Postlar filtri


ማስታወቂያ

የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና እና ምዝገባ ቀናት    የተራዘሙ መሆኑን ስለማሳወቅ


በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጋቢት 01/2017 መጠናቀቁ እና ፈተናው መጋቢት 05/2017 ከ3፡00 ጀምሮ  እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል።  ይሁን እንጂ በአንዳንድ ተፈታኞች ጥያቄ መሰረት ምዝገባው እስከ መጋቢት 04/2017 ዓ.ም እስከ ምሽቱ 12:00 የተራዘመ ሲሆን ፈተናው ደግሞ መጋቢት 12/2017 ከ3:00 ጀምሮ ይሰጣል።


በዚሁ መሰረት በተለያየ ምክንያት ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች ምዝገባችሁን ቀደም ሲል በተገለጸው ሊንክ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ፈተናውን ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት ተገኝታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡


ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3.  የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡


ማስታወቂያ

ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና እና ምዝገባ ቀናት የተራዘሙ መሆኑን ስለማሳወቅ

በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጋቢት 01/2017 መጠናቀቁ እና ፈተናው መጋቢት 05/2017 ከ3፡00 ጀምሮ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል። ይሁን እንጂ በአንዳንድ ተፈታኞች ጥያቄ መሰረት ምዝገባው እስከ መጋቢት 04/2017 ዓ.ም እስከ ምሽቱ 12:00 የተራዘመ ሲሆን ፈተናው ደግሞ መጋቢት 12/2017 ከ3:00 ጀምሮ ይሰጣል።

በዚሁ መሰረት በተለያየ ምክንያት ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች ምዝገባችሁን ቀደም ሲል በተገለጸው ሊንክ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ፈተናውን ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት ተገኝታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡




#በመካሄድላይ

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ114ኛ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረውን ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ( ማርች 8) ‹‹ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል›› በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ይገኛል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ኢ/ር አብደላ ከማልን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች፣ መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞችና ተማሪዎች ተሳትፈዋል ፡፡




ለዐይነ ሰውራን ተማሪዎች መሠረታዊ የኮምፕውተር ሥልጠና እየተሰጠ ነው

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዩች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት በዩኒቨርሲቲው ጫሞ ካምፓስ ለሚገኙ ዐይነ ሰውር ተማሪዎች መሠረታዊ የኮምፕውተር ሥልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳዩች አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ሰናይት ሳህሌ ሥልጠናው የተማሪዎችን የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል በትምህርታቸው ይበለጥ ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣይም ጽ/ቤታቸው ለተማሪዎቹ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ሁሉ ከጎናቸው እንደሚሆንም አረጋግጠዋል፡፡

በቦንጋ ዩኒቨርስቲ ዓለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ትምህርት ክፍል መምህርና አሰልጣኝ ታደለ ታፈሰ ሥልጠናው በዋናነት የዐይነ ስውራን ተማሪዎችን የዲጂታል ሊተረሲ ዕውቀትና ክሂሎት ለማሳደግ የተዘጋጀ ሲሆን ተማሪዎች ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር እንዲተዋወቁ በማድረግ ኮርሶችን በኦንላይን እንዲከታተሉ የሚያስችል ነው፡፡ በሥልጠናው ተማሪዎች ዐይነ ሰውራንን በኮምፕውተር አጠቃቀም ላይ የሚያግዙ የተለያዩ ሶፍትዌሮች አጠቃቀምን የሚሠለጥኑ መሆኑን የገለጹት አሰልጣኙ የኢሜይል አጠቃቀም፣ የፓውር ፖይነት አዘገጃጀትና ሌሎች ጉዳዮችም በሥልጠናው ይዳሰሳሉ ብለዋል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
የብሩህ ተስፋ ማዕከል!

ለተጨማሪ መረጃ በድረ-ገጽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችን ይከተሉን፡-

ድረ-ገጽ - https://www.amu.edu.et/
ቴሌግራም - https://t.me/arbaminch_university
ፌስቡክ - https://www.facebook.com/ArbaMinchUniversityccd/
ዩቲዩብ - https://www.youtube.com/channel/UCOO_nclhMo8M3r74OyPBlVA

የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት



7 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.