ልሣነ አምሐራ ሚዲያ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Siyosat


በዚህ ቻናል ፈጣንና ወቅታዊ የአማራ ፋኖ እለታዊ ዘገባዎች እንድሁም ፈጣን ዜናዎች ይቀርባሉ።
ለማንኛውም ጥቆማ በ @lisaneamhara ያናግሩን‼️

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Siyosat
Statistika
Postlar filtri


ሂሳቡን ስራው እያሉ የሚመፃደቁ የአገዛዙ አፈቀላጤዎች የዘመቻ 100 ተራሮችን ሪፖርት ሂሳብ ሰርተውት ይሆን? 

ከሻለቃ ዝናቡ ሪፖርት እንደተረዳሁት በ2 ሳምንት ውጊያ 1,305 ያህል ወታደሮች የአብይ አህመድን እብደት ለማስቀጠል ሲዋጉ ተደምስሠዋል።  በተመሳሳይ 699 ያህል ተማርከዋል፤ የቆሰሉት ደግሞ 418 ያህል ናቸው።  ይሄ ቁጥር የአብይ አህመድ እግረኛ ወታደር አቅም ለፋኖ ሃይሎች ስጋት አለመሆኑን ይነግረናል።

በዚህ ኦፕሬሽን የተገኘው የጦር መሳሪያ በብዛትም በዓይነትም ከዚህ ቀደም በ1 ኦፕሬሽን ከተገኘው ከፍተኛው ይመስለኛል። 120 ሚ/ሜ ሞርታርን ጨምሮ 882 በላይ ክላሽንኮቭ፣ ዲሽቃዎችና ከ23 በላይ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች 100 ሺህ ገደማ ከሚጠጋ ተተኳሽ ጋር መማረካቸውን ከሪፖርቱ ለመረዳት ይቻላል።

ሂሳቡን ስሩት እያሉ የድሃ ልጅ ወደ እሳት የሚከቱ ሰዎች ይህ መሰሉ ሽነፈት የ አበዳሪዎች ዶላር፤ ታሪካዊ ጠላትህን ግጠም እየተባለ የሚመለመለው የኦሮሞ ወጣት ሞት በቃኝ እስካላለ ድረስ  የሚያስደነግጣቸው አይመስልም። "የህልም ጉልበት" ወደሚል መፈክር የተሸጋገሩት ብዐዴኖችም ከባህር ዳር እስካልተነቀሉ ድረስ ሌላው እንደ አርማጌዶን ቢሆን የሚያሳስባቸው ጉዳይ አይደለም።

ጦርነቱን ለማሳጠርም ሆነ ህመሙ የማይሰማቸው ሰዎች እንዲሰማቸው የማድረጉ ጉዳይ በፋኖ እጅ ያለ ካርድ ነው።  በጣም እርግጠኛ ሆነን መናገር የምንችለው ነገር አብይ አህመድ ይህ ጦርነት እንዲቆም ፈጽሞ አይፈልግም። በብልጽግና አጠራር የኛ የሆነ የሚባል ህዝብ አለ። ያ ህዝብ  እስካልተነካ ድረስ ሌላው ህዝብ ቢጨፈጨፍ የበረሮና ትንኝ ተረት እየተተረተበት ሞቱ የቤተ መንግስቱ የምሽት ሳቅ ማድመቂያ ሆኖ ይቀጥላል። ምናልባት ጦርነቱ የብልጽግና ወደሚባሉት ዜጎች ደጅ ከደረሰ ሌላኛው የብልጽግና ገጽ ይገለጥ ይሆናል።


ሰበር ዜና!

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በተኩስ እየተናጠ ነው።

ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓም ኢትዮ 251 ሚዲያ።

ይህ ዜና እየተጠናቀረ ባለበት ሰዓት ባህርዳር ከተማ ላይ የሚገኘው የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ጣቢያው በተኩስ እየተናጠ ነው።

የአማራ ፋኖ በጎጃም አንደኛ ክፍለ ጦር ባህርዳር ብርጌድ በላይ ሻለቃ በአሁኑ ሰዓት በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋናው ጣቢያ ለይ የቦንብ ጥቃት መፈፀሙን ለኢትዮ 251 ሚዲያ አሳውቋል።

በዚህ ተቋም ላይ በፋኖ ሀይሎች የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎም የአገዛዙ ሀይሎች በንፁሀን መንደሮችና በባህርዳር ከተማ ባሉ በርካታ ትምህርት ቤቶች ላይ ጭምር  በህፃናትና ንፁሀን ላይ የቦንብ ጥቃቶችን እየፈፀመ እንዳለ የኢትዮ 251 ሚዲያ የመረጃ ምንንጮች ገልጠዋል።


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
"ልዩ ዘመቻ በቅርቡ እናውጃለን፤ ሕዝባችን ይዘጋጅ!" ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው!

ከአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የተሰጠ መግለጫ!


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


«በአዲሱ ዘመቻ እና ድሎቹ እንገናኛለን!» -አርበኛ ዘመነ ካሴ

“ከግድያ ሙከራ መትረፍ  የኦሎምፒክ ውድድር ቢሆን ኖሮ የወርቅ ሜዳሊያ አሸንፍ ነበር።"-ይህን ያለው ከ600 ጊዜ  በላይ ከግድያ ሙክራዎች እንዳመለጠ የሚነገርለት የቀድሞው የኩባ መሪ ፊደል ካስትሮ ነበር።

የግድያ ዜና በ 2025ቱ ( የፈረንጆች አቆጣጠር) የጃፓን ቶክዮ የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አንዱ የውድድር አይነት ከሆነ በሰሞኑ የነ አብይ አህመድ የተስፋ መቁረጥ "የገደልነው ዘመቻ" ብቻ ወርቅ ባላገኝ የብር ሜዳሊያ አላጣም። የመለያ ቁጥሬም 21-12 ይሆናል።

•በሁሉም ረገድ፣ በሁሉም ሰበብ እና ምክንያት ልትጠልፉኝና ልታጠለሹኝ የሞከራችሁ እና በየቀኑ የምትሞክሩ ሰዎችና ቡድኖች መጨረሻችሁ ውርደት እና የእድሜ ልክ መሸማቀቅ እንደሚሆን ዛሬ ድረስ በጥቂቱ በምታውቁት፣ነገና ከነገ ወዲያ ደግሞ ሰፊውን ማንነቱን በምትረዱት በዘመነ አምላክ ስም እነግራችኋለሁ። አምላኬ ይቅር ይበለኝና ብዙዎች አይሆን ሞክረውኝ፣ ደጋግመው ሞካክረውኝ መጨረሻቸው የሌባ ጣት ጥፍራቸው ውስጥ መደበቅ ሆነ። (ድንግል ማርያምን ያሳዝኑኛል።)

የቀብሮ ጫጫታ የማያስደነብረኝ፣ጀርባዬ ላይ ሊወጣ የሚሞክረው ሁሉ ቢሳካለት እንኳን የማይከብደኝ "ዝሆን" ነኝ።በቃ እንደዚህ ነው የሰራኝ።

•ከንግስና ዙፋንና ዘውድ ጀምሮ በተለያዩ የህዝብ አስተዳደር እርከኖች እና ሃላፊነቶች እስከ ጦር ሜዳ ውሎዎች  በብዙ ፈተና መሃል እያለፈ ሃገር የገነባ ቤተሰባዊ ማንነትና የመከራ ዘመን በቅጡ የገነባኝ ሰው ነኝ።በአለሙ ውስጥ በማንኛውም ሁኔታ  እንደ ህፃን በደስታና በሃዘን በእምባ የምሟሟ ተራ ሰው፣ ምድራችን በድንገት ጨረቃ ብትሆን እንኳን የማይጨንቀኝ ልበ-ሙሉ "ጨካኝ" ፍጡር ነኝና በጅራፍ ጩኸት ልታስደነብሩኝ የምትሞክሩ የዋሆች አትድከሙ።

•እኔና ጓዶቼ ፣ከትውልድ አጋሮቻችን ጋር እንደምናሸንፍ የተፃፈው የእናቶቻችን ማህፀን ውስጥ እያለን ነው።ወኔና ድል አድራጊነትንም የተጋትነው  በእትብት ነው።ይህ ትውልድ አሸናፊ ትውልድ ነው።ልድገመው!ይህ ትውልድ  የአሸናፊነት  እጣፋንታውን ግንባሩ ላይ ተነቅሶ ወደዚህ ምድር የተላከ ትውልድ ነው። እየታገለ ነው ፥ድል አድርጎ የአማራን ህዝብ ህልውና በፀሃይ ፊት ያረጋግጣል።

ይህ ትግል ለትግሉ ብቻ የተሰጠ እና የሚሆን ራሱን የቻለ ልዩ ነፍስ ይፈልጋል። እንጨት እንጨት የሚል ሰዋዊና ፖለቲካዊ ስብእና ተይዞ ፥ነፍስን ቅናት፣ምቀኝነትና ተንኮል በሚባሉ የመንፈስ ቆሻሾች መርዞ ታጋይም አታጋይም መሆን አይቻልም። እና "ልፋ ያለው በህልሙ ዳውላ ይሸከማል" እንዲሉ በብዙ የተበከለች ነፍስ ተሸክማችሁ ለ ደካማ ተልእኮ አጉል የምትደክሙ ወገኖች ከድል ሃውልት ውጭ ከፊታችን መቆም የሚችል ነገር የለምና ነፋስን ለማሰር በመሞከር ጊዚያችሁን አታጥፉ። ይህ ትውልድ እያለ የአማራን ህዝብ ጉልበት መሬት አታስነኩትም። በኩራት ቆሞ ገጥሟችኋል፥ ያሸንፋችኋል።

እና በባንዶች ፊታውራሪ በተመስገን ጥሩነህ አገላለፅ "ዘመነን አስወግደነዋል፥ ከዚህ በኋላ ድምፁን አትሰሙትም" የሚለውን የሰሞኑን ብልፅግናዊ አዲስ መዝሙር ስቃችሁበት እለፉ።ሌት ተቀን እያቀድንላቸው ነው።ከጠፋሁም ያጠፋኝ የጠላት ስሥ ብልት ልየታ ቢዚ አድርጎኝ ነው።የዘመነ ትውልድ የአለማችን እድለኛና ገድለኛ ትውልድ ነው።መንጋው እንዲበተን እረኛውን ምታው የቆዬ ብሂል በኛ ትግል ውስጥ አይሰራም።ትግሉ ሚሊዮን እረኞች ከበውታል፥መንጋው ራሱ ረኛ ከሆነ አመታት አልፈዋል።

ዘመነ የእናንተን ሞት ቆሞ ለማዬት ለተአምር ተፈጠረ እንጅ በዘመነ መጥፋት ለአንድ ሴኮንድ እንኳን የሚንገራገጭ ትግል የለም። ይህ ትውልድ ከቀደምቶቹም ከነገዎቹም ትውስታና መንፈስ ቀድቶ የትሸከመውና ያጎለበተው ከእድሜውና ተሞክሮው በላይ ያበሰለው አንዳች ነገር አለው።ስለሆነም ያሸንፋል።
ይኸው ነው! በአዲሱ ዘመቻ እና ድሎቹ እንገናኛለን!!

አዲስ ትውልድ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ
አርበኛ ዘመነ ካሴ
ጥቅምት 10 ቀን-2017 ዓ.ም

#Amhara #Ethiopia


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


አማራ በዚህ ጥልቀት ርህራሄህን በጭካኔ ቀይረህ ምርር ብለህ ለህልውናህ ታገል ..‼️‼️

ኦሮሙማ ውጊያ ሲያቅተው ንፁሀንን❗

የምንታገለው የግለሰብ እና የቡድን ፍላጎቶችን ሳይሆን ለህልወናችን ነው።

ይህ ድምፅ እድል አግኝተው ድምጻቸው ሳይለማ ታፍኖ በየቤታቸው በሀዘን ተኮራምተው እየማቀቁ ያሉትን እልፍ የአማራ እናቶችን ድምፅ ይወክላል።

እናት
" በእኩለ ሌሊት አጠፉኝ።በእኩለ ሌሊት አጠፉኝ።ልጄን ካሳደግኩ በኋላ ።ከእኔ ወሰዱት።በእኩለ ሌሊት ከእኔ ወሰዱት። በእኩለ ሌሊት ከእኔ ወሰዱት ።" 🥲

ጥያቄ ፡ የሟች ስም ማን ይባላል?
ወንድም ፡ መዝገቡ
ጥያቄ ፡ መዝገቡ ማነው?
ወንድም ፡ መዝገቡ ታደለ
ጥያቄ ፡- መዝገቡ ታደለ ላንተ ማን ነው?
ወንድም ፡ ወንድሜ
ጥያቄ ፡ ታላቅ ወንድምህ ነው?
ወንድም ፡ አይ ታናሽ ወንድም
ጥያቄ ፡ እሱ ታናሽ ወንድምህ ነው? ዕድሜው ስንት ነበር?
ወንድም፡ 7

እናት፡
"ከእኔ ወሰዱት፣ ልጄን ከእኔ ወሰዱት። ልጄ፣ ልጄን ከእኔ ወሰዱት። ከእኔ ወሰዱት። " 🥲

" ማነው ከጎኔ የሚሆነው? ልጄ ከጎኔ ሳልኖር እንዴት እተኛለሁ? " 🥲🥲

"ልጄን ወሰዱ፣ ልጄን ወሰዱት። እነዚያ ጭራቆች ልጄን ወሰዱት። " 🥲

ጥያቄ ፡ እንዴት ሞተ?
ወንድም፡- ድሮን አድማ

እናት፡
" ምን አደረጋቸው? ምን አደረገላቸው? ለምን እንዲኖር አልፈቀዱለትም? ለምን እንዲያድግ አልፈቀዱለትም? 🥲

መታሰብ ያለበት ነገር እንዴት ይበልጥ በህብረት መታገል አለብን የሚለው ደምቆ ይሰመርበት‼️‼️

*_*_*_*_*
"
#ወሎ#ጎጃም#ጐንደር#ሸዋ የአካባቢ መጠሪያዎች እንጂ አማራ ዝንታለም አንገቱ አንድ ነው


በዱር በገደሉ ላሉ ሁሉ ፋኖዎች እንኳን አደረሳችሁ ..🌼🌼

ፋኖነት መንፈስ ነው የጀግና ልጅነት የሚወረስበት
ፋኖነት አቅም ነው የጀግና ጉልበት የሚታደስበት
ፋኖነት ጥበብ ነው ልብ የሚበራበት፤ ፋኖነት ጥበብ ነው ታዳሚ ያለበት
ፋኖነት ረቂቅ ነው ሁሉም የሆነበት
ፋኖነት ሀሳብ ነው
በልባችን ፅላት ነው የተሞሸረው
ቃርሚያ ውስጥ ያደጉ የነቀርሳ እባጮች
አፍ ሲከፍቱ ታዩ በዚህ ቆራጥ ዘማች
ፋኖነት አይወይብ፣ አይገረጣ ቶሎ
ሲዘከር ይኖራል  በድፍረት ተንጣሎ
ተምጦ ተወልዶ ተጠምቆ በብሶት 
የሀገር መቋሚያ ነው የሚመረኮዙት
ፋኖነት ሀሳብ ነው
በልባችን ፅላት ነው የተሞሸረው
ፋኖነት መንገድ ነው መቋጫ የሌለው
በትውልድ መካከል  የሀረግ ገመድ ነው
ሁላችን ፋኖ ነን፤ ማን ከማን ይለያል
ባርነትን ጠልተን ነፃነት ናፍቆናል
ፋኖነት ራዕይ ነው ነፃ ሚወጡበት
ፋኖነት ሀሳብ ነው ትጥቅ ማይፈታበት
ፋኖነት ታሪክ ነው እውነት የሚያድርበት 
ፋኖነት ኩራት ነው አማራነት የሚፈካበት፡
ፋኖነት ኩራት ነው ወገን ሚድንበት፡፡
ፋኖነት ኩራት ነው ሀገር ሚድንበት፡፡


ታሪክ የማይዘነጋት ክህደት

በቀይ ቀለም ተቀልማ ለልጆቻችንና ለልጅ ልጆቻችን ማስተማሪያ የምትሆን ታሪካዊ የክህደት ምሳሌ ናት ይህች አሁን በክርስቲያን ታደለ ላይ የተፈፀመች ክህደት::

እሱ ወንድሜ ባላቸውና እነሱ ግን አማራዊ ወንድማማችነትን ለምግብና መጠጥ ብለው ክደው ከጠላት ኦሮሙማ ጋር አብረው መረጃ ማቀበል "የሀሰት ምስክርነት" የፈፀሙ የታሪክ ተወቃሾች::

የኦነጉ አቃቢህግ በክርስቲያን ታደለ ላይ ባዘጋጃቸው ብዙ የፈጠራ ክሶች ላይ በሀሰት የመሰከሩ 5 የሀሰት ምስክሮችን ታሪክ ይቅር አይላቸውም::

የአብንን የስራ አስፈፃሚ አባላት ውይይቶች ድምፅ መቅጃ እየቀዱ ለኦሮሙማ ደህንነቶች ከማቅበል ጀምሮ የተቋሙን ቃለ ጉባዔ አሳልፎ እስከመስጠት የደረሰው ታሪካዊ ክህደት !!!


የበዓል አከባበር የጥንቃቄ መልዕክት
***
የአዲስ ዓመት በዓል ስናከብር ካለንበት ወቅታዊ የትግል ሁኔታ አኳያ በከፍተኛ ጥንቃቄ ሊሆን እንደሚገባ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የጥንቃቄ መልዕክቱን ያስተላልፋል፡፡

በዓላት በመጡ ቁጥር የደም ግብር የለመደው የብልጽግና አገዛዝ የሚሸርባቸው ክፉ ሴራዎች በመኖራቸው፣ በዓሉ ሲከበር በመላው ሕዝባችን ዘንድ ጥበብ የተሞላበት የደህንነት ጥንቃቄ በመጠቀም የአገዛዙን ሴራዎች በማክሸፍ ሊሆን ይገባል፡፡

በተጨማሪም ለድሮን ጥቃት ተጋላጭ ሊያደርጉን ከሚችሉ መሰባሰቦችና የተጋላጭነት ሁኔታን የሚያሳድጉ ሁነቶችን ከመፍጠር ተቆጥበን፣ በተለመደው የመረዳዳት መንፈስ በዓሉ እንዲከበር ለሕዝባችን የጥንቃቄ መልዕክት እናስተላልፋለን።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ
ጎንደር፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ
ጷግሜ 5/2016 ዓ.ም.


የአርበኛ ዘመነ ካሴ መልእክት


ሰበር የጀብድ ዜና ሸዋ | ሸዋሮቢት ከተማ ..‼️‼️

ሰበር መረጃ!! ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ሸዋሮቢት በሸዋሮቢት ከተማ የስረዓቱ አገልጋይ የባጃጅ አሽከርካሪ ወጣቶችን ሲያገላቱና የንግድ ሱቆችን ሲያፈርሱ የነበሩ ባንዳ የሚሊሻ አባላት እርምጃ ተወሰደባቸው በዛሬው እለት የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ቃኝዎች ወደ ከተማው ገብተው ባንዳዎች ላይ እርምጃ የወሰዱ ሲሆን ግራ የገባው የፋሽሽት አብይ አህመድ ጎመን ሰራዊት በእውር ድንብር ከባድ መሳሪያ እየተኮሰ ነው ።

ድል ለአማራ ህዝብ !!
ድል ለአማራ ፋኖ !!


ፋኖ ንጉስ አበራ የአማራ የክፉ ቀን ደራሽ!

ልጥጥ ያለ ህይወት ይኖር የነበረ፤ የአማራ ህዝብ በአገዛዙ የሞት አዋጅ ሲታወጅበት የቅንጦት ህይወቱን እርግፍ አድርጎ ትቶ ዱር ቤቴ ያለ የአማራ ደም መላሽ ነው።

የብርሃኑ ጁላን ሰራዊት በገፍ በመማረክ “10 አለቃ ብርሃኑ አይችልም፣ ፋኖ ምሬ ወዳጆ ይችላል” ስታስብለው የዋለችው ይች ሰው ናት!💪


የዓመቱ ምርጥ ባንዳ DK

2016 ዓም ከተስተናገዱ ክስተቶች መካከል በእኔ እምነት በባንዳነት እና በወንጀለኛነት ይኼንን ግለሰብ የሚስተካከል የለም ።

* በአማራ ህዝብ ላይ የጥላቻ ንግግር ቀስቃሽ ማሽን !

* በአማራ ህዝብ ላይ የሃሰት መረጃዎች በመፈብረክ እና በማሰራጨቱ።

* በአማራ ህዝብ ላይ ጥቁሩ ናዚ ጥቃቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል በማቃጠር እና ህዝባችንን ትኩረት ያደረገ  አስነዋሪ ንግግሮችን በማህበራዊ ሚድያና በተለያዩ መድረኮች በማስተላለፉ ።

* ወልዳ አሳድጋ ኮትኩታ እከኩን ያራገፈችለትን እናት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ጓዳ ጎድጓዳዋን ለጠላት አሳልፎ ሰጥቶ ለትልቅ ውርደት በመዳረጉ።

*በአለቅላቂነቱ

ስንቱን እዘረዝረዋለሁ ?

ለእኔ የ2016 ዓም ባንዳ እና ወንጀለኛ ግለሰብ ነው !!

እርግጠኛው ነገር ዐብይ አህመድ ቀድሞ ካልበላው የእኔ ትውልድ ለህዝብ ፍርድ ሲያቀርበው እዚሁ ሰፈር ተቀምጨ እመለከታለሁ።

በየአመቱ በአዲስ አመት መግቢያ FB እንዲያስታውሰኝ ለታሪክ እዚህ ይቀመጥ


አድማ ብተና 5ሻለቃ ሻንበል አዛዥና ከልዩሀይል ወደ ፖሊስ ተመድ ከፖሊስ ወድ አድማ ብተና በመግባት ሸዋሮቢት ከተማ ላይ ከአውሬው የአድማ ብተና አዛዥ ሻለቃ ፀሀዬ ጋር ሆኖ የሸዋሮቢት ወጣቶችን ሲደበድብና ሲያንገላታ የነበረው ዋና ሳጅን እንግዳው ንጉሴ በመሀመድ ቢሆነኝ ክፍለጦር ከነነፍሱ ተይዞ መቷል !!


በፋኖ የመረጃና ደህንነት ልዩ ክትትል የአገዛዙ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች በቁጥጥር ስር ውለዋል ።

የ32ኛ ክፍለጦር ሻለቃ አመራርን  ጨምሮ ከ5 በላይ መስመራዊ መኮንኖች በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ልዩ የመረጃ ክትትል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን  ገልጿል።

መረጃው የኢትዮ251ሚዲያ ነው


አንገር ጉትን‼

ምስራቅ ወለጋ ዞን አንገር ጉትን ከተማ አስተዳደር አንድ ህዝቡን ሲያማርር የነበረ የኦሮሞ ሚሊሻ ወንድም ባልታወቁ ሀይሎች ከምሃል ከተማ መወሰዱን ተከትሎ ቤት ለቤት ፍተሻ እስርና እንግልት በኦሮሚያ ልዩ የይል በመከላከያና በኦሮማያ ሚኒሾች ጥምረት አማራውን ከትናንት ጀምሮ አጠናክረው ቀጥለዋል።


#Inbox
አስቸኳይ  የጥንቃቄና የጥቆማ መልእክት......!!!!

ዛሬ ጳጉሜ 1/13/2016 ዓ.ም ምስራቅ አማራ ፋኖ ከአገዛዙ አራዊት ሰራዊት ጋር ጎብየ ከተማ እና በዙሪያዋ ባሉት ማለትም ማማድሌ፣ ገንደጢስ፣ አሉላ መቃብር እና ጎብየ በር ላይ የከበባ ውጊያ እያደረጉ ይገኛል።
ከባድ ትንቅንቅ ውጊያም ተጀምሯል። ከሌሊቱ 11 ሰዓት ነው ውጊያው የጀመረው። ስለዚህ ጀግኖቻችን በተጠንቀቅ እንድቆሙ እና ከአገዛዙ ተጨማሪ ሃይል 49ኛ ኮር ስለገባ ብዙ ሃይልም ስለሆነ ለጀግኖቻችን አሳውቁልን።

#ድል_ለአማራ_ህዝብ
#ዘመቻ_ይታገሱ_አራጋው_ይቀጥላል


በዚህ ሊንክ በመግባት ተጠቀሙበት።
ከዚህ በፊት በ dogs ብዙዎች ጥሩ ገንበዝ ተቀብለዋ ተጠቅመዋል።
በቅርቡ ይሄም list ስለሚደረግ አሁኑኑ ገብታችሁ ስሩ

t.me/catsgang_bot/join?startapp=QZSirXDLUXU23ehZD2aJD
Meow, lets see who is OG 😼


#ብሩን_አስገልብጠው_ይረሽኑሀል !

በባህርዳር ከተማ ባለሀብቶችና አካውንታቸው ላይ የተሻለ መጠን ብር አለው የተባለ ግለሰብ:-
👉 በደሳለኝ ጣሳው፣
👉 በዋኛው እዘዘው፣
👉በደስየ ደጀን ቡድንና
👉በኮማንደር መሰረት እንዲሁም አብረዋቸው በሚሰሩ የእነሱ የዘራፊና ገዳይ ህዋስ ጥናት ይደረግበትና መኮድ ለሚገኙት:-
👉ኮሎኔል ቱሬ ኡስማን.........ኦሮሞ
👉 ሻምበል ካሳየ ..............ትግሬ ስማቸው ተላልፎ ይሰጣል።

ከዚያ መኮድ ላይ ተቀምጠው በስማቸው አካውንታቸውን አስፈትሸው የሚፈልጉት የብር መጠን ከተገኘ ታፍኖ ይወሰድና ገንዘቡን ወደ አካውንታቸው እያስገለበጡ ሚስጢር እንዳያወጣ ያስወግዱታል። ገንዘብ አካውንትህ ላይ ካለ አለቀልህ ተጠርጥረሀል ብለው የይዙሀል ብሩን አስገልብጠው ይረሽኑሀል። በቢሊየን ዘረፋ ላይ ናቸው ይሄ አካሄድ ደግሞ የትም አያደርስም የተስፋ መቁረጥ አንዱ ማሳያ ነው።

ቤት ተቀምጦ ተይዞ የውሻ ሞት ከመሞት በቁም ጉርምቦ ለጉርምቦ ተናንቆ መሞት ለራስም ለአማራነትም ክብር አለው።

#ድል_ለአማራ_ህዝብ
#ድል_ለአማራ_ፋኖ

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.