Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ፦
1) ከቁርኣን፣
2) ከሐዲሥ፣ [በሰለፎች አረዳድ]
3) ከታማኝ ዑለማዎችና
4) ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል።
√ አዳዲስና ወቅታዊ ኢስላማዊ የሆኑ ጉዳዮችም ይዳሰሳሉ።
√ አላማዬ በዲኔ ላይ ያለውን የመረጃ ክፍተት መሙላት ነው።
ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Murad_Tadesse ላይ አስፍሩት።
ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ።
ጀዛኩሙል`ሏህ ኸይራ!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹 dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የማለዳ ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②②①⑤]👌


#ቁርኣን


Mizan Tv - ሚዛን ቲቪ 🇪🇹 dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የምሽት ስንቅ ለቀልብዎ❤️

[Part: ②②①④]👌


#ቁርኣን


ግብዣ ለውዷ እህቴ!
እነሆ ዳሩ መርየም መድረሳ በጉጉት የሚጠበቀውን ረቢዕ አል-ቁሉብ የተሰኘውን የሴቶች በሴቶች የቁርአን ሂፍዝ ውድድር ለሶስተኛ ጊዜ አሠናድቶ አንቺን በመጠበቅ ላይ ይገኛል።
📍 ጦር ኃይሎች ኢሙ ታወር
🗓ቅዳሜ የካቲት 29
⏰ 2፡00-7፡00

7.2k 0 11 14 49

If you know how quickly people forget the dead, you will stop living to impress people.

11k 0 43 16 194

ከተዘነጉ ሱን'ናዎች መካከል፦

ውዱ ነቢይ ﷺ የዊትር ሶላት ካሰገዱ በኋላ 3 ጊዜ «ሱብሐነ-ል-መሊኪ-ል-ቁዱስ» ይላሉ። በ3ኛው ድምፃቸውን ከፍ ያደርጉ ነበር።


ኢማሞቻችን እንዲህ አይነት የተዘነጉ ሱን'ናዎችን እየተገበራችሁ ሕያው አድርጓቸው።



||
t.me/MuradTadesse

12.1k 0 68 15 229

በአጋጣሚ የዒሻእ የጀማዓህ ሶላት አምልጧችሁ ተራዊሕ እየተሰገደ ከደረሳችሁ፤ ዒሻእን በቀልባችሁ ነይቱና ተራዊሕ ከሚሰግዱት ጋር ስገዱ። ኢማሙ ሲያሰላምት እናንተ ተነሱና ለዒሻእ ሶላት የጎደላችሁን ረከዓህ ሙሉ።

ለምሳሌ፦ ከኢማሙ ጋር ሁለት ረከዓህ ተራዊሕ ሲያሰግድ ሁለቱንም ረከዓህ ካገኛችሁ፤ ኋላ የምትሞሉት ቀሪ 2 ረከዓህ ይሆናል።


ኢብኑ ዑሠይሚንና ኢብኑ ባዝ ከሰጡት ፈታዋ የተወሰደ


||
t.me/MuradTadesse

11.9k 0 80 13 208


14k 0 18 5 136

የካቲት 21/2017 በስልጤ ዞን ስልጢ ወረዳ በሚገኘው አዋይ ት/ቤት ሐኒፍ ኢስላማዊ ድርጅት ከበጎ አድራጊዎች እና ከት/ቤቱ አስተባባሪዎች ጋር በመተባበር የመማሪያ መጽሐፍት ድጋፍ አበርክተዋል። ለድጋፍ ስጪዎቹ እና ፕሮግራም አስተባባሪዎቹ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እያቀረብን አላህ ስራቸውን እንዲቀበላቸው እና በመልካም ስራ ሚዛናቸው ላይ እንዲያኖርላቸው እንማፀናለን።

Hanif Islamic Organization | مؤسسة حنيف الإسلامية

©: Hanif Multimedia


ለምንድን ነው ከዙህር ጀምሮ የምታኮርፉትና የምትኮሳተሩት¿
ኧረ! ተው እናንተ ፈገግና ነቃ በሉ። ቢያንስ ሰላምታም መልሱልን¡ አታስፎግሯ¡

12.5k 0 33 68 285



«የአዲስ አበባ መጅሊስ ከዚህ በኋላ በመስጂዶች ጉዳይ አይታገስም።

1446ኛው ታላቁ የረመዳን ወር መስጂዶች ደምቀውና ተውበው ህዝበ ሙሊሙን በተገቢው መንገድ በመቀበል እያሰተናገዱ ነወ።
በአብዛኛዎቹ መስጂዶች ህዝበ ሙሰሊሙ እምነቱ በሚያዘው መሠረት ዒባዳውን እያከናወነ ሲሆን በጣት በሚቆጠሩ መስጂዶች ሁከት ለማስነሣት የተደረጉ ሙከራዎችን በየመሰጂዱ የሚገኙ ኮሚቴዎች፣ ሀዲሞችና ህብረተሰቡ ባደረገው ጥረት በቁጥጥር ሰር ሊውሉ ችሏል።

በተለይም ጠሮ መስጂድ ፣ሎሚ ሜዳ(ዓሊ) መስጂድና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 የሚገኘው ሀምዛ መሰጂድ የረመዳንን መግባት ተከትሎ በአንዳንድ ሰውር አላማ ያላቸው ግለሰቦች ሁከትና ብጥብጥ በማሰነሣት ከፍተኛ ችግር ሲፈጥሩ የቆዩ አካላት መሸሸጊያ ሆኖ የቆየ ቢሆንም መጅሊስ ከዛሬ ነገ ይቀየራሉ ብሎ ሁኔታውን አባታዊ በሆነ ትዕግሰት ይዞት ቆይቷል።

መጅሊሰ በእነዚህ ጥቂት መስጂዶች የተፈጠሩትን ችግሮች ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶችን ቢያደርግም ዕድሉን ባለመጠቀም ቡድኑ መሰጂድ ሰብሮ በመግባት፣ ጄነሬተር በማጥፋት፣ ለደህንነት የተገጠመ ካሜራን በመሰባበር እና አማኞች የተረጋጋ ዒባዳ(የአምልኮ ስርዓት) እንዳይከውኑና የረመዳንን ወር የብጥብጥና የረብሻ አውድማ የማድረግ እንቅሰቃሴያቸውን ቀጥለውበታል።

ከወራት በፊት ማዕከላቸውንና የብጥብጥ መነሻቸውን ዓሊ መስጂድ በማድረግ ሴቶችና ህፃናትን ከፊት በማሰለፍና የተወሰኑ ግለሰቦችን በገንዘብ በመደለል የተጀመረው ውንብድና ኢማሞችን ማይክ ቀምቶ በመደብደብ የተራዊ ሰላት እንዲቋረጥ እሰከ ማድረግ ደርሰዋል

ይህ በግልፅ በሚታወቁ ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በተመረጡና ለማምለጥ ምቹ በሆኑ መስጂዶች ከተለያየ አካባቢ ተጠራርተው በመግባት አወል ሰፍን (የሰላቱን የመጀመሪያ ረድፍ) ለመሰጂድም ሆነ ለሸማግሌዎች ክብር የሌላቸው አሰቀድመው በመያዝ ረብሻ በማሰነሣት መሰጂዱን አውከዋል።

በየጊዜው በየመስጂዱ እየተዘዋወሩ ሁከት የሚፈጥሩ አካላት በሚገባ የሚታወቁና መረጃ ያለን ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ለህዝብ እንደምናሳውቅ እየገለፅን መጅሊሱ ከዚህ በላይ እንደማይታገሰና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የፀሎት ቦታዎች ሠላማዊ እንዲሆኑ መስራቱን እንደሚቀጥል ለህዝበ ሙስሊሙ ያሣውቃል።

መጅሊሱ ካለበት ሀላፊነትና ተጠያቂነት አኳያ ጉዳዩን በትዕግሰት መያዙ አግባብ ቢሆንም በዚህ የሠላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የመተዛዘን ወር በሁለቱ መስጂዶች በተፈጠረው አሳፋሪ ተግባር ክፉኛ ማዘኑን እየገለፀ ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ዒባዳውን(የአምልኮ ሥርዐቱን) የሚፈፅምባቸው መስጂዶች ሠላማቸው እንዲጠበቅ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሠራ በድጋሚ ለመግለፅ ይወዳል።»

የአ/አ/ከ/እ/ጉ/ከ/ም ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

13.5k 0 16 27 237

ትናንት ለጾመኞች ማስፈጠሪያ እንደ ባለፈው አመት እንጀምር ባልኳችሁ መሠረት፤ ኸይር ፈላጊዎች ባደረጋችሁት ርብርብ 232, 908.52 ብር (ሁለት መቶ ሰላሳ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስምንት ብር ከሃምሳ ሁለት ሳንቲም) ደርሰናል።

እስካሁን ሪከርዱን አንድ ወንድም በ54, 495 ብር እየመራ ይገኛል።

አላህ ከሁላችሁም ሶደቃችሁንና ጾማችሁን ይቀበላችሁ።


በአላህ ፈቃድ እኛም ዛሬ ማታ ጀምረን የማስፈጠር መርሃ ግብራችን ይጀመራል።


አሁንም ኸይር ፈላጊዎች ይህ በጎ ተግባር ሳይቋረጥ እስከ ረመዿን መጨረሻ ይቆይ ዘንድ፤ በዚህ በተከበረ ወር የሶደቃ እጃችሁ አይታጠፍ። ባረከ-ል'ሏሁ ፊኩም!




√ የተዘጋጀ ምግብ ወይም አስቤዛ መስጠት ለማትችሉና በጥሬ ገንዘብ ካላችሁ ላይ ለምትሰድቁ ይህን አካውንት ተጠቀሙ።

√ አካውንት: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000481376018
የአካውንት ስም: ዐብደላህ ሻፊ እና ወይም ሙራድ ታደሰ

የአንድ ሰው ማስፈጠሪያ ባለፈ አመት 250 ብር ነው። ዘንድሮ 300 ብር ነው። ይህን መሠረት አድርጋችሁ አቅማችሁ የቻለውንና የነየታችሁትን ያክል ጾመኛ ማስፈጠር ትችላላችሁ።


የከፈላችሁበትን ደረሰኝ በውስጥ መስመር በዚህ ሊንክ t.me/Murad_Tadesse ላይ ላኩልኝ።




አላህ ጾማችሁንም፣ ሶደቃችሁንም ይቀበላችሁ።
መቼም ጾመኛን ስለማስፈጠር ምንዳ ያውም ታማሚንና ማፍጠሪያን ያጣን ሚስኪን ማስፈጠር ስላለው ምንዳ አልነግራችሁም።



እና ደግሞ እስኪ አንድ ጊዜ ሰዳቂዎችን መርቋቸው፣ በዱዓችሁ አስታውሷቸው፣ ሁላቸውንም ሐጃቸውን እንዲሞላላቸው።




Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 dan repost
አድዋ ሲነሳ ይህንን ታሪክ አለማስታወስ ይከብዳል።


ወገኖቻችንን አላህ ከሸሂዶች ያድርጋቸው።


በዚህ መልኩ አጥንቱን ከስክሶ በገነባት ሃገር ውስጥ ህዝበ ሙስሊሙ ተቋም አልባና መሪ አልባ ሆኖ እስካሁን ድረስ መቀመጡ በራሱ ያሳዝናል።


https://youtu.be/l0MKhKqshGc

13k 0 25 5 198

Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 dan repost
አድዋ‼
=====
✍ የኢትዮጵያን ታሪክ ስናስብ ብዙ አሳዛኝና አሳፋሪ ታሪኮች አሉ።
በተለይም የውጭ ወራሪን ዲል ያደረግንባቸው የጦር አውድማዎች የአርበኞች ጀብዱ ሥራ ይደንቃል።

ከዚህ አሳዛኝ ክስተት መካከል አንዱ አድዋ ላይ የተከሰተው ነው።
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በዚህ የጦርነት ቀን ተሳትፈው የፋሽስት ጣሊያንን ጦር ድባቅ መተዋል።
ያው እንደሚታወቀው ከኛም ከኢጣሊያም በርካታ ዜጎች ሙተዋል።
ከዲሉ በኋላ የክርስቲያን ኢትዮጵውያን አጥንት እየተለቀመ ተቀበሩ።
የሙስሊም ኢትዮጵያውያን አፅም ግን ቀባሪ አጣ! ለአሞራና ጂብ ቀለብ ሆነ‼
በወቅቱ የነበረችው የነ ሚኒልክ ኢትዮጵያ ይህን ያክል ግፈኛ ነበረች‼
መድሎኛ‼
ዛሬ ላይ የጋራ ታሪክ አለን የሚሉን ሰዎች፤
ትናንት ላይ እንዲህም አይነት የጭካኔ ጥግ እንዳሳለፍን ይወቁት።

ለማንኛውም የትናንትን ጠባሳ ታሪክ ለመድገም ሳይሆን፤
ከርሱ ተምረን መጥፎውን ትተን በጎውን እንያዝ‼
||
t.me/MuradTadesse


Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 dan repost
አድዋ እንደ በድር ጘዝዋ‼
==================

✍ ዐድዋ የረመዷን ፆመኛ ሆነን የነሳውነው ድል፤ በእናት አገር ኩርፊያ የለም ብለን ከአፄ ምኒልክ ደመኛ የማስገበር ምሬት ማግስት ደምና አጥንት የገበርንበት ድል።

√ በቀን ማክሰኞ ማርች 2/1896 (2 March, 1896.) ኢትዮጵያውያን ከጣልያን ጋር ገጥመው ድል ያደረጉበት የድል ቀን ነው።

√ ይህ ቀን በሂጂሪ አቆጣጠር ረመዷን 17/1313 ዓመተ ሂጅራ ነው።

√ ይህ ማለት በዐድዋ ጦርነት የተሳተፉት ሙስሊሞች ረመዷን ፆም ላይ ነበሩ።

√ ረመዷን 17 ማለት የበድር ድል በዓል ቀን ነበር።

√ 1313 ዓመተ ሂጅራ ማለት እንደ ማሜ ዩሱፍ ትነተና 1000 የቁረይሽ ሙሽሪኮች 300 የነብዩን ጦሮች ገጥመው ድል የተደረጉበት ቀን ነው‼

የዐድዋ ጦርነት Adowa Victory celebrations day March 2 is Ramadan 17, the day of badir. The battle was fought on Tuesday, 13th March 624 CE, on the 17th Ramadan 2 AH (after Hijrah) in the Islamic calendar.

On the morning of Monday, Ramadan 17, 2 AH, which coincides with The Adwa Victory Day is a national holiday in Ethiopia which is celebrated on 2 March.

The Muslims were greatly outnumbered by the Quraysh tribe, whose army on this occasion consisted of approximately 1,000 men, including 100 horses. The Muslims had gathered an army of only a meek 300 men and only two horses in comparison. It appeared to all that the Muslims would be swiftly overcome by the immense Quraysh army.

ይህንን ቀን ወደ ኋላ ሄዶ ያሰላው ሙሐመድ ዩሱፍ ክብር ይገባዋል! ዐብዱ-ል-ጀሊል


በ40 ቀን አንድ ጊዜ ብቻ የሚመገቡ…

18 አመት…


ጾም ነው፤ ክፉ አታናግሩኝ!

13.3k 0 20 34 240

በምድር በላይ በደል ፥ በተንሰራፋበት፣
የጣዖት አምልኮ ፥ ጫፍ በደረሰበት፣
ጎሳ ከጎሳ ጋ ፥ በሚጋደልበት፣
ባለሃብት ደሃውን ፥ በሚጨቁንበት፣
ሴት ልጆችን መውለድ ፥ ወንጀል በሆነበት፣
ደጋግ የአላህ ባሮች ፥ መጠጊያ ባጡበት፣
የባርነት ቀንበር ፥ ድካ ባለፈበት፣
ምድር አልችል ብላ ፥ የፈሳዱን ብዛት፣
በድቅድቅ ጨለማ ፥ በተሞላችበት፣
ውዱን ነቢይ ሰጠን ፥ ለዓለማት እዝነት።

በእርሳቸው መላክ ፥ ጨለማው ተገፏል፣
የተውሒዱ ፋኖስ ፥ እስከ ጥግ አብርቷል፣
የተጋጨ ጎሳ ፥ ወንድማማች ሆኗል፣
የባርነት ቀንበር ፥ ቀስ በቀስ አክትሟል፣
የተውሒዱ ጮራ ፥ ዓለምን አዳርሷል፣
የኡማው አንድ አካል ፥ ክብሯ ተመልሷል።


Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 dan repost
የዕለቱ ሐዲሥ‼
============
✍ አቡ ሁረይራህ (አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና) ባስተላለፈው ሐዲሥ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

(من نسِي وهو صائمٌ فأكل وشرب فليتمَّ صومَه ، فإنَّما أطعمه اللهُ وسقاه!)


«ጾመኛ ሆኖ ሳለ ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ጾሙን ይሙላ (ሳይፈታ ይቀጥል)። የመገበውና ያጠጣው አላህ ነው፡፡»

[ሙስሊም: 1155፣ አል-ቡኻሪይ: 6669፣ ሒልየቱ-ል-አውሊያእ: 2/316]


النِّسيانُ أمرٌ جِبِلِّيٌّ في طَبيعةِ البَشَرِ، واللهُ تَبارَك وتعالَى يَعلَمُ ذلك مِن عِبادِه، ولا يُكَلِّفُهم شيئًا فوْقَ طاقتِهم، ومِن رَحمتِه سُبحانَه وتعالَى بهمْ أنْ تَجاوَزَ عن مُؤاخَذتِهم بسَبَبِ نِسيانِهم.
وفي هذا الحَديثِ بيَّن النَّبيُّ صلَّى اللهُ عليه وسلَّم أنَّ مَن أكَل أو شَرِب ناسيًا وهو صائمٌ، فإنَّه يَبْقَى على صِيامِه، ولا يُفطِرُ، وخَصَّ الأكلَ والشُّربَ مِن بينِ المُفَطِّراتِ؛ لغَلَبَتِهما، ونُدرةِ غيرِهما، كالجِماعِ، ثُمَّ بيَّن أنَّه لا يَلزَمُه القَضاءُ بقولِه: «فإنَّما أَطعَمه اللهُ وسَقاه»، فنَسَبَ الفِعلَ للهِ تعالَى لا للنَّاسِي؛ للإشعارِ بأنَّ الفِعلَ الصَّادرَ منه مَسلوبُ الإضافةِ إليه، فلوْ كان أفْطَرَ لأُضِيفَ الحُكمُ إليه، وهذا لُطفٌ مِن اللهِ تعالَى بعِبادِه، ورَحمةٌ بهم. وهذا بخِلافِ المتعَمِّدِ؛ فإنَّه يقضي اليومَ ولا كفَّارةَ عليه.
وفي الحَديثِ: التَّيسيرُ ورفْعُ المشقَّةِ والحرَجِ عن العِبادِ.
وفيه: دلالةٌ على عَدَمِ تكليفِ النَّاسي.


በምድር በላይ በደል ፥ በተንሰራፋበት፣
የጣዖት አምልኮ ፥ ጫፍ በደረሰበት፣
ጎሳ ከጎሳ ጋ ፥ በሚጋደልበት፣
ባለሃብት ደሃውን ፥ በሚጨቁንበት፣
ሴት ልጆችን መውለድ ፥ ወንጀል በሆነበት፣
ደጋግ የአላህ ባሮች ፥ መጠጊያ ባጡበት፣
የባርነት ቀንበር ፥ ድካ ባለፈበት፣
ምድር አልችል ብላ ፥ የፈሳዱን ብዛት፣
በድቅድቅ ጨለማ ፥ በተሞላችበት፣
ውዱን ነቢይ ሰጠን ፥ ለዓለማት እዝነት።

በእርሳቸው መላክ ፥ ጨለማው ተገፏል፣
የተውሒዱ ፋኖስ ፥ እስከ ጥግ አብርቷል፣
የተጋጨ ጎሳ ፥ ወንድማማች ሆኗል፣
የባርነት ቀንበር ፥ ቀስ በቀስ አክትሟል፣
የተውሒዱ ጮራ ፥ ዓለምን አዳርሷል፣
የኡማው አንድ አካል ፥ ክብሯ ተመልሷል።


ከ'ናት አባት በላይ ፥ ለኛ ተቆርቋሪ፣
መጥፎ ሠሪዎችን ፥ በ'ሳት አስፈራሪ፣
መልካም ሠሪዎችን ፥ በጀነት አብሳሪ፣
በሁሉም ሁኔታ ፥ በጎ ተናጋሪ፣
ክፉ 'ማይወጣቸው ፥ ጀግና ትጉህ መሪ፣
በየመንገዳቸው ፥ ወደ ተውሒድ ጠሪ።



ስነ ምግባራቸው ፥ ምን ቃል ይገልፀዋል፣
እንኳን ወዳጃቸው ፥ ጠላትም ያውቀዋል፣
በበጎነታቸው ፥ ብዙውን ማርከዋል፣
የበደሏቸውን ፥ በይቅር አልፈዋል፣
ቁርኣንን ኑረው ፥ ለኛ አስተምረዋል።


ገና ሳንወለድ ፥ በዓይናቸው ሳያዩን፣
"ወንድሞቼ" ብለው ፥ "ናፍቀውኛል" አሉን።
ይገባን ይሆን ወይ ፥ ይሄ ሁሉ ፍቅር፣
ከተዘፈቅንበት ፥ ካለንበት አንፃር?


ጥለውን ሄደዋል ፥ ፍንትው ባለ መንገድ፣
ሐቁን አብራርተዋል ፥ ሁሉንም አንድ'ባንድ፣

አደራ ብለዋል ፥ ከዚህ እንዳንለቅ፣
እስከፍፃሜያችን ፦ ዱንያን እስክንለቅ።

ሐቃቸው አለብን ፥ ልንከተላቸው፣
ከነፍስያችንም ፥ ልናስበልጣቸው፣
ከናት አባት በላይ ፥ የምር ልንወዳቸው፣
በተጠሩ ቁጥር ፥ ልናወድሳቸው።

ባሰመሩት መስመር ፥ ቀጥ ብለን ልንጓዝ፣
ያዘዙንን እንጂ ፥ ያላሉንን ላንይዝ፣
ያፈነገጥን እንደሁ ፥ አለው ትልቅ መዘዝ።

መጸጸት ብቻውን የማይጠቅምበት ቀን ፥ ከመምጣቱ በፊት፣
ከሺርክ እንውጣና ፥ ከቢድዓህ አዙሪት፥፣
በሱንናቸው መንገድ ፥ ተሳስረን በአንድነት፣
በተውሒድ ጎዳና ፥ እንጓዝ ወደፊት።

ያኔ እንሆናለን ፥ የምር ተናፋቂ፣
የሐውዳቸው ቀማሽ ፥ አደራ ጠባቂ፣
ሚዛናዊ ህዝቦች ፥ ግሩም አስደናቂ።

አላህ ይዘንልን ፥ መንገዱን ያግራልን፣
ከተዘፈቅንበት ፥ በቶሎ ያስወጣን፣
የሚደሰትብን ፥ ምርጥ ባሮች ያር'ገን፣
የዓለማቱን እዝነት ፥ በጀነት ያሳየን፣
የርሱን ፊት ተመልካች ፥ ወዳጆቹ እንሁን።


||
t.me/MuradTadesse

13.4k 0 114 21 179
20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.