Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል ከጀግኖች ከእነ ተፈራ ዳምጤ ፣ ከእነ መዝገቡ ዋለልኝ ፣ ከእነ ሐብታሙ ሁነኛው ፣ ከእነ መንበሩ ጌታዬ የትግል ሜዳ ከአናብስቶቹ ምድር ከመብረቁ ብርጌድ አባላት ጋር አሳልፈናል ።
ካደረግነው ረጅም ንግግር በአጭሩ

ክብር ለሰማዕታት !
ድል ለጀግናው አማራ !!


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


ዘመቻ አንድነት ወሎ ቤተ-አማራ ግንባር

አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ንጉስ ሚካኤል ኮር መብረቅ ክ/ጦር ከሚያዚያ 10/2017 ዓ.ም ጀምሮ ከባድ ትንቅንቅና ውጊያ ላይ ናቸው:: ውጊያው አሁንም እንደቀጠለ ነው::

አብይ አህመድ ጠንካራ የአማራ ፋኖ አለ በሚባልባቸው አካባቢዎች ያለ የለለ ሀይሉን በመጠቀም እሱ  ፋኖ የሚላቸውን ብቻ ሳይሆን ሙሉ የ አማራን ሕዝብ ጭምር ለማጥፋት በተነሳው መሰረት ለወግዲ ወረዳ ብቻ ከሰላሳ በላይ ካሶኒ ትራክ እና በህዝብ ማመላለሻ ባሶች ጭኖ በመግባት አለኝ የሚለውን መሳሪያ በመጠቀም ( ዙ 23 ፣ 107 ( መቶ ሰባት ) ፣በርካታ ሞርትሮች እና ድሮን ጭምር እያንዣበበ የደመነፍስ ጥረቱን ጀምሯል ።

በዚህም አርብ ስቅለት ስግደት ላይ የነበሩ ምዕመናን የጉባ ቦር ቦር ማሪያም ቤተ ክርስቲያን ላይ ሞርተር በመተኮስ 4 (አራት ) ሲገል የቆስሉ ብዙ እንዳሉም ነው:: በተመሳሳይ ደራ (ሸዋ ) በተባለው አካበቢ ጄኔራል መድፍ በመተኮስ ልዩ ቦታው ወይናያ የተባለ ቦታ ሶስት የገበሬ ቤቶች ሙሉ በሙሉ አውድማል ::
ነገር ግን አይበገሬዎቹ መበርቆቹ ጠላትን ሥቦ በማስገባት በማጥቃት ጠላት ላይ ከባድ ቁሳዊ ፣ ሞራላዊ እና ሰብአዊ ጉዳት አድርሰውበታል።

ከሚያዚያ 10 2017 ዓ.ም  ጀምሮ ወጊያው እንደቀጠለ
ሲሆን ከጠላት በኩል የደረሰ ኪሳራ (3) ሶስት የብልፅግና አጨብጫቢ የነበሩ ሚኒሻ ከነ ወዳኛው የተኙ ሲሆን የሶስቱም 3 (ሶስት ) ኮፍ ክለሽ እና ሙሉ ትጥቃቸው ፣ 6 (ስድስት ) ከባድ ቁስለኛ ሚኒሻ እንድሁም የአብይ አህመድ አራዊት 23 አባላት እስከወዳኛው ተሸኝተዋል:: ከሰባት በላይ እንቡላንስ ቁስለኛ ጭኖ ከፋኖ ከበባ ወደ ሆስፒታል በማምለጥ ላይ እያለም በርካታ ሙትና ቁስለኛ ሰብስቧል።

በዚህም ብሰጨቱ ዱባ ላይ መሞት ፈረድ ነው ያለው ወንበር አስጠባቂ ዛሬም በፋሲካው ዕለት ከጠዋት ጀምሮ ዙ 23 እና ሞርተር በማስወንጨፍ በርካታ የግለሰብ ቤቶች አፈራርሷል:: ንስሮቹ ይህንን ሁሉ በመቋቋም ከባድ መሳሪያ ሳይቀር በመጋፈጥ በርካታ ሙትና ቁስለኛ አስታቅፈው ሸኝተዉታል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ በዘመቻ አንድነት ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ዘመቻ አንድነት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)
ሚያዚያ 12/2017 ዓ.ም


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል ከጀግኖች ከእነ ተፈራ ዳምጤ ፣ ከእነ መዝገቡ ዋለልኝ ፣ ከእነ ሐብታሙ ሁነኛው ፣ ከእነ መንበሩ ጌታዬ የትግል ሜዳ ከአናብስቶቹ ምድር ከመብረቁ ብርጌድ አባላት ጋር አሳልፈናል ።
ካደረግነው ረጅም ንግግር በአጭሩ

ክብር ለሰማዕታት !
ድል ለጀግናው አማራ !!




"የአማራ ፋኖ በጎጃም የአደረጃጀት መምሪያ"
ሚያዚያ 12/08/2017 ዓ.ም

አሁን በድል የከበሩ ሰመዓታትን እያሰብን
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::: አንቆዝምም!!
:::::::::::::::::

በመሰዋትነት የታጀበ ድልን ተቋማዊ ባህል እና ወታደራዊ ስነ ምግባር ካደረግነው ውለን አድረናል።

ለሀዘን የምንቀመጠው ጠላቶቻችን ድል አድርገን  የጋራ ነጻነታችን ባወጅን ማግስት በረራ ላይ 4ኪሎ ፊት ለፊት በመላው አማራ ምድር በክብር ለወደቁት እህት ወንድሞቻችን ገንብተን ከምናስመርቀው የዝክረ ሰመዓታት ሀውልት ስር ይሆናል!!!

ይህ የአዲሱ ትውልድ ቃል ኪዳን መሆኑንም መዝገቡ ዋለልኝን፣ተፈራ ዳምጤን ፣ጀንራል መንበሩ ጌታየን እና መሰል ሰመዓታትን ያፈራውን ግዙፉ መብረቁ ተፈራ ዳምጤ ብርጌድን ወደ ሌላ ግዳጅ  የሚገቡበትን ተቋማዊ አቅጣጫ ለማስቀመጥ በተገኘንበት መድረክ ማረጋገጥ ችለናል።!!!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!!

አርበኛ ስለሺ ከበደ




ልብን በሚያቀልጠው በረሀ ቁልቁል ይንደረደራሉ ጉልበትን ሸምቅቆ በሚዘው ውርጭ እንደ ሳንቃ የተገተረውን ተራራ ያለ መታከት ይምዘገዘጉታል፤ እግራቸው ሁሌም ይጓዛል ከመካከላቸው ሰውነቱን የሚያሳርፍ አይገኝም የትራንስፖርት አማራጭ በሌለው አስቸጋሪ መልከዓ ምድር 360° እየተሽከረከሩ ብርቱ ክንዳቸውን በጠላት ትክሻ ላይ በማሳረፍ 62 ግዳጆችን በብቃት ተወጠዋል ።

ቁራራት ላይ ቁመው ከተራራው ማዶ ቦረና መካነ ሰላምን አሻግረው ይመለከታሉ ፣ እንደ ቋያ በሚጋረፈው የሶማ በረሀን ተወዳጆተው እናርጅን አንጋጠው ይቃኛሉ፣ከምድርም ከሰማይም ውሀ ጠብ አይልም ለመጠጥ አይደለም ለመታጠቢያ እምብዛም የማያገለገሉትን የአባይና የጭየ ወንዝን በተሳሰሩ ተራራዎች ስር ተረማምደው የሚያገኟቸውን ይሁን እንጅ ተፈጥሮ ያሸከመቻቸው ን መከራ መጋፈጥ ግድ ሆነና እነዚያ የአሳ ፣ የአዞ፣ የጉማሬ መሽከርከሪያ የሆኑ ድፍርስ ወራጅ ወንዞችን ከከብቶች ጋር እየተጋፉ ይጎነጫሉ።

ቡናያም ዞባርም፣እነብሬም እሳላሞ፣አንሳም እነጉዚ ፣ደርጅ ባቄላየ የግሩ መረገጫ፤
ዶማ ላይሚካኤል ጠላትን መቅበሪያ አንገቱን መቁረጫ፤

መጠሪያቸው ግዙፍ ተልዕኳቸው ገደብ የለውም እና 24 ወራትን ማንም ባልተረዳው ውስብስብ የትግል ቀጠና መከራውን ሁሉ ተጋፍጠዋል ፤ብዙዎች ባልነቁበት የተጠላለፈ ሴራ አካባቢው በዶላር መንዛሪዎች ሲታመስ ከጎናቸው የተሰለፈ አንድም አልተገኘም ።ቦታቸው ወሳኝ ነው ኮሊደሩ እጅግ አስፈላጊ የትግል ስትራቴጂ ሜዳ በመሆኑ ከ30 ሚሊዬን እረብጣ ገንዘብ በላይ በማፍሰስ ጎጃምን ከወሎ የሚወስደውን መነገድ በማጠር ትግላችን ከፍ እንዳይል የተገነባው የጠላት ወጥመድን በብቃት በጣጥሰውታል።

ከሚያዚያ 12 - ሚያዚያ 12 በበዓለ ትንሳኤ ካሲናው አባይ ሸለቆ ብርጌድ በአርበኛ አስረስ ማረ ዳምጤ በ2015 ዓ.ም በግዙፉ የአባ ሚኒዎስ ተራራ ግርጌ ከተመሰረተ በኋላ የመጀመሪያው የጎጃሙ ብርጌድ ሁለተኛ አመቱን ዛሬ ደፈነ።

ከመካነ ሰላም -ቢቸና ከ መርጡለ ማርያም -ሞጣ ግንደወይንና ደብረወርቅን ጨምሮ ከ19 ጊዜ በላይ ግዳጆችን በብቃት በመወጣት የአባይ ሸለቆ ዘብነቱን አስመስክሯል።

ዛሬም ትናትም ከተልዕኮው ፈቀቅ ያላለው ካሲናው እስከ ዕለተ ፋሲካ ጥንቅቅ ያለ ፖለቲካዊም ወታደራዊ ድል የሚገኝበትን ትግል የማዳን ተልዕኮ በማንገብ በርሀብ ፣በውሀ ጥም፣በሙቀት፣እየተሰቃየ በጊንጥ እየተነደፈ ከመጋቢት 2 እስከ ሚያዚያ12 ለአለፉት 40 ቀንና ሌሊቶችን ተፈትኖ ለአማራ ህዝብ ትግል ትሩፋት ይሆን ዘንድ ክሩ ብርሀን ሁኖ እንዲበራ አባይ ሸለቆ ብርጌድ እራሱን ሰም አድርጎ ቀልጧል።

ሳይንትም እነብሴም፣ ቦረናም እናርጅም ፣ እነማይ ወግዲም አንድላይ ይምከሩ ፤
ጎጃምና ወሎ አባይ ላይ ይደሩ፤
ጀግናው የእነብሴ ልጅ አለ ደመ ኩሩ፤

በጎጃም ፀሀይ መውጫ የመጨረሻ ጫፍ፣በአማራ ሰማይ ስር እምብርት በሆነው ማዕከላዊ ቦታ መገኘቱንና ጊዜው በሚመጥነው ልክ ከፍ ብሎ ለመብረር የማያንቀላፋው ታሪካዊው ብርጌድ በዘመቻ አንድነት ከመካነሰላም አባይ ሸለቆ ብርጌድ ጋር በመጣመር የአባይን ወንዝ በጋራ እየተጎነጩ የእነብሴው የአባይ ሸለቆ ብርጌድ በዚህ ስኬት ውስጥ መረማመዱን በዚህ የሁለተኛ አመት የምስረታ ቀኑ እንደማየት እድለኝነት የለም።

24 ስዓት የሚብከነከኑ የብርጌዱ አመራሮች ወንድሞቸን ስቃይ ማየት የልብ ህመም ነው ፍፁም የማይዝሉ የማይረቱ ክንደ ብርቶዎች በፈተናዎች ሁሉ የፀኑ በእሳት ነበልባል ያልቀለጡ ወርቆች ለአለፉት ወራት ከብርጌዱ ከወጡ አመራሮች ውጭ አንድም በአማራ ፋኖ በጎጃም አመራር ያልተጎበኘ አንዳችም ድጋፍ ያልተደረገለት(የማያኮርፉ የማይቀየሙ) በሸለቆ ውስጥ የተረማመደው አብሪው ኮከብ አባይ ሸለቆ ብርጌድ የጎጃም ትግል ላይ የሚወረወረውን አለሎ ቀድሞ እየቀለመ እራሱን ፈክቶ በራሱ ደም ተለውሶ ወንድሞቹ እንዲፈረጥሙ ስብራቱን አስሮ የመረቀዘ ቁስሉን በዝንቦች እየተበላ ለአላማው ፈቅቅ ሳይል እንደ ክርስቶስ እራሱን አሳልፎ የሰጠ የማይበገር የእነብሴው ነበልባል የጎጃሞች ኩራት አባይ ሸለቆ ብርጌድ በደማቅ ቀለም ደምቆ የሚጻፍ ታሪክ ሰንዶ ይዟል።

የአባይ ሸንተራራማ ቦታዎች በተቆጣጠርን ማግስት ከእስክንድር ውጅሌዎች ማስታዎሻ የተገኘው ማስረጃ እንደሚያሳያው የአባይ ሸለቆ ብርጌድን ለመበተን እና ቀጠናውን ለመቆጣጠር በህዝብ ስም የተሰበሰበውን የዲያስፖራ ገንዘብ ከባህር ማዶ እስከ ጎጃም ያለውን የ11,000,000 (የአስራ አንድ ሚሊዬን) ብር ጉድና ኔትዎርክ በጊዜው ይፋ የምናደርግ ሁኖ ዓለት ተንተርሰው፣ጥሬ ቆርጥመው፣የጎርፍ ውሀ ጠጥተው በከፍታ እየተምዘገዘጉ ላሉት ወንድሞቸ ስሜቴን መቆጣጠር እያቃተኝ በወጣውበት ብርጌድ እጅግ ኩራት እየተሰማኝ በተበጣጠሰ ቃላት ይህንን ከተብኩ።

መልካም የትንሳኤ በዓል! መልካም ልደት ! ጓዶች እንበርታ!
ሚያዚያ 12/2017 ዓ.ም
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!

ባዬ ደስታ


አሸባሪዉ የብልፅግና ቡድን ንፁሀንን በመረሸን ገንዘባቸውን ዘረፈ

ትላንት ሚያዚያ 11/2017. ዓ/ም በትንሳኤ ዋዜማ አቶ አሻግሬ አሰጋ የተባለዉን የአፍራ ኪዳነምህረት ኑዋሪ አርሶ አደር በጥይት ደብድበዉ በግፍ በመረሸን በሬ ሽጦ የያዘዉን 60000 |ስልሳ ሺ| ብር የዘረፉት አዲስ ቅዳም ከተማ የተወሸቁ የሸባሪዉ የብልፅግና ቡድን ደም መጣጭ አራዊቶች
ዛሬ ሚያዝያ 12/2017 ዓ/ም በእለተ ትንሳኤ ከቀኑ 8:00 ስዓት አካባቢ ወጣት አበባዉ እያሴ የተባለን የከተማዋ ኑዋሪ ዘመድ ቤት ለበኣል ጥሪ በሄደበት የፋኖ ቤተሰብ ነህ በሚል ግቢ ዉስጥ በግፍ እረሽነዉታል።

ይህ በእናት ጡት ነካሽ ባንዳዎች ጌታቸዉ ታፈረ፣ ታገል እጅጉ፣ ምንተስኖት ሁነኛው፣ መሰረት በሌ፣ ነብዩ እና መሰሎቻቸዉ የሚዘወረዉ ፀረ አማራዉ የብልፅግና አራዊት ከዚህ ቀደም በትንሳኤ ማግስት ሚያዚያ 28/2016 ዓ/ም
ወጣት ጌትነት ታምር፣
ወጣት እንደሻዉ አያል ፣
ወጣት ባምላኩ ቸኮለ፣
ወጣት ፈንታሁን ዘገየ፣
ወ/ሮ ሙሉነሽ ፈንቴ የ6 ወር ነፍሰ ጡር፣
ወጣት አማረ ደስታ የሙሉነሽ ቤተሰብ፣
ወጣት ሀብታሙ |አገዉ| ካሬታ የሚገፋ፣
ወጣት አበባው አለሙን ጨምሮ በጠቅላላዉ 13 ንፁሀን የከተማዋ ኑዋሪዎችን ወጣቶችን በግፍ መጨፍጨፉ የሚታወስ ነዉ።

በፀረ አማራዉ የብልጽግና አሸባሪ ቡድን በግፍ የተጨፈጨፉ ወገኖቻችንን ነፍስ ፈጣሪ ይማርልን።

የወገኖቻችንን ደም በትግላችን እንመልሳለን።

አዲስ ትዉልድ፣
አዲስ አስተሳሰብ፣
አዲስ ተስፋ!!!

ፋኖ ተሻገር አደመ ከ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ ህ/ግንኙነት
ሚያዚያ 12/2017 ዓ/ም


የፋሽስቱ አብይ አህመድ ሰራዊት ጤና ጣቢያዎችን አወደመ።
የይልማና ዴንሳ ወረዳ አንጋር ጤና ጣቢያ በዚህ መልኩ አውድሞ እና ዘርፏል
ሚያዚያ 12/2017ዓ.ም


16000 ብር በግ በህዝብ ገንዘብ ገዝቶ ሊበላ ነጨ መሬት አካባቢ ወደ ውሽማው ቤት የሄደው ኮማንደር ካሳሁን በጉንም ሳይበላ በጀግናው አረንዛው ዳሞት ብርጌድ በራሪ ሀይሎች እስከነ አጃቢወቹ ወደማይመለስበት ተሸኝቷል።

12k 0 2 2 118



የአደረጃጀት መረጃ በዕለተ ፋሲካ!

ድርጅታችን ካሉት ግዙፍ ክፍለጦሮች አንዱ የሆነው 4ኛ ክፍለ ጦር የነበሩበትን ውስጣዊ ችግሮች የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር ጋሹ ክንዱ እና አርበኛ ምናልባት ይታየው በተገኙበት ጥልቅ ግምገማ ካደረገ በኋላ በዛሬው ዕለት የአመራር ሪፎርም በማደረግ አጠናቋል።
በዚህ መሰረት፦
1. ሰብሳቢ..........................ፋኖ ግርማው አየለ
2. ምክትል ሰብሳቢ...............ፋኖ አመሃ አይሸሽም
3. የጽህፈት ቤት ሀላፊ...........ፋኖ አደራጀው አድማስ
4. ህዝብ ግንኙነት.................ፋኖ ያዕቆብ ጌታሁን
5. ፓለቲካ ዘርፍ ሀላፊ.............ፋኖ አጃናው ስሜነህ
6. አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ.........ፋኖ ዳዊት አይችሌ
7. ፋይናንስ ሀላፊ....................ፋኖ ሸጋው አለም
8. ወታደራዊ አዛዥ................ፋኖ 50 አለቃ ተገኜ ደጀኔ
9. ምክትል ወታደራዊ አዛዥ........ፋኖ ሻለቃ ጌጡ አለሙ
10. ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ........... ፋኖ ቻሌ መንግስቴ
11. ም/ዘመቻ መምሪያ...............ፋኖ ሳሙኤል አታላይ
12. ሎጅስቲክ መምሪያ ሀላፊ...........ፋኖ ወርቁ አድባሩ
13. ስልጠና መምሪያ ሀላፊ.......ፋኖ ቻሌ አበበ
14. ኦርዲናንስ.........ፋኖ 10 አለቃ ሀብታሙ ይበልጣል
15. ጤና መምሪያ ሀላፊ.........ፋኖ ዶ/ር ይታየው ገበየሁ
16. ወታደራዊ አስተዳደር..........ፋኖ ጌትነት አበባው
17. የሰው ሃይል.......................ፋኖ ሻለቃ አዳነ በቀለ
18. ቀጠና ትስስር....................ፋኖ አወቀ ሞላ
19. መረጃና ደህንነት................xxxxxxx

በመሆን ተመድበዋል።

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ

[አማራ ፋኖ በጎጃም]
ሚያዝያ 12/2017 ዓ.ም


የአብይ የግል ጠባቂ መከላከያ እየከዳ ፋኖን መቀላቀል ቀጥሏል።
ሀዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለጦር - አብራጅት ብርጌድ






#ጉድ በል አማራ
ብልፅግና የራሱ ኮሌኔል በድሮን ደምስሻለሁ አለ‼

የራሳቸው የ73ኛ ክ/ጦር አዛዥ ኮ/ል ድባቤ የተባለ ተላላኪ በድ''ሮን ተመ''ቷል😂😂


ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮችና በየጫካው በየገደሉ የምትዋደቁ የፋኖ አባላት እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ።

ኢየሱስ ክርስቶስ ወገኖቹን አዳምን ከእነ የልጅ ልጆቹ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ለማውጣት  ወይም ለማዳን ለአዳም በገባው ቃል ኪዳን መሰረት በዕለተ አርብ ተገረፈ፣ተቸነከረ፣ተሰቀለ፣ሞተ፣ተገነዘ፣ተቀበረ።

ኢየሱስ ክርስቶስ ከስቅለቱ በኋላ አዳም ገብሩ ለዲያብሎስ ሄዋን አመቱ ለዲያብሎስ(አዳም የዲያብሎስ ባሪያው ነኝ ሄዋን የዲያብሎስ አገልጋዩ ነኝ) ብለው የፈረሙበትን የሞት ዕዳ ደብዳቤያቸውን ሻረላቸው(አጠፋላቸው)።  አይሁድም ኢየሱስን ከሰቀሉት በኋላ ከመስቀል አውርደው ቀበሩት ከቀበሩም በኋላ ከመቃብሩ ላይ ትልቅ ድንጋይ በመጫን የመቃብሩን ዙሪያ በአይሁድ ወታደር አሰጠበቁት። ኢየሱስም መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል በሀይሉ በስልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ ተነሳ። በባርነት ውስጥ የነበሩትን የአዳምን ልጆች በሙሉ ነጻ አወጣቸው፤ ከሞት ወደ ህይወት ተሸጋገሩ በአንድ ላይ ዘመሩ።

ፋሽስቱ አብይ አህመድ እና ግብረ አበሮቹ እነ ሽመልስ አብዲሳ አማራን አከርካሪውን ሰብረን  ቀብረነውል ቢሉም ዳሩ ግን አማራው በሀይሉና በስልጣኑ ማንንም አግዙኝ ሳይል እራሱን አደራጅቶ ከሞት ተነስቷል።

እነ አብይ አህመድ የአማራውን መቃብር ጠባቂ ብዙ ሽህ ሰራዊት አማራ ክልል ቢያስቀምጡም ዳሩ ግን አማራው መግነዝ ፍቱልኝ መቃብር ክፈቱልኝ ሳይል ተነስቷል። መቃብር ጠባቂዎች የአብይ ወታደሮችን በቆፈሩት ጉድጓድ ቀብሯቸዋል።

የተከበራችሁ በየጫካው እና በየገደሉ የምትገኙ የፋኖ አባላት ቀብረናቸዋል ያሉንን እራሳቸው በቆፈሩት ጉድጓድ ቀብረናቸዋል፣ አሁን ላይ ዕለተ አርብ ላይ እንገኛለን ትንሣኤውን ለማዬት ስቅለቱን መከራውን፣ ግርፋቱን፣ እራቡን፣ ጥሙን  አልፈን እሁድ መድረስ የግድ ይለናል።

ከጌታችን ከኢየሱስ የምንማረው ጽናትን፣ትግስትን፣ፍቅርን፣መከባበርን፣አንድነትን እንማራለን። ስለዚህ በመከባበር በመቻቻል አንድ በመሆን የአማራን ትንሣኤ ለማዬት ያብቃን።

በድጋሜ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!!

የቻለ አድማሱ የግዮን ብርጌድ ህ/ግ


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ዘመቻ አንድነት ቤተ-አማራ ግንባር

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ) ንጉሥ ሚካኤል ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክ/ጦር "በሻለቃ ጎሹ ታረቀኝ የሚመራው አትሮንስ ብርጌድ" እንደተለመደው በወራሪው ጠላት ላይ ድል ተቀዳጅቷል።
10/08/2017 ዓ.ም የሥልጣን ጠባቂው ጦር በቀበሮ ሜዳ፣ ጉዲት ተራራና ወጀድ መገንጠያ በሚባሉ ቦታዎች ላይ ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ ተጠዝጥዟል።ጠላት በሞርተር አካባቢውን እያናወፀው ቢውልም የአትሮንስ ብርጌድ ሠራዊት ሲያርበደብዱት ውለዋል።የኦህዴድ/ብልፅግናው ወራሪ ኃይል በሚያሳፍር ሁኔታ ሙት እና ቁስለኛን እያንጠባጠበ ሲሸሽና ሲቅበዘበዝ የወገን ጦር እየተከታተለ ሲያፍረከርከው ውሏል።የወራሪው ጠላት ሙታኖች በየጥሻው እንደወደቁ ቀርተዋል።
በውስጥ አርበኞች እንደተረጋገጠው የህክምና ማዕከሉም በቁስለኞች ተጨናንቋል።

ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ድል ለአማራ ሕዝብ!!!
ፋኖነት ይለምልም ወራሪው ጠላት ይውደም!!!
12/08/2017 ዓ.ም


ከአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት

ለመላው የክርስትና ዕምነት ተከታዮችና ለመላው የፋኖ ሰራዊታችን እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው አደረሳችሁ።

በተለያዩ ፈታኝ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ አመርቂ ድል እያስመዘገብን ባለበት በዚህ ጊዜ በአንድነትና በመተሳሰብ፣በመቻቻልና በማስተዋል፣በመደጋገፍና በትህትና፣የዕንከን ቋጠሮዎችን ፈተን አጠቃላይ ማህበረሰባዊ የመጥፋት አደጋ በመታደግ የሚቀጥለውን ዓመት ትንሳኤ ስናከብር ምድራዊ መከራውን ቀልብሰን እንዲሆን ከምኞት የዘለለ ገቢራዊ ርምጃ በመራመድ ጭምር ይሆናል።

የውስጥ ጉዳያችን የመፍቻ ቁልፍ "አንድነታችን" ነውና ለሁሉም የፋኖ ሰራዊት የአንድነት ጥሪ እናስተላልፋለን።

መልካም የትንሳኤ በዓል!
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
አፋአጎ

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.