የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የአየር ንብረት ለውጥ ፎረም ተቋቋመ፡፡
ፎረሙ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች፣ የፕላንና ልማት ሚኒስቴር እና የትምህርት ሚኒስቴር ጥምረት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
34 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ፎረሙን ለማቋቋም ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ሰነድ ዛሬ ተፈራርመዋል።
ፎረሙን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር በሰብሳቢነት፤ ትምህርት ሚኒስቴር እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምክትል ሰብሳቢነት እንደሚመሩት ተገልጿል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፎረሙ ቋሚ ሴክሬታሪያት በመሆን የሚያገለግል ሲሆን፤ የዩኒቨርሲቲው ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) የፎረሙ ጠቅላላ ጉባኤ ምክትል ስብሳቢ ሆነው ተመርጠዋል፡፡
ፎረሙ የአየር ንብረት ለውጥ እያስከተለ ያለውን ችግር ስልታዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት የሚያስችሉ የመፍትሔ ሀሳቦችን ያመነጫል ተብሏል፡፡
ጥምረቱ በዓመት አንድ ጊዜ ጉባኤውን እንደሚያካሒድ ተጠቁሟል፡፡ #EPA #AAU
@tikvahuniversity