ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


በትናንትናው እለት ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ተጓዦች ታገቱ‼️

🗣መሠረት ሚድያ

- በተከፈተ የተኩስ እሩምታ የሞቱ መንገደኞችም እንዳሉም ታውቋል

ከባህር ዳር ከተማ ተነስተው በትናንትናው እለት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ የነበሩ የአንድ አውቶቡስ ተሳፋሪ መንገደኞች በመንገዳቸው መሀል እንደታገቱ ታውቋል።

ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው እገታው የተፈፀመው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጎሀፂዮን ከተማ አቅራቢያ ነው። ታጣቂዎቹ የተኩስ እሩምታ አውቶቡሱ ላይ በመክፈታቸው የተገደሉ መንገደኞች እንዳለ የታወቀ ሲሆን የተረፉትን ይዘው ወደ ጫካ መግባታቸው ታውቋል።

"ከእገታው ያመለጡ የተወሰኑ ሰዎች አሉ፣ የፌደራል ፖሊስ ደርሶ ከታጣቂዎች ጋር እየተታኳሱ ነው" በማለት አንድ የአካባቢው ምንጭ ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

ድርጊቱ መፈፀሙን 'የሹፌሮች አንደበት' የተባለው ገፅ ያረጋገጠ ሲሆን "ከጎሀፂዮን እና ቱሉ ሚሊክ ማዕከል አንድ አውቶብስ ሙሉ ሰው ታፍነው መወሰዳቸውን እና በተተኮሰ ጥይት የተሳፋሪ ህይወት ማለፉ ተሰምቷል" ብሏል።

በተመሳሳይ ከሁለት ሳምንት በፊት በፍቼ እና ጎሀፂዮን ከተሞች መሀል 58 ዜጎች መታገታቸው ይታወሳል። እነዚህን መንገደኞች ለመልቀቅ መንግስት 'ኦነግ ሸኔ' ብሎ የሚጠራቸው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት ለአንድ ታጋች እስከ 1.5 ሚልዮን ብር እየጠየቁ እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።

መጋቢት 8 ቀን የተፈፀመው ይህ እገታ በመንግስት ሚድያዎችም ሆነ በባለስልጣናት ምንም ቃል ያልተተነፈሰበት መሆኑ እጅጉን እንዳሳዘናቸው የታጋች ቤተሰቦች ገልፀው አሁን ላይ የቻሉትን ለመሰብሰብ የየቤቱ እየዞሩ እየለመኑ እንዲሁም በሶሻል ሚድያ ለህዝብ የእርዳታ ጥሪ እያቀረቡ መሆኑን ጠቁመው ነበር።

በዚህ መስመር ከዚህ በተደጋጋሚ እገታዎች የሚፈፀሙ ሲሆን በአካባቢው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት በስፋት እንደሚንቀሳቀሱበት ይታወቃል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




በሰሜን ሸዋ የቀጠለዉ እገታና አንድምታ ዝምታዉ ለምን?

🗣ታዬ ደንደአ ከፃፉት

ሰሜን ሸዋ ኦሮሚያ ክልል... እጅግ አደገኛ የእገታ ወንጀል ለዓመታት ቀጥሏል። የዞኑ ነዋሪዎች በየተራ ከከተማና ከገጠር ይታገታሉ። እገታዉ በተመሳሳይ በመንገደኞች ላይም ሲፈፀም ዛሬ ደርሷል። ለታጋቾች ማስለቀቂያ በሚሊየኖችና በመቶ ሺዎች ይጠየቃል። የቻለ ጥሪቱን ሽጦ ወይም ዘመድ አዝማድ አስቸግሮ በመክፈል ይለቀቃል። ከፍያዉ ደግሞ ከካሽ ባሻገር በባንኮች ጭምር እንደሚፈፀም ኢሰመኮም አረጋግጧል። መክፈል ያልቸለዉ እንደሚገደልም ታዉቋል። በዚህ ምክንያት ብዙዎች ጥሪታቸዉን በመነጠቅ ለከባድ ችጋር ተጋልጧል። በርካቶችም ህይወታቸዉን አጥቷል።

ትላንትም በሰሜን ሸዋ ወረ-ጃርሶ ወረዳ የተለመደዉ አሳዛኝ የእገታ ወንጀል መፈፀሙን ሰምተናል። አንድ የመንገደኞች አዉቶቢስ ላይ ተኩስ ተከፍቶ በርካቶች ሲቆስሉ ከአስር በላይ ንፁኃን ዜጎች መገደላቸዉ ተዘግቧል። ታፍነዉ የተወሰዱ ስለመኖራቸዉም ይነገራል። ዜጎች በዚህ ሁኔታ መንገድ ላይ መቅረታቸዉ እጅግ ያሳዝናል። የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት አካል ግን  የፓርክና የሪዞርት ግንባታ ላይ አተኩሯል።

ከሁለት ቀን በፊት አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር ሁለት መቶ ብር  ጉቦ መቀበሉ ትልቅ ዜና ነበር። ኢቲቪና ፋናም "ሌብነት ላይ ለተጀመረዉ ትግል አበረታች እርምጃ" ብለዉታል። ከሳምንት በፊትም "ሀሰተኛ መረጃን ለማጋለጥ" ጥረዋል። ጉዳዩ የማይመለከታቸዉ ባለስልጣናት ጭምር በየተራ ወጥተዉ የብርቱካን ድራማ "ኢትዮጵያን ለመግደል የተሸረበ ሴራ ነዉ" ብለዉናል። የበርካታ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈዉና አካል ያጎደለዉ የትላንቱ ወንጀል ግን ዝም ተብሏል። የሁለት መቶ ብር ጉቦ ያንበገባቸዉ ኢቲቪና ፋና በሚሊዬኖች እየዘረፈ ብዙ ዜጎችን ለመከራ ያጋለጠዉ ተደጋጋሚ የእገታ ወንጀል ምንም ያልመሰላቸዉ ለምን ይሆን? የኢትዮጵያ ህዝብ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይጎዳ በዚያ ልክ የተረባረቡት ሚዲያዎችና ባለስልጣናት ንፁኃን ዜጎች በየግዜዉ በመታገት ሲገደሉና አካላቸዉን ሲያጡ ለምን አያማቸዉም? በድራማዉ የታሰበለት የኢትዮጵያ ህዝብ የትላንቱን ተጎጂዎች አያጠቃልልም እንዴ?

ተጨማሪ ጥያቄዎችም አሉ። መጠኑ ቢለያይም በኦሮሚያ የነዋሪዎች እገታ በየቦታዉ ተለምዷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በአብዛኛዉ ቅንጦት ሆኗል። ሰላም ሳይረጋገጥ ስለብልፅግና መስበክም ቀልድ ይሆናል። ይሁንና በዚህ ሁሉም ይመሳሰላል። በመንገደኞች እገታ ላይ ግን ግልፅ ልዩነት ይታያል። ከመንገዶች ሁሉ የጎጃም መስመር በዋናነት ተደጋጋሚ ጥቃቶችን አስተናግዷል። የዚህ መስመር ላይ ብዙዎች ተዘርፈዉ ለመከራ ሲጋለጡ በርካቶች ህይወታቸዉንና አካላቸዉን አጥተዋል። ሚስጢሩ ምንድ ነዉ? አጋቹስ በትክክል ማን ይሆን? ተመሳሳይ ወንጀል በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ቦታ ላይ ለምን ይፈፀማል? ኃላፊነት ያለበት አካልስ ለምን ዝም ይላል? ይህ አደገኛ ወንጀል በመንግስት ሚዲያ የማይዘገበዉስ ለምንድነው? በርግጥ የእገታዉ ዓላማ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ነዉ ወይስ የፖለቲካ ቁማር አለበት? ምናልባት የፖለቲካ ቁማር ኖሮበት ዓላማዉ ኦሮሞንና አማራን ለማጣላት ከሆነ ውጤቱ ማንን ይጠቅማል? ኢቲቪና ፋና ልክ እንደብርቱካን "ድራማ" ተረባርበዉ ቢያጋልጡትስ?

ለሟች ወገኖቻችን እጅግ አዝኛለሁ! የቆሰሉትም ፈጥነዉ ይድኑ ዘንድ እመኛለሁ! ዋናዉ ጉዳይ ግን የፖለቲካ ቀዉሱንና እንቆቅልሹን መፍታት መሆኑን ልብ እንበል እላለሁ!

@Esat_tv1
@Esat_tv1




Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በፖሊስ ተሽከርካሪ ውስጥ ሆኖ ብር ሲቀበል በቪዲዮ የታየ የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር ዋለ‼️

በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው ሰሜን ማዘጋጃ አካባቢ ኢንስፔክተር ኤርሚያስ ኤርጌኖ የተባለው የፖሊስ አባል በፖሊስ ተሽከርካሪ ውስጥ ሆኖ ሁለት መቶ የብር ኖት ሲቀበል የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ መዘዋወሩን መነሻ ባደረገ መረጃ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቀው ተንቀሳቃሽ ቪዲዮ አባሉ በተሽከርከሪ ውስጥ ተቀምጦ ሪሲቲ እየሰጠ የ200 ብር ኖት ጉቦ ሲቀበል የሚያሳይ ነው፡፡

በፖሊስ አገልግሎት አሰጣጥ ተገልጋዩን የሚያማርሩ እና የተቋሙን መልካም ገፅታ ከሚያበላሹ ህገ-ወጥ ተግባራት ውስጥ ጉቦ መቀበል አንዱ መሆኑን የገለፀው ፖሊስ፤ መሰል ህገ-ወጥ ተግባር በሚፈፅሙ አመራርም ሆነ አባላት ላይ እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት መብታቸውን በገንዘብ የሚገዙም ሆነ ህገ-ወጥ ተግባር ፈፅመው ጉቦ በመስጠት ከተጠያቂነት ለማምለጥ የሚሞክሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ያሳሰበው ፖሊስ ብልሹ አሰራርን ለማጋለጥ በተለያዩ አግባቦች መረጃን የሚሰጡ አካላትን በማመስገን በቀጣይም መረጃዎችን በማድረስ የህብረተሰቡ ተባባሪነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አሰ‍እተላልፉዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱን ካቆመች ጀምሮ ከ1 ሺህ በላይ ፍልስጤማዊያን መገደላቸዉ ተገለጸ‼️

ባለፉት 24 ሰዓታት ብቻ በጋዛ እና አከባቢዉ ላይ 1መቶ ፍልስጤማዊያን መገደላቸዉ ተዘግቧል፡፡

እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነቱን ካቆመች በኋላ ባደረሰችዉ ጥቃት የሞቱ ፍልስጤማዊያን ቁጥር 1ሺህ 1መቶ 63 ደርሷል ተብሏል፡፡

እንደ ፍልስጤም ጤና ሚኒስቴር ከሆነ በጥቅምት 7 በተጀመረዉ ጦርነት ህይወታቸዉ ያለፉ ፍልስጤማዊያን ቁጥር 50ሺህ 5መቶ23 ደርሷል፡፡

ደህንነቱ የተጠበቀ ነዉ በተባለዉ በምዕራብ ካን ዩኒስ በሚገኘዉ አል-ማዋሲ የስደተኞች መጠለያ ዉስጥ የነበሩ ተፈናቃይ ፍልስጤማዊያን የእስራኤል የዓየር ጥቃት ኢላማ መሆናቸዉም ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም በጋዛ ከተማ በሚገኝ አንድ መንደር ላይ ባደረሰችዉ ሌላ ጥቃት 9 ሰዎች ህይወታቸዉ ሲያልፍ፤ 15 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል፡፡

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚመራ ክሊኒክ ላይ ባደረሰቸዉ እና 70 ሰዎች በተገደሉበት ሌላ ጥቃት  ብዙ ህጻናት ሲገደሉ የፖሊስ አባላትም ህይወታቸዉ አልፏል ሲል ሚድል ኢስት ሞኒተር አስነብቧል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በዛፍ ጥላ ስር የሚኖሩት ከ6 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች ‼️

🗣መሰረት ሚድያ

ከዛሬ ሶስት አመት በፊት ከኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች ተፈናቅለው በደቡብ ወሎ ዞን ሐይቅ ከተማ አቅራቢያ ተጠልለው እንደሚገኙ የተናገሩት ተፈናቃዮቹ ቀደም ሲል በመንግስት ሲቀርብ የነበረው ወርሃዊ ድጋፍ መቋረጡን እና በመጠለያ ካምፑ ውስጥ ርሀብ መከሰቱን ተናግረዋል።

በመጠለያው ውስጥ ከሚኖረት አንዷ ወ/ሮ ሐሊማ ሙሄ ለመሠረት ሚዲያ እንዳረጋገጡት "ሕፃናትና እድሜያቸው ዘለግ ያሉ አረጋውያን በበሽታ ወድቀዋል። ሞተው አፈር ያለበስናቸውም አሉ። ከወለጋ ተፈናቅለን በዚህ ካምፕ ውስጥ የተጠለልነውን ሰዎች የፌደራሉም ሆነ የክልሉ  መንግስት እንደ ዜጋ አይመለከተንም፣ ምግብና መድሀኒት ከተቋረጠ ከአራት ወር በላይ አልፎታል። የሚላስ የሚቀመስ የለም" ሲሉ ነው የነገሩን።

"ካምፑ ለሌላ አገልግሎት ታቅዶ የተቋቋመ በመሆኑ ከወለጋ የመጣው ተፈናቃይ ብዛትና ካምፑ የመያዝ አቅሙ ባለመመጣጠኑ ምክንያት አብዛኛዎቻችን ውለን የምናድረው በአካባቢው ባለ ዛፍ ስር እና ቁጥቋጦ ተጠግተን ነው። ሕፃናት፣ እናቶች እና ሽማግሌዎች ሲኖሩበት የነበረው  ድንኳንም በእርጅና ምክንያት ተቀዳዶ አገልግሎት እየሰጠ ባለመሆኑ ሁላችንም ፀሀይ ላይ ተሰጥተናል" ሲሉ የነገሩን ደግሞ ከተፈናቃዮቹ አንዱ የሆኑት አቶ መሐመድ ይመር ናቸው።

ኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ዞኖች በፀጥታ መደፍረስ ምክንያት በሺህዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች በአማራ ክልል በተለይ በደቡብ ወሎ ሐርቡ፣ ሐይቅ አቅራቢያ፣ መካነ ሰላም፣ መቅደላ ማሻ በሰሜን ወሎ ጃራ፣ በምስራቅ እና በምዕራብ ጎጃም ዞኖች ተጠልለው ይገኛሉ።

እነዚህን ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ለመመለስ እቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም "አሁንም ድረስ ቤትና ንብረታችን  በታጣቂዎች እጅ በመሆኑ ብንመለስ ጥቃት ይደርስብናል" በማለት ተፈናቃዮቹ ስጋታቸውን ገልፀዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




በሚያንማር ከእገታ ነፃ ወጥተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው የሚመልሳቸው አካል በመጥፋቱ ወደ አስፈሪ ካምፖች ሊመለሱ መሆኑን ተናገሩ‼️

በሚያንማር በእገታ ተይዘው ከባድ ስራ ካለ ክፍያ ሲሰሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በአንድ የአካባቢው ጦር ሀይል ከሳምንታት በፊት ነፃ ቢወጡም ወደ ሀገራቸው የሚመልሳቸው አካል በመጥፋቱ ወደ አስፈሪ ካምፖች ሊመለሱ መሆኑን ተናግረዋል።

"ወደ ሀገራችን ለመውጣት ዛሬ ነገ እያልን ወደ አስፈሪው ካምፓኒ ተመለሱ ተባልን" ብለው ለመሠረት ሚድያ ቃላቸውን የሰጡት ኢትዮጵያውያኑ አብዛኞቹ ተዳክመው የሞት አፋፍ ጭምር ላይ ያሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

"በሚያንማር ተገደን የማጭበርበር ስራ ላይ የነበርንና በሚሊተሪ ድጋፍ ነጻ የወጣን ከ730 በላይ የምንሆን ኢትዮጵያዊን በሁለት የሚሊተሪ ካምፖች ሆነን የሀገራችን ምላሽና የማጓጓዝ ስራ ከተጠባበቅን ሁለተኛ ወራችን እያገባደድን እንገኛለን" የሚሉት ዜጎች ይህም ከካምፓኒ ለመውጣት ሲጠየቁ ከነበረው 5 ሺህ ዶላር ነጻ ያደረጋቸው እና የኢትዮጵያ መንግስትም ፓርኮቹ ድረስ ገብቶ ዜጎቹን ለማውጣት ተፈጥሮበት የነበረውን ፈተና ያቀለለ ምቹ አጋጣሚ ነበር ይላሉ።

"እዚህ ካምፕ በቆየንበት የሁለት ወር ጊዜ ውስጥ በየጊዜው ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የወላጆች ኮሚቴ ሒደቱ እየተሰራበት እንደሆነ በሚደርሱን መረጃዎች እየተጽናናን ቆይተናል፡፡ በመካከላችንም የቀዶ ጥገና የተሰራላቸውና ማገገም ያልቻሉ፣ በተፈጥሮ አደጋው አደጋ የደረሰባቸውና የሚፈሳቸው ደም አሁን ድረስ ያላቆመ፣ በአንጀት እና አንገት ህመም ራሳቸውን ችለው መንቀሳቀስ ማይችሉ እና ሌሎችም ጽኑ ህሙማን እንዳሉ እና በቂ ህክምና ማግኘት ማይቻልበት ጠረፍ ላይ መሆናችን ሰው እንዳናጣ እየሰጋን መሆኑን ለሚዲያዎች እና ለመንግስት ተቋማት እያሳወቅን የቆየን መሆናችን ይታወቃል" ብለው አስረድተዋል።

አክለውም "ሚሊተሪው የተያዘውን ምግብ ቢያቀርብም ከሀይማኖታችንና ከሀገራችን የአመጋገብ ባህል ጋር ፈጽሞ የማይሔድ የእስያ ምግብ በመሆኑ በውድ ዋጋ በሽያጭ የሚያቀርቧቸውን ምግቦች እየገዛን እንጠቀም ነበር። አሁን ግን ሁላችንም እጃችን ላይ የነበረንን ገንዘብ ጨርሰን ምግብና መድኃኒት ምንገዛበት የሌለን በመሆኑ ለረሀብ እና ለጤና ችግር ተጋልጠናል፡፡ ይህንን ሁሉ ችግር ያልፋል ብለን በኢትዮጵያ መንግስት እና ኤምባሲዎቹ እየተሰሩ ያሉ እኛን የመመለስ ስራ በተስፋ እየጠበቅን ባለንበት ወቅት ሁላችንንም ያስደነገጠ እና ተስፋችን የቀማን ችግር ተከስቷል፡፡"

"ይህም ከአረመኔያዊ አያያዝ አውጥቶ ካምፕ ውስጥ ያስገባን ሚሊተሪ የእለት ምግብ የሚለውን እያቀረበ የሀገራችን ምላሽ እየተጠባበቀ የነበረ ቢሆንም ከኢትዮጵያ መንግስት እና በኤምባሲዎቻችን በኩል እየተሰራ ያለው እኛን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ እጅጉን የተጓተተ በመሆኑ እና ከ29 ሀገራት እኛ ብቻ በመቅረታችን ሚሊተሪው በኢትዮጵያ መንግሥት ተስፋ ቆርጦ ወዷ ካምፓኒዎች እንዲንመለስ ሊጠይቀን ችሏል" በማለት በሀዘን ያሉበትን ሁኔታ ለመሠረት ሚድያ አስረድተዋል።

"ይህም በብዙዎቻችን ላይ ትልቅ ሽብርና መደናገጥ የፈጠረ አደገኛ ክስተት ሆኖ ለጭንቀት የዳረገን ጉዳይ ነው። በመሆኑም ሚዲያዎች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ኤምባሲዎች ለዚህ አደገኛ ሒደት ፈጣን ግብረ መልስ በመስጠት ወደ ሀገራችን መመለስ ካልቻሉ መቀልበስ የማንችለው የ735 ወጣት ህይወት አደጋ ውስጥ እየገባ እንደሆነ ማሳወቅ እንፈልጋለን" ብለዋል።

"የኢትዮጵያ መንግስት እኛን የመመለስ አቅም የለውም ወይ? መልሱ አዎ ከሆነ ተመልሰን እዛ ካምፓኒ ከምንገባ እዚሁ እራሳችንን እናጠፋለን፣ የመጨረሻ አማራጭ እሱ ነዉ፣ የመጨረሻ ዛሬ ተስፋ ቆርጠናል፣ ጭንቀታችን በርትቷል ስለዚህ መልስ እንፈልጋለን" በማለት ተናግረዋል።

እስራኤል የተባለ አንድ ኢትዮጵያዊ "አሁን በምንገኝበት ቦታ ላይ ምግብ በቀን አንዴ እና አልፎ አልፎ ሁለቴ ይሰጣሉ፣ የሚጠጣ ውሃ ስለሌላ የመጸዳጃ ውሃ ነው የምንጠጣው። የምንተኛው መሬት ላይ ነው፣ በረሀብ እና በህክምና እጦት እያለቀን ነው፣ እኛ ያለንበትን አካባቢ የሚያስተዳድረው DKBA (Democratic Karna Buddhist Arm) ይባላል። አካባቢው ያልተረጋጋ እና ጦርነት ያለበት ነው ስለዚህ ለእኛ ትልቅ ስጋት ፈጥሮብናል፣ ሌሎች አገራት ወጥተው አለቁ፣ ዛሬ ራሱ ዩጋንዳ አውጥቷል። ኢትዮጵያውያን ብቻ ቀርተዋል። ሌሎች አገራትን ሊያወጡ ሲመጡ ስንጠይቃቸው የኢትዮጵያ መንግሥት መልስ አይሰጥም ይሉናል" ብሏል።

"የሌሎች ሀገራት 40 እና 30 ዜጎች እየወጡ ነው፣ ነገር ግን የኢትዮጵያ መንግሥት ከ250 በላይ ዜጎች እያሉ ዝምታን መርጧል፣ መንግስት ለምን እንደዚህ ይጨክንብናል? እኛ ኢትዮጵያዊን አይደለንም። የደቡብ አፍሪካ መንግስት እዚህ ያሉ 3ቱንም ዜጎቹን ከትናንት በስትያ ፍለጋ መጥቶ ወስዳል፣ እኛስ?" ብሎ ጠይቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ለአንድ ዓመት እንዲያስተምሩ ሊገደዱ ነው‼️

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከመመረቃቸው በፊት ማኅበረሰቡን ለአንድ ዓመት በቅድሚያ እንዲያስተምሩ ወይም እንዲያገለግሉ የሚያደርግ አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ዕቅድ መያዙን አስታወቀ።

ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2017 ዓ.ም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ የሆነበትን መንስዔ በተመለከተ በቀረበ ጥናት ላይ ውይይት ሲደረግ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ ስለተያዘው እቅድ አብራርተዋል።

ላለፉት ዓመታት(እሳቸው በኃላፊነት ከተሾሙ ጀምሮ)፣ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተማሪዎች ውጤት በከፍተኛ ደረጃ ዝቅተኛ እንዲሆን ካደረጉ መንስዔዎች መካከል፣ የመምህራን ብቃትና የተነሳሽነት ማነስ ተጠቃሽ መሆናቸው ጠቁመዋል።

ችግሩን በአጭር ጊዜ ለመፍታት እንዲቻል የተለያዩ ተግበራት እየተሰሩ መሆኑን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

''የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ'' የሚል መጠሪያ የተሰጠው አሠራር ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ ዕቅድ የተያዘ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሩ፣ "በአራት ዓመት የሚመረቅ ተማሪ፣ የሦስተኛ ዓመት ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ወደ አስተማረው ማኅበረሰበብ ተመልሶ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ይሰጥና (ማኅበረሰቡን እንዲያገለግል ይደረግና) እንዲመረቅ ይደረጋል"ሲሉ ተናግረዋል። ይህም ሲሆን የተማሪዎቹ መሠረታዊ ወጪ የሚሸፈን እንደሚሆንም አክለዋል።

ይህ አሰራር ለተማሪዎች ለራሳቸው የተግባር ትምህርት እንደሚሆንና የበለጠ እንዲበስሉ እንደሚያደርጋቸውም ተናግረዋል።

ተማሪዎች የመምህርነትን ሙያ ተላብሰው በዚያው ወደ ሙያው እንዲያመሩ ዕድል በመፍጠር ለጊዜውም ቢሆን በዘርፉ እየቀነሰ የመጣውን ወደ ሙያው የሚገባ የአስተማሪን ቁጥር ለማሳግ እንደሚረዳም ሚንስትሩ አብራርተዋል።

በቅርቡ በመምህራን ላይ በተደረገ ግምገማ ፣ 100,000 የሚደርስ የመምህራን ዕጥረት መኖሩ መታወቁን የተናገሩት ብርሃኑ (ፕሮፌሰር)፣ አሰራሩ በከፍተኛ ደረጃ ያለውን የመምህራን ዕጥረት እንዲቀንስ የበኩልን እንደሚወጣ አስረድተዋል።

ወደ መምህርነት ሙያ የሚገቡ ሰዎችን ክፍተት ለማስተካከል ከተያዙ ዘርፈ ብዙ የማትጊያ ሥርዓቶች አንዱ፣ መምህራን በአገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ውስጥ የራሳቸው ድርሻ እንዲኖራቸውና የኑሮ ውድነቱን እንዲቋቋሙ ለማድረግ፣ "የመምህራን ባንክ" ማቋቋም አንዱ እቅድ መሆኑን አንስተዋል።

ባንኩ "በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ሥራ ይገባዋል ብለን እንጠብቃለን" ያሉት ሚኒስትሩ፣ በ2019 ዓ.ም ደግም በእርግጠኝነት ወደ የኢትዮጵያ ዩኒቨርስቲ ሰርቪስ አሰራር እንደሚገባ ጠቁመዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




ከመጋቢት 24 /2017 ዓ.ም ጀምሮ፤ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ እንዲሰጥ ተፈቀደ‼️

የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት በየአቅራቢያው እና በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ እንዲሰጥ መፈቀዱን የተናገረው የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ባለሥልጣን ነው።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፤ በመታወቂያ አድራሻ ሳይገደብ በአቅራቢያ መንጃ ፈቃድ የማደስ ጥያቄ ዓመታትን የተሻገረ ነበረ ብሏል።

አገልግልሎቱን የፈለገ ማንኛውም ሰው ፋይሉ ያለበት ቅርንጫፍ ሳይጠየቅ፤ በሚቀርበው ቅርንጫፍ፤ የጤና ምርመራ ሰርተፊኬት በመያዝ የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት አገልግሎት ማግኘት ይችላል ተብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በኢቢኤስ ቴሌቪዥን የሚተላለፈውን “አዲስ ምዕራፍ” የቴሌቪዥን ፕሮግራም በተመለከተ የተወሰደ አስተዳደራዊ እርምጃ‼️

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ አዲስ ምዕራፍ በተሰኘ ፕሮግራሙ እሑድ መጋቢት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ያሰራጨውን ፕሮግራም ከመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና ከዘርፉ ሕጎች አንጻር በመገምገም አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል፡፡

በዚሁ መሰረት በቴሌቪዥን ጣቢያው የቀረበው ፕሮግራም በሐሰተኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ፣ ሕዝብን የሚያሳስትና ጥርጣሬን የሚፈጥር፣ የመገናኛ ብዘኃን አዋጅ 1238/2013፣ የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ 1185/2012 እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያ ስነ-ምግባርን፣ መደበኛ የጋዜጠኝነት አሰራርን የሚጥስ የፓራጆርናሊዝም አሰራርን የተከተለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

ጣቢያውም በፕሮግራሙ ዙሪያ ተጠይቆ ለባለሥልጣኑ በሰጠው ምላሽ ያሰራጨው ፕሮግራም ሐሰተኛ መሆኑንና ስህተት መፈጸሙን ገልጿል፡፡

በመሆኑም ባለሥልጣኑ ጉዳዩን መርምሮ በጣቢያው የሚሰራጨው “አዲስ ምዕራፍ” የተሰኘ ፕሮግራም በኤዲቶሪያል አሰራሩ ላይ አስፈላጊውን እርምት ወስዶ ለባለሥልጣኑ እስኪያሳውቅና ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ የአዲስ ምዕራፍ ፕሮግራም በመገናኛ ብዙኃን አዋጁ መሰረት ከስርጭት ታግዶ እንዲቆይ የተወሰነ እና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው መሆኑን ባለሥልጣኑ አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ብርቱካን ተመስገንን ጨምሮ በሽብር ወንጀል በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊጊዜ ተፈቀደ‼️

ብርቱካን ተመስገንን በተመለከተ በመገናኛ ብዙኃን ከተላለፈው ሐሰተኛ ዘጋቢ ፊልም ጋር በተያያዘ በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ለፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ፡፡

ፍርድ ቤቱ ለፖሊስ ተጨማሪ 14 ቀን የምርመራ ጊዜ የሰጠባቸው ተጠርጣሪዎች፤ ብርቱካን ተመስገን፣ ነብዩ ጥዑመልሳን የኢቢኤስ ቴሌቪዥን ሥራ አስኪያጅ፣ ታሪኩ ኃይሌ የአዲስ ምራፍ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ፣ ደረጀ ሉቃሌ፣ ኅሊና ታረቀኝ፣ ንጥር ደረጀ እና መታገስ ዓለሜ ናቸው፡፡

በተጠረጠሩበት የሽብር ወንጀል ስልጣንን በኃይል ለመያዝ ፣ የጦር መሣርያ በመታጠቅ፣ በሕገ-ወጥ መንገድ በመደራጀት፣ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች እየተንቀሳቀሰ ከሚገኘው ጽንፈኛና ፀረ ሰላም ቡድን አመራሮች ጋር በጥቅም በመመሳጠር፣ መንግሥት የሕዝብ ተቀባይነት እንዲያጣና ዓለም አቀፍ ተፅዕኖ እንዲደረግበት በማሰብ፣ ተዋድደውና ተከባብረው በሚኖሩ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች መካከል ቅራኔ በመፍጠርና ወደ ግጭት እንዲገቡ ለማድረግ፣ በውጭ ሀገር ከሚገኝ የፀረ ሰላም የቡድኑ አመራሮች ጋር በተለያዩ መገናኛ መንገዶች በመገናኘት እና ተልዕኮ በመቀበል የሥራ ባህሪያቸውን እንደመልካም አጋጣሚ መጠቀም የሚሉ የምርመራ የጥርጣሬ መነሻውን ለችሎቱ አቅርቧል፡፡

ፖሊስም የምርመራ ሥራየን በሰውና በሠነድ ማስረጃ በስፋት ማጣራት እንድችል 14 ተጨማሪ ቀናት ይፈቀድልኝ ሲል ባሳለፍነው ዓርብ መጠየቁን ተከትሎ፤ ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት የፖሊስን ጥያቄ በመቀበል 14 የምርመራ ቀን ፈቅዷል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ምክር ቤቱ የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት የሚደነግገውን አዋጅ አፀደቀ‼️

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 22ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅን መርምሮ በአብላጫ ድምጽ አፅድቋል፡፡

የማሻሻያ አዋጁ ከዚህ ቀደም በነበረው አዋጅ ላይ በትግበራ ላይ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ምክር ቤቱ ዛሬ የፌደራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ የወጣ ማሻሻያ አዋጅ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል‼️

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው 22ኛ መደበኛ ስብሰባው የፌደራል መንግሥት በክልሎች ጣልቃ የሚገባበትን ሥርዓት ለመደንገግ በወጣ ማሻሻያ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ያጸድቀዋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከሌ/ጄል ታደሰ ወረደ ጋራ መግባባት የተደረሰባቸው ስምንት ነጥቦች‼️

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ ሌ/ጄኔራል ታደሰ ከጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ እንዲሁም በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ተወካዮች ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ተመካክረዋል።

1 የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ወደቦታው ይመለሳል፤ የጊዜያዊ አስተዳደሩን ተግባር የሚያድናቅፍ ማንኛውም አካል ላይ ተመጣጣኝ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል፣

2) በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት ይሰየማል፣

3) ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረደ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆኖ ይሰራል፣

4) ጄኔራል ተኽላይ አሸብር (ወዲ አሸብር) የታደሰ ወረደ የሃላፊነት ቦታ ይሰየማል፣

5) የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት መቐለ ከተማን ጨምሮ በነባር ካምፖች ውስጥ ይገባል።

6) የትግራይ ታጣቂ ሃይል ወደተዘጋጀላቸው ካምፕ እንዲገቡ ይደረጋል። የተቋረጠው የ DDR ተግባር በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በትክክል ይተገበራል፤ ለ DDR ገንዘብ የለገሱ ሃገራት (አሜሪካን ጨምሮ) ገንዘብ እንዲለቁ ይሰራል፣

7) የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ እንደገና የሚደራጅ ሆኖ በአዲሱ አደረጃጀት ህወሓት 50%፣ ብልጽግና 25% እንዲሁም በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ድርጅቶችና የሲቪክ ማህበራት 25% ድርሻ ይኖራቸዋል። በመጀመሪያው የጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ ውስጥ የሰራዊት/ታጣቂ ወኪል የካቢኔ አባል የነበረ ሲሆን በአዲሱ አደረጃጀት ውክልና አይኖረውም፣

8) ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው መመለስ በልዩ ትኩረት እንዲሰራ ፤ ከዚህ በፊት የተደራጀው የብሔራዊ ኮሚቴና የክልል ቴክኒክ ኮሚቴዎች በአዲስ መልክ ስራ እንዲጀምሩ የሚሉ ናቸው።

(... ሌሎች ስምምነት የተደረሰባቸው ሦስት ጉዳዮች ለጊዜው በ Classified document የሚመደቡ ናቸው የተባለ ሲሆን ህወሓትን ከውጭ ኃይሎች እና ለወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲታቀብ ያሰመሩ መሆናቸው ይገመታል።)

@Esat_tv1
@Esat_tv1




በማይናማር የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1,600 በላይ ደርሷል ከ3,400 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል‼️

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የዒድ አል-ፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ መድፍ ይተኮሳል‼️

1446ኛውን የዒድ አል-ፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ የመከላከያ ሠራዊት ገለጸ።

መከላከያ ሠራዊት ለኢቢሲ በላከው መግለጫ፣ “በመጋቢት 21/2017 ዓ.ም የሚከበረውን የዒድ አልፈጥር በዓል ምክንያት በማድረግ ነገ ማለዳ 12 ሰዓት ላይ 9 ጊዜ መድፍ የሚተኮስ መሆኑን እንገልፃለን” ብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.