Postlar filtri


በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ለ108 የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማጎልበቻ ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል።

ተማሪዎቹ ከአርባ ምንጭ፣ መቐለ እና ድሬዳዋ ከተሞች የተውጣጡ ናቸው።

English Access Scholarship የተሰኘው ፕሮግራሙ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ሲሆን፤ ተማሪዎቹ በትምህርታቸው ስኬታማ እንዲሆኑና ወደፊት የስኮላርሺፕ ዕድሎችን ለመጠቀም የሚያስችላቸውን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው።

ተማሪዎቹ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ስልጠና፣ ዓለም አቀፍ ዜግነት እንዲሁም የአሜሪካ ባህልና ዕሴቶች ላይ ስልጠና እንደሚወስዱ ተገልጿል።

ስልጠናው የተማሪዎቹን የተግባቦት፣ ትብብር እና መሪነት ክህሎቶች በሚያጎለብት መልኩ ይሰጣል ተብሏል።

@tikvahuniversity

24.6k 0 15 35 154

#ጥቆማ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በማንኛውም የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተመድበው "የጀማሪ መርሐግብር የቅድመ ምህንድስና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ" ተማሪዎች መካከል በዘርፉ የተሻለ ክህሎትና ዝንባሌ ያላቸውን ተማሪዎች #በዝውውር ተቀብሎ #በመጀመሪያ_ዲግሪ ማስተማር ይፈልጋል።

በዝውውር ቅበላ የሚደረግባቸው የትምህርት መስኮች፦

1. ፋሽን ኢንጂነሪንግ (Fashion Engineering)
2. ቴክስታይል ኢንጂነሪንግ (Textile Engineering)
3. ቆዳ ውጤቶች ኢንጂነሪንግ (Leather Products Engineering)
4. ቴክስታይል ኬሚካል ፕሮሰስ ኢንጂነሪንግ (Textile Chemical Processing Engineering )

የትምህርት ካምፓስ፦
በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ቴክስታይል እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ለማመልከት፦
https://forms.gle/gSypn17ttmm8k4746

ለተጨማሪ መረጃ:-
0938882020 / 0918187249

@tikvahuniversity


#ጥቆማ

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በድሬዳዋ እና አካባቢው ለሚገኙ ከ7-12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሳይንስ የትምህርት አይነቶች (ፊዚክስ፣ ሂሳብ፣ ኬሚስትሪ እና ባይሎጂ) ተግባር-ተኮር ስልጠና አዘጋጅቷል።

ስልጠናው ሙሉ ለሙሉ በተግባር የተደገፈ ሲሆን፤ በቅዳሜና እሑድ መርሐግብር የሚሰጥ ነው፡፡

የስልጠና ዘርፎች፦
- Information Technology
- Electronics

የመመዝገቢያ መስፈርቶች፦
- ከዚህ በፊት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በቅዳሜና እሁድ ስልጠና ያልወሰዱ፣
- ከ7-12ኛ ክፍል ተማሪ የሆኑ፣
- በሳይንስ የትምህርት አይነቶች ጥሩ ውጤት ያላቸው፣
- ለ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በGeneral Science ጥሩ ውጤት ያላቸው፣
- የሳይንስ ፈጠራ ተሰጥዎ/ዝንባሌ ያለው/ያላት፣

የመመዝገቢያ አማራጮች፦
- በቴሌግራም ግሩፕ👇
https://t.me/+SIGIdGywKdM3Mzg0
- በስልክ ቁ. 0912233221 ላይ ሙሉ ስም፣ የትምህርት ቤታችሁን ስም እና ክፍላችሁን በአጭር የፅሁፍ መልዕክት ይላኩ።

🔔 ምዝገባው ሰኞ የካቲት 3/2017 ዓ.ም ያበቃል፡፡ የመግቢያ ፈተና የካቲት 8/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

@tikvahuniversity


41ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በምዝገባ ላይ ነን!

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


በክረምት መርሐግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ መምህራን የመውጫ ምዘና ነገ ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም ይሰጣል።

በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በክረምት መርሐግብር ለተከታታሉ #መምህራን የመውጫ ምዘና እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ወደ መፈተኛ ማዕከል ስትሔዱ ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ የሚጠበቅባችሁ ሲሆን፤ እንደ ተንቀሳቃሽ ስልክ ያሉ የተከለከሉ ነገሮች ይዞ ወደ ፈተና ማዕከል መሔድ አይቻልም፡፡ ፈተናው ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ ቀድማችሁ ልትገኙ ይገባል፡፡

@tikvahuniversity

32.9k 0 17 133 116

ላለፉት አምስት ተከታታይ ቀናት በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ የቆየው 4ኛው የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ አመሻሹን ተጠናቋል፡፡

ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በ87 የፈተና ማዕከላት የተሰጠ ሲሆን፤ 176 ሺህ የሚሆኑ ተፈታኞች ለመውጫ ፈተናው ተቀምጠዋል።

በፈተና አሰጣጡ ተንቀሳቃሽ ስልክ ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ ለመገባት መሞከር፣ ዘግይቶ ፈተናውን መስት መጀመር እና የመብራት መቆራራጥ ችግሮች መታየታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የደረሱ መልዕክቶች ያሳያሉ። ከተገለፁት ችግሮች በስተቀር ፈተናው መጠናቀቁን ሰምተናል።

ምስል፦ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

34k 0 17 39 42

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) የተመደቡለትን ተማሪዎች በመቀበል ላይ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው በ2017 ዓ.ም ለሪሚዲያል ፕሮግራም በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን ተማሪዎች ከጥር 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ እየተቀበል ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው በተፈጥሮ እና በማኅበራዊ ሳይንስ መስኮች በአጠቃላይ 2,187 የሪሚዲያል ተማሪዎች ተመድበውለታል።

@tikvahuniversity


ስለ M-PESA ኢትዮጵያ አዳዲስ ዜናዎች እና አገልግሎቶች ለማወቅ የማኅበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን ይቀላቀሉ! 💚📲

Telegram: https://t.me/+-cP9IxZdfKBkNTQ0

Facebook: https://www.facebook.com/share/14qsy45H7u/?mibextid=wwXIfr

Titkok: https://www.tiktok.com/@mpesa.ethiopia?_t=ZM-8tcz302wLwL&_r=1

LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/m-pesaethiopia/about/

Instagram: https://www.instagram.com/mpesa.ethiopia/

YouTube: http://www.youtube.com/@M-PESAEthiopia

#MPESASafaricom 
#MPESAEthiopia


ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ዛሬ ይጠናቀቃል።

ፈተናው 5ኛ ቀኑ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ በዛሬው የጠዋት 2:30 መርሐግብር የነርሲንግ ፈተና እየተሰጠ ነው።

በጁምዓ ምክንያት ጠዋት 5፡30 የሚጀመረው የመውጫ ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 የሚጀመረው ፈተና ወደ 10፡30 ተቀይሯል።

የመውጫ ፈተና መጠናቀቅን ተከትሎ በሚኖሩ ቀጣይ ቀናት ውጤት እንደሚገለፅ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በክረምት መርሐግብር ሲከታታሉ የቆዩ #መምህራን የመውጫ ምዘና ነገ ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

38.6k 1 83 86 210

ያመልክቱ!

ዛሬ ይጠናቀቃል!


በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የተቋቋመው የሰብዓዊነት ትምህርት ቤት (School of Humanity) በመደበኛ መርሐግብር በሰብዓዊነት ትምህርት በዲፕሎማ ፕሮግራም ለአንድ ዓመት ፍላጎት ያላቸውን አመልካቾች ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡

መስፈርቶች
➭ በማንኛውም የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪ ያለው/ያላት፣
➭ በሰብዓዊነት መስክ ለማገልገል ጥልቅ ፍላጎት ያለው/ያላት፣
➭ ዕድሜያቸው ከ20-40 ዓመት የሆኑ አመልካቾች ይበረታታሉ፣
➭ አመልካቾች ትምህርት ቤቱ የሚሰጠውን የፅሑፍ ፈተና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል።

የማመልከቻ ቦታ፦
ሳሪስ አደይ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ግቢ

የማመልከቻ ጊዜው የሚያበቃው፦
ጥር 30/2017 ዓ.ም


ለማመልከት ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➭ የመጀመሪያ ዲግሪ ዋናውና ሁለት ኮፒ፣
➭ ስቱድንት ኮፒ ዋናውና ሁለት ኮፒ፣
➭ 2x3 የሆነ ሁለት ፎቶግራፍ፣

ሳሪስ፥ አደይ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሰብዓዊነት ትምህርት ቤት ካምፓስ ሲደርሱ ተጨማሪ ክፍያን የተመለከ መረጃ የሚያገኙ ይሆናል፡፡

ዛሬ ብቻ ነው የቀረው። ያመልክቱ! የሰብዓዊነት ዲፕሎማ ያግኙ!

@tikvahuniversity


20ኛ ዙር የድረ-ገጽ እና የሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ (Full-Stack Website and Mobile Application Development) ስልጠና በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በምዝገባ ላይ ነን።   

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 ፕሮግራሚንግ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 Front-end እና Back-end በአንድ ላይ እስከ Deployment ያካተተ
👉 በተግባር ድረ-ገጾችን እና ሞባይል መተግበሪያዎችን እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


በአማራ ክልል የ2017 ትምህርት ዘመን የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ተፈታኞች የበይነ መረብ ምዝገባ የካቲት 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
- የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ

@tikvahuniversity

43.7k 0 16 41 138

#MoE

አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም ጠዋት 5፡30 የሚጀመረው የመውጫ ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 የሚጀመረው ፈተና ወደ 10፡30 የተቀየረ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

የመፈተኛ ማዕከላት በነበሩበት የሚቀጥሉ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

50k 1 453 23 122

#ተጨማሪ

ነገ አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም በሚሰጡ የመውጫ ፈተና ላይ የሰዓት ለውጥ መደረጉን ዩኒቨርሲቲዎች እየገለፁ ነው፡፡

በዚህም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተሸጋሸገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡ ጠዋት 2:30 የሚጀምረው የነርሲንግ ፈተና ባለበት ይሰጣል።

@tikvahuniversity

42.3k 1 150 16 95

#Update

ነገ አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም በሚሰጡ የመውጫ ፈተና ላይ የሰዓት ለውጥ መደረጉን የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየገለፁ ነው፡፡

በዚህም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተሸጋሸገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ምስል፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

47.7k 1 289 22 144

ቅመም Itel Proን ዛሬውኑ ገዝተን ያለ ባትሪ ስጋት በሽ በሽ እንበል!

ዛሬውኑ ወደ ሳፋሪኮም ሱቆች በመሔድ ስልካችንን ገዝተን ለ90 ቀናት በሚቆይ 5ጊባ ወርሃዊ ጥቅል እና 1000 የሳፋሪኮም ደቂቃ ጉርሻ እናግኝ!

የቴሌግራም ቦታችንን https://t.me/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!

🔗 የ M-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit #FurtherAheadTogether


ለ4ኛ ጊዜ በመሰጠት ላይ የሚገኘው የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ አራተኛ ቀኑ ላይ ደርሷል፡፡

ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በ87 የፈተና ማዕከላት እየተሰጠ ሲሆን፤ 176,045 ተፈታኞች ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ብቻ ከ18 ሺህ በላይ ተፈታኞች ፈተናውን እየወሰዱ እንደሚገኙ በዩኒቨርሲቲው የትምህርትና ምርምር ተቋም የፈተና ማዕከል ዳይሬክተር ብርሃኑ አበራ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

ባለፉት ሦስት ቀናት በነበረው የፈተና አሰጣጥ፤ ተንቀሳቃሽ ስልክ ይዘው ወደ ፈተና ጣቢያ ለመገባት ከሞከሩ ጥቂት ተማሪዎች እና አልፎ አልፎ የመብራት መቆራራጥ ከማገጠሙ በስተቀር ሌላ በዩኒቨርሲቲው ያጋጠመ ችግር አለመኖሩን ኃላፊው ለትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ዴስክ ተናግረዋል፡፡

የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ነገ ጥር 30/2017 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

@tikvahuniversity

39.4k 0 17 17 133
17 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.