"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


ድንግል ሆይ
ደስ ብሰኝ በንቺ ደስ እሰኛለሁ፣ ባዝንም ባንቺ እፅናናለሁ።
መከራ ችግርም ቢያገኘኝ ወደ አንቺ እጮሃለሁ።
የአመፀኛም ምላስ ቢያስከፋኝ ወደ አንቺ ፊት እማለላለሁ።
ሰውነቴም የወደደችው ነገር ቢኖር አንቺን እለምናለሁ🙏
በመታመን ያሻሁትን የተመኘሁትንም በንቺ አገኛለሁ🙏
(መፅሐፈ አርጋኖን ዘአባ ጊዮርጊስ)

ድንግል ማርያም ሀዘናችሁን በደስታ ትቀይረው🙏


ጌታ ሆይ ዛሬም ተመስገን !!!
(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 50 )
----------
6፤ እነሆ፥ እውነትን ወደድህ፤ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ።
7፤ በሂሶጵ እርጨኝ፥ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ፥ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ።
8፤ ሐሤትንና ደስታን አሰማኝ፥ የሰበርሃቸውም አጥንቶቼ ደስ ይላቸዋል።
9፤ ከኃጢአቴ ፊትህን መልስ፥ በደሌንም ሁሉ ደምስስልኝ።
10፤ አቤቱ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልኝ፥ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ አድስ።
11፤ ከፊትህ አትጣለኝ፥ ቅዱስ መንፈስህንም ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ።
12፤ የማዳንህን ደስታ ስጠኝ፥ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።
13፤ ለሕግ ተላላፎች መንገድህን አስተምራለሁ፥ ኃጢአተኞችም ወደ አንተ ይመለሳሉ።
14፤ የመድኃኒቴ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፥ ከደም አድነኝ፥ አንደበቴም በአንተ ጽድቅ ትደሰታለች።
15፤ አቤቱ፥ ከንፈሮቼን ክፈት፥ አፌም ምስጋናህን ያወራል።

መልካም ቀን
✝🥰🌷

635 0 14 3 33

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
🌷መልክአ ቅዱስ መርቆሬዎስ📗

የቅዱስ መርቆሬዎስ አምላክ ሆይ የገብረ ማርያም ነፍስ ማርልኝ /፫/

የገብረ ማርያምን ነፍስ ማርልኝ
የገብረ ማርያምን ነፍስ ማርልኝ
የገብረ ማርያምን ነፍስ ማርልኝ


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
              ✥  ✞ ✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ የካቲት /፳፭/25/

@Orthodoxtewahdoc

#የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን❤️🥀




ሕይወት አንዳንዴ ፊልም ትሆንብናለች
ደራሲው እግዚአብሔር ሲሆን
ተዋናዮቹ ደግሞ እኛው ነን።
ሁሉም ሰው በግሉ አሪፍ አክተር ለመባል ይሮጣል
ነገር ግን ሁሉም ከተፃፈለት ውጪ አይተውንም።!

🌷ደህና እደሩ ቤተ
ሰብ🥰✝

1k 0 11 7 48

እናቴ አዛኝቷ ስማፀን በስምሽ
ድንግል ማርያም ብዬ ስማፀን በስምሽ
በቅድመ እግዚአብሔር ልመናዬን አድርሽ
.
እኔ ደካማ ነን ኃጢአቴ የበዛ
እኔ ጎስቋላ ነኝ በደሌ የበዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በዋዛ ፈዛዛ
ጊዜዬን ያባከንኩ በከንቱ በዋዛ
.
እመብርሃን ስልሽ ፈጥነሽ ድረሽልኝ
ልመናዬን ሰምተሽ ቆመሽ ለምኝልኝ
.
ኃጢአቴ ቢበዛም ይዣለው አንችን
አስምረሻልና በላዔ ሰብን
.
አንገቴን ቢያስደፋኝ በዝቶብኝ ኃጢአቴ
ምልጃሽን ፈለኩኝ ድንግል ሆይ እናቴ
.
ያን ክፉ ጨለማ እንዳላይ አደራ
ድንግል ሆይ ከልይኝ ከዲያብሎስ ጭፍራ
.
እመብርሃን እያልኩ ቆሜ ከደጅሽ
በብርሃን እጆችሽ እንባዬን አብሽ
.
አለም አታላይ ነች ወደሷ ተሳብኩኝ
ታማልጅኝ ብዬ አንቺኑ ተራብኩኝ🙏


#የሕሊና_ጸሎት

🙇አቤቱ ሆይ አንደበቴ በሞት ሳይዘጋ ሰውነቴም በማይፈታ ሰንሰለት ከመታሰሩ በፊት ምስጋናህን እናገር ዘንድ አብቃኝ ለንስሓ ለስጋወ ደሙ አብቃኝ አሜን በእውነት🙏


ነገ የካቲት 25 ሰማእቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ነው እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ከክፈ ነገር ሁሉ ይሰውረን ምልጃ ጸሎቱ አይለየን አሜን🙏🌷


"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
🌹ወር በገባ በ 25/ታስባ የምትውለው ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት ☑የሕሙማን እናት የተባለችው ሐምሌ 25 ያረፈችው በብዙ ሊቃውንት የተወደሰችው የቅድስት ቴክላ ድንቅ ታሪክ +

❖ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ብዙዎች አበው በድርሳናቸው የመሰከሩላትን በድንግልናዋ ጸንታ የኖረችውን ቅድስት ቴክላ ናት፤ ይኽቺ ቅድስት ሴት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን ከተከተሉት ቅዱሳን ሴቶች አንዷ ስትኾን እጅግ ውብ፣ ሀብታምና የተማረች ነበረች ፤ በዚኽም ከልዑላኑ ታሚሪስ የሚባል ወጣት ሰው አጭቷት ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስ በ45 ዓ.ም. ከአንጾኪያ ከተማ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ኼዶ ወንጌልን ሲሰብክ በተመስጦ ኾና ትምህርቱን ትከታተል እንደነበር ከሊቃውንት ቅዱስ አምብሮስና ቅዱስ አውግስጢኖስ ጽፈዋል።

❖ በሐዋርያውም ትምህርት ልቧ በመነካቱ የድንግልና ሕይወትን በመምረጥ ለእናቷ የታሚሪስ እጮኝነቷን ማፍረሷንና ክርስቲያን እንደምትኾን ነገረች፤ ወላጆቿ ግን ርሱን እንዳትሰማ ቢያግባቧትም ርሷ ግን እነርሱን አልሰማቻቸውም፤ በዚኽ ምክንያት አባቷ ዲማኖስና ርምጋኖስ ከሚባሉ ዳኞች ኺዶ ከሰሳት፤ እነርሱም ሊያስገድዷ ቢሞክሩም አልቻሉም፤ ከዚያም የቀደመ ልብሷንና ጌጦቿን ኹሉ ትታ ከቅዱስ ጳውሎስ ጉባኤ ተቀመጠች፡፡

❖ በዚኽ ተበሳጭተው በመኰንኑ ዘንድ እንደገና ከሰዋት፤ ርሱም ሌሎቹ ፈርተው ወደ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳይኼዱ በእሳት እንዲያቃጥሏት አዘዘ፤ ርሷ ግን በሚያቃጥሏት ጊዜ ልቧን አጽንታ ቅዱስ ጳውሎስን ተመለከተችው፤ ያን ጊዜ ሐዋርያው በመስቀል ምልክት ባማተበ ጊዜ ወደ እሳቱ ምድጃ ተወረወረች፡፡

✍️ “ፈነወ እግዚአብሔር ዝናመ ብዙኀ ወበረደ ወመብረቀ ወኮነ ዕቶነ እሳት ከመ ጠል ቈሪር ወሮጸት ቴክላ ወበጽሐት ኀበ ቅዱስ ጳውሎስ ኀበ ኀሎ መካነ ኅቡአ” ይላል፤
❖ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ብዙ ዝናብን፣ በረድን፣ መብረቅን ላከ፤ የእሳቱም ምድጃ እንደ ቀዝቃዛ ጠል ኾነ፤ ቴክላም ሩጣ ቅዱስ ጳውሎስ ተሰዉሮ ወደ አለበት ቦታ በመድረስ፤ ወንጌልን ለመማር በኼደበት ኹሉ ትከተለው ዘንድ ለመነችው፡፡

❖ ከዚያም ከርሱ ጋር አንጾኪያ ከተማ በመኼድ ለዐዲስ አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል ትነግራቸው ነበር፤ ከመልኳ ውበትም የተነሣ ከመኳንንቶቹ አንዱ ሊአገባት ፈለገ፤ ርሷ ግን ዘለፈችው፤ ከዚያም ለአንበሶች እንድትጣል ቢደረግም ልክ እንደ ነቢዩ ዳንኤል አንበሶቹ ሳይነኳት በነርሱ መኻከል ኹለት ቀናት ቆየች፤ ከዚኽም በኋላ በኹለት በሬዎች መኻከል አስረው በከተማው ውስጥ አስጐተቷት፤ ነገር ግን ምንም ክፉ ነገር አልደረሰባትም፤ ከዚያም በኋላ ለቀቁዋት፡፡

❖ ርሷም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ኼደች ርሱም አጽንቶና አረጋግቶ የሰማችውን እንድትመሰክር አዘዛት፡፡ ርሷም ወደ ወላጆቿ ሀገር በመኼድ ስለ ክርስቶስ መሰከረች፤ አባትና እናቷም አምነው ክርስቲያን ኾኑ፤ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቷት ብዙዎችን ትፈውሳቸው ነበር በዚኽም “የሕሙማን እናት” በመባል ትታወቃለች፤ በመጨረሻም ተጋድሎዋን ፈጽማ ሐምሌ 25 ዐረፈች፤ መስከረም 27 ትታሰባለች፤ ሥጋዋም በግብጽ ደቡብ ሰንጋር በሚባል ቦታ ተቀመጠ፤ በዚያም ከሥጋዋ የተነሣ ብዙ ድንቅ ተአምር ተገልጧል፡፡

❖ በርካቶች ቅዱሳን አበው በየድርሳናቸው የቅድስት ቴክላን ቅድስናና ተጋድሎ ጽፈውላታል፤ በተለይ ቅዱስ ሜቶዲየስ ቅድስት ቴክላ ከቅዱስ ጳውሎስ በተማረችው ትምህርት ምን ያኽል ጠንካራ እንደነበረች፤ በጊዜው ከነበሩት የደናግል ኅብረት ከፍ ከፍ ያለች፤ ድንግልናቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ በዝማሬም ትመራቸው እንደነበር ይገልጣል ፡፡

❖ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ስለ ርሷ ክብር ሲጽፍላት የተባረከች ድንግል ቴክላ ንጽሕናዋን ሰማዕትነቷን ለልዑል እግዚአብሔር በማቅረብ በአንድ እጇ በሥጋው በደማዊ ፈቃድ ላይ የድል ዘውድን ስትይዝ፤ በሌላኛው እጇ በአደገኛ ሥቃይና መከራ ላይ የክብር አክሊሏን እንደያዘች ዐውቃለኊ ብሏል፡፡

❖ ቅዱስ ጀሮምም በደብዳቤው ላይ “የጌታ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የደናግልን ማኅበር አስከትላ እናንተን ለመገናኘት የምትመጣባት የዚያቺ ቀን ክብር እንደምን ያለ ነው!... ያን ጊዜ ቴክላ እናንተን ለማቀፍ በደስታ ትበርራለች ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያም የድንግልና ሕይወቷን አብነት እንዲያደርጉ ሲያስተምር
✍️“የንጽሕና አምሳል ከምትኾን ወደር ከሌላት ከአምላክ እናት በመቀጠል ከሴቶች አስቀድማ ሰማዕት የኾነች ቴክላን ምሳሌ አድርጌ አነሣለኊ፤ እናንተም የርሷን መንፈሳዊ ውበት ተላብሳችኊ ሰማያዊ ጸጋን ለማግኘት ነፍሳኹን በተለያዩ መንፈሳዊ መልካሞች ሥራዎች ታስጌጧት ዘንድ ይገባል” በማለት አስተምሯል፡፡

❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አርከ ሥሉስም ተጋድሎዋን በማዘከር
✍️“ሰላም እብል ለሐዋርያዊት ቴክላ እግዚአብሔር ዘአኀየላ ኢያቊስልዋ አናብስት ወእሳተ ዕቶን ኢያሕልላ እስመ አምነት ትምህርተ ጽድቅ ከመ ጳውሎስ ይቤላ እስከኀደገት አበዊሃ ወገደፈት ብዕላ”
👉አንበሶች እንዳያቈስሏት የእሳት ምድጃም እንዳያቃጥላት እግዚአብሔር ያበረታት ሐዋርያዊት ለኾነች ለቴክላ ሰላምታ ይገባል፤ አባቶቿን እስክትተውና ሀብቷን እስክትጥል ድረስ ደርሳ ጳውሎስ እንዳላት የእውነት ትምህርትን አምናለችና እያለ የተቀደሰ ሕይወቷን በአድናቆት ጽፎላታል፡፡
❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ
✍️“ሰላም ለጤቅላ (ቴክላ) ዘሞአቶ ለተኲላ በገድል ንጽሕት ድንግል”
👉ንጽሕት ድንግል በገድል ተኲላውን ያሸነፈችው ለኾነች ለጤቅላ ሰላምታ ይገባል)እያለ ያወድሳታል።

የቅድስት ቴክላ በረከት ረድኤት ይደርብን
https://t.me/zikirekdusn
ምንጭ ገብረ ክርስቶስ መርዓዊ አቡየ




"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
☞ ወር በገባ በ 25 የጻድቁ አባታችን አቡነ ሕፃነ ሞዓ ወርሐዊ መታሰቢያቸው
ነው፡፡
☞የአቡነ ህፃን ሞዓ ቤተሰቦቻቸው ልጅ ባለ መውለዳቸው እድሜያቸው በጣም
አርጅተው ሰለነበር ፈጣሪያቸውን ዘወትር ይማፀኑ ነበር፡፡
☞ለጻድቁ አባታችን ለህፃን ሞዓ አባት ለሆኑ አርኬሌዲስ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ
ገብርኤል ተገልጾ ለሰማይ ለምድር የበቃ ልጅ እንደሚወልዱ አበሰራቸው፡፡
☞ለጻድቁ እናታቸውም ትቤፅዮን ታላቁ አባታችን አቡነ ዜና ማርቆስ እንዲሁ
የበቃ የነቃ የልጅ ፍሬ እንዳለቸው ነገሯቸው፡፡
☞በዚህም መሠረት አባታችን በግንቦት 25 ቀን ተፀንሰው በብርሃን ክርታስ
ተጠቅልለው በጥር 25 ቀን ተወለዱ፡፡
☞አባታችን አብነ ሕጻን ሞኣ የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ዘመድ
ናቸው፡፡
☞አቡነ ህፃን ሞዓ ሌላኛው ስማቸው ህፃን ዘደብረ በግዕ ተብለው ይጠራሉ፡፡
ይኸውም የደብረ በግዑ ገዳም የመሠረቱት እርሳቸው ሰለሆኑ ነው፡፡
☞ጻድቁ አባታችን ወይንዬ ተክለ ሐይማኖት (ከደብረ ብርሃን) በቅርበት ከሚገኝ
ቦታ አንድ ሀብታም ገበሬ ጋር በጉልበታቸው ተቀጥረው እያገለገለገሉ ሳለ፡፡
☞ከእለታት በአንድ ቀን ያ ገበሬ እርሻ ለመሄድ እተሰናዳ ሳለ በጠዋት አንደኛው
ገበሬ ይሰወራል ገበሬውም ዛሬ እርሻ ከመሄድ አልቀርም ብሎ ለግዜው በጠፋው
በሬ ተተክተው አባታችን አቡነ ሕጻን እንዲያርሱ ያደርጋቸዋል፡፡
☞በዚያም ሲያርሱ የጎተቱበት ፈሩ(መስመሩ) ከዛም በጣም ደክሟቸው ሰለነበር
ከሰውዬው ሽሽት እየሮጡ ከትልቅ ተራራ አናት ሲደርሱ ሰውነታቸው ተብረብርኮ
በእግራቸው ወደ፡ታች ስርጉድ ያለች ድንጋይ ከሩጫቸው የተነሣ በቆሙበት ቦታ
ሆነው እጅጉን ደክሟቸው በሐይል የተነፈሱበት ምድር ዛሬም የተነፈሱበትን
ለማሰብ እፍ እፍ የሚል ትንፋሽ ልክ እንደ ሰው የሚሞቅ ትንፍሽ ታወጣለች፡፡
☞ያም በፃድቁ እስትፋስ የተመሰለው ይህ ከመሬት ውስጥ የሚወጣ እስትንፋስ
ለአስም በሽታ መድሐኒት ሆኖ ብዙዎችን እየፈወሰ ይገኛል፡፡
☞ይህ የጻድቁ የአብነ ሕጻን ገዳም ከደብረ ብርሃን በቅርብ ርቀት ከወይንዬ
ተክለሐይማኖ
ወረድ ብሎ ይገኛል በዚህ በተጸነሱበት በግንቦት 25 ቀን በደማቅ ሁኔታ
ይከበራል፡፡
☞ጌታች መድኃኒታች እየሱስ ክርስቶስ የሰጣቸው ቃል ኪዳን፡፡
☞ወር በገባ በ25 ቀን ሰምህን የሚጠራ፤ ዝክርህን ያዘከረውን፤ገድልህን
ያነበበውን ያስነበበውን የሰማውን ለቤተክርስቲያን መገልገያ ጧፍ እጣን
የሰጠውን፤ገዳማቸውን የረገጠውን እሰከ 12ትውልድ እምርሃለሁ የሚል ቃል
ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡
☞እኛንም የቃልኪዳናቸው ተካፋይ ያድርጉን፡፡
☞ጻድቁ አባታችን አቡነ ሕፃን ሞኣ ገዳማትን ከቀኑ ሀይማኖት ካስተማሩ በኃላ
በሐምሌ 25 ቀን እረፍታቸው ሆነ፡፡
☞የጻድቁ አባታችን አቡነ ህፃን ሞዓ ረድኤትና በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን፡፡
☞የጻድቁ አባታችን የአቡነ ህፃን ሞዓ በዓለ እረፍታቸው ሐምሌ 25 ነው፡፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ




"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
♨ #አቡነ_አቢብ_ማለት⁉

🌹#ወር በገባ በ25 " አቡነ አቢብ (አባ ቡላ) መታሰቢያው ነው🌹
📘ይህን ታላቅ ቅዱስ በምን እንመስለዋለን⁉ ¤እኛ ኃጥአን ጣዕመ ዜናውን ነገረ ሕይወቱን ሰምተን ደስ ተሰኝተናል! ¤ቅዱሱ አባታችን:- "ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ" ብለን እንጠራሃለን::¤ዳግመኛም "አቢብ - የብዙኃን አባት" ብለን እንጠራሃለን::
♨¤እርሱ ቅሉ አባትነትህ አንተን ለመሰሉ ቅዱሳን ቢሆንም እኛን ኃጥአንን ቸል እንደማትለንም እናውቃለን::
¤አባ! ማነው እንዳንተ የክርስቶስን ሕማማት የተሳተፈ!

¤ማን ነው እንዳንተ በፈጣሪው ፍቅር ብዙ መከራዎችን የተቀበለ!

¤ማንስ ነው እንዳንተ በአንዲት ጉርሻ አማልዶ ርስትን የሚያወርስ!

¤የፍጡራንን እንተወውና በፈጣሪ አንደበት ተመስግነሃልና ቅዱሱ አባታችን ላንተ ክብር: ምስጋናና ስግደት በጸጋ ይገባሃል እንላለን::

+"+ ልደት +"+

=>አባታችን አቡነ አቢብ የተወለደው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ አካባቢ ሲሆን ሃገረ ሙላዱ ሮሜ ናት:: ወላጆቹ ቅዱስ አብርሃምና ቅድስት ሐሪክ እጅግ ጽኑ ክርስቲያኖች ነበሩ:: ልጅ ግን አልነበራቸውም:: ዘመነ ሰማዕታት ደርሶ ስደት በሆነ ጊዜ እነርሱም በርሃ ገቡ::

+በዚያም ሳሉ በቅዱስ መልአክ ብሥራት ሐሪክ ጸንሳ ብሩሕ የሆነ ልጅ ወለደች:: ቅዱሱ ሕጻን ሲጸነስ ማንም ሳይተክለው የበቀለው ዛፍ ላይ መልአኩ እንዲህ የሚል የብርሃን ጽሑፍ ጽፎበት ወላጆቹ ዐይተዋል::
"ቡላ ገብሩ ለእግዚአብሔር: ወቅዱሱ ለአምላከ ያዕቆብ: ዘየኀድር ውስተ ጽዮን"

+"+ ጥምቀት +"+

=>ቅዱሱ ሕጻን ከተወለደ በሁዋላ ሳይጠመቅ ለ 1 ዓመት ቆየ::
ምክንያቱም ዘመኑ የጭንቅ ነውና ካህናትን እንኩዋን በዱር በከተማም ማግኘት አይቻልም ነበር:: እመቤታችን ግን ወደ ሮሙ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሰለባስትርዮስ ሒዳ "አጥምቀው" አለችው::

+ወደ በርሐ ወርዶ ሊያጠምቀው ሲል ሕጻኑ ተነስቶ: እጆቹንም ዘርግቶ:- "አሐዱ አብ ቅዱስ: አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውዕቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ አመስግኖ ተጠመቀ:: ከሰማይም ሕብስትና ጽዋዕ ወርዶላቸው ሊቀ ዻዻሳቱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የሕጻኑ ወላጆች "ለልጃችን ስም አውጣልን" ቢሉት "ቡላ" ብሎ ሰየመው:: እነርሱም ምሥጢሩን ያውቁ ነበርና አደነቁ::

+"+ ሰማዕትነት +"+

=>የቅዱሱ ቡላ ወላጆች ለ10 ዓመታት አሳድገውት ድንገት ሕዳር 7 ቀን ተከታትለው ዐረፉ:: ሕጻኑን የማሳደግ ኃላፊነትን የአካባቢው ሰዎች ሆነ:: ሕጻኑ ቡላ ምንም የ10 ዓመት ሕጻን ቢሆንም ያለ ማቁዋረጥ ሲጾም: ሲጸልይ ክፉ መኮንን "ለጣዖት ስገዱ" እያለ መጣ::

+በዚህ ጊዜ በሕጻን አንደበቱ አምልኮተ ክርስቶስን ሰበከ:: በዚህ የተበሳጨ መኮንኑ ስቃያትን አዘዘበት:: በጅራፍ ገረፉት: በዘንግ ደበደቡት: ቆዳውን ገፈፉት: በመጋዝ ቆራርጠውም ጣሉት:: ነገር ግን ኃይለ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበርና 2 ጊዜ ከሞት ተነሳ:: በመጨረሻ ግን ሚያዝያ 18 ቀን ተከልሎ ሰማዕት ሆኗል::

+"+ ገዳማዊ ሕይወት +"+

=>ቅዱስ ቡላ ሰማዕትነቱን ከፈጸመ በሁዋላ ቅዱስ ሚካኤል በአክሊላት አክብሮ ወስዶ በገነት አኖረው:: ከሰማዕታትም ጋር ደመረው:: በዚያም ቡላ ቅዱስ ጊዮርጊስን ተመልክቶ ተደነቀ:: መንፈሳዊ ቅንዐትን ቀንቷልና "እባክህን ወደ ዓለም መልሰኝና ስለ ፍቅርህ እንደ ገና ልጋደል" ሲል ጌታን ለመነ::

+ጌታችን ግን "ወዳጄ ቡላ! እንግዲህስ ሰማዕትነቱ ይበቃሃል::
ሱታፌ ጻድቃንን ታገኝ ዘንድ ግን ፈቃዴ ነውና ሒድ" አለው:: ቅዱስ ሚካኤልም የቅዱስ ቡላን ነፍስ ከሥጋው ጋር አዋሕዶ: ልብሰ መነኮሳትንም አልብሶ ግብጽ በርሃ ውስጥ አኖረው::

+"+ ተጋድሎ +"+

=>አባ ቡላ ወደ በርሃ ከገባ ጀምሮ ዐርብ ዐርብ የጌታን ሕማማት እያሰበ ራሱን ያሰቃይ ገባ:: ራሱን ይገርፋል: ፊቱን በጥፊ ይመታል: ሥጋውን እየቆረጠ ለአራዊት ይሰጣል: ከትልቅ ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ወደ ታች ይወረወራል::

+በጭንቅላቱ ተተክሎ ለብዙ ጊዜ ጸልዮ ጭንቅላቱ ይፈሳል:: ሌላም ብዙ መከራዎችን የጌታን ሕማማት እያሰበ ይቀበላል:: ስለ ጌታ ፍቅርም ምንም ነገር ሳይቀምስ ለ42 ዓመታት ጹሟል:: ጌታችንም ስለ ክብሩ ዘወትር ይገለጥለት ነበር::

+የሚታየውም እንደ ተወለደ: እንደ ተጠመቀ: እንደ ተሰቀለ: እንደ ተነሳ: እንዳረገ እየሆነ ነበር:: አንድ ቀንም ጌታችን መጥቶ "ወዳጄ ቡላ! እንዳንተ ስለ እኔ ስም መከራ የተቀበለ ሰው የለም:: አንተም የብዙዎች አባት ነሕና ስምህ አቢብ (ሃቢብ) ይሁን" አለው::

"እስከ ይቤሎ አምላክ ቃለ አኮቴት ማሕዘኔ:
ረሰይከኑ ለባሕቲትከ ኩነኔ:
ዘመጠነዝ ታጻሙ ነፍስከ በቅኔ" እንዲል::

+" ዕረፍት "+

=>አቡነ አቢብ ታላቁ ዕብሎን ጨምሮ በርካታ ደቀ መዛሙርትን አፈራ:: ከእመቤታችን ጋርም ዕለት ዕለት እየተጨዋወተ ዘለቀ:: በተጋድሎ ሕይወቱም ከ10 ጊዜ በላይ ሙቶ ተነስቷል:: በዚህች ቀን ሲያርፍ ገዳሙ በመላእክት ተሞላ::

+ጌታም ከድንግል እናቱ ጋር መጥቶ "ወዳጄ ቡላ! ስምህን የጠራውን: መታሰቢያህን ያደረገውን እምርልሃለሁ:: አቅም ቢያጣ "አምላከ አቢብ ማረኝ" ብሎ 3 ጊዜ በዕለተ ዕረፍትህ የሚለምነኝን: በስምሕ እንኩዋ ቁራሽ የሚበላውን ሁሉ እምርልሃለሁ" ብሎት ነፍሱን በክብር አሳረገ: በሰማይም ዕልልታ ተደረገ::

>




"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
††† እንኳን ለጻድቁ አባታችን ቅዱስ አቡፋና እና ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† አባ አቡፋና †††

††† ታላቁ አባ አቡፋና፦
በምድረ ግብጽ ተጋድሏቸውን የፈፀሙ፣
በመዐልት አምስት መቶ ጊዜ በሌሊትም አምስት ጊዜ አቡነ ዘበሰማያትን ይጸልዩ የነበሩ፣
በአርባ ቀን አንድ ጊዜ ብቻ እህል ይቀምሱ የነበሩና ሙሉ ዘመናቸውን በበርሃ በታላቅ ጽሙና የፈፀሙ አባት ናቸው።

ጻድቁ በጣም የሚታወቁት ከማበጡ የተነሳ እጅግ ግዙፍ በነበረ እግራቸው ነው። ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ ስለ መድኃኔ ዓለም ፍቅር አልቀመጥም፤ አልተኛም ብለው ለአሥራ ስምንት ዓመታት በመቆማቸው ነው።

አሥራ ስምንት ዓመት የመቆማቸው ዜናስ እንደምን ነው ቢሉ፦
አንድ ቀን "እኔ ግን ከዚህ ዓለም የምለየው መቼ ይሆን?" ሲሉ አሰቡ። በእርግጥ ይህንን ሐሳብ ብዙ ሰዎች ሊያስቡት ይችላል። ሐሳቡ ጠቃሚም ያልተፈቀደም ነው።
፩. "ጠቃሚ ነው።" ያልኩት አንድ ሰው ሞት እንዳለ ካወቀ ወይም 'መቼ ነው የምሞተው' ብሎ ካሰበ ንስሐ ይገባል፤ ክፋትን ይተዋል ተብሎ ስለሚታመን ነው። ወገኔ ሁሉ እንደ አውሬ ሲባላ፣ ደም ሲያፈስ፣ ክፋትን ሲጐነጉን የሚውል "እሞት ባይ" ሳይሆን "እኖር ባይ" ሆኖ ነውና።
ግን ሞት በቅርቡ እንዳለ በኃያሉ አምላክ ፊት ራቁቱን ለፍርድ እንደሚቀርብ ለወገኔ ማን በነገረው!
፪. "ያልተፈቀደ ነው።" ያልኩት ደግሞ በሁለት ምክንያት ነው።
"ኢትበሉ ለጌሰም (ለነገ አትበሉ።)" የሚል አምላካዊ ቃል ስላለ።
ማቴ. ፮፥፴፬
ሰው (በተለይ ዓለማዊው) የሚሞትበትን ቀን ቢያውቅ አጭር ጊዜ ከሆነ ሽብር ጭንቀት ይበላዋል። ወዲህ ደግሞ ጊዜው ረዥም ቢሆን እንደ ሰብአ ትካት (ማለትም በኖኅ ዘመን እንደ ነበሩ ሰዎች) 'ብዙውን ልዝናናበት (ኃጢአት ልሥራበት')ና ንስሐ እገባለሁ።' ይላልና ነው።

በዚያውም ላይ በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት ቅዱስ ሰውና የነቢያት አለቃ ቅዱስ ሙሴ የሞቱን ጊዜ ጠይቆ እጅግ መቸገሩን መጥቀሱ በራሱ በቂ ነው። ጌታ "ዓርብ ቀን ትሞታለህ።" ብሎት ለሁለት ዓመታት ዓርብ ዓርብ ሲገነዝ ሲፈታ ኑሯል።

በመጨረሻም ዓርብ ቀን ድንገት መልአከ ሞት መጥቶበታል። ስለዚህ "ወድልዋኒክሙ ንበሩ - ተዘጋጅታችሁ ኑሩ። መባላችንን አስበን ልንኖር ግድ ይለናል።
ማቴ. ፳፬፥፵፬

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ቅዱስ አቡፋና ይህንን የዕረፍታቸውን ነገር ሲያስቡ ቅዱስ መልአክ ተገልጦ "ተርፈከ አሠርቱ ወሰመንቱ - አሥራ ስምንት ቀርቶሃል።" አላቸው። እርሳቸውም "ጌታዬ አሥራ ስምንት ምን?" ሲሉ ቢጠይቁትም ሳይመልስላቸው ተሠወረ።

ከደቂቃ እስከ ኢዮቤልዩ ብዙ አሥራ ስምንቶች አሉ። እርሳቸው ግን "አሥራ ስምንት ቀን ነው!" ብለው ለጌታ ተሳሉ። ስዕለታቸውም "ከዚህ በኋላ አልቀመጥም።" የሚል ነው። እየጾሙ እየጸለዩ ለአሥራ ስምንት ቀናት ቆሙ። ሞት አልመጣም።

"አሥራ ስምንት ሱባኤ ይሆን!" ብለው አሥራ ስምንት ሱባኤ (መቶ ሃያ ስድስት ቀናት) ቆመው ጸለዩ። አሁንም ሞት አልመጣም። "አይ! አሥራ ስምንት ወር ሊሆን ይችላል።" ብለው ለአሥራ ስምንት ወራት (ለአንድ ዓመት ከስድስት ወር) ቆመው ተጉ። አሁንም ግን ሞት የውኃ ሽታ ሆኖ ቀረ።

ይህን ጊዜ ግን ወደ ፈጣሪ ለመኑ። "ጌታዬ! ያልከኝ ምን አሥራ ስምንት ነው?"
ቅዱስ መልአኩም መጥቶ "አቡፋና ሆይ! የቀረህ አሥራ ስምንት ዓመት ነውና ጽና።" ብሏቸው ተሰወረ። ልብ በሉልኝ "እስክሞት አልቀመጥም።" ብለው ተስለዋል።

ቅዱሱ ገዳማዊ በቃላቸው የሚገኙ እውነተኛ ክርስቲያን ነበሩና ለአሥራ ስምንት ዓመታት እንደተተከለ ምሰሶ ቆመው ጸለዩ፣ ጾሙ። እንዲህ ያሉትን ቅዱሳን ሊቃውንት፦
"ሰላም ለከ ጽኑዕ ከመ ዓምድ
ዘኢያንቀለቅሎ ሞገድ።"
(ማዕበለ ዓለም የማያናውጸው ብርቱ ምሰሶ ሆይ! ምስጋና ይገባሃል።) የሚሏቸው።

ስለ ቅዱሱ የተጻፈ አርኬም፦
"ሰላም ለቁመተ አቡፋና ዘአልቦ ኑታጌ
እስከ ተመሰለ እግሩ ከመ እግረ ነጌ።" ይላል። ከመቆም ብዛት አካላቸው ደቆ እግራቸው የዝሆን እግር እስኪመስል ወፍሮ ነበርና።

††† አባ አቡፋና በዘመናቸው ብዙ ተአምራትን ሠርተው በዚህች ቀን አርፈዋል።

††† ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት †††

††† ቅዱስ እንጦኒ (Anthony) በትውልዱ ከሶርያ ዐረቦች ሲሆን በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን ያሳድድ፣ ካህናትን ይደበድብ፣ አብያተ ክርስቲያናትንም ያቃጥል ነበር። እግዚአብሔር በንስሐ ሲጠራው ግን ደግ፣ ጻድቅና ምርጥ ዕቃ ሆኖ ተገኘ። በመጨረሻም ከብዙ መከራ በኋላ ለሰማዕትነት በቅቷል።

††† አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ትጋት፣ ጽናት፣ ፍቅርና በረከት ያድለን። ከማስተዋልም አያጉድለን።

††† የካቲት ፳፭ ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
፩.ቅዱስ አባ አቡፋና ጻድቅ
፪.ቅዱስ እንጦኒ ሐዲስ ሰማዕት
፫.ቅዱሳን ሰማዕታት አውሳንዮስ፣ ፊልሞናና ሉቅያ ድንግል (የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ደቀ መዛሙርት)
፬.ቅዱስ ቶና ዲያቆንና ሰማዕት
፭.ቅዱስ ሚናስ ዘሃገረ ቁስ

††† ወርኀዊ በዓላት
፩.ቅዱስ መርቆሬዎስ ሰማዕት
፪.ቅድስት ቴክላ ሐዋርያዊት
፫.ቅዱስ አበከረዙን ሰማዕት
፬.ቅዱስ ዱማድዮስ ሶርያዊ
፭.አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)

††† "ኃይል የሰጠኝን ክርስቶስ ኢየሱስን ጌታችንን አመሰግናለሁ። አስቀድሞ ተሳዳቢና አሳዳጅ አንገላችም ምንም ብሆን ይህን አደረገልኝ። ነገር ግን ሳላውቅ ባለማመን ስላደረግሁት ምሕረትን አገኘሁ።" †††
(፩ጢሞ ፩፥፲፪-፲፫)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††




"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 dan repost
🌹#ቅዱስ መርቆሬዎስ🌹

📌•••ወር በገባ በ25 ታላቁ ሰማእት ቅዱስ መርቆርዮስ መታሰቢያ በዓል እንኳን አደረሳችሁ አደረሰን ቅዱስ መርቆርዮስ የቀድሞ ስሙ ፒሎፓደር ሲሆን ትርጉሙም #የአብ ወዳጅ የወልድ አገልጋይ ማለት ነዉ፡፡ በወጣትነቱ ከሃዲው ንጉስ ኡልያኖስ ላቆመው ጣኦት አልሰግድም ብሎ የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለውን መከራ ተቀበለ፤በመጨረሻም ህዳር 25 ቀን አንገቱን ቆርጠው ገደሉት ደም ውኃና ወተት ከአንገቱ ፈሰሰ። ንጉሱ በዚያዉ ዘመን ክርስቲያኖችን በጣም ያሰቃይ ነበር፡፡ቅዱስ ባስልዮስም ይገስጸዉ ነበር በዚህም ምክንያት ንጉሱ ቅዱስ ባስልዮስን አሰረዉ፡፡ጳጳሱ በታሰረበት እስር ቤት የቅዱስ መርቆርዮስ ሥዕል ነበር፡፡ቅዱስ ባስልዮስም ከሥዕሉ ስር በመሆን ጸለየ ሥዕሉም ከቦታዉ ታጣ ያ ሥዕል ወደ ዑልያኖስ ቤት ሄዶ በጦር ወግቶ ገደለዉ፡፡በስዕሉ ላይ ያለዉ ጦር ጫፉ ደም ይንጠባጠብ ነበር፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ከሀዲ ዑልያኖስን ቅዱስ መርቆርዮስ በሥዕሉ አማካኝነት እንደገደለዉ አዉቆ እግዚአብሔርን አመሰገነ፡፡ ይህ ሰማዕት በአገራችን በስሙ በርካታ ገዳማትና አብያተክርስቲያናት አሉት በተለይም ቅዱስ ላሊበላ ካነጻቸው 11 ውቅር አብያተክርስቲያናት አንዱን ቤተ መርቆሪዎስ ብሎ ሰይሞለታል፤ በዚህ በሰሜን ሸዋ ደግሞ የሚገርም ገዳም አለው፤ ካህናት በማህሌት ወረብ ሲያቀርቡ ስዕሉ ያሸበሽባል ይዘላል፤ ይህንንም አይቶ ማረጋገጥ ይቻላል፤ በመዲናችን አዲስ አበባ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ ታቦቱ አለ:: መርቆሪዎስ ከሞተ በኃላ ፈረሱ ለሰባት ዓመት ወንጌልን አስተምሯል፤ በኃላም አንገቱን ቆርጠው ገድለውታል እንዴት ብሎ የሚገረም የበልአምን አህያ ይጠይቃት፤ እኛስ እስመ አልቦ ነገር ዘይሳኣኖ ለእግዚያብሔር ብለን እንመልሳለን፤ ዘኁልቁ 22፤28 ቅዱስ ጴጥሮስም እንዲህ አለ ቃል የሌለው አህያ በሰው ቃል ተናግሮ የነብዩን እብድነት አገደ ይላል 2ጴጥ 2፤16። ከሰማዕቱ በረከት ያሳትፈን።

አሜን አሜን አሜን+++

https://t.me/Orthodoxtewahdoc





20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.