ሐሽማል ቤተ-መዘክር


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Kitoblar


👉Only for readers
👋መግቢያ👋
መግቢያ ለመግባቢያ
ገታ አርገነዋል የቃላትን ግልቢያ
እናም በዚህ ሀሳብ ከተስማማህበት
ያንኳኳኸዉን በር የገለፅከዉን ገፅ ፈቅደናል ግባበት
ምንጭ - ካልታወቀ ገጣሚ
Join the group
@amharicbooksforeadersgroup
አድሚኑን በ ቀጥታ ለማናገር ይህንን ቦት ተጠቀሙ @Digitallibraryofhashmal_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ተይው
(kerim)


ተይው አላገግም
መዳን አልፍልግም

ስለ አንቺ መታመም መዳኔ ነው እና
አንቺን በማፍቀር ውስጥ እኔ ልጣ ጤና
ተይው........

By @poem2513


✅በህይወታችን ከሶስት ሰዎች ጋር በፍቅር እንወድቃለን: ሶስቱም የራሳቸው ምክንያት አላቸው ይላሉ

👇🏾

✅ የመጀመርያው ፍቅር በአፍላ እድሜ ወቅት የሚከሰት ነው: ድንገት መጥቶ እፍ ያስብልና ከዚያም እዚህ ግባ በማይባል ምክንያት መራራቅ ይፈጠራል

ከቆይታ በኃላ በእድሜ ስንበስል መለስ ብለን ስናየው ፍቅር እንደነበር ራሱ የምንጠራጠረው አይነት ስሜት ነው: ግን በወቅቱ ፍቅር እንደሆነ ተሰምቶን አልፏል

.............

✅ሁለተኛው ፍቅር ከባዱ ነው

በፍቅር ከወደቅነው ሰው ጋር እፍ ማለት ብቻ ሳይሆን ብዙ ህመም እና ስብራትም ይዞ የሚመጣ ነው:: እንዲህ አይነት ፍቅር ስሜቱ ሃያል ሲሆን ቁርኝቱ ከመክረሩ የተነሳ ከዚያ ሰው ጋር መለየት የሞት ያህል የከፋ ይመስለናል

ስለዚህ በዚህ ፍቅር የተጎዳነውን ስብራት በምንጠግንበት ሂደት "ከዚህ ወዲያ ልቤን ብሰጥ እርም" ወደሚል አጥር የመስራት ውሳኔ ውስጥ እንገባለን: ጠባሳው ትልቅ ሊሆን ይችላል

ስለዚህ ተጠራጣሪ እንሆናለን: በቀጣይ ፍቅር ሲይዘን እንዴት እንደምንሆን ቀመሩን እንወስናለን: ከስሜታዊነት ፈቀቅ እንላለን

.................

✅ ሶስተኛው ፍቅር መምጫው ሳይታወቅ ድንገት የሚመጣ ነው ይሉታል

ይህንን አይነት ፍቅር ብዙም ለማግኘት ተደክሞ ሳይሆን ድንገት የሚይዘን ነው: ድንገት የገነባነውን ግድግዳ ሁሉ የሚያፈራርስ አይነት ፍቅር ይሉታል

እዚህ ጋር ካፈቀርነው ሰው ጋር የሚኖረን ግንኙነት "ከወደዱማ ከነግሳንግሱ" አይነት ሲሆን አንዱ ሌላውን እየቀረፀ የተሻለ ማንነት የሚሰራበት ነው

ጠዋት ከእንቅልፍ ስትነሳ "Good Morning my Sunshine” የምትልለት እና ማታ ስትተኛ ደግሞ "Good Night Darling” ብለህ ቀንህን ጀምረህ ቀንህን የምታሳርግበት

✍ እንማር

752 0 12 1 12



ስወድሽ በቅፅበት ነበር ፥ ሳፈቅርሽ ቀን አላለፈም
ቆም ብሎ እንኳን ለማሰብ ፥ በመሀል ጊዜ አልተረፈም ::
አይኖቼ አይንሽን አዩ ፥ የልቤ መቃን ወለቀ
ፈገግታሽ ሙት አፌን ነክቶት ፥ ግማታም ጥርሴ በድንገት ሳቀ።
መዳፍሽ መዳፌን ያዘ፥ ትንሽ ላብ እጄን አራሰው
ያን ጊዜ ሞፈሩ ፍቅርሽ ፥ ደንዳና ልቤን አረሰው ።

አየሻ... ❓

ከአይን ጥቅሻ ቀድሞ ነበር፥ ፍቅርሽ ልቤን ያነቀው
ነገር ግን ዓመት ፈጀበት ፥ የኔ ፍቅር ልብሽን ሊያውቀው
"ወደድኩህ " አልሺኝ ባመቱ
ደስ ብሎኝ ነበር በውነቱ
ግን እቱ.....

ማፍቀርሽ እሩጫ ነበር፥ ከራስሽ ችግሮች ሽሽት
ትዝ ይልሻል የዛን ምሽት ?
[ I Know, You Don' Give A Shit ]
ግን አስታውሺ,....
" የት ነሽ ? " ብየሽ ስትዋሺ....

ማጋጣነት ካቀለመው ፥ ድፍን ጥቁር ልብሽ ግርጌ
ጥለሽ መክዳትሽ ሲረግጠኝ ፥ መሞት ሲያቅተኝ ፈልጌ
የሞት ከንፈር ዳሩን ስሜ ፥ ልክ ስመለስ ወደ ቀለቤ
ጠላሁሽ.......፥ [ በወደደሽ ልቤ ። ]

[ አየሽ አይደል ? ]
ፍትህ ሰፍኖ ሲደላደል ?

በቅፅበት እንዳልወደድኩሽ ፥ በቅፅበት ስጠላሽ ደግሞ
በንክሻ ሲያስወጣሽ ልቤ ፥ እንዳላስገባሽ ስሞ ?

ግን ደግሞ... ግን ደግሞ....
ማታ አፍቅሬሽ ተኝቼ ፥ ጠዋት ጠልቼሽ ብነቃም
( ልፋ ሲለኝ እንጂ...)
ጨርሶ አንቺን ለመርሳት ዘላለም እንኳን አይበቃም።




✅አንዳንዴ ጉረኛ ሰዎች ደስ ይላሉ ። ወርያቸው አካሄዳቸው ላይ Energy አለ ። ጨለማ ..ጨለማ.. ብሶት.. እዬዬ ። አይ ጉድ.. ብዙ ግዜ አያወሩም ።

በራሳቸው ጉዳይ በፍቅር ወድቀዋል ።

✅ተስፈኛ ናቸው ። ያላቸው ነገር ላይ ይመሰጣሉ ያጎሉታል ።

ምን ለማለት ነው
አንዳንዴ እየጎረርን 😄

✍ እንማር


የሆነ ቦታ የሆነች የተረጋጋች ሴት ያለች ይመስለኛል። የሰውን ትኩረት የማትፈልግ ፤ ሰዎች እንዲወዷት የተለየ ነገር የማታደርግ የራሷን ኑሮ የምትኖር...

ህይወቷ በእውነት እንጂ በፈጠራ ድራማ ያልተሞላ ፤ ሰዎች እግረመንገድ ላይ ድንገት ዋነኛዋ ሴት የምትሆን ። የተሰማትን የፈለገችውን ደስ ያሰኛትን የምታደርግ ፤ ምታደርገው የማይፀፅታት ...

ምድር ላይ ያለውን የህይወት ብሶቷን አልያም ችግሯን ለመደበቅ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወ'ታ ከመንዘባዘብ ይልቅ ከአምላኳ ጋር የምትነጋገር። ስለራሷ እሷ እና አምላኳ ብቻ የሚያውቁ። ይህቺ ሴት ብርቱ ናት....

ለጓደኝነት ትመቻለች። ነፃነት ትሰጣለች። ለጊዜያዊ የፍቅር ግንኙነት ታስፈራለች። ወንዶች ይጠነቀቁላታል። የትኛውም ወንድ ደፍሮ ሌላዋን ሴት የሚያወራበት መልኩ ይቺን ሴት ሊያወራት አይችልም። ልባም ናት። ለዘላቂ ትዳር የምታስተማምን ሴት። የቤቱ ራስ መሆን የሚችል ፣ ሚስቱ እንድትገዛለት ሆኖ መኖር የሚችል ባል የሆነ ወንድ የሚመኛት እና የሚያገኛት ሴት ናት።

ይህቺ ሴት ብርቅ ናት ! ፀሎቷ ልኬት ያለው ይመስለኛል። ከሚያስፈልጋት በላይ እንዲሰጣት አትለምንም። ተመስገንን ታውቃለች በተሰጣት አታማርርም ።

Via MP ET


❤አውቃለሁ!❤

ባንቺ ዝምታ ውስጥ ነፍሴ ማህሌት ቆማ
ሰማሁ ተመስጬ የልብሽን ዜማ።
አውቃለሁ ዓለሜ ..
ከንፈሮችሽ አፍረው ባይወጣ አንድም ቃል
እንደምትወጂኝ ዓይንሽ ያሳብቃል።

✍️ገጣሚ ዘሪሁን ከ አሰላ
የካቲት 1/2017


ቻርሊ ቻፕሊን አንድ ቀን ህዝብ ተሰብስቦ ወደሚጠብቀው አዳራሽ አመራ። በጭብጨባ ከተቀበሉት በኋላ ወደ መድረክ እንዲወጣ ተጋበዘ።

#በመጀመርያ የሚያምር ቀልድ ነገራቸው። አዳራሹ በፉጨት ተቀወጠ በሳቅ ደመቀ።

ከዚያም ያንኑ ቀልድ #ለሁለተኛ ጊዜ ደገመላቸው። ግማሾቹ ሳቁ፤ ግማሾቹ ደግሞ ግራ ተጋቡ....

#ለሶስተኛ ጊዜ አሁንም ያንኑ ቀልድ ደገመው። በዚህ ጊዜ ግን አንድም የሚስቅ ሰው አልነበረም።

ያኔ ቻርሊ በጣም ደስ አለው። ከዛም የሚከተለውን ንግግር ተናገረ.....

"በአንድ ቀልድ ደጋግማችሁ እንደማትስቁ ሁሉ ስለምን በአንድ ነገር ደጋግማችሁ ታለቅሳላችሁ?

ህይወትኮ እጅግ ውብ ናት። ዛሬ በህይወት ካላችሁ ነጋችሁን ማስተካከል ትችላላችሁ።

በትላንት ውስጥ ስላጣችሁት ነገር አታስቡ ዛሬን ብቻ በህይወት በመኖራችሁ ፈጣሪን አመስግኑ።

ዛሬ ጠንካራ ከሆናችሁ ነጋችሁ የተዋበ ይሆናል፤ ነጋችሁ የሚጥም ይሆናል። አሁንም አሁንም አሁንም በህይወት መኖራችሁን ብቻ እያያችሁ ፈጣሪን አመስግኑ!"

#ወዳጆቼ ከተሰጠን ስጦታዎች ሁሉ ህይወታችን ይበልጣልና በህይወት ካላችሁ በነጋችሁ ላይ ለውጥ መፍጠር ትችላላችሁ።"
---------------------------
ዳን TELL


የሠርጌ ቀን እንኳ ብትይ እወድሃለሁ
ሙሽራዬን ትቼ ወዳንቺ እመጣለሁ
ፍቅር ያዘኝ ብልሽ ወደድኩኝ ሌላ ሴት
እየዋሸሁሽ ነው አትስሚኝ በሀሴት
✍Henok


ሌላ ሴት ልታገባ ያልክ ቀን እንኳ ብደውልልህ እሷን ትተህ እኔ ጋር ነው አይደል የምትመጣው...? እለዋለሁ ሁሌ ….

ፈገግ ብሎ ያየኝና “ደፋር ኮ ነሽ….ይለኛል።

ካለው ነገር ሁሉ እኔን አስበልጦ እንደሚወደኝ ጠንቅቄ አውቃለሁ...

ሲሳሳልኝ...ከራሱ ሲያስቀድመኝ...ሲጨነቅልኝ...ለኔ ሲኖር ዓይቻለሁ።

....በእርግጥ እንዲህ ማለት ከባድ ይመስላል።

እኔ ግን ዓይኑን ሳያርገበግብ...ይሄን ልጅ ግን ምን አስነክታው ነው እስኪባል... የሚያውቁን ሁሉ እስኪገረሙ ድረስ ሳናድደዉ... እና ሳበሳጨው ችሎ በክፉ ቀናቶቼ ላይ ለደስታዬ ሲፈጋ አብሮነታችንን ለማቆም ብዙ ሲለፋ በህመሜ ወቅት ሃሳቡን ጊዜውን ገንዘቡን ሰጥቶ ከጎኔ ሲቆም አውቅ ነበር....

ይመስለኛል የበዛ መውደዱ.... የትም አይሄድም ብዬ እንዳስብ... ለኛ እንዳልጨነቅ እና በተወዳጅነት ተኮፍሼ ለሚሰጠኝ መውደድ እና ክብር ትንሽ እንኳ አፀፌታን መስጠት የማልችል ሴት አድርጎኛል...

ከዛ በአንዱ ቀን በትንሽ ነገር ተጋጨን እና ….ሂድልኝ አልኩት...

ለመነኝ አስለመነኝ…ከቀልቤ መሆን ያልቻልኩት እኔ ግን ግድ አልሰጠኝም እና ምንም እንደጎደለብኝ አልተሰማኝም።

መሄዱ እንደሚያም እንዴት እንደሚናፍቀኝ ለመረዳት ብዙ ረፈደብኝ...

ሄደ...

ከዛ አልተመለሰም...

ልመልሰዉ ሞከርኩ…መሄድ አለማምጄው ኖሮ መመለስ አቃተኝ...

እናማ አሁን የገፋሁት እኔ....ወዶኛል አይጠላኝም ያልኩት እኔ በተራዬ እጅግ እየናፈቀኝ...እያመመኝ...ነው።

እያስመሰልኩ አብሮነታችን ማክበር ያልቻልኩት እኔ … ሲያቅፈኝ ሕይወት እንደሚቀለኝ ችግሮቼን ችሎ ማሸነፍ ብቻን ያለማመደኝ እሱ እንደነበር...በጣም እንደሚናፍቀኝ...በጣም እንደማመሰግነው እንደምወደው ያልነገርኩት እኔ...

....የሄደበትን ቀን ሻማ እያበራሁ በሐዘን በፀፀት አስታውሰዋለሁ።

(ወግ ብቻ)
(በማ ሂ )


ዛሬ ላይ የጎዳህ ሁኔታም ይሁን ሰው ፤ ነገም ላይ መጉዳቱ አይቀርም። የባሕርን ጨዋማነት ለማረጋገጥ ባሕሩን ሙሉ መጠጣት አይጠበቅብህም።


የማወራው ስለባሕር አይደለም።
©ሶፊ


ህይወት እንደ ማስታወሻ ደብተር ናት።ሁለቱ ገፆች በእግዜር የተፃፉ ናቸዉ።የመጀመሪያው ገፅ የተወለድንበት ቀን ሲሆን ፤የመጨረሻው ገፅ ደግሞ የመሞቻ ቀናችን ነዉ።በመሀል ያሉትን ባዶ ገፆች በፍቅርና በመልካምነት አኛ የምንሞላቸዉ ናቸዉ።

2.5k 0 13 13 27

ኮስታራ ናት እንኳን ገና ላልቀረበቺው ቀርቶ ለቀረቧትም ፊቷ አይፈታም።ጭምት ናት።ለሰዎች ደግ እና ቁምነገረኛ መሆኗን ግን ብዙ ሰው ይስማማበታል።እኔ ደግሞ ጥሎብኝ ኮስታራ ሰው እወዳለሁ፤ምንም እንኳን ሳቂታ ብሆንም...ለምንም ነገር ሳቅ ይቀድመኛል...ስናደድ እንኳን እስቃለሁ።
"ያለ ሳቅ ህይወት ምንድነው?" ብዬ የማስብ አይነት ሰው ነኝ።

የእሷ ህይወት?
ሳቅ ፈፅሞ የማይታወቅበት ጨለማ ነው ብዬ ደመደምኩ...የማስፈልጋት መስሎ ተሰማኝ...ለጨለመ ህይወቷ ጭላንጭል ብርሃን ልሆን...ፋኖሴን ይዤ ቀረብኳት፥ፈገግታዬን።
አልገርምም?
ማን ነኝ ብዬ ነው የማስበው?

የመጀመሪያ ሰሞን በቀልድ የተከሸኑትን ረጃጅም አረፍተ ነገሮች...በአጭር መልስ ድባቅ መትታ ጨዋታ ታስጠፋብኝ ነበር።እንኳን ለማሳቅ በወጉ ለማውራትም ቃላት እያጠረኝ መጣ...ይቺ ሴት ፋኖሴን፥ፈገግታዬን እፍ ብላ አጥፍታ እኔንም ያለሳቅ ልታስቀረኝ ነው?

እሷን ሳያት "በፌዘኞች ወንበር አትቀመጥ" የሚለውን የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አስታውሰዋለው...በተገናኘንባቸው አጋጣሚዎች ላስቃት ስውተረተር፣ቃላት ጠፍቶብኝ ስደናበር...ርቃኝ ልደርስባት ስንጠራራ...በቀልዶቼ ሳይሆን በሁኔታዬ ፈገግ ማለት ጀመረች...ኋላ ላይ ሁኔታዬ አሳዝኗት ነው መሠል እሷው ታስቀኝ ጀመር...

አልፎ አልፎ እንደ ቅመም ጣል የምታደርጋቸው ቀልዶቿ ሆዴን አስይዘው ያስቁኛል...በሳቄ እሷ ትስቃለች...ሳቋ ደስ ይለኛል...ሳቋን ለማየት አንዳንዴ እንዲሁ እገለፍጣለሁ።

አንድ ቀን ብዙ ግርግር በማይበዛበት እሷ ባሳየቺኝ ካፌ ቁጭ ብለን ስንጨዋወት..."ከሳቅ ያኳረፈሽ ምንድነው?" ብዬ ጠየኳት።መልሱን ለመስማት ከመጓጓቴ የተነሳ መላ አካላቴ ጆሮ የሆነ እየመሰለኝ።

ጥያቄን በጥያቄ መለሠች። " ሰው ስለሳቀ ደስተኛ ነው ማለት ነው? " አለቺኝ በአይኖቿ ትኩር ብላ እየተመለከተቺኝ።
"ይመስለኛል...ሳቅ የደስታ መገለጫ አይደል፤እንባ ደግሞ የሐዘን።" አልኳት።
"ሐሴት ምን እንሆነ ታውቃለህ?" አለቺኝ።
"ደስታ አይደል"አልኳት በጥርጣሬ።
"አዎ ነው ግን ምን አይነት ደስታ?" ዝም አልኳት ግራ መጋባቴን አይታ ቀጠለች።
"ውስጣዊ ደስታ!" አለችና እርካታ የተሞላበት ፈገግታ ተጎናፀፈች...ሐሴት አደረገች?
ማብራሪያዋን ቀጥላለች "...ሐሴት ማለት ከትክክለኝነት የሚመነጭ ደስታ ነው...አደርገዋለሁ ያልከውን ስታደርገው ነኝ ያልከውን ስትሆን...ብዙዎቹን የራቀው ደስታ ይሄ ነው...እኔ ደስ እንዲለኝ...በየማዕበራዊ ገፁ የሚያሥቅ ነገር ሳስስ ውዬ አላውቅም...ውጪያዊ ደስታ ውሥጥን አርክቶ አያውቅም፤ይልቅ ባዶነት እንዲሠማህ ያደርጋል አንዳንዴም...ሰዎች ደስታ ውስጣቸው እንዳለ ዘንግተውት ደስታን ፍለጋ አይሆኑ ሲሆኑ ያሳዝኑኛል።እኔ ምንም እንኳን ባልስቅም ውስጤ ባለው ሰላም ሐሴት አደርጋለሁ። "

አለች ፍፁም መረጋጋት እና ስክነት ከሁናቴዋ እያነበብኹ።

ከተለያየን ፤ ከሄደች በኋላ ራሴን ጠየቅኹ...

እውነት ደስተኛ ነኝ?
እንጃ!

እኔም ብሎ ፋኖስ ለኳሽ፤ብርሃን አብሪ

እፍፍፍፍፍ....ፋኖሴን(ፈገግታዬን) አጠፋዋት!

ደግሞ ለፀሐይ የፋኖስ ብርሃን ምኗ ነው?
ለካ ጨለማ የነበረው የእኔ ህይወት ነው።




ከተቀደደው ማስታወሻ
©ሶፊ


እቴ ወይ ልዋል(2)
ከደረትሽ መሀል
ናፈቀችኝ ጎንደር(2)
የእነ አሞራው ሀገር

በቅዳሴው ቦታ ቀለሀ ሲዘምር
እንዴት ሰንብተሻል እናትዋ ጎንደር
እናትዋ ብልሽ
ትንፋሽዋ ብልሽ
አካልዋ ብልሽ
መቼ ደረስኩልሽ

ሹርባ ሆኗል ጎፈሬው
እንደ መይሳው ሊያደርገው
ያ ጎንደሬው
ምነው ገብርየን ቢያረገኝ
አሞራው ውብነህ ቢያረገኝ
ከፊት እንድገኝ

አሞራው ከአሞራ(4)

ያየም ሰው ይናገር የነበረም ያውጋ
ተጋጥሟል ይባላል አሞራው ከአሞራ
ጎንደር ጀግና ትውለድ ታሳድግ ፀንሳ
እንደአሞራው ውብነህ ስሙ ማይረሳ
ሀገርና እምነቱን ከእራሱ አስበልጦ
ለጠላት ያለቅሳል ውዳሴውን ገልጦ

ጎንደር ጎንደር ደስ ይበልሽ
ደም መላሽ አርበኛው አሞራው መጣልሽ
የሰው ነው የሰው የሰው አመሉ
ማን መጣ ቢሏችሁ ጎንደሬው ነው በሉ

አሞራው ከአሞራ
ኢትዬጵያን ሊያገባት አብጠሊሷን ቀዶ
ልጇ ደረሰላት ሞት ወዶና ፈቅዶ
ወይ አንች እናታለም ወይ አንች መበለት
እንድሜ ብርክ ሲይዘው ልጅ ይሆናል ጎልበት
ወልቃይት ጠገዴ አጅሬ ጃኖራ
ምን አይነት ፍርድ ነው አሞራው ከአሞራ
አሞራው ከአሞራ(3)

ሲሆን መጡ መጡ እንባል ነበረ
እንሂድባቸው ማሸነፍ ካልቀረ
ደሞ ተዚ ተዚህ ተወዲያ ተወዲህ
ጎንደር ከአንች በፊት ያድርገኝ ተንግዲህ
እናትዋ ጎንደር እጅ የዘረጋችው
ዘነበች መሸሻን ወልዳ የሳመችው
ምድር ቀዝቀዝ ሲል ተላይ እያሞቀው
ይኸው ቀብረር ብሎ አሞራው ጠበቀው
አሞራው ጠበቀው

ሀገር እንደዋዛ ናፍቆት እንደዋዛ
የእነ አሞራው ሀገር የመይሳው ካሳ
አዘዞ ድማዛ
የጃንተከል ዋርካው ወደ መሬት ዘሟል
እንኳን ያደገብሽ ያየሽ በአይኑ ታሟል
እናትዋ ጎንደር

ተይ ደሜ(3)
በላ ልበልሀ እንካንጅ ተቀበል
አሞራው ተነሳ ከእንግዲህ ዝም አትበል
የአለም ፀሀይ እታባ ፊትሽ አይቀየር
የተጠማው በልቶ ለብሶ ጠግቦ ቢያድር
ከተኮሰ ማይስት ጀግና ክንደ ብርቱ
ያ የአርበኛው ምንጣፍ ያ ምጅምር ገጡ
የጦሩ መሳፍንት ፈሪሀ እግዜር ያለው
ከጦር መሀል ሲሄድ ይመስላል ክንፍ ያለው
አሞራው ከአሞራ(8)
አሞራ ምት ለምዶ አካሌ ተቆጣ
ልሂድ ወንድነቴን አሳድሸው ልምጣ
ከዳሽን ላይ ፈልቆ ቀድታ የጠጣችው
የነካትን ሁሉ አቃጥላ ፈጀችው
ከሱዳን ገዳሪፍ ተስቦ እንደ ሰርዶ
ኢትዬጵያን ሰቀላት ያን ሰንደቅ አውርዶ
የአበቅየለሽ ልጆች ዳር እስከዳር ኩሩ
ጎንደር ጀግና አታጣም አትጠራጠሩ(3)
አሞራው ከአሞራ (2)

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ |


አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ


ኔግሮ የሚባል ፍሬንድ ነበረኝ ፀባይኛ ነው፣ ሌባ ነው፥ እናቱን ይወዳታል፥ ትምህርት አይገባውም፤ ተንኮል፣ ኳስ ፣ጆተኒ ፣ ትረባ ጎበዝ ነበር።

በአንድ ሴሚስተር መቶ እና ሁለት መቶ መፅሃፍ ይሰርቃል መቼ? ...እንዴት?...ከማን?... አላውቅም!

መጨረሻ ላይ  ውጤቱን እየሳቀ ይነግረኛል።
አንድ ቀን እንኳን ሲሰርቅ ተይዞ አያውቅም !

የሰረቀውን መፅሐፍ ሲሸጥ አብሬው ሄጄ አውቃለሁ። ከሚገዙት ጋር ደምበኛ እንደሆነ ሰላምታ አለዋወጣቸው ያስታውቃል። አሻሻጡ የሰረቀ ፣ ሳይለፋበት ያመጣ አይመስልም፤ በቸልታ አይደለም።  በርጋታ እንደትልቅ ሰው... "አይሆንም...፣ ይቅር...፣በቃ፣ ጨምር " እያለ ነው ።

እናቱን  "ሸቅዬ... እዛ ማዶ ያሉት ሃብታም ሰዎች፤ ለእናትህ ስጣት ብለው ብር ሰጡኝ" እያለ እንደሚሰጣት ነገሮኝ ያውቃል ።

ሰባተኛ ክፍል ፣ ስምንተኛ ክፍል እያለን እናቱን ያግዛት ነበር ።  ይወዳታል፤  አወዳደዱ እንደትልቅ ሰው  ነው። "ማሚዋ  ደብሯታል ...አሟታል. . . ገበያ ቀዝቅዞባታል" እያለ ያስብላታል።

ከጓደኛው አይሰርቅም። ለጓደኛው ለኔ ለሚለው ሰው ይሳሳል።

አይኖቹ ትናንሽ ናቸው፣ አካባቢውን በትኩረት ያያል፣ ከወሬ ሁኔታን ያያል። ሌባ መሆኑን ብዙ የሩቅ ሰዎች አያውቁም።

ኔግሮ ቁርንጫጭ ፀጉር ያለው፣ ድቅቅ ያለ ገላ ያለው፣ ሲስቅ ቀጭን ድምፅ የሚያወጣ ልጅ ነበር ።

አንዳንድ  ቀን  ይፎርፍና ሜዳ ጥግ ውኃ ልኩ ጋር ብቻውን ይሆናል ። ዝም ይላል ኳስ አይጫወትም። ቀጭን ድምፅ እያወጣ የሚስቃት ሳቅ አትኖርም። ለመኮረጅ ብዙ አይሰቃይም።

...ጨዋታ ያበዛል...።

ስለ አባቱ አላውቅም፤ እናቱ ግን ትምህርት ቤታችን በር ጎን ላይ ቃርያ ፣ ቲማቲም፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ድምብላል፣ ኮሰረት፣ ስኳር ድንች ...ምናምን ይሸጣሉ። ብዙ ደንበኛ ያላቸው አይመስለኝም። ስንወጣ ስንገባ የደራ ገበያ አንድም ቀን አይቼ አላውቅም ።  

ኔግሮ የትምርት ቤት ስሙ መቆያ ነው። እኛ ነን ኔግሮ የምንለው።

እኛ ትምህርት ቤት የሚማሩ የሰፈሩ ልጆች ሲጠሩት ሰምተን መሰለኝ መቆያን ትተን ኔግሮ የምንለው።

መቆያ የሚባለው ክላስ ስም ሲጠራ ብቻ ነው። ኔግሮ ሲባል ነው እሱም ደስ የሚለው።

የሆነ ቀን ሃይሚ ግርማ መፅሃፍ ጠፍቶብኝ ኔግሮ ሰጠኝ አለችኝ። ጠየኩት "ከራሷ ቦክመህ ለራሷ ገጫሃት ኣ?" ስለው ፤ ሲስቅ የሚያወጣትን ቀጭን ድምፅ አውጥቶ ሳቀ  "ባክህ እኔ እንደኔ ችስታ እናት ካለው ቤተሰብ አልሰርቅም "አለ ።

ከስምንት ወደ ዘጠኝ ስንዘዋወር ኔግሮ ታስሯል አሉን። ስሰማ "ዕድሜው ለእስር ደርሷል ወይ?" ብዬ ያኔ አልጠየኩም።

የመንግስት ትምህርት ቤት ስለተማርን ለብዙ ነገር  ከዕድሜያችን በላይ ነበርን። የሚታሰሩት በግሩፕ የሚጣሉ ልጆች ስለነበሩ ብዙ  አልገረመኝም።

መስከረም አስራ ሰባት ቀን ኔግሮ ሞተ አሉን።  እናቱን ስናያቸው ጥቁር ለብሰዋል፥ ጉስቁልናው ብሶባቸዋል። ጉሊት የደረደሩት ከዚህ ቀደም ለመሸጥ ከሚደረድሩት በዐይነትም በመጠንም ቀንሶ አየሁ ።

ሞትን ያኔ ነበር በቅርብ ያወኩት ....በቅርብ የማውቀው፣ ሲያወራ የሰማሁት፣ አብሬው የተጫወትኩት ጓደኛዬ ሞተ ሲባል። ያኔ ነው ለመጀመሪያ ግዜ ያመንኩት።

የታሰሩበት ክፍል የነበረው ካቦ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ፖሊስ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ታሞ ነው ይላሉ ....
ኔግሮ ሞተ። እውነት  ነበር!

"ልጅ ይሞታል እንዴ?!" አልኩኝ
ለምን መቆያ አሉት ግን  እናቱ??
በዛ ዕድሜው እንዴት በዛ ልክ አሰበላቸው??
በምን ይሆን የሚፅናኑት??
ለምን ሌባ ሆኖ ለጓደኞቹ ታመነ??

እንዴት  የሰረቀውን እንደትልቅ ሰው አስቦ ተከራክሮ ሸጠ?? ላለፋበት ነገር እንዴት ዋጋ ሰጠ?? ለምን ምንም ከሌላቸው ሰዎች አልሰርቅም አለ??

በዛ ዕድሜው እንዴት አረጀ ?
እሺ ይሁን መርህ እና ሌብነት እንዴት አብሮ ሄደለት!!

እኔንጃ ኔግሮ ግን ሞተ አሉ !!!
      © Adhanom Mitiku


እድሜህ ምን አስተማረህ ...??

ሁላችንም ባልተመረመርናቸው በሽታዎች የምንሰቃይ ምስኪኖች ነን ፤ እድሜያችን ያስተማረንን እንኳ የማናውቅ ።

ብዙ ያልተጠየቅናቸው ጥያቄዎች አሉብን በግዜ ሂደት ህመም እየሆኑ እኛነታችንን ከእግዜር የነጠሉ

ብንጠየቅም
ደሞ መልስ የማናገኝላቸው ሺህ ጥያቄዎች ...

እኔ እድሜዬ መዳብ የሆነብኝን ወርቅ ከሔደ ደግሜ እንደማላገኝ አስተማረኝ..እናንተስ

✍ ሔኖክ


አንድ በእድሜ ብዛት የጫጨ አዛውንት አልጋ ላይ ሊሞት እያጣጣረ ነው።

✔️አምስት የቤተሰቡ አባላት ቆንጅዬ ሚስቱና አራት ልጆችሁ ከአልጋው አጠገብ ቆመው የማይቀረውን ሞት እየጠበቁ ነበር።

✔️ ከልጆቹ መካከል ሦስቱ ታላላቆች ረጃጅሞች፣ ቆንጆዎች እና አትሌቲክስ ነበሩ፤ ነገር ግን አራተኛውና የመጨረሻው ልጅ የቤተሰቡ አስቀያሚ ነገር እንደነበር ጥርጥር የለውም።

ባልየው በሹክሹክታ "ውድ ሚስቴ ትንሹ ልጅ በእውነት የእኔ መሆኑን አረጋግጭልኝ። ከመሞቴ በፊት እውነቱን ማወቅ እፈልጋለሁ ሃቅ ከነገርሽኝ ይቅር እልሻለሁ" ሚስትየው በእርጋታ አቋረጠችውና "አዎ የኔ ውድ በፍፁም ምንም ጥያቄ የለውም በእናቴ መቃብር ላይ እምላለሁ አባቱ አንተ ነህ" አለችው። ሰውየው በመጨረሻ ለብዙ አመታት ያስጨነቀውን ጥያቄ በመጠየቁ ደስተኛ ሆኖ ሞተ።

ውድ ባል ትንፋሹ ፀጥ ካለ በኋላ ሚስትየው ቁና ቁና እየተነፈሰች "ፈጣሪ ይመስገን ስለ ሶስት ታላላቆች አልጠየቀኝም" 🤦🏼‍♀


ባለቅኔ ነበርኩ
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!

ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።

ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?

ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥

ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?

እውነት!

ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።

ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ

ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።

Red-8


አንዳንድ ነገሮችን መቀየር አልችልም።ለምሳሌ አንቺን ማፍቀሬ ስዕተት መሆንን እያወኩ እንኳን ፍቅሬን ማስቆም አልቻልኩም ነበር።ምክንያቱም ከባዷ እጣፋንታዬ በአንቺ ህይወት መካካል አቅም-አጥታ ወደቃ ነበር.......

ጓደኞቼ ጠየቁኝ.....ቤተሰቦቼም በደምብ ጠየቁኝ....ሁሉም ወዳጆቼ የምር እንዳፈቀርኩ ማመን ፈልገው ነበር......ያ ዝምተኛው ሰው፤ያ ከክፍሉ የማይወጣው ሰው፤ያ አይናፋሩና ሴቶችን ማውራት በጣም የሚከብደው ሰው ያፈቅራል ብለው አላሰቡም ነበር።

ግን የሆንኩትን የማውቀውና የምረዳው እኔ ብቻ ነበርኩ።ማንም ሰው ማፍቅር ስለፈለገና ስላልፈለገ እንደማያፈቅር ተረድቻለው።በሌሎች ማፍቀር የሚስቀው ሁሉ ነገ እሱም ተረኛ እንደሆነ አውቂያለው።ፍቅር ባልጠበቅነውና ባላሰብነው ጊዜ የሚመጣ ከባድ ነገር መሆኑንም በደምብ ተገንዝቢያለው......ስለዚህ ፍቅር ወደደንም ጠላንም እኛ ስለፈለግንና ስላልፈለግን የሚሆን ሳይሆን እንደ ድንገት የሚከሰት ምትሃታዊ ሀይል ነው።

(ከአንቺ ፍቅር እንደማይዘኝ ያጣጣልኩት እኔ አንቺን ያፈቀርኩበት የማይታመን ጊዜ)

(Unreal)
✍️ Bemni Alex

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.