ለዐይነ ሰውራን ተማሪዎች መሠረታዊ የኮምፕውተር ሥልጠና እየተሰጠ ነውየአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዩች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በዩኒቨርሲቲው ጫሞ ካምፓስ ለሚገኙ ዐይነ ሰውር ተማሪዎች መሠረታዊ የኮምፕውተር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዩች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ሰናይት ሳህሌ ሥልጠናው የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል በትምህርታቸው ይበለጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ጽ/ቤታቸው ለተማሪዎቹ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ሁሉ ከጎናቸው እንደሚሆንም አረጋግጠዋል፡፡
በቦንጋ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ትምህርት ክፍል መምህርና አሰልጣኝ ታደለ ታፈሰ ሥልጠናው በዋናነት የዐይነ ስውራን ተማሪዎችን የዲጂታል ሊተረሲ ዕውቀትና ክሂሎት ለማሳደግ የተዘጋጀ ሲሆን ተማሪዎች ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ በማድረግ ኮርሶችን በኦንላይን እንዲከታተሉ የሚያስችል ነው፡፡ በሥልጠናው ተማሪዎች ዐይነ ሰውራንን በኮምፕውተር አጠቃቀም ላይ የሚያግዙ የተለያዩ ሶፍትዌሮች አጠቃቀምን የሚሠለጥኑ መሆኑን የገለጹት አሰልጣኙ የኢሜይል አጠቃቀም፣ የፓውር ፖይነት አዘገጃጀትና ሌሎች ጉዳዮችም በሥልጠናው ይዳሰሳሉ ብለዋል፡፡
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!
ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-
ድረ-ገጽ -
https://www.amu.edu.et/ቴሌግራም -
https://t.me/arbaminch_universityፌስቡክ -
https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/ዩቲዩብ -
https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVAየሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት