"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


የልብህን መሻት (ፍላጎት) ለእግዚአብሔር በጸሎትህ ውስጥ ንገረው፤ ገና ከመውለዳችን አስቀድሞ ሁላችንንም ለሚያውቀን ለእርሱ። ሁሉም ነገር እንደኔ ፈቃድ ይሁን ብለህ አትጠይቅ፤ ምክንያቱም ሰው ለእርሱ የሚጠቅመውን ምን እንደሆነ ላያውቅ ይችላልና። ስለዚህ ለእግዚአብሔር እንዲህ በለው እንደ ፈቃድህ ይሁን! እርሱ ሁሉን ለጥቅማችን ያደርገዋልና። #ብፁዕ_አቡነ_ሺኖዳ


ጌታችን ወደዚህ ዓለም የመጣው ቤዛ ሆኖ ሊያድነን ነው። ቅዱስ ጳውሎስ " ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው።" እንዳለ(1ጢሞ 1:15)። እርሱ ራሱ ለቤዛነት ሰው መሆኑን "እንዲሁም የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።" ብሎ እንደተናገረ(ማቴ. 20:28)።

ይህም ማዳን በዕለተ አርብ በመስቀል ላይ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን ከፅንሰቱ ጀምሮ በእያንዳንዱ መንገድ ካሳ እየከፈለልን መጥቶ በመስቀል ላይ የተፈጸመ ነው። እርሱ በእያንዳንዱ ጉዞው ካሣ እየከፈለልን ለድኅነታችን የሚያስፈልገውን ሥራ ሠራ። ስለዚህም የቤዛነት ሥራው በጽንሰት የተጀመረ ነው። እርሱ በጽንሰቱ ተስፋ ሰጠን፥  በጽንስ ይቆራኝ የነበረ ዲያብሎስንም አራቀ። በልደቱ የዲያብሎስን ልብ አራደ፥ ሰውና መላእክትም አብሮ እንዲዘምሩ አደረገ። በስደቱ ከገነት የተሰደደ አዳምን ክሶ ስደታችንን ሻረልን፥ ተሰዶ የሰማዕታትን ስደት የባረከላቸውም እርሱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። በጥምቀቱ የአዳምና የሔዋንን የዕዳ ደብዳቤ ፋቀ፥ በእኛ ላይ የነበረችውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰ። በጾሙ አርእስተ ኃጣውዕን አደከመ፥ ዲያብሎስን ድል የምንነሳባትን ሥርዓተ ጾም ሠራልን። በተአምራቱ ኃይል ሰይጣንን አደከመ። በስቃዩ ስቃያችንን አራቀ። በሞቱ ሞትን ደመሰሰ። በትንሣኤው ትንሣኤን አበሠረ። በዕርገቱ ወደ ቀደመ ክብራችን መመለሳችንን አበሠረ። በዚህ ጉዞ እኛ ድኅነትን(መዳንን) አገኘን።

ሥራ በሠራበት ሁሉ ካሳ ከፍሎልን(ቤዛ ሆኖን) ያዳነን መድኃኒታችን እርሱ የተመሰገነ ነው።አሜን በእውነት
🤲


+ ለምን ትቀናለህ? + 

በዜና አበው ላይ አጋንንት አንድን መነኩሴ ለማሰናከል ሲማከሩ የሚያሳይ ታሪክ ተጽፎአል፡፡ መነኩሴው ለብዙ ዘመናት በተጋድሎ አሳልፎ ከብቃት የደረሰ መናኝ ነበር፡፡ የአጋንንቱ ጭፍራ በአለቃቸው ተመርተው ይህንን መነኩሴ ለማሳት ዘመቱ፡፡ ተራ በተራ ወደ እርሱ እየሔዱ የፈተና ወጥመዳቸውን ዘረጉበት፡፡ በዝሙት ሊፈትኑት ሞከሩ፡፡ አልተሳካም፡፡ በምግብም ሞከሩ ድል ነሣቸው፡፡ የሚያውቁትን የፈተና ስልት በተለያየ መንገድ እየተገለጹ አንዴ ሰው አንዴ መልአክ እየመሰሉ ሊጥሉት ቢሞክሩም አልቻሉም፡፡

አለቃቸው ይኼን ጊዜ በሉ እኔ የማደርገውን ተመልከቱ አላቸውና መንገደኛ መስሎ ወደ መነኩሴው ቀረበ፡፡ በጆሮው የሆነ ነግሮት ወዲያው ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ይህንን ጊዜ አጋንንቱ እያዩት መነኩሴው መንፈሳዊ ገጽታው ተገፍፎ ፊቱ በቁጣና በንዴት ሲለዋወጥ ተመለከቱት፡፡ በዚህም ተደንቀው ምን ብለህ ነው ያሸነፍከው? ብለው አለቃቸውን ጠየቁት፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ ‘ከአንተ ጋር ያደገውና ከአንተ ጋር የተማረው ጓደኛህ እኮ የእስክንድርያ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ’ ብዬ ነገርኩትና ወጣሁ፡፡ አሁን ልቡ በቅናት እየነደደ ነው አላቸው፡፡ አጋንንቱ በደስታ ጨፈሩ፡፡

ሰይጣን የቅናትን ኃይል ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ መጽሐፈ ቅዳሴ ሞትን ሲገልጸው ‘በሰይጣን ቅናት ወደ ዓለም የገባ’ ይለዋል፡፡ ሰይጣን በሰው ልጅ ጸጋ ቀንቶ አዳምና ሔዋንን በፈጣሪያቸው እንዲቀኑና አምላክ መሆን እንዲመኙ አድርጎ ዓለምን ያመሰቃቀለ ነውና ይህንን መነኩሴ ለመጣል ለሺህ ዓመታት ብዙዎችን ወግቶ የጣለባትን ሰይፉን መዘዘበት፡፡ መነኩሴው የእኩያውን መሾም ሲሰማ ቅናቱን መቋቋም አቃተው::

ቅናት እጅግ ክፉ ኃጢአት ነው፡፡ ሰው ቢዘሙት ቢሰክር በሥጋው ነው:: ቅናት ግን በምታስተውል ነፍሱ ውስጥ የሚበቅል መርዝ ነው፡፡   ቃየልን በየዋህ ወንድሙ ላይ ያስጨከነው ቅናት ነበር፡፡ የአቤል ስኬት ለቃየል ውድቀት መስሎ ስለተሰማው በግፍ ሊገድለው በቃ፡፡

ዮሴፍ የለበሳት ቀለምዋ ብዙ የሆነ ጌጠኛ ቀሚስ በወንድሞቹ ዘንድ የመረረ ጥላቻን አትርፋለት ነበር፡፡ አንዱ አጊጦ አምሮ ሲታይ ቢሞትና ቢገላገሉት ደስ የሚላቸው የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ አሉ፡፡  

ዮሴፍም አርፎ አልተቀመጠም፡፡ እየሔደ ሕልሙን ይነግራቸው ነበር፡፡ ስለ ሕልሙም የበለጠ ጠሉት ይላል፡፡ ወዳጄ ሕልምህን ዝም ብለህ ለሰዎች አትዝራ፡፡ ሕልም ስልህ ተኝተህ የምታየውን ብቻ ማለቴ አይደለም፡፡ ራእይህን ፣ ተስፋህን ዕቅድህን ሲያውቁ የሚንገበገቡ የዮሴፍ ወንድሞች በየዘመኑ  አሉ፡፡ ፍቺው ባይገባቸውም ባልተፈታ ሕልም ይጠሉሃል፡፡ ምንም ነገር ሳታደርግ እንኳን "ለምን አለምከው?" ብለው ጥርስ ይነክሱብሃል፡፡ ዮሴፍ ግን ይኼ ስላልገባው ነገራቸው፡፡ ወዳጄ አንተም ሕልምህን እንደ ዮሴፍ በየዋህነት የምትዘራ ከሆንህ እንግዲህ የዮሴፍ አምላክ ይጠብቅህ፡፡

ቅናት እጅግ ከባድ ነው፡፡ እረኛው ዳዊት ጎልያድን የገደለ ዕለት የተዘፈነለት መዘዘኛ ዘፈንም ነበረ፡፡ ‘ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ ገደለ’ ብለው ዘፈኑለት፡፡ ይህች ዘፈን በሳኦል ጆሮ ስትደርስ ዳዊት ላይ ብዙ ጦር አስወረወረች፡፡ ሳኦሎች ሌላ ሰው ከእነርሱ በላይ ሲመሰገን የሰሙ ዕለት በቅናት ታውረው ገበታ ላይ ሳይቀር ሰይፍ ይመዛሉ፡፡

የጠፋው ልጅ ወንድምን አስበው፡፡ (ሉቃ 15:20) ወንድሙ ከጠፋበት ተመልሶ ደስታ ሲደረግ እርሱ ግን ከፍቶት ውጪ ቁጭ አለ፡፡ ወዳጄ ቅናት ከቤተ ክርስቲያንና ከእግዚአብሔር መንግሥት ያስወጣል፡፡ የሌላው ስኬት ካበሳጨህ እንደጠፋው ልጅ ወንድም ውጪ ቁጭ ብለህ አፈር እየጫርክ ‘እምቢየው አልገባም’ እያልክ እያልጎመጎምክ ትቀራለህ፡፡

ክርስቶስ ላይ አይሁድ ያቀረቡት ትችት ሁሉ ለሕግ ከመቆርቆር ሳይሆን ከቅናት ነበር፡፡ ጲላጦስ እንኳን ‘በቅናት አሳልፈው እንደሠጡት ያውቅ ነበር’ ይላል፡፡ አንዳንዴ ሰዎች ቅናታቸውን በሌላ ነገር እንደ አይሁድ ሸፍነው ትችት ያቀርባሉ፡፡ ለእግዚአብሔር ሕግ እንደተቆረቆሩ ፣ ለሥርዓቱ እንዳዘኑ መስለው ውስጣቸው ያለውን ቅናትና ጥላቻ ያንጸባርቃሉ፡፡

የሰንበት መሻር ፣ ለቄሣር ግብር መከፈል ፣ የመቅደሱ በሦስት ቀን ፈርሶ መሠራት እንዳንገበገባቸው እርር እያሉ ቢናገሩም እውነታው ግን ቅናት ነው፡፡ ‘የቤትህ ቅናት በላኝ’ እንዳለው ጌታ በየዘመኑ የሰዎች ቅናት ብዙ ንጹሐንን ትበላለች፡፡

ወዳጄ በሌላው ትቀና እንደሆን አሁኑኑ ከዚህ ውስጥን በልቶ ከሚጨርስ ካንሰር ራስህን አድን፡፡

ራስህን ከሌሎች ጋር አታወዳድር፡፡ በምድር ላይ እግዚአብሔር የፈጠረው አንተን የሚመስል ሌላ ሰው የለም፡፡ ካንተ ቀድሞም በትክክል አንተን የሆነ ሰው አልተፈጠረም ለወደፊትም አይፈጠርም፡፡ እግዚአብሔር ቀድሞ ያልሠራው ደግሞም የማይሠራው ምርጥ ዕቃው ነህና ራስህን ከሌላ ጋር አታወዳድር፡፡

ለአንተ ብቻ የሠጠው ጸጋ አለና ሌሎችን መመልከት ትተህ ውስጥህ ያለውን ውድ ማንነት ቆፍረህ አውጣ፡፡ ያንተ ሕይወት ቁልፍ የተቀበረው አንተው ውስጥ ነው፡፡ ሌሎችን ረስተህ ወደ ራስህ ጠልቀህ ግባ፡፡ መብለጥ ከፈለግህም አሁን ያለውን ራስህን ብለጠውና ሌላ ትልቅ አንተን ሁን፡፡ 

በቅናት እንዳትቃጠል ሌሎችን ሰዎችንም ውደዳቸው፡፡ ከወደድሃቸው ‘ፍቅር አይቀናም’ና የእነርሱ ስኬት የደስታህ ምንጭ ይሆናል፡፡ የቅናት ስሜት ሲሰማህም ‘ቀናተኛ ልቤን ፈውስልኝ’ ብለህ ለምነው፡፡

‘በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን’ ሮሜ 13፡13

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ 20

https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊




‹‹በአንቺም ምሰሶዎች ቆሙ ሕንፃዋም ባንቺ ጸና ግድግዳዋም ባንቺ ተሠራ፡፡ ጠፈርዋም ባንቺ ተፈጠረ ፣ ዋልታዋም ባንቺ ተዋቀረ ጭምጭምታዋም ባንቺ ተጨመጨመ፡፡ ደጆቿም ባንቺ ተከፈቱ ፣ መቃን መድረኳም በልጅሽ ደም ተረጨ ፡፡ በአንድ ልጅሽ መስቀል ፍሬ ያፈራችው ቅድትስ ቤ/ክ ታመሰግንሻለች ፤ ከርኩሰቷም በሆድሽ ፍሬ ደም የነጻችው ፣ ያዘነች ስትሆን በልጅሽ በወዳጅሽ ትንሣኤ የተጽናናችው ፣ የተዋረደች ስትሆን በድንግልናሽ ቡቃያ ከፍ ከፍ ያለችው ቅድስት ቤ/ክ ታመሰግንሻለች፡፡ ቅድስት ድንግል ሆይ ምስጋናሽ በሁሉ መላ ውዳሴሽም በዓለም ዳርቻ ሁሉ ሰፈፈ የውቅያኖስ ባሕር በመደቡ የተወሰነ ነው ፣ የሐኖስም ባሕር እንደ መጠኑ ልክ አለው ያንቺ ምሥጋና ግን ልክ፣ወሰን፣ሥፍር፣ቁጥር፣ማለቂያ የለውም ፤ አዕምሮ ሊወስነው፣አንደበት ተናግሮ ሊፈጽመው አይችልም፡፡ በዕብራይስጥ ማሪሃም የተባልሽ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሆይ ሁሉ ላንቺ ሆነ ፣ ሁሉ ስላንቺ ተፈጠረ፡፡ አዳም ከኅቱም ምድር የተፈጠረ አንቺን ያፈራ ዘንድ ነው፡፡ ሔዋንም ከአዳም ጎን የተፈጠረች አንቺን ትወልድ ዘንድ ነውና›› ፡፡ (አርጋኖን ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ)

ቅድስት ሆይ ለምኝልን🤲✝


ትህትና አንገትን ደፍቶ መሄድ አይደለም ከማንኛውም ነገር ሌላውን ማስቀደም ነው።
ትህትና ለታላላቆች መቀመጫ ወንበር መልቀቅ አይደለም፤ለታናናሾችም መቀመጫ ወንበር መልቀቅ ነው።
ትህትና አንገትን ማቅለስለስ አይደለም ልብን መስበር ነው።
ትህትና ለአምላክ ብቻ መገዛት አይደለም ለሰውም ራስን ማስገዛት ነው።
ትህትና ሰው ትሁት እንዲልህ  ሰው ሰራሻዊ ራስን ዝቅ ማድረግ አይደለም፤ ተፈጥሮአዊ የሆነ ወዝ ሲኖርህ ነው።
ትህትና ፈጣሪ ሆኖ ሳለ ከሰው እንደተወለደው አምላክ ራስን ማውረድ ነው።
ትህትና ፈጣሪ ሆኖ ሳለ ከፍጡሩ ጋር ጓደኛ ሆኖ  የተመላለሰውን አምላክ መምሰል ነው።
ትህትና ፈጣሪ ሆኖ ሳለ በጥፊ ሲመቱት የታገሰውን አምላክ መምሰል ነው።
ትህትና ፈጣሪ ሆኖ ሳለ ሊገድሉት  በመስቀል ለሰቀሉት ጠላቶች ፍቅርን መስጠት ነው። ትህትና ወልደ እግዚአብሔርን  (ኢየሱስን) መምሰል ነው።


መቃብሩ በፈርጣማ ወታደሮች ተጠበቀ። በትላልቅ ደጎራ ተዘጋ።
አይሁዶች በደስታ ሰከሩ። ፖለቲከኞች በፍርዳቸው እረኩ።
እናቱ እንባዋ እንደ ጅረት ፈሰሰ። ሐዋርያት የሀዘን ደመና ከበባቸው። ከበረከቱ፣ ከፈውሱ የተጠቀሙት ሕዝቦች በአምላክነቱ ተጠራጠሩ። ጥቂቶቹ በሀሰት በመገደሉ አለቀሱ።
እውነት በዝምታ ተቀበረች።
ነገር ግን ሙታንን የሚያስነሳው አምላክ መቃብሩን ፈንቅሎ ወጣ -
እሁድ ሌሊት 6:00።
የአርብ ልቅሶ በእሁድ ደስታ ተሻረ። የወላጅ እናቱ የጠነከረ ሀዘኗ እንደ ጤዛ ተነነ። ሐዋርያት በደስታ ተሰባበቡ። የተጠራጠሩት ወደ ማመን ተመለሱ። የተቀበረችው እውነት ተገለጠች።
በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጪም እምትኖሩ የክርስትና እምነት ተከታዮች የድንግል ማርያም ወዳጆች እንኳን ለዳግማ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ


ከዛፎች ሁሉ  ጠማማው ዛፍ ተመርጦ የመጥረቢያ እጀታ ይሆናል።  ስለት ተገጥሞለት ጓደኞቹን ዛፎች እየቆረጠ ይኖራል። እጀታው ሲያረጅ ስለቱ ወጥቶ እጀታው ወደ ምድጃ ይወረወራል። ይከስላል። አመድ ይሆናል።
ሰውም ልክ እንደ እጀታው መጨረሻ ላይ የእጁን ያገኛል።
....
ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤"
(ወደ ገላትያ ሰዎች 6:7)


"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
❇#ፃድቁ_አባ_ዮሐንስ_ሐፂር_።

☞•••ወር በገባ በ20 የአቡነ ዮሐንስ ሐፂር ወርሐዊ መታሰቢያቸው ነው አቡነ ዮሐንስ ሐጺር ቁመታቸው አጭር ስለ ነበር ዮሐንስ ሐጺር አጭሩ ዮሐንስ ተብለዋል፡፡ ☞በ18 ዓመታቸው እስቄጠስ ገዳም ገቡ ☞አባታችን አቡነ ዮሐንስ በታዛዥነታቸው በእጅጉ ይታወቃሉ፡፡ ይህንንም ለመፈተን አንድ ቀን አባ ባይሞይ የደረቀ እንጨት አንስተው ለአቡነ ዩሐንስ ሰጧቸውና ይህን ደረቅ እንጨት ትከለውና ውሃ እያጠጣህ አብቅለው ፍሬ እስኪያፈራም ተንከባከበው አሏቸው፡፡

☞አቡነ ዮሐንስም በፍጹም መታዘዝ እሸ ብለው ደረቁን እንጨት ተክለው ሦስት
ዓመት ሙሉ ከሩቅ ቦታ በቀን ሁለት ጊዜ ውኃ እየቀዱ በማምጣት ማጠጣት
ጀመሩ፡፡
☞በ3ኛውም ዓመት ደረቁ እንጨት ጸድቆ ለመለመ ታላቅ ዛፍም ሆኖ አብቦ
አፍርቶ ጣፋጭ ፍሬ አፈራ፡፡ አባ ባይሞይም ፍሬውን ቆርጠው ወስደው የታዛዡን
የትሑቱን ፍሬ እንሆ ቅመሱ እያሉ ሀቅዱሳን ሰጧቸው፡፡ ቅዱሳኑም እግዚአብሔርን
እያመሰገኑ ተመገቡ፡፡
]አባታችን ትልቁ የቅድስና ደረጃ ላይ ሲደርሱ ቀና ቢሉ ሥልሱ ቅዱስን
ይመለከታሉ ዝቅ ቢሉ ደግሞ እንጦሮጦስን ያያሉ፡፡ አቡነ ዮሐንስ ሐጺር በታላቅ
ተጋድሎአቸው ሥሉስ ቅዱስን በገሃድ ለማየት የበቁ ታላቅ አባት ናቸው፡፡
☞ከአባታችን ከአባ ዮሐንስ ሐጺር የህይወት ትምህርቶች መካከል
☞1'1☞የጠላቱን ከተማ ለመቆጣጠር የዘመተ ንጉሥ አስቀድሞ የውኃውን
መንገድ ይዘጋል፤ የእህሉንም መግቢያ ይይዛል፡፡ ያንጊዜ ጠላቶቹ ይራባሉ
ይጠማሉ፡፡ በመጨረሻም እጃቸውን ይሰጣሉ፡፡ የነፍስን ፆር ለማሸነፍም
በተመሳሳይ መንገድ መጠቀም ይገባል፡፡ በጾም በረኃብ ከጸና የነፍሱ ጠላቶች
ይዳከማሉ፡፡
☞1'2☞እኔ በትልቅ ዋርካ ሥር የተቀመጠንና አራዊት ሊጣሉት የመጣን ሰው
እመስላለሁ፡፡ ሊቋቋማቸው እንደማይችል ከተረዳ ሸሽቶ ወደ ዛፋ በመውጣት
ነፍሱን ያድናል፡፡ በእኔም የተፈጸመው ይኸው ነው፡፡
☞በባኣቴ ተቀምጪ ክፋ ሐሳቦች ሊቃወሙኝ ሲመጡ ልቋቋማቸው እንደማልች
ባወቅኩ ጊዜ በጸሎት ወደ፡እግዚአብሔር ሸሽቼ እመሽጋለሁ፡፡ በዚያም ከጠላቶቼ
ፍላፃ እድናለሁ፡፡
☞1'3☞መለወጥ የምትፈለግን ነፍስ በተመለከተ አባ ዮሐንስ እንዲህ አለ
በአንዲት ከተማ ውስጥ ብዙ ወዳጆች የነበሯት አንዲት አመንዝራ ሴት ነበረች፡፡
ከገዥዎቹ አንዱ ቀረባትና መልካም ሴት ለመሆን ቃል ግቢልኝና አገባሻለሁ
አላት፡፡ እርሷም ቃል ገባችለትና ተጋቡ፡፡ ወደ ቤቱም ወሰዳት፡፡
☞የቀድሞ አፍቃሪዎቿ ያቺን ሴት ፈለጓት እርስ በርሳቸውም ያ ልዑል ወደ ቤቱ
ወሰዷታል ወደ ቤቱ ብንሔድ ይቀጣናል፡፡ ነገር ግን ፧ጓሮ በኩል እንሒድ፤
ለርሷም እና ፏጭላት የፋጨቱን ድምጽ ስትሰማ ከደርቡ ወርዳ ወደኛ
ትመጣለች በዚህም ያለ ችግር እናገኛታለን ተባባሉ፡፡ ወደ ቤቷም ጓሮ ተጉዘው
ያፏጩ ጀመር፡፡
☞እርሷ ግን የፋጨቱን ድምፅ ስትሰማ ጆሮዎቿን ደፈነች፡፡ ወደ ውሳጣዊው
እልፍኝም ገባች፡፡ በሩንም ጥርቅም አድርጋ ዘጋች፡፡
☞ይቺ ሴት የኛ ነፍስ ምሳሌ ናት፡፡ ወዳጆቿ የተባለም ፈተናዎቿ ናቸው፡፡ ገዥ
የተባለውም ክርስቶስ ነው፡፡ እልፍኝ የተባለው ዘለዓለማዊ ቤት ነው፡፡ እነዚያ
የሚያፏጩት ክፋዎች አጋንንት ናቸው፡፡ ነገር ግን ነፍስ ሁለጊዜም በክርስቶስ
አምባነት ትሸሸጋለች፡፡
☞(በዲያቆን ዳንኤል ክብረት"በበረሓው ጉያ ውስጥ ከሚለው መጻሐፍ
የተወሰደ፡፡)

☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ ዮሐንስ ሐጺር የጸሎታቸው በረከት አይለየን፡፡




"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
🌹#ቅዱስ_በብኑዳ ሰማዕት🌹

❖📌 ወር በገባ በ20 የቅዱስ በብኑዳ መታሰቢያ ነው ይህ ቅዱስ ለብቻው የሚኖር ዕውነተኛ ተጋዳይ ነው የእግዚአብሔር መልአክም ተገልጦለት የመቀደሻ ልብስ ለብሰህ ወርደህ ለመኰንኑ ተገለጥለት አለው።

❖ በዚያን ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ከመርከብ ወርዶ ወደዚያች አገር ወደብ መድረሻው ጊዜ ነበር፤ ይህንንም ባሕታዊ ፈልጎት አላገኘውም ነበር፤ እነሆ ቅዱስ በብኑዳም በፈቃዱ መጥቶ ወደ መኰንኑ ሔዶ በክብር ባለቤት በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የማምን በግልጥ እኔ ክርስቲያን ነኝ ብሎ በታላቅ ቃል ጮኸ።

❖ መኰንኑም ፈልጎ ያጣው የታወቀ ባሕታዊ መሆኑን በአወቀ ጊዜ እንዲአሠቃዩት በእግር ብረትም አሥረው ከጨለማ ቤት እንዲጥሉት አዘዘ፤ በዚያን ጊዜም ብርሃን ወጣ የእግዚአብሔር መልአክም ከሕማሙ ፈወሰው አበረታው አጽናናውም።
❖ በዚያችም አገር ስሙ ቄርሎስ የሚባል ምእመን ሰው ነበረ ከእርሱ ጋራም ሚስቱና ዐሥራ ሁለት ጐልማሶች ልጆቹ አሉ፤ እነዚህን ሁሉንም የከበረ በብኑዳ አስተማራቸው አጽናንቷቸውም ራሶቻቸውን ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ሙተው አክሊልን ተቀበሉ።

❖ አርያኖስም ተቆጥቶ በቅዱሱ አንገት ከባድ ደንጊያ ሰቅለው ወደ ባሕር ይጥሉት ዘንድ አዘዘ በእግዚአብሔር ኃይልም ከድንጋዩ ጋራ ዋኘ ደግሞ ከሰሌን ዛፍ ላይ ይሰቅሉት ዘንድ አዘዘ ያቺም ሰሌን ዐሥራ ሁለት ዘለላን አፍርታ ለመጪው ትውልድም መታሰቢያ ሆነች፤ ከዚህም በኋላ የከበረች ራሱን ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን።

አርኬ
✍️ሰላም ዕብል ለበብኑዳ ሰማዕት። እንተ አግሀደ ብርሃነ በቤተ ጽልመት። ወአመ ሰቀልዎ ሎቱ መልዕልተ በቀልት። አውጽአት ፍሬ በይእቲ ሰዓት። እስከ ጉቡአን አንከሩ እምዛቲ ትእምርት።
✍️ሰላም ለክሙ ማኅበረ በብኑዳ በሕቁ። ዐሠርተ ወክልኤቱ እለ ትትኌለቁ። ወሰላም ካዕበ ለዘተለውዋ ለጽድቁ። ቄርሎስ ወብእሲቱ ወዓዲ ደቂቁ። እስከ በደሞሙ ኅቡረ ተጠምቁ።

🌹ጆይን እያላችሁ ተቀላቀሉ🌹https://t.me/Orthodoxtewahdoc




"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
✝እንኳን አደረሳችሁ✝
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

❖ ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት=

✞ ሰማዕቱ በብኑዳ ✞

+ቅዱስ በብኑዳ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አካባቢ በምድረ
ግብፅ ተባሕትዎን መርጦ የሚኖር ገዳማዊ አባት ነው::
በበርሃ
በጾምና በጸሎት ተወስኖ ለእግዚአብሔር የምስጋናን
መስዋዕት እየሠዋ አገልግሏል::

+በዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያኖች በግፍ ሲገደሉ ቅዱሱ
ሰው በበርሃ ውስጥ ነበር:: አንድ ቀን የእግዚአብሔር
መልአክ መጥቶ
ሰማዕት እንዲሆን መከረው:: እርሱም ነጭ በነጭ ለብሶ
አምሮበት ወደ ንጉሡ ሔደ:: በፊቱም ቀርቦ በክርስቶስ
ስም ታመነ::
ብዙ ጸዋትወ መከራም ተቀበለ::

+ንጉሡ (መኮንኑ) "አመጣጥህ ወደ ሞት ሳለ ምነው
እንዲህ እንደ ሠርገኛ ማጌጥህ?" ቢለው "እኛ
ክርስቲያኖች ትልቁ
ሠርጋችን ሞታችን ነው:: ልንሔድ ከክርስቶስም ጋር
ልንኖር እንናፍቃለንና" ብሎታል::

+ቅዱስ በብኑዳ ብዙ ተሰቃይቶ: ተአምራትን ሰርቶ በዚሕች
ቀን ተሰይፏል:: የጽድቅን አክሊል ከሰማዕትነት ጋር ደርቦ
አግኝቷል::

❖ቸሩ አምላክ ከሰማዕቱ በረከትን ያካፍለን::

❖ሚያዝያ 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ በብኑዳ (ሰማዕት ወጻድቅ)
2.ቅዱስ ቄርሎስ: ሚስቱና 12 ልጆቹ ሰማዕታት (ከቅዱስ
በብኑዳ ጋር የተገደሉ)

በ 20 የሚከበሩ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
6.ቅዱስ ወክቡር ማር ቴዎድሮስ ሰማዕት


++"+ በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን
ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ
ብጹዓን ናችሁ::
ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ:: አትናወጡም:: ዳሩ ግን
ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: በእናንተ
ስላለ ተስፋ
ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር
የተዘጋጃችሁ ሁኑ:: ነገር ግን በየውሃነትና በፍርሃት
ይሁን:: +"+ (1ዼጥ.3:13-16)

>
💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠 /ማቴ ፫:፫/
🔷ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!

❇️ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)❇️

" 🔶ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::🔸
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/zikirekdusn




*©እም እቶነ እሳት*
        ጥራዝ2.ቁ.113

እም እቶነ እሳት /፪/ዘይነድድ አንገፈነ በሰፊሐ እድ ሊቀ መላእክት/፪/

ታላቅ መመኪያ ነህ ለሚያምኑብህ ሁሉ
ናዛዜ ኅዙናን /፪/ ገብርኤል ለልዑል መልአከ ኃይሉ

የነባልባል ኃይሉ ሞገዱ ሲበዛ
ለሠለስቱ ደቂቅ የሆንካቸው ቤዛ

አዝ....ታላቅ መመኪያ ነኽ
ፈጥነህ የምትደርስ በዕለተ ጻሕቅ
ምስጉን ነህ አንተ ከፍ ያልክ በጽድቅ

አዝ...ታላቅ መመኪያነኽ
ዜናዊ ፍስሐ ለሰው ልጅ ድህነት
የሰላም መልአክ ነህ ሊቀ መላእክት

አዝ....ታላቅ መመኪያ ነኽ
በአማላጅነትህ እንኮራለን
እኛ ክርስቲያኖች ደቂቀ ጽዮን

የግእዙ ትርጉም፡-ከሚነደው የእሳት ነበልባል የመላእክት አለቃ እጆቹን ዘርግቶ አተረፈን።
በዕለተ ጻሕቅ/ጭንቅ ቀን/


በመልአከ ሞት ከመውደቅ የምትታደግ ገብርኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን። አማላጅነትህን በመታመን ተስፋ እናደርጋለንና በመዓልትም በሌሊትም አንተ ጠብቀን🙏
ገብርኤል ሆይ  ከሰው ወገን ከቶ ጠዋትና ማታ እንደኔ ኀዘንና ትካዜ የሚበዛበት የለም። ከመላእክትም ወገን እንዳንተ ያዘኑትን የሚያረጋጋ የለም። ገብርኤል ሆይ ስለዚህ እኔም አውቄና አንተን አምኜ። ይህን ያቀረብኩልህን ጸሎት እንደትልቅ ዋጋ ቆጥረህ የማረጋጋት ቃለህን አሰማኝ።መልክአ ገብርኤል

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል አደረሳችሁ
🤲✝🦋


ቅዱሳት አንስት (ቅዳሜ)

ከትንሳኤ ሳምንት ይህች ዕለት "ቅዱሳት አንስት" (የተቀደሱ ሴቶች) ተብላ ትጠራለች::


በወቅቱ በኢየሩሳሌምና ዙሪያዋ ከተከተሉት ሴቶች ጌታችን 36ቱን መርጧል:: እነዚህ እናቶች ከዋለበት ውለው : ካደረበት አድረው : የቃሉን ትምሕርት ሰምተዋል:: የእጁንም ተአምራት አይተዋል:: ፈጽመውም አገልግለውታል::

መጽሐፍ "አንስተ ገሊላ ኩሎን::
አዋልዲሃ ለጽዮን::
አስቆቀዋሁ ለመድኅን:: ከመ ዖፈ መንጢጥ እንዘ ይሤጽራ ገጾን::" ይላልና በዕለተ ዐርብ ፊታቸወውን እየነጩ : ደረታቸውን እየደቁ : እንባቸውም እንደ ጐርፍ እየፈሰሰ አብረውት ውለዋል::

ጌታም ፍጹም ፍቅራቸውን ተመልክቷልና ከሁሉ አስቀድሞ ትንሳኤውን ለእነሱ ገለጠላቸው:: እነርሱም ትንሳኤውን በመፋጠን አብሥረዋል:: "ሰበካ ትንሳኤ፡ አዋልዲሃ ለጽዮን" እንዳለ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ፡፡ በዚህም ምክንያት ይህች ዕለት "ቅዱሳት አንስት" ተብላ ትከበራለች::

አምላካችን በፍቅርና በቅድስና ጌጥ ካጌጡ እናቶቻችን በረከትን ያድለን::

መልአኩም መልሶ ሴቶቹን አላቸው:- 'እናንተስ አትፍሩ:: የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና:: እንደተናገረ ተነስቷልና በዚሕ የለም:: የተኛበትን ሥፍራ ኑና እዩ:: ፈጥናችሁም ሒዱና ከሙታን ተነሣ: እነሆም ወደ ገሊላ ይቀድማቹሃል:: በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሯቸው' . . . እነሆም ኢየሱስ አገኛቸውና ደስ ይበላችሁ አላቸው:: እነርሱም ቀርበው እግሩን ይዘው ሰገዱለት:: (ማቴ. 28:5-10)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን! †


"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
🌷መልክአ ቅዱስ ገብርኤል📗
ደስታን አብሳሪው ቅዱስ ገብርኤል ሆይ ሰላም እልሃለሁ/፫/

ቅዱስ ገብርኤል በዕለተ ቀኑ ከክፉ ነገር ሁሉ ይሰውረን ለሀገራችን ፅኑ ሰላምን ያምጣልን አሜን🙏


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ 19።፲፱

https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.