እህታችን ዘህራን ረሳችኋት እንደ ጓዶች!
ምንም እንኳ እኔ በግሌ በአካል ባላውቃትም ለማጣራት የላኳቸው ኡስታዞችና ወንድሞች በአሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ የምትገኝ መሆኗን ጠቁመውኛል። እናት ናት፣ ከ10 አመት በላይ ልምድ ያላት ፋርማሲስትም ነበረች። አሁን ላይ ግን የተገኘባት የጡት ካንሰር ደረጃው ከፍ ብሎ ወደ አጥንቷ መሸጋገሩን ነው የተነገራት። ወደ ጉበቷና መሰል ወሳኝ የሰውነቷ ክፍሎች ሳይዛመት ቶሎ መታከም እንዳለባት ተነግሯታል።
እኔንም፣ እሷንም፣ እናንተንም ያገናኘን ኢስላም ነውና በዚህ በተባረከ የጁሙዓህ ቀን ለእህታችን የሶደቃ እጃችሁን በመዘርጋት አላህ ከሰጣችሁ ሪዝቅ ላይ አካፍሏት። እርሷም ቶሎ ታክማ በአላህ ፈቃድ ለልጆቿ እናብቃት።
አሁን ላይ 730,306 ብር ደርሶላታል። ገና ግማሽ እንኳ አልሆነላትም። የሚያስፈልጋት 1.5 ሚሊዮን ብር ነው። እርሷ ያላትን ገንዘብ ባለፉት አመታት ታክማ ስለጨረሰች አማራጭ ስታጣ ነውና ወደናንተ ብቅ ያለችው ከአላህ በታች ትብብራችሁን ትፈልጋለች።
አነሰ በዛ ሳትሉ አላህ ከሰጣችሁ ላይ በመሰደቅ ካንሰሩ የበለጠ ወደ ሰውነቷ ሳይሰራጭ እናሳክማት። በሽታው ጊዜ ባገኘ ቁጥር የመዳን እድሉ አናሳ እየሆነ ነው የሚሄደው።
√ የአካውንት ስም፦ ዘሃራ ኸድር
√ የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1000236374754
ስልክ፦ 0903202647
የምትሰድቁበትን ደረሰኝ በውስጥ መስመር
@Murad_Tadesse ላይ ላኩልኝ። አላህ ይጠብቃችሁ። ቡሪክቱም!
||
t.me/MuradTadesse