲያገኙ ለመደገፍ ታልሞ ነው ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1

19 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.