The Ethiopian Economist View


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


Wase.belay12@gmail.com(0913243956)

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ከIMF ለመስማማት የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም የመጨረሻው ጥይት ብርን ከዚህ በላይ ማዳከም ነው!


የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልኡካን የዓለም የገንዘብ ድርጅት የተጨማሪ ብድር ስምምነት ለማድረግ በአሜሪካ ውይይት መጀመሩ ይታወቅ ነበር! ዛሬ የወጣው የሮይተርስ ዘገባ "There are still "difference" between IMF and Ethiopia over a loan and reform package" ይላል! ዋናው ያለመስማማት ነጥብ ከዶላር አንፃር #ብር_መዳከም አለበት የሚለው ላይ ነው!

ዜናውን በቀጣዩ ሊንክ ተመልከቱት....

IMF says still 'differences' with Ethiopia over new loan programme | Reuters
https://www.reuters.com/world/africa/imf-says-still-differences-with-ethiopia-over-new-loan-programme-2024-04-19/




#ለመረጃ

የመጋቢት ወር ሀገር አቀፍ የዋጋ ግሽበት 26.2 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አሳወቀ።

በወሩ ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት ፦

➡️ ምግብ ነክ ዕቃዎች (food items) 29 በመቶ ድርሻ ይዘዋል።

➡️ ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎች (Non-food Items) 22 በመቶ በመሆን ተመዝግቧል።

በአጠቃላይ የዋጋ ግሽበቱ #በየካቲት_ወር ከነበረበት 28.2 በመቶ ወደ 26.2 በመቶ በመሆን መጠነኛ ቅናሽ ማሳየቱን የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት አመላክቷል።


የችርቻሮ ገበያው ለውጪ ባለሃብቶች ክፍት ቢሆን (Retail Liberalization)....


የሀገር ውስጥ ነጋዴ ዓለም አቀፍ ብራንድ የሆነ ምርት አስመጥቶ በመሸጥ እና አምራቹ እራሱ በሀገር ውስጥ ሱቅ ከፍቶ መሸጥ ቢጀምር ያለው ልዩነት ምንድን ነው?


#ለምሳሌ፦ ኦርጅናል Nike የሚያስመጣ የኢትዮጵያ ነጋዴ ሱቅ ከፍቶ መሸጥ ይችላል/ይፈቀዳል! ነገር ግን የአሜሪካው የNike ጫማ አምራች ኢትዮጵያ ውስጥ ሱቅ ከፍቶ ምርቱን መሸጥ አይችልም/አይፈቀድም!


ልዩነቱ ምንድን ነው?


መሰረታዊው ምክንያት #የችርቻሮ_ገበያን ለውጪ ባለሃብቶች ክፍት ያለማድረግ የፖሊሲ መነሻ ሲሆን ነገር ግን የማምረት እና ለውጪ ገበያ ብቻ ማቅረብን ግን ያበረታታል። ለዚህ ደግሞ የሀገር ውስጥ አምራቾችን ለማበረታታት/ጥበቃ ለማድረግ (Protectionism) እና የካፒታል/የውጪ ምንዛሬ ወደውጪ ሀገር የሚኖር ፈሰስን ለመከላከል ነው።


#ለምሳሌ፦ የNike ጫማ ከውጪ አስመጥቶ የሚሸጥ የሀገር ውስጥ ነጋዴ ግብይቱ በኢትዮጵያ #ብር ከመሆኑ በተጨማሪ የአስመጪነት አስገዳጅ የውጪ ምንዛሬ ጥያቄ ላያደርግ ይችላል! ነገር ግን የውጪ ድርጅት ጫማ ለሸማቹ በብር ቢሸጥም በሂደት ከብሄራዊ ባንክ በምትኩ በዶላር/በውጪ ምንዛሬ እንዲለወጥለት መጠየቁ አይቀርም (የዓለም የንግድ ድርጅት ከአስገዳጅ ህጎቹ መካከል ነው! የዓለም የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የአስገዳጅ ህጉ አስገዳጅ  አስፈፃሚዎች ናቸው)።


በተለያየ ምክንያት ተፎካካሪ ምርት ለማቅረብ የሚቸገረው የሀገር ውስጥ አምራች የተሰጠውን የጥበቃ ፖሊሲ ባለመጠቀሙ ገበያው በተዘዋዋሪ የከውጪ አስመጪዎች ሆኗል (ደካማ የደጋፊ ፖሊሲ አማራጭ መኖር፤ የምርት ጥራት እና የማምረቻ ወጪ ዝቅተኛነት ይህንን ሁኔታ አግዘውታል)።


ቸርቻሪዎችን በሀገር ውስጥ ገበያ የማስገባት ሁኔታ ከ1990ዎቹ ጀምሮ ባሉ ጥናቶች አዎንታዊም አሉታዊም ውጤት ማምጣቱን ያሳያሉ (የምርት ጥራት፤ የዋጋ ምክንያታዊነት፤ የሰራተኛ ደሞዝ እና የገበያ ስልት መሻሻል ሲፈጠር አነስተኛ የሀገር ውስጥ አምራቾች መዳከም መከሰቱን አሳይቷል)።


ኢትዮጵያ ውስጥ የችርቻሮ ገበያ ለውጪ ባለሃብቶች የመክፈት (Retail Liberalization) ሃሳብ መኖሩ ተገልጿል (በጠቅላይ ሚኒስትሩ) ይህን በተመለከተ የኔ ሃሳብ አነስተኛ አሉታዊ ጎን ብቻ ነው የሚታየኝ....


1. የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በብዙ ዘርፍ በሩን የዘጋበት ምክንያት በጣም አሳማኝ ነበር ለማለት ያስቸግራል (ሲያከራክር የኖረው የቴሌኮም ገበያ ሲከፈት  ውጤቱ አሉታዊ አይደለም!)፤ ከሪፖርቶች ተነስተን ከተመለከትን ላለፊት 30 ዓመታት የባንክ ሴክተሩ የመሮጫ ሜዳው ከውጪ ጫና ተጠብቆም ከከተማ ለመውጣት አልደፍር ብሏል፤


2. በጥበቃ ውስጥ ያሉ የሀገር ውስጥ አምራቾች በተለያየ በራሳቸውም ሆነ በመንግስት ችግር በኢኮኖሚው በዋጋ፤ በጥራት እና በመጠን የምርት ፍላጎትን ለማርካት ተቸግረው Import በገበያው ነግሷል፤


3. በአነስተኛ የኢኮኖሚ፤ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ፋይዳ በትንሹም በትልቁም በሩን ለውጪ ገበያ በመዝጋቱ ዓለም አቀፍ ጫናው ለጠቅላላ ኢኮኖሚው የሚገባው አይደለም፤


4. ኢኮኖሚው ከፖሊሲ ይልቅ የአምራቾች እና የአስመጪዎች የገበያ ትንበያን ተከትሎ የሚሄድ ሆኗል (ለኢንዱስትሪ የታለመው ኢኮኖሚ በአገልግሎት ዘርፉ ጥላ ስር አርፏል)፤ ወዘተ


ማሰብ የሚያስፈልገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሬ ካዝና የማይገመት አይደለም (ካፒታል በተፈለገ ፍጥነት ወደ ውጪ ምንዛሬ የሚለውጥ ሊሆን አይችልም)፤ የዜጎች የዓለም አቀፍ ብራንዶች የመሸመት አቅም ሁኔታ፤ ሌሎች አሳሪ የፖሊሲ እና የፖለቲካ ሁኔታ ተደራርቦ በውጪ ቸርቻሪ ገበያተኞች ገበያው ይጥለቀለቃል የሚል ግምት የለኝም።


ስለሆነም የውጪ ቸርቻሪዎች አጋዥ ፖሊሲዎችን መጠበቃቸው ካለመቅረቱ (የውጪ ምንዛሬ በገበያ መወሰን፤ የፈጠራ መብት ጥበቃ፤ ወዘተ) በተጨማሪ የሀገር ውስጥ አነስተኛ አምራቾችን ከተፎካካሪት በላይ የማምረት አቅማቸውን የሚፈትነውን ችግር ለመፍታት ጥረት ቢደረግ መጥፎ እርምጃ እና የሚታይ አሉታዊ ውጤት ኢኮኖሚው ላይ ያመጣል ብዬ አላስብም።


ጥናት የምትሰሩ ሰዎች የነዋሪዎችን የነፍስ ወከፍ ገቢ (Per Capita Income) እና የድህነት ወለል (Poverty Line) መነሻ በመውሰድ ከድህነት ወላል በታች የሚኖሩ ሰዎች ቁጥር (Poverty Headcount Index)፤ ከድህነት ወለሉ አማካይ መጠን አካባቢ የሚገኙ ሰዎችን (Poverty Gap Index) እና ከድህነት ወለሉ በጣም የራቁ/ድህነታቸው የከፋ ደረጃ ላይ የደረሱ (Poverty Severity Index) መረጃ መተንተን የምትችሉበት በዓለም ላይ የተለመደው የድህነት መለኪያ የሆነው The Foster–Greer–Thorbecke Indices (FGT) በምሳሌ ለመማር የሚከተለውን https://youtu.be/u-acopM4frA ቪዲዮ ይጠቀሙበት፡፡


ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች፡ እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ።

ኢድ ሙባረክ!


የድህነት ወለል፤ የድህነት ጥልቀት (Poverty Gap) እና የከፋ ድህነት (Poverty Severity) መለኪያ The Foster–Greer–Thorbecke (FGT) poverty measures በምሳሌ ይማሩበት!
(https://youtu.be/u-acopM4frA


የጉምሩክ ኮሚሽን በነዳጅ የሚሠሩ እና ሙሉ በሙሉ ውጭ ሀገር ተገጣጥመው ወደ ሃገር  የሚገቡ አውቶሞቢሎች ላይ የውጪ ምንዛሬ #እቀባ መጣሉን አሳውቋል።



ከውጪ ሃገር ምርት እንዳይገባ ለመከልከል የሚደረገው በሞንተሪ ፖሊሲ፡ ብሄራዊ ባንክ (የውጪ ምንዛሬ ባለመፍቀድ) እና በፊስካል እርምጃ፡ ገቢዎች ሚኒስትር እና ጉምሩክ ኮሚሽን (ወደብ ላይ የውጪ ምንዛሬ ያልተፈቀደለት ምርት እንዳይገባ በማድረግ ነው)።


በነዳጅ የሚሰራ አውቶሞቢል ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት የውጪ ምንዛሬ መከልከል! ኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ኤሌክትሪክ አውቶሞቢል መኪኖች የመዞር ግዴታ መጣል ኢኮኖሚው ላይ የሚኖረው እድል እና ስጋት! ለምልከታ ይህንን ቪዲዮ https://youtu.be/JYKOrEybvWY መመልከት ትችላላችሁ!


ዜናው በገቢዎች ሚኒስትር የማህበራዊ ገፅ ላይ ይገኛል!


አዋጁ ምን ይላል ?

➡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን የተመለከተው የአዋጁ አንቀጽ የመኖሪያ ቤት አከራዮች በዘፈቀድ የኪራይ ዋጋ እንዳይጨምሩ ይከለክላል።

➡ አከራይ የኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው ተቆጣጣሪው አካል በዓመት አንድ ጊዜ ነባራዊ የኢኮኖሚውን ሁኔታ እና ሌሎች አግባብነት ያላቸውን ጉዳዮች ከግምት በማስገባት ሊወስን የሚችለውን የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ መሠረት በማድረግ ነው።

➡ በአዋጁ መሠረት የሚደረገው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ጭማሪ፤ በተቆጣጣሪው አካል በሰኔ አንድ ለሕዝብ ይፋ ተደርጎ ከሰኔ 30 ጀምሮ ለአንድ አመት የፀና ይሆናል።

➡ የቤት ኪራይ ውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ተከራይን ከቤት ማስወጣት ወይም በዚህ አዋጅ ከተፈቀደው ሁኔታ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ አይቻልም። ይህም አስገዳጅ ድንጋጌ ነው።

➡ አከራዮች ከሁለት ወር የቤቱ ኪራይ በላይ ቅድመ ክፍያ መጠየቅ #አይችሉም።

➡ የቤት ኪራይ ክፍያዎች በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የኤሌክትሮኒክ ዘዴ መፈፀም አለባቸው። አከራይ እና ተከራይ የቤት ኪራይ ክፍያ ሰነዶችን አደራጅተው የመያዝ ግዴታ አለባቸው።

➡ ማንኛውም የቤት ኪራይ ውል በጽሁፍ የሚደረግ ሆኖ በተቆጣጣሪው አካል መረጋገጥ እና መመዝገብ አለበት። ሁለቱም ወገኖች የቤት ኪራይ ውሉ በተፈረመ ሰላሳ ቀናት ውስጥ ውሉን አቅርበው እንዲረጋገጥ እና እንዲመዘገብ የማድረግ ግዴታ አለባቸው። ያልተረጋገጠ እና ያልተመዘገበ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እንዳልተደረገ ይቆጠራል። አዋጁን ተከትሎ የሚደረግ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም።

NB. በአዋጁ መሠረት ተቆጣጣሪ አካል ማለት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውልን እና ዋጋን እንዲቆጣጠር በክልሎች ወይም በአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደሮች የሚሰየም አካል ነው፡፡

@tikvahethiopia


13202016.pdf
1.0Mb
#ለመረጃ የተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ያጸደቀው የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ!


ለጥናት ስራ የተበተነ መጠይቅ ወይም የተሰበሰበ መረጃ ትክክለኛ እና ገላጭ /Data Reliability and Consistency Test/ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚደረገው የ "Cronbach Alpha Test" አሰራር እና ትንታኔ!
https://youtu.be/K63vanO8qy4


ለጥናት ስራ የተበተነ መጠይቅ ወይም የተሰበሰበ መረጃ ትክክለኛ እና ገላጭ /Data Reliability and Consistency Test/ መሆኑን ለማረጋገጥ የሚደረገው የ "Cronbach Alpha Test" አሰራር እና ትንታኔ!
https://youtu.be/K63vanO8qy4


ትክክለኛ የተዛማጅ ጽሁፎች (Empirical Review) አጻጻፍ!

በጥናት ወቅት ከአርቲክል (Articles)፤ ከመጽሃፍ (Books) እና ከመመረቂያ ጥናቶች (Thesis) እንዴት ትክክለኛ የEmpirical Review አጻጻፍ ስልት መጠቀም እንደምትችሉ የሚከተለውን https://youtu.be/1C32HXci5So ምሳሌ ተጠቀሙ!


ትክክለኛ የተዛማጅ ጽሁፎች (Empirical Review) አጻጻፍ!

በጥናት ወቅት ከአርቲክል (Articles)፤ ከመጽሃፍ (Books) እና ከመመረቂያ ጥናቶች (Thesis) እንዴት ትክክለኛ የEmpirical Review አጻጻፍ ስልት መጠቀም እንደምትችሉ የሚከተለውን https://youtu.be/1C32HXci5So ምሳሌ ተጠቀሙ!


#የአፍርሶ_ማልማት_ኢኮኖሚ!

የከተማ መሰረተ ልማት ግንባታ ሶስት አይነት ባህሪ ሊኖረው ይችላል! (በተለይ የኢኮኖሚ፤ የማህበራዊ እና የፖለቲካዊ ማዕከል ሆነው በሚያገለግሉ ዋና ከተሞች ላይ)፡፡

አንደኛ፡- አብዛኛው የዋና ከተሞች እንደሚቆረቆሩት በልዩ ምክንያት አልያም በጥናት የረጅም ጊዜ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መሰረቶችን ከግምት ከቶ ዋና ከተማ ማዋቀር (መንገድ፤ መኖሪያ፤ የንግድ ቦታ፤ የማህበራዊ አገልግሎት ቦታ፤ ወዘተ የመጪውን ጊዜ የእድገት ፍላጎት እና የህዝብ ቁጥር ከግምት የሚከት አልያም በዘመናት ውስጥ በሂደት ቅርጹ የሚለዋወጥ ሊሆን ይችላል)፤

ሁለተኛ፡- ነባር ከተሞችን ከወቅታዊ የህዝብ ቁጥር ሁኔታ እና ከአገልግሎት ባህሪ አንጻር ማሻሻያዎችን እያደረጉ ማዋቀር (መንገዶች ሲጠቡ፤ የመኖሪያ ቤቶች እጥረት ሲኖር፤ የኢንቨስትመንት እና የንግድ የፖሊሲ ባህሪ ሲለዋወጥ፤ በተቀራራቢ ቦታ ሰፊ የደረጃ ለውጥ ሲስተዋል፤ ወዘተ በነባር ቦታዎች ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ነባሩን ከአዲስ ይዘት ጋር እያጣጣሙ ለመሄድ መሞከር፤

ሶስተኛ፡- በብዙ ኢኮኖሚያዊ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ምክንያቶች ነባር ከተሞችን በመተው በአዲስ ስትራቴጂካዊ ከተሞች መተካት! በዋናነት ሀገራቶች በተለይ ዋና ከተሞችን የሚለውጡት ዋና ከተማው የሀገሪቷ ማዕከላዊ/አማካይ ቦታ ባለመሆኑ እና በነባር ከተማ የተጨናነቀ አኗኗር መፈጠር ሲጀምር ሲሆን! የሚከተሉት ሀገራት ዋና ከተማ የለወጡ ናቸው….

ካዛኪስታን (ከአልማታ ወደ አስታና)፤ ማይናማር (ከያንጎን ወደ ናይፒዳው)፤ ታንዛኒያ (ከዳሬሰላም ወደ ዶዶማ)፤ ናይጄሪያ (ከሌጎስ ወደ አቡጃ)፤ ብራዚል (ከሪዮ ዲ ጄኔሮ ወደ ብራዚሊያ)፤ ፓኪስታን (ከካራቺ ወደ ኢስላማባድ)፤ ራሽያ (ከሴንት ፒተርስፐርግ ወደ ሞስኮ)፤ ግብጽን ጨምሮ አሁን ላይ አዲስ ዋና ከተማ እየገነቡ ያሉ ሀገራቶች አሉ፡፡

ሁለት ዋና ከተሞችን የአስተዳደር እና የዲፕሎማሲ መቀመጫ እና የንግድ ማዕከል አድርገው የሚጠቀሙ ሀገራቶችም አሉ (ቤኒን፤ ቦሊቪያ፤ ደቡብ አፍሪካ፤ ኔዘርላንድ፤ ማሊዢያ፤ ሲሪላንካ፤ ቺሊ፤ ሲዋዚላንድ፤ ኮትዲቫር፤ ጆርጂያ እና ሞንቲኔግሮ ናቸው፡፡

አዳዲስ ዋና ከተሞችን በእቅድ መገንባትም ሆነ ነባር ከተሞችን እያፈረሱ መገንባት ላይ የሚነሱ ጠንካራ እና ደካማ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ውጤቶች አሉ፡፡

እንደ ኢትዮጲያ ዝቅተኛ ኢኮኖሚ ባለው ሀገር አዲስ ዋና ከተማ መገንባት (ከኢኮኖሚ አንጻር፡ የቦታ ዝግጅት እስከ የግንባታ ወጪ ቢሊየን ዶላሮችን መጠየቁ እና ከፖለቲካ አንጻር፡ የፌደራል አወቃቀር ስርዓቱ የቦታ መረጣን እና ዝግጅትን ቀላል ሂደት የሚሰጠው ባለመሆኑ) ቀላል አይሆንም! እንዲሁም ነባር ዋና ከተማ እና መንደሮችን አፍርሶ በመገንባት ሂደት ላይም ነባር ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች የሚኖራቸው Opportunity Cost ቀላል አይሆንም፡፡

#ለምሳሌ፡- በዋጋ 200ሚሊየን ብር የሚያወጣ እና በዓመት ከ200ሚሊየን ብር በላይ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቀሴ (በኪራይ፤ በክፍያ፤ በሽያጭ፤ በግዢ፤ ወዘተ) እንዲፈጠር የሚያደርግ ህንጻ ቢፈርስ በቅስፈት 400ሚሊየን ብር Negative ኢንቨስትመንት አለው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ በምትኩ የሚከናወነው ፕሮጀክት ይህንን 400ሚሊየን ብር በዘላቂነት የሚመልስበት ፍጥነት የተጠና መሆን አለበት ማለት ነው! (ህንጻው በፈረሰበት ቦታ ለዓይን የሚማርክ የሰዎች ማረፊያ አረንጓዴ ቦታ ቢሰራ ይህንን አዝጋሚ የገንዘብ እንቅስቀሴ ያለበት የኢኮኖሚ ሴክተር ካጣው 400ሚሊየን ብር ጋር ለማቀራረብ ምን ያህል ጊዜ ይፈጃል? ከተባለ ማህበራዊ ፋይዳው ሰፊ ግን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው ጠባብ እና ጊዜ የሚወስድ ሊሆን ይችላል)፡፡

በአንድ ሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ የመንግስታት ሚና የግል ሴክተሩ በቀዳሚነት የኢኮኖሚ ፋይዳ ላይ ስለሚያተኩር ማህበራዊ ፋይዳዎች ሳይዘነጉ ተጠብቀው እንዲሄዱ ማድረግ እና የግል ሴክተሩ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው እንዲጨምር ማገዝ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ነባር ከተሞች ከአዲስ የከተማ እድገት እሳቤ አንጻር እንዲለወጡ የመልሶ ግንባታ እንቅስቃሴ በስፋት ይስተዋላል፡፡ ይህ እያፈረሱ መገንባት አሁን ባይሆን እንኳን ወደፊት በጊዜ ሂደት ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ገፊ ምክንያቶችን ተከትሎ መደረጉ ስለማይቀር ለምን? የሚባል አይሆንም፡፡

ስለዚህ ከጠባብ ሌላ አማራጭ የሚወሰድ መፍትሄ እንደመሆኑ በመልሶ መገንባት እና ይዞታ በማሻሻል ሂደት መታሰብ ያለበት የሚፈርሱ ቦታዎች የነበራቸው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በምትካቸው ከሚሰሩት ፕሮጀክቶች ከሚጠበቅ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ጋር በአመክንዮ ማወዳደር ተገቢ ነው፡፡

በምትኩ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች የነበሩ አዎንታዊ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን ትርፋማነት በከፍተኛ ሁኔታ መለወጥ መቻል እንዳለባቸው ማረጋገጥ ይገባል፡፡ ለምሳሌ በአዲስ አበባ የቢዝነስ እንቅስቃሴን የሚቀንስ የተጨናነቀ የትራንስፖርት እንቅስቀሴ አለ! የመንገድ ፕሮጀክቶች ፈጣን የትራንስፖርት ኮሪደርን መፍጠር ከቻሉ ቀላል ፋይዳ የለውም፡፡

የታዳጊ ሀገራት ከተሞች ፈጣን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ለማስመዝገብ ሲያስቡ ተቀዳሚ ትኩረት ወጪ እና ተጠባቂ ፋይዳ/ገቢ ነው! በርግጥ የገጽታ ጉዳይ በሂደት የሚታሰብ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለሆነም መንደሮችን በማፍረስ ሂደት ተጠባቂ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ የተጠና መሆኑን እና ዝቅተኛ Opportunity Cost ያለው መሆኑን ማረጋገጥ ይገባል፡፡


የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መጠን በኑሮ ደስተኝነትን አይፈጥርም (IMF, 2023)!

የዜጎችን በኑሮ ያላቸውን ደስተኝነት ከGDP እና ከነፍስ ወከፍ ገቢ መጠን ለይቶ መመልከት ይገባል (IMF: Looking beyond GDP)!

በ2023 ጠንካራ ኢኮኖሚ ኖሯቸው ዜጎቻቸው በደስተኝነት መለኪያ ዝቅተኛ የሆኑ ሀገራት ዝርዝር!

በ2023 ደካማ ኢኮኖሚ ኖሯቸው ዜጎቻቸው በደስተኝነት መለኪያ የተሻሉ ሀገራት ዝርዝር! የኢትዮጲያ ዜጎች በኑሮ ያላቸው የደስተኝነት ደረጃ ከመጨረሻዎቹ መካከል ነው!


የዚህን የIMF: World Happiness Report, 2023 ሪፖርት ንጽጽር ለመመልከት የሚከተለውን የትንታኔ ቪዲዮ https://youtu.be/SdCqjjHrXOI ይመልከቱ!


የህዝብን የህይወት ለውጥ ከነፍስ ወከፍ ገቢ ባሻገር ማሰብ ያስፈልጋል! (የIMF: World Happiness Report, 2023፡ Looking beyond GDP)……

ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት (GDP) በአንድ ሀገር ኢኮኖሚ ውስጥ ያሉ በአንድ ዓመት ውስጥ ለፍጆታ የወጣ ወጪ (Consumption) ለኢንቨስመንት የወጣ ወጪ (Investment) የመንግስት ጠቅላላ ወጪ (Government Expenditure) እንዲሁም ከውጪ ምርት ለማስገባት የሚወጣን ወጪ (Import) ለውጪ ምርት በማቅረብ ከሚገኝ ገቢ (Export) በማቀናነስ ያሰላል፡፡

የዛሬ 50 ዓመት በወቅቱ የአሜሪካ ሴናተር የነበሩት ሮበረት በጠቅላላ ሀገራዊ ምርት (GDP) ላይ ጠንከር ያለ ትችት አቀረቡ እሱም “ጠቅላላ ሀገራዊ ምርት (GDP) ህይወትን ጠቃሚ ከሚያደርጉት ምክንያቶች በስተቀር ሁሉንም ነገር ይለካል“(GDP measures everything...except that which makes life worthwhile) የዚህ አይነቱ ትችት ጠቅላላ ሀገራዊ ምርትን በተለየ ሁኔታ ማሰብ ያስፈልጋል የሚል ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡

ፖሊሲ አውጪዎች የአንድ ሀገርን ነዋሪዎችን የህይወት ለውጥ ሁኔታን በጠቅላላ ሀገራዊ ምርት ከማየት ይልቅ ዜጎች በህይወታቸው ደስተኛ ስለመሆናቸው መለካት መጀመር አለባቸው ከሚለው አመክንዮ በመነሳት በየዓመቱ ከተለያዩ መለኪያዎች በመነሳት የዓለም የገንዘብ ድርጅት የዓለም ህዝቦች የደስተኝነት ደረጃ (World Happiness Report) ያወጣል፡፡

የጠቅላላ ሀገራዊ ምርት መጠን ለጠቅላላ ህዝቦች ሲካፈል የነፍስ ወከፍ ገቢ ስሌትን ይሰጣል (GDP per capita) ይህ ቁጥር እየጨመረ በመጣ ቁጥር በኢኮኖሚ የተሻለ ሀገር ወይም የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ ዜጎች ያላት ሀገር በሚል ሲሰላ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን የነፍስ ወከፍ ገቢ (Per Capita Income) ወይም ዜጎች በዓመት የሚያገኙት ገቢ መጠንን ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርት ብቻ ለመውሰድ ከሞመከር ዜጎች ያላቸው ማህበራዊ ድጋፍ፤ የጤና ሽፋን፤ በህይወት የመኖራቸው እድሜ ጣሪያ፤ የመኖር እና የመናገር ነጻነታቸው፤ ደግነታቸው/ልግስናቸው፤ አነስተኛ ሙስና መኖር፤ ወዘተ የዜጎች የኑሮ ደስተኝነት መለኪያ አድርጎ መጠቀም ያስፈልጋል በሚል ወደተግባር ሀገራት ገብተዋል፡፡

የዓለም የገንዘብ ድርጅት የዚህ ዓመት የዓለም ሀገራት ዜጎች ያላቸውን የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መጠን እና የደስተኝነት ደረጃ ምን እንደሚመስል ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርት ባለፈ ማሰብ ያስፈልጋል በሚል ርዕስ (Looking Beyond GDP) ሪፖርት አውጥቷል (World Happiness Report, 2023) ፡፡ ዜጎቿን ደስተኛ በማድረግ ቀዳሚዋ ሀገር ፊንላንድ ስትሆን የመጨረሻዋ ሀገር ደግሞ አፍጋኒስታን ሆናለች፡፡

በዓለም ዜጎቻቸውን ደስተኛ ያደረጉ ሀገራት ከ1 እስከ 10 በደረጃ ፊንላንድ፤ ዴንማርክ፤ አይስላንድ፤ እስራኤል፤ ኔዘርላንድ፤ ሲዊዲን፤ ሲዊዘርላንድ፤ ሉግዘምበርግ፤ ኒውዚላንድ እና ኦስትሪያ ሲሆኑ፤

በዓለም የዜጎቻቸው የደስተኝነት ደረጃ የመጨረሻዎቹ ሀገራት ከ1 እስከ 10 በደረጃ አፍጋኒስታን፤ ሊባኖስ፤ ሴራሊዮን፤ ዛምቢያ፤ ኮንጎ፤ ቦትስዋና፤ ማላዊ፤ ኮሞሮስ፤ ታንዛኒያ፤ እና ዛምቢያ ናቸው፡፡

በዓለም ላይ ዜጎቻቸው ደስተኛ ከሆኑባቸው ሀገራት 14ኛ የሆነችው ሃያሏ ሀገር አሜሪካ (ዜጎች 76ሺ ዶላር የነፍስ ወከፍ ገቢ ላይ ደርሰዋል) ስትሆን ከመጨረሻዎች ሀገራት 14ኛላይ ደግሞ የተቀመጠች ኢትዮጲያ (ዜጎች 1ሺ ዶላር የነፍስ ወከፍ ገቢ ላይ ደርሰዋል) ነች፡፡

የዓለም የገንዘብ ድርጅት ሪፖርት ለማነጻጸር እየሞከረ ያለው በጠቅላላ የነፍስ ወከፍ ገቢ ከፍተኛ የሆነችው ሉግዘምበርግ (120ሺ ዶላር በላይ የነፍስ ወከፍ ገቢ) ነገር ግን ዜጎቿ በደስተኝነት መለኪያ በዓለም 9ኛ ናቸው፡፡ ዜጎቿ በደስተኝነት መለኪያ አንደኛ የሆኑላት ሀገር ፊንላንድ በነፍስ ወከፍ ገቢ (48ሺ ዶላር የነፍስ ወከፍ ገቢ) ሲታይ በዓለም ላይ ከ20ኛ በታች ነች፡፡

ስለዚህ የዓለም የገንዘብ ድርጅት አመክንዬ የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ከጠቅላላ ሀገራዊ ምርት (የነፍስ ወከፍ ገቢ) በዘለለ መመልከት ይገባል (ዜጎች ያላቸው ማህበራዊ ድጋፍ፤ የጤና ሽፋን፤ በህይወት የመኖራቸው እድሜ ጣሪያ፤ የመኖር እና የመናገር ነጻነታቸው፤ ደግነታቸው/ልግስናቸው፤ አነስተኛ ሙስና መኖር፤ ወዘተ) ለማለት ነው፡፡

የዜጎች የነፍስ ወከፍ ገቢ መጠን በኑሮ ደስተኝነትን አይፈጥርም (IMF, 2023)! የዜጎችን በኑሮ ያላቸውን ደስተኝነት ከGDP እና ከነፍስ ወከፍ ገቢ መጠን ለይቶ መመልከት ይገባል (IMF: Looking beyond GDP)! በ2023 ጠንካራ ኢኮኖሚ ኖሯቸው ዜጎቻቸው በደስተኝነት መለኪያ ዝቅተኛ የሆኑ ሀገራት ዝርዝር! በ2023 ደካማ ኢኮኖሚ ኖሯቸው ዜጎቻቸው በደስተኝነት መለኪያ የተሻሉ ሀገራት ዝርዝር! የኢትዮጲያ ዜጎች በኑሮ ያላቸው የደስተኝነት ደረጃ ከመጨረሻዎቹ መካከል ነው! የዚህን የIMF: World Happiness Report, 2023 ሪፖርት ንጽጽር ለመመልከት የሚከተለውን የትንታኔ ቪዲዮ https://youtu.be/SdCqjjHrXOI ይመልከቱ!


1. ብሄራዊ ባንክ (Central Bank)= የገንዘብ ስርዓት ባንክ

2. ልማት ባንክ (Development Bank)= የፖሊሲ ባንክ

3. ንግድ ባንክ (Commercial Bank)= የንግድ ባንክ

3. ኢንቨስትመንት ባንክ (Investment Bank)= የመዋዕለ ሰነድ ባንክ/የካፒታል ገበያ ባንክ

እነዚህ በተግባር የሚለያዩት ባንኮች መካከል ያለውን መሰረታዊ እሳቤ እና በኢኮኖሚው ውስጥ የሚያከናውኑትን ዋና ተግባራት ለመረዳት የሚከተለውን https://youtu.be/B1CwrVZuwKI ቪዲዮ ይመልከቱ።


#Ethiopia የውጭ ምንዛሬ ፈቃድ ክልከላ በተደረገባቸው እቃዎችና ተሽከርካሪዎች ላይ የተደረገ ማስተካከያ !

Via Ministry of Finance


1. ብሄራዊ ባንክ (Central Bank)= የገንዘብ ስርዓት ባንክ

2. ልማት ባንክ (Development Bank)= የፖሊሲ ባንክ

3. ንግድ ባንክ (Commercial Bank)= የንግድ ባንክ

3. ኢንቨስትመንት ባንክ (Investment Bank)= የመዋዕለ ሰነድ ባንክ/የካፒታል ገበያ ባንክ

እነዚህ በተግባር የሚለያዩት ባንኮች መካከል ያለውን መሰረታዊ እሳቤ እና በኢኮኖሚው ውስጥ የሚያከናውኑትን ዋና ተግባራት ለመረዳት የሚከተለውን https://youtu.be/B1CwrVZuwKI ቪዲዮ ይመልከቱ።

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.