አዲስ ሪፖርተር - NEWS


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


🔖 ይህ የአዲስ ሪፖርተር የቴሌግራም ገፅ ነው !
=> በቻናሉ
📌 ፈጣን ፥
📌 ትኩስ ፥
📌 ወቅታዊ እና
📌 አዳዲስ መረጃዎች እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ ይደርሳችኋል !
🔖 ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል !
For promotion @Addis_reporter_bot
#ADDIS ABABA, ETHIOPIA

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


" በሚቀጠለው ዓመት ምንም አይነት አዳዲስ ፕሮጀክቶች አይኖሩም " - ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ

የትምህርት ሚኒስቴር እና የ22 ዩኒቨርሲቲዎች የ2017 በጀት ዕቅዳቸው መገምገሙን ገንዘብ ሚኒስቴር አሳውቋል።

የትምህርት ሚኒስቴር፣ የሚኒስቴሩ ሁለት ተጠሪ ተቀማት፣ የ8 የምርምር እና የ14 የአፕላይድ አጠቃላይ 22 ዩኒቨርስቲዎች የ2017 በጀት እቅድ በገንዘብ ሚኒስቴር በተካሄደ የበጀት ስሚ መርሀ ግብር መገምገሙ ተነግሯል።

በግምገማው ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ፤ የመንግስትን በጀት በእቅድ ለተያዘለት አላማ ብቻ በአግባቡና በቁጠባ መጠቀም ይገባል ብለዋል።

አስፈጻሚ መ/ቤቶች እና የስራ ሀላፊዎች በጀትን በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲውል የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ በበኩላቸው ፤ " በሚቀጠለው ዓመት ምንም አይነት አዳዲስ ፕሮጀክቶች አይኖሩም " ብለዋል።

ሚኒስቴር መሰሪያ ቤቱ እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ የበጀት እቅዳቸውን በተቀመጠላቸው የበጀት ጣሪያ መሰረት አስተካክለው በጠቂት ቀናት ውስጥ ለገንዘብ ሚኒስቴር እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡

@Addis_Reporter


በ Notcoin ስትነገሩ ያልሰማቹህ ሰዎች አሁንም ስሙኝ ይሔ እድል እንዳያመልጣችሁ።

Tapswap  10ሚሊየን ሰው እየተጫወተው ነው May 30(15ቀን ቀረው)  መሰብስብ ያቆማል ። ከአሁኑ ጀምራችሁ ሰብስቡ👇👇👇
https://t.me/tapswap_mirror_bot?start=r_1870060772

  ይሔንን መልእክት ለጓደኞቻችሁም ሼር አድርጉላቸው


በገጠር የመሬት ሽያጭ እና ግዢ የሚያከናውኑ ሰዎችን እስከ አምስት አመት በእስር የሚያስቀጣ አዋጅ በፓርላማ ጸደቀ!

የገጠር መሬትን በሸጠ ወይም በገዛ ማንኛውም ሰው ላይ እስከ አምስት ዓመት የሚደርስ ፅኑ እስራት ቅጣት የሚጥል አዋጅ በተወካዮች ምክር ቤት ጸደቀ። አዲሱ አዋጅ የግል፣ የወል ወይም የመንግስት ይዞታን በህገ ወጥ መንገድ ወርሮ ለተገኘ ሰውም ተመሳሳይ የእስራት ቅጣት ደንግጓል።

የተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 6፤ 2016 በነበረው መደበኛ ስብሰባው በሙሉ ድምጽ ያጸደቀው ይህ አዋጅ፤ ከ18 ዓመት በፊት የወጣውን የገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም አዋጅን ያሻሻለ ነው። አዲሱ አዋጅ አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች እና ከፊል አርብቶ አደሮች በመሬት ላይ ያላቸውን መብቶች ያሻሻለ ሲሆን፤ የሴቶች እና ድጋፍ የሚሹ ሰዎችን የመሬት ተጠቃሚነት መብት ያረጋገጡ ድንጋጌዎችንም አካትቷል።

አዋጁ በረቂቅ ደረጃ ለፓርላማ ከቀረበ በኋላ ከተደረጉ ማሻሻያዎች መካከል፤ “የወንጀል ተጠያቂነት” በሚመለከተው የተጨመረው አንቀጽ ይገኝበታል። “ከመሬት ጋር ተያይዘው የሚፈጸሙ ወንጀሎች ላይ አስተማሪ እና ተመጣጣኝ ቅጣት ማስቀመጥ አስፈላጊ በመሆኑ” ምክንያት እንደተካተተ የተነገረለት ይህ ድንጋጌ፤ ከመሬት ወረራ እስከ መሬት ሽያጭ ድረስ ያሉ የህግ ጥሰቶች የሚያስከትሏቸውን ቅጣቶች ዘርዝሯል።

Via:ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

@Addis_Reporter


የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አመራረጥ አዲስ መመሪያ በመዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡

ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሃብት ብክነት እና ብልሹ አሰራር ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) እንደገለፁት፤ በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በመላክ ዩኒቨርሲቲዎቹ ያሉባቸውን ችግሮች መጠናቱን ገልፀዋል፡፡

"ዩኒቨርሲቲዎች የብዙ ደሃ ሕዝብ ሃብት የሚፈስባቸው ቦታዎች ናቸው" ያሉት ሚኒስትሩ፤ ስለዚህ ተቋማቱ በሙስናና ብልሹ አሰራር የተጨመላለቀ አስተዳደር ሊኖራቸው አይገባም ብለዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎች በዋናነት የተማረ የሰው ኃይል ከማምረት ይልቅ፣ ህንጻ ማምረት ላይ የተሰማሩ ተቋማት እንደነበሩ ያስታወሱት ሚኒስትሩ፤ "ዩኒቨርሲቲዎች የሚታለቡ የጥገት ላሞች ናቸው" የሚለው የአንዳንድ ግለሰቦች አባባል አሁን ላይ አይሠራም ብለዋል፡፡

ሦስት ጊዜ መጥፎ የኦዲት ግኝት ያለበት ዩኒቨርሲቲን የሚመሩ ከፍተኛ አመራሮች በሙሉ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ የሚያዝ የገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ መኖሩን ጠቁመዋል፡፡ ኃላፊዎቹም በህግ የሚጠየቁበት አግባብ መኖሩንም አክለዋል፡፡ ይህንን አሰራር በመከተል "ሦስት ጊዜ መጥፎ የኦዲት ግኝት ያለበት ዩኒቨርሲቲን የሚመሩ አመራሮችን በሙሉ እንቀይራለን" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

@Addis_Reporter


አምባሳደር ማይክ ሀመርና ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ በአሜሪካን ኤምባሲ ተወያይተዋል
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ ሊቀመንበር እና የአሜሪካ የምስራቅ አፍሪካ ልዩ መልዕክተኛው በኢትዮጵያ ጉዳይ የተወያዩት

በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት

የፖለቲካ ምህዳሩ እያደር መጥበብ

በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገሪቱ ሰላም ላይ ያላቸው ሚና

የመሳሰሉትን ሀሳቦች አንስተው መክረዋል።

@Addis_Reporter


የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀል እና መልሶ የማቋቋም የቀድመ-ማስጀመሪያ ውይይት መርሃ-ግብር በትግራይ ተጀመረ

የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን፤ የቀድሞ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀል እና መልሶ የማቋቋም (DDR) የቀድመ ማስጀመሪያ ውይይት ትላንት ግንቦት 5፣ 2016 በ መቀሌ ከተማ መጀመሩን ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ እና ሌተናለ ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳዔን ጨምሮ የትግራይ ከልል ግዚያዊ አስተዳደር እና የፌደራል መንግስት ተወካዮች ተገኝተዋል።
በተጨማሪም የአፍሪካ ህብረት የሰላም ስምምነቱ ተቆጣጣሪ ኮሚቴ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተወካዮች መገኘታቸውን ኮሚሽነሩ በኤክስ ገጻቸው ላይ አስፈረዋል።

ተመስገን አክለውም የቅድመ ማስጀመሪያው ውይይቱ በተመረጡ አካባቢዎች የመስክ ጉብኝትን ያካትታል ብለዋል።

@Addis_Reporter


የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ ጸደቀ

ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 26ኛ መደበኛ ስብሰባው አዲሱን የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አጽድቋል፡፡

የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ የውሳኔ ሃሳቡን ለምክር ቤቱ በንባብ ያቀረቡ ሲሆን ፥ የረቂቅ አዋጁን መሻሻል አስፈላጊነት እና በምርመራው ሂደት የተከናወኑ ተግባራትንም በዝርዝር ለጉባኤው አስረድተዋል፡፡

አዋጁ የአርሶና አርብቶ አደሩን እና ከፊል አርብቶ አደሩን የኑሮ ደረጃ ሀገሪቱ ከደረሰችበት ዘርፈ ብዙ እድገት ጋር እኩል ለማራመድ የሚያስችል መሆኑ መገለጹን ከምክርቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ረቂቅ አዋጁ የተፈጥሮ ሃብቶችን በዘላቂነት በመጠበቅና በማልማት ለመጪው ትውልድ ለማስተላለፍ፣ የሴቶች፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞችና ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን የመሬት ተጠቃሚነት መብት ማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ረቂቅ አዋጁ በምክርቤት አባላት ሰፊ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ምክር ቤቱ ረቂቅ አዋጁን አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አድርጎ አፅድቆታል፡፡

@Addis_Reporter


በሱዳን ጥገኝነት ለጠየቁ የቀድሞ ሰላም አስከባሪዎች ጥበቃ እንደሚያደርግ የስደተኞች ተቋሙ ገለጸ!

በሱዳን በጥገኝነት እየኖሩ ያሉ የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ አባላት፣ ተፋላሚው የሱዳን "ፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች"፣ በሰሞኑ መግለጫው ካቀረበው የጣልቃ ገብነት ክስ ጋራ ተያይዞ የደኅንነት ስጋት እንዳደረባቸው ገለጹ፡፡

ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁን የትግራይ ተወላጅ የሰላም አስከባሪ አባላት፣ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፣ የሱዳን "ፈጥኖ ደራሽ ኀይሎች" ባወጣው መግለጫ፣ የህወሓት ታጣቂዎች በሱዳኑ ጦርነት እየተሳተፉ እንደኾነ ያቀረበው ክስ፣ “በመጠለያ ጣቢያዎች ያለነውን ስደተኞች ለጥቃት እንዳይዳርገን ስጋት ፈጥሮብናል፤” ብለዋል፡፡

ስለ ጉዳዩ ለአሜሪካ ድምፅ በኢሜይል አስተያየት የሰጠው የተባበሩት መግሥታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በበኩሉ፣ “የስደተኞቹን የደኅንነት ስጋት እረዳለኹ፤ ኹኔታውን የተመለከተ መፍትሔም እያፈላለግኹ ነው፤” ብሏል፡፡

Via:VoA

@Addis_Reporter


ሶማሊላንድ ከኢትዮጵያ ጋር የደረሰችበት የባሕር በር መግባቢያ ስምምነት አተገባበር ወደ ኹለተኛ ምዕራፍ መሸጋገሩን አስታውቃለች።

የመግባቢያ ስምምነቱ አተገባበር ግብረ ኃይል ሰብሳቢ ባሺ ሐጂ ኦማር፣ በመጀመሪያው ዙር የትግበራ ምዕራፍ፣ ስብሰባዎችን የማካሄድ፣  አማራጭ የባሕር ኃይል ጣቢያ ቦታዎችን የመለየት ሥራዎችና የሕዝብ አስተያየቶችን የማካተት ሥራዎች ሲሠሩ እንደቆዩ መግለጣቸውን የራስ ገዟ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ሶማሊላንድ የመጨረሻውን የመግባቢያ ስምምነት ለመፈራረም በምትሄድበት ሂደት ዙሪያ የሚያማክራትን አንድ የእንግሊዝ አማካሪ ኩባንያ መቅጠሯንም ሰብሳቢው መናገራቸውን ዘገባዎቹ አመልክተዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የመግባቢያ ስምምነቱ አተገባበር ምን ደረጃ ላይ እንዳለ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ መረጃ ሰጥቶ አያውቅም። ሱማሊያ በበኩሏ፣ ኢትዮጵያ የመግባቢያ ስምምነቱን ሙሉ በሙሉ ካልሰረዘች በባሕር በር ዙሪያ ከኢትዮጵያ ጋር አልነጋገርም በሚለው አቋሟ እንደጸናች ናት።

@Addis_Reporter


የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ በዮሃንስ ቧያሌው መዝገብ ከተከሰሱ ተከሳሾች የእስር ቤት አያያዝ ጋር በተያያዘ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ችሎት ቀርበው ማብራሪያ እንዲሰጡት ትናንት አዟል።

ክርስቲያን ታደለ፣ በቤተሰብ ጥየቃ ሰዓት ላይ በተደረገ ለውጥ ሳቢያ ለቀናት ምግብ እንዳልተመገቡ ለፍርድ ቤቱ መናገራቸውን የአገር ውስጥ ዜና ምንጮች ዘግበዋል። ካሳ ተሻገር በበኩላቸው፣ ከፍርደኞች ጋር ታስረናል፤ ፍርደኞችም ማስፈራሪያ ፈጽመውብናል በማለት አቤቱታ ማቅረባቸው ተገልጧል። ፍርድ ቤቱ፣ ኢሰመኮ የተከሳሾችን አቤቱታ መርምሮ እንዲያቀርብለት ማዘዙም ተሰምቷል። ወህኒ ቤቱ፣ ለተከሳሾቹ በመንግሥት የሥራ ሰዓት ምግብ መቀበል እንዲችሉ እንዲያደርግም ትዕዛዝ ሰጥቷል ተብሏል። 

@Addis_Reporter


መንግሥት ፍልሰተኞችን ለመመለስ ያቋቋመው ብሄራዊ ኮሚቴ፣ ትናንት ከሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ኹኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 179 ፍልሰተኞችን ወደ አገራቸው መልሷል።

ከተመላሾቹ መካከል፣ 14ቱ ከ18 ዓመት በታች እድሜ ያላቸው ታዳጊዎች እንደኾኑ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር ገልጧል። የትናንቱ ኹሉም ተመላሾች ወንዶች ናቸው ተብሏል። ብሄራዊ ኮሚቴው ከሚያዝያ ጀምሮ በቀጣይ ሳምንታት በአጠቃላይ ከሳዑዲ ዓረቢያ ለመመለስ ያቀደው፣ 70 ሺህ ኢትዮጵያዊያን ፍልሰተኞችን ነው።

@Addis_Reporter


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ  አስተዳደር በራያ ወረዳዎች መሠረታዊ የሕዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር ከፌደራል መንግሥቱ ጋር እየተወያየ እንደኾነ ለዋዜማ ተናግሯል።

በአካባቢዎቹ የመንግሥት ተቋማት እንደተዘጉና መደበኛ እንቅስቃሴዎች ባብዛኛው መስተጓጎላቸውን ዋዜማ ከነዋሪዎች አረጋግጣለች። ከአካባቢው የተፈናቀለ ነዋሪ የለም ሲሉ ያስተባበሉት የደቡብ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሃፍቱ ኪሮስ፣ በፈረሱት አስተዳደራዊ መዋቅሮች ውስጥ ይሠሩ የነበሩ አመራሮችና ሠራተኞች ግን ተፈናቅለው ሊኾን ይችላል ብለዋል። የተባበሩት መንግሥት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ ግን፣ በቅርቡ በትግራይ ኃይሎችና በአማራ ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ከራያ አከባቢዎች ከ36 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን አስታውቆ ነበር። ዋና አስተዳዳሪው፣ ከጦርነቱ በፊት በመንግሥታዊ መዋቅሮች ተመድበው ይሠሩ የነበሩ ሠራተኞች ወደ ሥራ እንዲመለሱ እየተደረገ መኾኑን ገልጸዋል።

@Addis_Reporter


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ ባለፈው ሚያዝያ 29 ቀን ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የመንገደኞች አዉሮፕላን ውስጥ የታየው ጭስ መነሻው የአውሮፕላኑ ዘይት መቃጠል እንደኾነ መናገራቸውን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

መስፍን የጭሱ መነሻ የእሳት ቃጠሎ እንዳልኾነ ጠቅሰው፣ የዘይት መቃጠል ግን አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ክስተት እንደኾነ መግለጣቸውን ዘገባው አመልክቷል። ክስትቱ ያጋጠመው፣ የበረራ ቁጥሩ "ET154" በኾነው የመንገደኞች አውሮፕላን ላይ ሲኾን፣ የኢትዮጵያ ሲቪል አቬሽን በክስተቱ ዙሪያ ጥልቅ ምርመራ እንደሚያደርግ መግለጡ አይዘነጋም።

@Addis_Reporter


እንባ ጠባቂ ተቋም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ26,900 በላይ ቅሬታዎችን ከሕዝብ መቀበሉን አስታውቋል።

ተቋሙ፣ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ 26 ሺህ 912 ሰዎች የአስተዳደር በደል እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አቤቱታ ማቅረባቸውን ጠቅሷል። በዘጠኝ ወራት ውስጥ ለመቀበል አቅዶ የነበረው 2 ሺህ 823 የአቤቱታ መዝገቦችን እንደነበር የገለጠው ተቋሙ፣ የነጻ ጥሪ መቀበያ የስልክ መስመሩ ከተቋሙ አቅም በላይ በኾነ ምክንያት ለሰባት ወራት አገልግሎት ባለመስጠቱና ባንዳንድ ክልሎች ባሉ የጸጥታ ችግሮች ሳቢያ 1 ሺህ 454 የአቤቱታ መዝገቦችን ብቻ እንደተቀበለ ገልጧል። በተያያዘ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ለእንባ ጠባቂ ተቋም ምክትል ኮሚሽነሮችን ለመሾም የእጩዎች ጥቆማዎችን መቀበሉን ከቀናት በፊት መግለጡ አይዘነጋም።

@Addis_Reporter


0952400019 ሰላም እዴት ቆያቹ ቤተሰቦቼ
በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚኖሩም
1 � ለመፍትሄ ሀብት
2 � ለህማም
3 � ለመስተፋቅር
4 � ቡዳ ለበላው
5 � ለገበያ
6 � የዛር ውላጅ ለተዋረሰው
7 � ሚስጥር የሚነግር
8 � ራዕይ የሚያሳይ
9 � ለዓቃቤ ርዕስ
10�ለመክስት
11� ለቀለም(ለትምህርት)
12� ሰላቢ የማያስጠጋ
13� ለመፍትሔ ስራይ
14� ጋኔን ለያዘው ሰው
15� ለሁሉ ሠናይ
16� ለቁራኛ
17� ለአምፅኦ
23� ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ
24� ለግርማ ሞገስ
25� መርበቡተ ሰለሞን
26�ለዓይነ ጥላ
27�ምስሐበ ንዋይ ወምስሐበ ሰብእ
28� ለሁሉ መስተፋቅር
29� ጸሎተ ዕለታት
30� ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
31� ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
32� ለትዳር የሚሆን የኮከብ ቆጠራ
33� ለድምፅ
34� ለብልት

ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ

1� የመኖሪያ ፍቃድ ላላገኙ  መፍትሄ
2.� ከሀገር ውጪ ስራ እድል ላጡ
3.� ንግድ ጀምረው አልሳካ ላላቸው
4.� ገንዘብ ለሚያባክኑ
5� ሰውፊት መቆም መናገር ለሚፈሩ 
6.� ለሀብት  ለንብረት ሚሆንም አለን
7�  ለስንፈተ ወሲብ መፍትሄ ለውጪ ሀገር ለሚኖሩትም እየሰራን ነው
8� ፍቅረኛ አልያዝ ላላቸውም አለን
9.� ትምህርት አልገባ ላለው
10� መስተፋቅር ፣የህዝብ መስተፋቅር
11.� ከሀገር መውጣት እየፈለጉ ላልተሳካላቸው ። ከሀገር ውጪ ላላችውም መፍትሄ በልዩ ሁኔታ አለን  ይምጡ ይደውሉ ያማክሩን ።
ለምንኛውም ጥያቄዎ ይደዉሉ
�0952400019
 
ባላቹህበት እንሰራለን

ሰላም እዴት ቆያቹ ቤተሰቦቼ
በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚኖሩም መምጣት ሳያስፈልግ ባሉበት እንሰራለን 
የምንሰጣቸው የጥበብ አገልግሎቶች ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል
1 � ለመፍትሄ ሀብት
2 � ለህማም
3 � ለመስተፋቅር
4 � ቡዳ ለበላው
5 � ለገበያ
6 � የዛር ውላጅ ለተዋረሰው
7 � ሚስጥር የሚነግር
8 � ራዕይ የሚያሳይ
9 � ለዓቃቤ ርዕስ
10�ለመክስት
11� ለቀለም(ለትምህርት)
12� ሰላቢ የማያስጠጋ
13� ለመፍትሔ ስራይ
14� ጋኔን ለያዘው ሰው
15� ለሁሉ ሠናይ
16� ለቁራኛ
17� ለአምፅኦ
23� ጠላት እንዳይጎዳ የሚያደርግ
24� ለግርማ ሞገስ
25� መርበቡተ ሰለሞን
26�ለዓይነ ጥላ
27�ምስሐበ ንዋይ ወምስሐበ ሰብእ
28� ለሁሉ መስተፋቅር
29� ጸሎተ ዕለታት
30� ለታሰረ ሰው እነዲፈታ የሚያደርግ
31� ለእጅ ስራ (እንዲቀናህ)
32� ለትዳር የሚሆን የኮከብ ቆጠራ
33� ለድምፅ
34� ለብልት

ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ

1� የመኖሪያ ፍቃድ ላላገኙ  መፍትሄ
2.� ከሀገር ውጪ ስራ እድል ላጡ
3.� ንግድ ጀምረው አልሳካ ላላቸው
4.� ገንዘብ ለሚያባክኑ
5� ሰውፊት መቆም መናገር ለሚፈሩ 
6.� ለሀብት  ለንብረት ሚሆንም አለን
7�  ለስንፈተ ወሲብ መፍትሄ ለውጪ ሀገር ለሚኖሩትም እየሰራን ነው
8� ፍቅረኛ አልያዝ ላላቸውም አለን
9.� ትምህርት አልገባ ላለው
10� መስተፋቅር ፣የህዝብ መስተፋቅር
11.� ከሀገር መውጣት እየፈለጉ ላልተሳካላቸው ። ከሀገር ውጪ ላላችውም መፍትሄ በልዩ ሁኔታ አለን  ይምጡ ይደውሉ ያማክሩን ።
ለምንኛውም ጥያቄዎ ይደዉሉ
�0952400019☎️☎️☎️☎️🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿


በአፍሪካ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ለሚደረገው ፈጣን ሽግግር ኢትዮጵያ ማሳያ ናት ተባለ

ኢትዮጵያ በነዳጅ ከሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ይልቅ በኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን የመጠቀም ልምድ እንዲያድግ የወሰደችው እርምጃ በአፍሪካ ጥሩ ምሳሌ መሆኑን ግሪን ቴክኒካ የተሰኘ የዜና አውታር አስታውቋል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ በሚሰሩ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ዘገባዎችን የሚሰራው ግሪን ቴክኒካ፤ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሸከርካሪዎችን ቁጥር 148 ሺህ ለማድረስ ማቀዷን ዘግቧል።

አገሪቱ ባለፉት 2 ዓመታት ብቻ በሀገሪቱ ያሉ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሸከርካሪዎች 100 ሺህ እንዲደርሱ ማድረጓ ለአረንጓዴ ልማት ምን ያህል ቁርጠኛ መሆኗን ያሳያል።

በኢትዮጵያ ጎዳናዎች ከሚነዱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል 10 በመቶ ያህሉ በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ መሆናቸው "አስደሳች ዜና ነው" ሲል ገልጾታል ተቋሙ፡፡

ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ለሚያመርቱ ኩባንያዎች ልዩ ድጋፍ እንደምታደረግ ይፋ ማድረጓን ተከትሎ በዘርፉ ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱን በዘገባው ተመላክቷል።

@Addis_Reporter


በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኙ ከ 6 ሺህ በላይ ሱዳናዉያን ስደተኞች በዉሃና በምግብ እጦት እንዲሁም በከፋ የፀጥታ ችግር ምክንያት ህይወታቸው ለአደጋ መጋለጡን አስታወቁ


ከግንቦት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኙ ከ 6 ሺህ የሚበልጡ ሱዳናዉያን ስደተኞች በሀገሪቷ ታጣቂዎች የጥቃት ሰለባ ከመሆናቸው በላይ ከፍተኛ የምግብ እጥረት እና የህክምና አገልግሎት እጦት አጋጥሞናል ብለዋል።

በሱዳን በጦር ኃይሎች እና ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይሎች መካከል እኤአ በሚያዝያ 2023 ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን በአማራ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በሚገኙ ካምፖች ውስጥ ስደተኞችን መቀበላቸው ይታወቃል ።

በአማራ ክልል ኦላላ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ካርሙክ መጠለያ ካምፕ ዉስጥ የሚገኙት እነዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ ሱዳናዉያን ስደተኞች ለሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እንደተናገሩት በውሃ እጥረት እና በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች ሳቢያ ህይወታቸው ለአደጋ ተጋልጧል።

የችግሩን አሳሳቢነት በማረጋገጥ ትኩረት እንዲሰጣቸው የጠየቁት ስደተኞቹ በካምፕ ዉስጥ እየገጠመው ካለዉ ችግር ለመሸሽ በማለት ወደ ጫካ በመሰደድ ላይ መሆናቸው ታዉቋል።

የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) በአማራ ክልል 27,000 ሱዳናውያን ስደተኞች እና 20,000 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እንደሚገኙ ግምቱን አስቀምጧል ።

@Addis_Reporter


በኬንያ አዲሱ የግብር ፖሊሲ የዳቦ ዋጋ ላይ ጭማሪ ያስከትላል መባሉ ቁጣን ቀሰቀሰ

አዳዲስ የታክስ ጭማሪ እና ያለዉን የማሳደግ እቅድ በኬንያ ሰፊ ትችት አስከትሏል።የብሔራዊ ግምጃ ቤት የስንዴ ምርትን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ዝርዝር ውስጥ ለማስወገድ ሀሳብ ካቀረበ በኋላ የዳቦ ዋጋ ጭማሪን እንደሚያስከትል ይጠበቃል።

መንግስት በሀምሌ ወር በሚጀመረው የፋይናንስ አመት ተጨማሪ 2.4 ቢሊዮን ዶላር ታክስ ለመሰባሰብ በማቀዱ የሞባይል ገንዘብ ማስተላለፍ፣ የአየር ሰአት እና ዳታ ወጪዎች እንደሚጨምሩ ይጠበቃል፡፡መንግስት አሽከርካሪዎች ተሽከርካሪዎቻቸውን በመንገድ ላይ ለማቆየት በየዓመቱ እስከ 750 ዶላር የሚከፍሉበትን አዲስ የሞተር ተሽከርካሪ ቀረጥ ተግባራዊ አድርጓል፡፡

የታክስ ጭማሪው የፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግስት ሰፋፊ የመሠረተ ልማት አውታሮችን እና ማህበራዊ መርሃ ግብሮችን ለመደገፍ የወሰዳቸው ተከታታይ የፋይናንስ እርምጃዎች አካል መሆኑን አስተዳደሩ ገልጿል።ርምጃው የሰላ ትችት ያስከተለ ሲሆን ፖለቲከኞች እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ግብሩን "ሸክም" ሲሉ ጠርተውታል።

መንግስት አዲሱን የግብር ርምጃ ቢወስድ ተቃዋሚዎች በመላ ሀገሪቱ የተቃውሞ ሰልፎችን እንደሚያደርጉ ዝተዋል።ባለፈው አመት የኬንያ መንግስት ከፍተኛ ተቃውሞ ቢገጥመዉም አከራካሪ የሆነውን የመኖሪያ ቤት ቀረጥ ጨምሮ በርካታ ታክሶችን ተግባራዊ ከማድረግ አልገደበዉም፡፡ በፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የታክስ ጭማሪ የሚበሳጩ ኬንያዉያን በቅዱስ መጽሃፍ በሰፈረዉ ግፈኛ ቀራጭ ዘኪዮስ ሲሉ ፕሬዝዳንቱን በቅጽል ስም እየጠሩ ይገኛሉ፡፡

@Addis_Reporter


በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኙ ከ 6 ሺህ በላይ ሱዳናዉያን ስደተኞች በዉሃና በምግብ እጦት እንዲሁም በከፋ የፀጥታ ችግር ምክንያት ህይወታቸው ለአደጋ መጋለጡን አስታወቁ


ከግንቦት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚገኙ ከ 6 ሺህ የሚበልጡ ሱዳናዉያን ስደተኞች በሀገሪቷ ታጣቂዎች የጥቃት ሰለባ ከመሆናቸው በላይ ከፍተኛ የምግብ እጥረት እና የህክምና አገልግሎት እጦት አጋጥሞናል ብለዋል።

በሱዳን በጦር ኃይሎች እና ፈጣን ድጋፍ ሰጭ ሃይሎች መካከል እኤአ በሚያዝያ 2023 ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን በአማራ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች በሚገኙ ካምፖች ውስጥ ስደተኞችን መቀበላቸው ይታወቃል ።

በአማራ ክልል ኦላላ እና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ካርሙክ መጠለያ ካምፕ ዉስጥ የሚገኙት እነዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ ሱዳናዉያን ስደተኞች ለሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን እንደተናገሩት በውሃ እጥረት እና በኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች ሳቢያ ህይወታቸው ለአደጋ ተጋልጧል።

የችግሩን አሳሳቢነት በማረጋገጥ ትኩረት እንዲሰጣቸው የጠየቁት ስደተኞቹ በካምፕ ዉስጥ እየገጠመው ካለዉ ችግር ለመሸሽ በማለት ወደ ጫካ በመሰደድ ላይ መሆናቸው ታዉቋል።

የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ (UNHCR) በአማራ ክልል 27,000 ሱዳናውያን ስደተኞች እና 20,000 በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እንደሚገኙ ግምቱን አስቀምጧል ።

@Addis_Reporter


የአሳማ ኩላሊት በንቅለ ተከላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለገሰው ግለሰብ ህይወቱ አለፈ


በዘረመል ምህንድስና የተሻሻለ የአሳማ ኩላሊት በንቅለ ተከላ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለገሰው ግለሰብ ከህክምናው ሁለት ወራት በኋላ ህይወቱ ማለፉን ሆስፒታሉ አስታወቀ።

የ62 ዓመቱ ሪቻርድ "ሪክ" ስላይማን ቀዶ ህክምናውን በመጋቢት ወር ከማድረጉ በፊት በከፋ የኩላሊት ህመም ይሰቃይ ነበር።

ህይወቱ ያለፈው በንቅለ ተከላው ምክንያት ስለመሆኑ ምንም ምልክት የለም ሲል የማሳቹሴትስ አጠቃላይ ሆስፒታል (ኤምጂኤች) እሑድ ዕለት አስታውቋል።

በዘረመል ምህንድስና ከተሻሻሉ አሳማዎች የተገኙ ክፍሎችን ሌሎች የመተካት ሙከራ ቀደም ሲል አልተሳካም ነበር። የስላይማን ቀዶ ህክምና ግን ታሪካዊ ምዕራፍ ነው ተብሎ ተወድሷል።
ከኩላሊት ህመም በተጨማሪ ስላይማን የስኳር በሽታ እና የደም ግፊት ነበረበት።

እአአ በ 2018 የሰው ኩላሊት ንቅለ ተከላ ቢያከናውንም ከአምስት ዓመታት በኋላ መሥራት ማቆሙ ተነግሯል።

የአሳማ ኩላሊት ንቅለ ተከላውን ተከትሎ፤ አዲሱ ኩላሊቱ በጥሩ ሁኔታ እየሠራ በመሆኑ የኩላሊት እጥበት (ዳያሊሲስ) እንደማያስፈልገው ዶክተሮቹ አረጋግጠው ነበር።
"ስላይማን በዓለም አቀፍ ደረጃ ስፍር ቁጥር ለሌላቸው ህሙማን የተስፋ ብርሃን ፈንጣቂ ሆኖ ይታያል። ‘የዜኖትራንስፕላንቴሽን’ መስክን ወደፊት እንዲራመድ ላሳየው እምነት እና ፍቃደኝነት በጣም እናመሰግናለን" ሲል ሆስፒታሉ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

ዜኖትራንስፕላንቴሽን ህይወት ያላቸው ሴሎችን ወይም የአካል ክፍሎችን ከአንድ ዝርያ ወደ ሌላ ዝርያ መተካት ነው።

@Addis_Reporter

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.