Ethiopian Media Authority


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


This channel is an official channel of Ethiopian Media Authority (EMA).
EMA is an autonomous government organization accountable to the House of Peoples’ Representatives of the FDRE.

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri




የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለመቄዶንያ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 02/2017 ዓ/ም (Ethiopian Media Authority)

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የተለያዩ መገልገያ ቁሳቁሶችን ለመቄዶንያ በጎ አድራጎት ድርጅት አስረክቧል፡፡

ባለሥልጣኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት ከመወጣት ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቶችን እየተወጣ ይገኛል፡፡


ልዩ ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የመገናኛ ብዙኃን  ተጠቃሚነት

በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ 1238/2013 አንቀፅ 56/1/ሸ መሰረት ማንኛውም የህዝብ ብሮድካስት አገልግሎት ባለፈቃድ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ  ክፍሎች አገልግሎት የመስጠትና ትኩረት እንዲያገኙ የሚያስችሉ  ዜናዎችን እና ፕሮግራሞችን የማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡

  በመገናኛ ብዙኃን እና በማስታወቂያ ይዘቶች ላይ የህግ ጥሰት፣ የሙያ ስነ-ምግባር ግድፈት፣ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሲመለከቱ በ9192 ነፃ የስልክ መስመር ደውለው ማሳወቅዎን አይርሱ፡፡

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት
#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል


በሃይማኖት ብሮድካስት አገልግሎት ለሥርጭት የሚቀርብ ማንኛውም ኘሮግራም ፡-

1.  ሕገ መንግስቱን፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጁን እና ሌሎች  የሀገሪቱን ሕጎች ማክበር ይኖርበታል፣

2.  በኃይማኖቶች ተከታዮች መካከል የእርስ በእርስ ግጭት ማነሳሳት፣ የሌሎችን ሀይማኖታዊ አስተምሮ ወይም እምነት ተገቢ ባልሆነ ሁኔታ ማንኳስስ ወይም በሀይማኖቶች ተከታዮች መካከል አለመቻቻል እንዲፈጠር መቀሰቅስ፣ ወይም የሃይማኖት እኩልነትን መፃረር የለበትም፡፡

3.  ማንኛውንም የሰው ዘርን፣ ቋንቋን፣ ብሔርን፣ ኃይማኖትን ወዘተ መሰረት በማድረግ የወንጀል ድርጊት እንዲፈጸም፣ ሰላምና ፀጥታ እንዲደፈርስ መቀስቀስ የለበትም።

4.  ከማህበረሰቡ ባህልና ሥነ -ምግባር የተቃረነ፣  የማህበረሰቡን ጤና የሚጎዳ፣ማህበረሰቡን በሐሰት የሚያሳስት ይዘት ማሰራጨት የለበትም፡፡

  በመገናኛ ብዙኃን እና በማስታወቂያ ይዘቶች ላይ የህግ ጥሰት፣ የሙያ ስነ-ምግባር ግድፈት፣ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሲመለከቱ በ9192 ነፃ የስልክ መስመር ደውለው ማሳወቅዎን አይርሱ፡፡

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት
#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል






"ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል"


አለም አቀፍ የሴቶች ቀን "ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል" በሚል መሪ ቃል እየተከበረ ይገኛል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28/2017 ዓ.ም (Ethiopian Media Authority)

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ሰራተኞች ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን በትኩረት ለሴቶች እና ለህፃናት ማህበር በመገኘት በጋራ አክብረዋል።

ዝርዝር መረጃውን ለማንበብ ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ

https://www.facebook.com/share/p/1A6c6TVMxc/




"የንግድ መገናኛ ብዙኃን ለማህበረሰቡ የመረጃ ምንጭ ከመሆን ባለፈ በሰላም ግንባታ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ሊጫወቱ ይገባል" ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር)፣ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

ቢሾፍቱ፣ የካቲት 26/2017 ዓ.ም

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በሰላም ግንባታ ዙሪያ ከንግድ መገናኛ ብዙኃን ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ የተገኙት የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር)፤ የንግድ መገናኛ ብዙኃን ለማህበረሰቡ የመረጃ ምንጭ ከመሆናቸው ባለፈ በሰላም ግንባታ ሂደት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ በመግለፅ፤ ትልቁ ስኬት ችግሮች ከተፈጠሩ በኋላ ለማብረድ ከመሞከር ይልቅ ከመፈጠራቸው በፊት የመከላከል ስራ መስራት አዋጭ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የንግድ መገናኛ ብዙኃን ትውልድን በመቅረጽ ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በኃላፊነትና በአንድነት መንፈስ በሰላም ግንባታ ላይ በትኩረት መስራትና ሚናቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል።

በመድረኩ የንግድ መገናኛ ብዙኃን በሰላም ግንባታ ዙሪያ ያላቸው ሚና በተመለከተ እንዲሁም ህብረ ብሔራዊ አንድነት እና አሰባሳቢ ትርክት በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የመነሻ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት
#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል

10 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.