ሐሽማል ቤተ-መዘክር


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Kitoblar


👉Only for readers
👋መግቢያ👋
መግቢያ ለመግባቢያ
ገታ አርገነዋል የቃላትን ግልቢያ
እናም በዚህ ሀሳብ ከተስማማህበት
ያንኳኳኸዉን በር የገለፅከዉን ገፅ ፈቅደናል ግባበት
ምንጭ - ካልታወቀ ገጣሚ
Join the group
@amharicbooksforeadersgroup
አድሚኑን በ ቀጥታ ለማናገር ይህንን ቦት ተጠቀሙ @Digitallibraryofhashmal_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri




ስንቶቻችን እኮ ነገን ለመኖር ብለን ስንት ዛሬዎችን የሞትን ፤ ነገ ለመብላት ስንት ዛሬ የተራብን ፤ ነገ ለመልበስ ስንት ዛሬዎች በቀዳዳ ሱሪ የተሳቀብን ....ግን ከነገ በፊት ለሚገጥመን ሞት ግድ ያልሰጠን ሰለ ነገ የምናለቅስ ...ቅዠታሞች


HENOK


"አዕምሮ ህጻን ነው!"
short story



"እንኳን ለዚህ አበቃህ" አለው ጋዜጠኛው።

"ባልድን ይሻለኝ ነበር" አለው የቀድሞ ታማሚ

ደነገጠ ጋዜጠኛው "ምነው?"

"ከአማኑኤል ስወጣ ሀገሩ ከኛ ጊቢ ብሷል። ሙሉ ከተማው በዘነጡ ታማሚዎች ተሞልቷል።"

ጋዜጠኛው መለሰ
" አንተ የምትለው ነገር ግን የለም። ሰው ለመኖር እየጣረ ነው። ተስፈኛ ነው። ደስተኛ ነው። ጠያቂ ነው ትውልዱ አለው።"

"ሲመለስልህ የምትረዳበት ልብ ሳይኖርህ መጠየቅ ምን ጥቅም?"

ጋዜጠኛው
"እንደምታየው እንደሀገርም እንደግለሰብም ሁሉም የሚፈልገውን ነገር ለማሳካት እየሞከረ ነው።"

" ለምንድነው የምትፈልገውን ነገር ሁሉ የምታገኘው።የምትፈልገውን ባታገኝስ ምን ልትሆን?"

ጋዜጠኛው ግራ ተጋባ።


የዳነው ሰው ወደጋዜጠኛው ጆሮ ተጠጋ።

"ሁሉም ያሰበውን ካላገኘሁ ብሎ መክለፍለፍ ላን ነው። ስማ አዕምሮ እኮ ህጻን ነው።
የጠየቀው ሁሉ አይሰጠውም።
ልጅ ነው አዕምሮ
ላለው ነገር ሁሉ መልስ አይመለስም።"

ቀጠለ

"ታውቃለህ ትልቅ ነኝ ብሎ የሚያስብ ግን የፈለገውን ሲከለክሉት የሚያኮርፍ ፍጡር ነው አዕምሮ።
ከሰውነት ክፍላችን አብዝቶ ስለራሱ ብዙ የጻፈው ያሰበው የተመራመረው አዕምሮ ብቻ ነው።
እንደሚያውቅ ለማሳወቅ መከራውን ያያል። አታውቅም ሲሉት ክብሬ ተነካ ብሎ ይጋጫል።

ህጻን ነው አዕምሮ።
ማግኘትን ብቻ ማጣትንም አለማምዱት እንጂ።"

ጋዜጠኛው
"እንደዛማ ከሆነ ደስታ የሌለው ህይወት ነዋ ሚሆነው"

ደስታ ምንድነው አለው

ጋዜጠኛው ቀላል ጥያቄ መስሎት ሊያወራ ሲል ቃል አጣ።

"ንገረኛ ደስታ ምንድነው?"

ቃለመጠይቁ ከተቋረጠ 10 አመት አለፈው።

~ ~ ~ ~ ~ ~
ኤልያስ ሽታኹን

856 0 15 1 21





ይፈውሰኛል ያልከው ሰው ቁስልህ ላይ ጨው ሲነሰንስበት እንደማየት የሚያም ነገር የለም....የቆሰለው ሰውነትህ አቅምህን ከተጫነው በላይ....ከፈሰሰው ደምህ በላይ የሚፈሰው እንባህ ያቃጥልሀል...."....ማውራቷን ቀጥላለች...


"ከዛ በኃላ ሁሉም ነገር ይታክትሀል...ማውራት ብቻ ትልቅ ዳገት ይሆንብሀል....ማውራት...እንዲህ ሆንኩ ማለት ትርፍ የሌለው ነገር ይሆንብሀል....በቃ ዝምም...በራስህ አለም ውስጥ ጭጭጭ....የራስህ ዋሻ ውስጥ ዘግተህ ትቀመጣለህ..."


"እኔ ነኝ አይደል እንደዚህ ያደረግኩት...?"....በሆዴ አይ አንተ አይደለህም እንድትለኝ እየተመኘሁ በአፌ ይቺን ጠየቅኩ....

"አንተ አይደለህም...."....ኡፎፎፎፎፎይ አልኩኝ በሆዴ....ቀጠለች....

"ጊዜ ነው....ጊዜ ነው አንተ ላይ የጣለኝ....ጊዜ ነው እንደ ፌስታል አሳስቶ የሚያንኮሻኩሸኝ....እሱ ነው...".....ያረጋጋሁት ልቤ በቅፅበት በፀፀት ይነድብኝ ጀመር....እንደድሮ አይደለችም...እንደድሮ የሁሉም ሰው ፊት ላይ ሳቅ ለመፍጠር አትጣጣርም....አይኔን በጥልቀት አታይም...አይኗን ምታሳርፍበት አጥታለች...አንዴ ሰማዩን አንዴ መሬቱን ታያለች....

"ከማልሞግተው ጋር ተጣላሁ...ጊዜን ምን ብለህ ትሞግተዋለህ.....እንዲሁ ቶሎ እለፍ እስኪ ትለው ይሆናል እንጂ "....

✍Shewit


ልጅነቷ ያሳዝናል ...

እኔ ትልቅ ሆኜ ነው ? እሷ ትንሽ ሆና ?
መጠርጠር አታውቅም። አማራጭ ያለው ሰው ክፉ ሊሆን የሚችል አይመስላትም ?

ሳቅፋት የልብ ምቷ ይሰማኛል...

ስስማት ፊቷ ይግላል ? ሳከብራት ብርቅ ይሆንባታል፥ ስጠራት በቶሎ ነው የምትመጣው፥ ስደውላልት ስልኳ ሁለቴ እንኳን እስኪጠራ አትታገሰም።

መጠርጠር አታውቅም። ተራራ ጫፍ ጀርባዋን ሰጥታኝ ከፊት ክፉ እንዳያገኛት አድፍጣ ትጠረጥራለች..

ቆንጆ ነች፣ እርጋታዋ ደስ ይላል ...

የዓለም ክፋት አልበላትም ...

ለካ

አትሆነኝም ብሎ ከመተው፤ አልሆናትም ብሎ መተው ውስጥ ፅድቅ አለ መሰለኝ !

ተውኳት !!
©Adhanom Mitiku


"የሚፈልጉትን አይፈልጉትም "
short story




ግልጽ ሰው እወዳለሁ አለችው

ህይወቱን ግልጽ ነገራት ጠላችው

ቀላል ሰው ደስ ይለኛል አለችው

ቀለል ሲል ረከሰባት ሸሸችው

ኩሩ ሰው ምርጫዬ ነው ስትለው ኮራ አለ

ጠበርክ ብላው ሄደች።

የተረጋጋ ሰው እወዳለሁ አለችው

ሲረጋጋ ተንቀራፈፍቅ ብላው ሄደች

የማይጨቃጨቅ ሰው ነው ምርጫዬ አለች

ስህተቷን ሲያልፋት ባትወደኝ ነው ግድ ያለሰጠህ አለችው

አስሬ መገናኘት መደዋወል ምናምን አልወድም አልችው።

መደወሉን ሲቀንስ ብትፈልገኝ ኖሮ ይሄንንም ብልህ ገፍተህ ትመጣ ትደውል ነበር። በቃኸኝ አለችው።


ምን እንዳጠፋ አሰበ።

እስካሁን አልገባውም።

ለአባቱ ነገረው ሁሉንም። አባቱ መለሰለት።

"ሰው ወዳለሁ ያለው ሁሉ አይኮንለትም።

ያለውን ሁሉ የምደረግለት ለአምላክህ ነው።

ሰው እኮ የፈለገውን ነገር ገና መፈለጉን አርግጠኛ አደለም።

የሚወደውን ነገር ለይቶ ያልጨረሰ ፍጡር ነው።

በተለይ እነሱ ወጣቶቹ የሚፈልጉትን ራሱ በቅጡ አይፈልጉትም"

"ምን ልሁንላት?"

"ራስህን ሁንላት!
የምትልህን ትተህ የማትልህን ሁንላት።
ሴቶች ከንግግራቸው ጋ ሩቅ ናቸው።
ያሉህን ትተህ ያላሉህን ስማቸው"

የልጁ ስልክ ጮኸ። እሷ ናት።

~ ~ ~ ~ ~ ~

ኤልያስ ሽታኹን




"... ብራሶል አስቀድሞ በእርዳታ ድርጅቶች እጅ ኢትዮጵያን ሲሰልል ነበር። ስለላ ማለት ለግል ጥቅሙ እንጂ ፣ ለሀገሩ ሩሲያ ጥቅም አይደለም። ብራሶል የሚያቀርበው የጠብመንጃ ሽያጭ ሲሆን ፣ እስካሁን በዞረበት ሀገር ሁሉ ለግሉ የሚሰልለው ማዕድናትን ነው። አንድ ሀገር የእርሱ ዓይን ያርፍባት ዘንድ ብዙ ማዕድናት እንዳላት ማወቅ አለበት። የብራሶል አመለካከት እንዲህ ነው። ዓለም ውስጥ ያሉ መንግሥታት በሙሉ ማሳያዎች ናቸው። በህዝብ የተመረጡ ወይም በህዝብ ሳይመረጡ የወጡ ህጋዊ ማፍያዎች። እኛ ከዚህ የምንለየው ህጋዊ አለመሆናችን ብቻ ነው። ፖለቲካ በሚሉት የውሸት አብዮት ፣ ህዝቡን ስለማናታልል ነው።" ይላል ሁልጊዜም።

                ~ከመጽሀፉ የተወሰደ

🌟 ዛምራ የተሰኘው መፀሀፌን ምን ያክሎቻችሁ አንብባችሁታል?

@yismakeworku


@official_elias_shitahun

ኤልያሴ ለናፈቃችሁ የኤልያስ ሽታሁንተማሪ መሆን የምትፈልጉየ ሁለት ወር ኮርስ በ አካል እና በOnlineአዘጋጅቷል በዚህ ስልክ 09 5216 84 29 ደውሉ@malefiatraining


✅ባሻዬ! የትንሽነትና የዘረኝነት መንፈስ ውሻ ነው። ከሮጥክለት ይከተልሃል። በተለይ የበታችነት መንፈስ (Inferiority complex) አደገኛ ነው። ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ባልችልም አልበርት አንስታይን "የበታችነት መንፈስ ከተሰማህ ዛፍ ላይ ውጣ" ይላል። እኔ ግን እልሃለሁ እንኳን ዛፍ ላይ ይቅርና የንግድ ባንክ አዲሱ ፎቅ ላይ ብትወጣ የበታችነት ስሜትን ማጥፋት አትችልም።

ባሻዬ! ስለ ትንሽነት ስነ ልቦና በዚች ጨዋታ ላዋዛልህ፣

አህያና ፈረስ ተገናኙና ማውራት ጀመሩ። አህያው ፈረሱን ጠየቀው

"ሥራህ ምንድነው?"

"ስፖርተኛ ነኝ። በፈረስ ግልቢያ፣ በፈረስ ጉግስና የመሰናክል ዝላይ ብዙ ዋንጫዎችና ሜዳሊያዎችን ተሸልሜያለሁ"

አህያው ይሄንን ሲሰማ ከፍተኛ የመንፈስ ቅናት ተሰማው። የተሰማውን የበታችነት ስሜት ለመደበቅ ሲል በቀጣዩ ሣምንት ፈረሱን በቤቱ ምሳ ሊጋብዘው ቀጠረው።

የቀጠሮው ቀን ሲደርስ አህያው ፈረሱን ሊያስደምመው ፈለገና ሁለት የሜዳ አህያ (ዜብራ) ፎቶ ገዛና ቤቱ ግድግዳ ላይ ሰቀለ።

ፈረሱ አህያው ቤት ገባና ዙሪያውን ተመልክቶ ጠየቀው፣

"ቤትህ ያምራል። እነዚያ ሁለት ፎቶዎች ላይ የሚታዩት ዜብራዎች እነማን ናቸው?"

✅"አልነገርኩህም ለካ! እኔም እኮ እንዳንተ ስፖርተኛ ነኝ። ፎቶዎቹ የኔ ናቸው። አንደኛው ባለፈው ሲዝን ለጁቬንቱስ ስጫወት የተነሳሁት ነው። ሁለተኛው አሁን ለኒው ካስትል ስጫወት የተነሳሁት ነው። እንዲያውም ነገ ከሊቨርፑል ጋር የካራባእ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ እሰለፋለሁ

"Tesfaye H/Mariam


#Alert@amharicbooksforeaders Eliyas Shetahun Author and poet will be in malefiya training center this Sunday 9 lt




ይደክማታል!

"የኔ ማር" ይላታል
"ወዬ" ትለዋለች ሰፍ ብላ
"ታላቁ ራሽያዊ የብዝሀህይወት ባለሙያ ኢቫኖቪች ሎቭኮቭ ገነት የነበረችው ኤስያ ውስጥ ሳይሆን አይቀርም ምክንያቱም የመጀመሪያው አፕል የበቀለው እዚያ አካባቢ ስለሆነ ይላል..."

ይደክማታል! ማይመለከታትን ነገር ሲያወራት  'ምን አይነቱ ሞኝ ነው በሞቴ' ትላለች በውስጧ። ተነስታ ጥላው ለመሄድ ያሰኛታል ግን ደግሞ ትወደዋለች። ዝም ብላ ታየዋለች ይቀጥላል ወሬውን

"... እኔ ግን በእሱ ሀሳብ አልስማማም። ለምን አልሽኝ? ምክንያቱም ለእኔ ገነት ያለችው ሩቅ ሳይሆን እዚሁ አንቺ ከንፈር ላይ ነው"
አሁን ተሳበች.. ሙሉ ሰውነቷን ለንግግሩ ሰጠች
"ተው ባክህ?" እንደማፈር እየሞከራት
"አዎ ካላመንሽኝ..." ይጠጋታል ይጠጋታል ይጠጋታል ትታገሰዋለች እስኪደርስ ይርቅባታል ትንሽ ሲቀረው

"የኔ ማር"
"ወዬ" እየተናደደች
"ከሰውነታችን ጠንካራው ጡንቻ የቱ እንደሆነ ታውቂያለሽ?"

ይደክማታል! በረ.........ጅሙ ተንፍሳም አይቀላትም! ይቀጥላል አሁንም
"ምላስ ነው" ብቻውን ያወራል... ብቻዋን ትነጉዳለች
ድንገት አቋረጠችው
"እኔ እምልህ"
"እ"
"ለምን 'አርዳ' ተባልክ"
"ነግሬሽ የለ አባቴ ቱርካዊ ነው ብየ  እሱ ነው ያወጣልህ ብለውኛል"
"ታዲያ ይሄ'ኮ በቂ መልስ አይደለም አባትህን ለምን 'አርዳ' አልከኝ አላልከውም?"
"ትልቅ ከሆንኩ በኋላ ነው አባቴን ያገኘሁትኮ"
"እና አልጠየቅከውም?"
"ተርኪኛ አልችልማ" በራሱ ቀልድ ይስቃል  አብራው መሳቅ ይኑርባት አይኑርባት ግራ ይገባታል። የምር ይሄ ቀልድ ነው? ትላለች ለራሷ

ዝም ብላ ታፈጥበታለች ማውራቱን ቀጥሏል። ይሄኔ 3 ርዕስ አንስቶ አምስት ደግሞ ጥሎ ይሆናል። ትወደዋለች። ግን ምኑን እንደሆነ ግራ ይገባታል። ምኑ አምሮኝ ይሆን ግን ተስቤ የቀረሁት? ሉጫ ፀጉሩ አይሆንም መቼስ!
ድንገት ቀኝ ጉንጯን ሳማት ደንግጣ አየችው
ምንም እንዳልተፈጠረ ስለ አንድ ግሪካዊ ፈላስፋ ማውራት ጀመረ...  'ያመዋል እንዴ?' ትላለች ለራሷ

"የኔ ማር"
"ወዬ" ትለዋለች አሁንም ጓጉታ
"ግሪኮች ግን አይገርሙም?"

ይደክማታል!  ተነስቼ ጥየው ልሂድ ወይስ ምን ላርግ እያለች ትምታታለች። መወሰን አለብኝ ጎኑ ሆኜም እንዳለሁ አይሰማውም! እንዲህ እንዳልል ደግሞ ለእኔ ብሎ ነው ያንንም ይሄንንም እያነሳ ሚያወራኝ... ትምታታለች። ያምታታታል! ይደክማታል!

"የኔ ማር" ይላታል
"ወዬ" ትለዋለች  የተለየ ነገር እንደማይላት እያወቀችም መጓጓቷ ራሷን ያስገርማታል
"ዴዝዴሞናን ታውቂያታለሽ?"
"ኦቴሎ ላይ ያለችውን ከሆነ አዎ!"
"ሞናሊዛንስ?"
"አዎ"
"አያምሩም?"
በተሰላቸ መልክ በትክሻዋ 'እኔእንጃ' ትለዋለች።
"ለእኔ ግን አንቺ ከነሱ በላይ ውብ ነሽ! እነሱኮ ሼክስፒር እና ዳቪንቺ ምናብ ውስጥ የቀሩ ማይጨበጡ ቆንጆዎች ናቸው። አንቺ ግን ድንቅ እና ምርጥ የእግዜር ስራ"
ደስ ይላታል እንዲ ሲያወራት.. ሌላ ነገር እንዳያስብ ተመኘች
"የፀሀየ ዮሐንስ ዘፈን ላይም አለ ይሄ" አለችው
"ምን ሚለው?"
"በአለም አይገኝም አንቺን የሚመስል
ዴዝዴሞናም ታሪክ ሞናሊዛም ስዕል"
"ሀሳብ ግን አይገርምሽም? በተለያየ ሰአት እና ቦታ ሆነን እኔም ፀሀየም ይሄን ማሰባችን..."
አጠፋሁ ትላለች ለራሷ

"የኔ ማር"
"ወዬ"
"ሀሳብ ግን ላንቺ ምንድን ነው? ለእኔ ሀሳብ..."

ይደክማታል! መሄድ ያሰኛታል
'መጨከን አለብኝ  መሄድ አለብኝ! አዎ መብሰል ይቀረዋል።' ትላለች መጨከን ደሞ ይከብዳታል። ይደክማታል!

ከራሷ ጋር እልህ ትጋባለች! እስከ 3 ቆጥሬ እነሳለሁ ትላለች።

1.... የምሬን ነው መሄድ ያለብኝ። አሁን ከሄድኩ መመለስ ብሎ ነገር የለም  በቃኝ!

2.... ግንኮ አርዳ ጥሩ ሰው ነው። እንደሱ የሚሆንልኝ አላገኝም። እንደው ዝም ብየኮ ነው።

2... ( አውቃ እንደደገመችው ታውቋታል!) ግን ቢሆንም በቃ መሄድ አለብኝ። እሱጋ እንዲኖረኝ የምፈልገውን ያህል ቦታ አልሰጠኝም።

ሶስ...

"የኔ ማር" ይላታል...  ድንገት ያሰበችው ፣ የተነተነችው ፣ ያሰለፈችው ነገር ሁሉ ብትንትኑ ሲወጣ ይታወቃታል

"ወዬ"
"በቃ የሚጠብቁኝ ሰዎች ስላሉ እኔ ልሂድ.. አንቺም ብቻሽን ብዙ አትቆይ እዚህ " ብሎ ግንባሯን እና ጉንጯን በስሱ ሳም አርጓት ይሄዳል።

ይደክማታል!
ለራሷ ይሄን አለችው።
እንደውም አልሄድም!😡



                 በአቤኒ የተጻፈ✒️✒️


(🤗እኔ-"ዮዳA"ወድጄዋለሁ 👌 አቤኒ ይችላል ! ) https://t.me/danutell




Eneho Books እነሆ መጻሕፍት dan repost
ዓለማየሁ ዋሴ
በቅርብ ቀን ገበያ ላይ የሚውል መጽሐፍ
ፍካሬ


ልክ እንደ ወተት ጥርስ የነቀልነው ወተት ልብ ኖሮን ይሆን እንዴ ጥላቻችን መስመር ያለፈው .. እላለሁ አንዳንዴ

ፍቅር አናውቅም ጥላቻ በደማችን እንደገባ አንድያ ነገር ያንገበግበናል ..

✍️ሔኖክ





20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.