Postlar filtri




ሰበር ዜና አቸፈር ወንድዬ !

የስርዓቱ አገልጋዮች ጭቃ ሆነዋል
በትላንትናዉ እለት ከሊበን ወደ ይስማላ ያቀናዉ የስርዓቱ አገልጋይ ይስማላ ከተማ ከገባ በሆላ የአፋጎ የጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር የቢትወደድ አያሌዉ መኮነንን ብርጌድ የአቤ ጉበኛ ሻለቃ ደፈጣ በመያዝ ጥቃት ስታደርስበት ይስማላ ከተማ በመግባት የማህበረሰቡን ሃብትና ንብረት ዘርፎ አንድ ሞተር ሳይክል ካቃጠለ በሆላ የወጣት ተሻገር ላየሁን የግል ቲወታ መኪና ቁልፍ በመስበር ዘርፎ 20 የሚሆኑ የስርዓቱ አገልጋይ ባንዳዎችን በመጫን ወደ ሊበን በመጎዝ ላይ እንዳለ መኪናዋ ተገልብጣ 4 ባንደዎች ወዲያዉኑ ሲሞቱ 1 እግሩ የተቆረጠ ሲሆን 15ቱ በሊበን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታ ቆስለዉ እየተረዱ ይገኛሉ ከነዚህም መካከል አንድ ከፍተኛ የአድማ ብተና አመራር እና የወረዳዉ ሚሊሻ ጽ/ቤት ሃላፊ ባንዳዉ #ግርማ የተባሉት ቆስለዉ በሆስፒታሉ ህክምና እየተደረገላቸዉ መሆኑን አረጋግጠናል

ይቀጥላል ገና

የብርጌዱ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ይበልጣል የዉነቱ ጀግናዉ


በእናረጅ እናውጋ ወረዳ አቶ አስራቱ ሙሉጌታ የተባለ ካድሬ ተገደለ!

በጎጃም እናረጅ እናውጋ ወረዳ ጎልውቅማ ቀበሌ አቶ አስራቱ ሙሉጌታ ቢሸው የተባለ ካድሬ መገደሉን መረብ ሚዲያ ከአማራ ፋኖ በጎጃም የበላይ ዘለቀ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

አቶ አስራቱ ከድርጊቱ እንዲቆጠብ ከዚህ ቀደም ተደጋጋሚ የሆነ ማሳሰቢያ ተሰጥቶት የነበረ ሲሆን ትናንት ጥር ጥር 27/2017 ዓ /ም በክፍለጦሩ ስር በሚገኙት በሶማ ብርጌድ አባላት መገደሉ ነው የታወቀው።

መረብ ሚዲያ




"በጅምላ ካፈሱን በኋላ ከእያንዳንዳችን 2 ሺህ ብር እየተቀበሉ ለቀቁን"
| የአዲስ አበባ ፖሊስ የደኅንነት ስጋት ትፈጥራላችኹ በሚል ጠርጥሬያቸዋለሁ ያላቸውን ነዋሪዎች በዘፈቀደ ካሠረ በኋላ በነፍስ ወከፍ 2 ሺሕ ብር እየተቀበለ እንደሚለቅ  ታስረው የተፈቱ የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። [ዋዜማ]




አልነጋለት ያለው ፈርጣጩ የአገዛዙ ሰራዊት በሌሊት ቢገሰግስም ፀሀይ ስትቀትር 2 (ሁለት) ሞርተር ፣4(አራት)ብሬን ፣ 2(ሁለት)ስናይፐር፣ 103(መቶ ሶስት ) ክላሽ  13 ሰራዊቱን በቁማቸው አሰረክቦ ፣82 (ሰማኒያ ሁለት) አስክሬን በመስታወት እና ማነቆ በር ተራራ አንጠባጥቦ ዕሮብ ገበያ ገባ ማምሻውንም ከሞት የተረፉ የሞርተር ምድብተኛ 20 አባላቱን ከተማ ውስጥ ረሸነ።
ማህበረሰቡ የወደቁ አስክሬኖችን ሰባስቦ በክብር በአካባቢው ቢቀብርም ከቀናት በኋላ መቃብሮች በጅብ እየተከፈቱ በተፈጠረው መጥፎ ሽታ በአካባቢው መንቀሳቀስ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን በቦታው ተገኝተን እኛም አይተናል የጠላት መቃብርና የተከፈቱ መቃብሮችን ተዘዋዉረን ጎብኝተናል።
የተቀመጥኩበትን እስከምረሳ ድረስ ተጋድሏቸውን እየተቀባበሉ የሚናገሩት ጀግኖቹ ኩራታቸው ከፊታቸው እየተነበበ አሁንም የማክቤልን አራት ቦንቦችን እንደ ዳዊት እየደጋገሙ ይናገሩ ነበር።
እኔም ከወንድሞቸ ጋር ጠላት የተንበረከከበትን ተራራ ፣ከጠላት የተማረኩ 3(ሶስት )ብሬኖችን ጎብኝቸ በጀግንነት ከተፋለሙ አይበገሬ የስናን አባ ጅሜ ብርጌድ አባላት ጋር ፎቶ ተነስተን ትዝታዎችን በስልኬ ሰንጀ ወደ ግዛታችን ተመለስን።
"የማክቤል 4(አራት)ቦንቦች "ይቀጥላል


"የማክቤል (4) አራት ቦንቦች"
ከጉዞ ማስታዎሻ የተወሰደ፦
የመዝገበ ጮቄ ብርጌድ የአንድነት ጉባኤን በአጠናቀቅን ማግስት የጮቄን ተራራ አቋርጠን የጀግኖች ምድር ወደሆነው የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክ/ጦር ግዛት በማምራት  ከደብረ ማርቆስ አናት ላይ መዳረሻችንን አድርገን ከንጉሥ ተክለ ኃይማኖት ብርጌድ አባላትና አመራሮች ጋር  ተወያይተን ልምድ ተለዋውጠናል ።
በጉዟችን መካከል የህዝባችን እንክብካቤ የለገሰን ፍቅር እጅጉን የሚያስደስት ነበር።
ከፋኖ ኢ/ር እስቲበል አለሙ ጋር የነበረን ጓዳዊ ፍቅር፣ውይይት፣የትግል ተሞክሮና ምክር ቀስመን ጉልበታችንን አድሰን በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክ/ጦር አሰራር ፣የሰራዊት አየያዝና አስተዳር፣የሰራዊቱን ስነ ምግባር ተመልክተን በእጅጉ ተደንቀናል።
ቀናትን በወሰደው ቆይታችን ብዙ ጉዳዮችን በመልካም ሁኔታ ተረድተናል፣ በጎነትን አትርፈናል፣ ለተደረገልን አቀባበል እንክብካቤ አመስግነን ወንድሞቻችን ተሰናብተን እኛም ወደ ግዛታችን ተመለስን።
"በጉዟችን መጀመሪያ በፍጥነት አቋርጠን የተራመድነውን የስናን ወረዳ ስንመለስ የተረገጥነውን መሬት ሁሉ በትኩረት እየቃኘን የመሬት አቀማመጡን፣መልካምድራዊ ይዘቱን፣የህዝቡን ስነ ልቦና ፣የጠላትን አቀማመጥ፣የጓዶቻችንን የትግል መስመርና ጀግንነት እያስተዋልን እንጓዝም ነበር።
ዕረቡ ገበያ ከተማን በቅርበት ከበው የተቀመጡት የስናን አባ ጅሜ ሻለቃዎች ቁርጠኝነት እጅግ ይገርማል።ጠላት አንድ ስንዝር ከምሽጉ በማይንቀሳቀስበት ደጋማው የጎጃም ክፍል የሆነው የስናን ወረዳ ሲሆን ጠላት ቀን ያለ ቀን ፣ሞርተር፣Bm፣እያስወነጨፈ የአርሶአደሩን ቂየ ይደበድባል ማህበረሰቡም ለምዶት በፍርሀቱ እየሳቁ ይዘባበቱበታል።ይህንና መሰል ጉዳዮች እያሰላሰልን ቀኑን አጋምሰን ማምሻውን መስተዋት ከሚባለው ቦታ ደረስን በቦታው ጀግና የአባ ጅሜን ልጆች አግኝተን መጨዋወት ጀመርን ፣ድካማችንን ከፊታችን ያነበቡት ወንድሞቻችን የሚበላውን የሚጠጣውንም አቅርበው እርሀቡ አስታገስን።
ጨዋታችን በሳቅ የታጀበ ነው ቋንቋችን ሁሉ ፋኖነት ሲሆን ተጋድሏቸውን እያወሱ ያወጉናል ፣በተለዋወጠ መንፈስ ሞቅ እያልን እንጨዋወታለን በዚህ መካከል የመስከረም 12ቱ እና የታህሳስ 24ቱ ተጋድሏቸው ትኩረቴን ሳበው።
ከኋላው ይልቅ የፊቱን አስቀድሜ ስለ ታህሳስ 24 ተጋድሏቸው ደጋግሜ ጠየኳቸው።ሁሎችም በእለቱ ለነበረው ጀግንነት ከኛ ይልቅ ማክቤልን ጠይቀው አሉኝ።ግራ ገባኝ የተባለውስ ሰው ማነው? ምንስ ሊነግረኝ ይችላል ? ማክቤል ማነው ? የሚሉ ጥያቄ በውስጤ ተመላለሱ ። መልሸ ለእነሱ ጠየኩ ።
ማክቤል የስናን አባ ጅሜ ብርጌድ ዘመቻ ኃላፊ ሲሆን ከትንሽ እስከ ትልቅ ከህዝብ እስከ ሰራዊቱ ያለ መሸራረፍ በጀግንነቱ ተስማምተው የምንግዜም ጀግናቸው አድርገውታል።
ማክቤል ካለ በውጊያዎች በተጋድሎዎች ከሰራዊቱ ጋር ከተሰለፈ ወደ ኋላ የሚል የለም ፣የሚያመነታ የሚያፈገፍግ ሰራዊት የለም።አርሶ አደሩ በገፍ ከኋላው ይከተለዋል፣ አባሉም በወኔ ይፋለማል ፣ጥይት እንደ በረዶ በሚወርድበት አውደ ውጊያ ማክቤል ክላሹን አስቀምጦ ጠላትን በቦንብ ያጋያል ይህንን ጀብድ እያየህ እንዴት ወደ ኋላ ትላለህ ? በማለት የማክቤል ጓዶች ለወንድማቸው የሚሰጡት ጀግንነት በመጠየቅ ይመሰክራሉ።
በዕለተ እሮብ ታህሳስ 24 የአገዛዙ ሰራዊት በሌሊት ግራ-ቀኝ የአባ ጅሜን ብርጌድ መስተዋት ላይ የምትገኘውን ሻለቃ ለመክበብ እንቅስቃሴ በማድረግ የከበባ ቀለበቱን በማስፋት የጮቄን ተራራ ግርጌ የደገፉትን ተራሮች ቀድሞ በመያዝ ጥቃት ለመፈፀም ንጋትን ብቻ ይጠብቃል።
ከፋኖዎች ካምፕ በሰሜን በኩል ተዘርግቶ የወገን ኃይል እንዳያፈገፍግ መውጫ ዘግቷል ፣በ ዕሮብ ገበያ አቅጣጫ ሌላ ተጨማሪ ኃይል በማሰማራት ጠላት ከንጋት 12:00 ገደማ እሩምታ ተኩስ ካምፕ ነው ብሎ በገመተው ት/ቤት ላይ አዘነበ።
ነገር ግን ጠላት አነጣጥሮ የሚተኩስበት ት/ቤት አንድም ፋኖ አነበረም በአንፃሩ ጠላት ፈርቶ ቀድሞ ያልያዘው በጫካ የተሸፈነውን" ማነቆ በር" ተራራን የአባ ጅሜ ብርጌድ አባላት ቀድሞው በመቆጣጠር ጠላት የመጀመሪያውን ተኩስ እስኪከፍት ይጠባበቁ ነበር።
ብቻውን ትምህርት ቤት ሲደበድብ የነበረው ጠላት ከበባውን እያጠበበ ትምህርት ቤቱን ሲጠጋ የአባ ጅሜ ልጆች ከኋላ ተራራው ከለላ በማድረግ ከጀርበው ከበው ጠላትን ከኋላው እሩምታ ከፈቱበት በዚህም ሚዛኑ የተዛባበት የጠላይ ኃይል ፊቱን ወደ ኋላ በመመለስ ለማጥቃት ቢሞክርም የስናን ልጆች ከፍተኛ ውጊያ በማድረግ ከባቢውን ከበው ከኋላ ጠንካራ ጥቃት ፈፅመውበታል።
ባልጠበቀው ጊዜ ጥቃት የደረሰበት ጠላት ሞርተር፣ዲሽቃ፣ብሬን፣ስናይፐር፣በስፋት በመጠቀም ከበባውን ለመጣስ ፊቱን ወደ ኋላ አዙሮ አጥብቆ መዋጋት ጀመረ።
በወገን በኩል ውጊያው የተራዘመና ጠላት የሚጠቀማቸውን መሳሪያ በማሰብ ተተኳሻቸውን እየ ቆጠቡ ምሽጋቸው ሳይለቁ ይዋጋሉ፣ጠላት ወደ ማጥቃት የሚያሻግረውን ተኩስ በማጠናከር ወደ ፊት እግረኛውን ለመላክ ሽፋን ሲሰጥ የአባ ጅሜ ጀግኖች ያልታሰበው የማጥቃት ውጊያ ከምሽጋቸው ወጠው ቁመው እየተኮሱ ፎክረው ወደ ፊት ይምዘገዘጉ ጀመር።
በዚህ ስዓት ነበር ልብን ቀጥ የሚያደርግ ትዕይንት የተፈጠረው፦
እሩምታው ከግራና ቀኝ እንደቀጠለ ነው ነበልባሎች ተራራውን እየተሳቡ ይራመዳሉ የጠላት ተኩስ ጠንካራ ነው የሚወድቅ ግን አንድም የለም የሚተማመኑትን ጀግና ከኋላ ተከትለው ወደ ጠላት ምሽግ ተኩሳቸውን አደረጉ።
"ማክቤል" ጠላት ከየትኛው አቅጣጫ ጠንካራ ውጊያ እንደሚያደርግ አስተዋለ ሰራዊቱም ለማጥቃት እንደተነሳ ተመልክቷል ያለው አማራጭ አንድ ነው ተጠጋግተው የሚተኩሱ የጠላት ሶስት ብሬኖችን ማጋየት የሱ ድርሻ ነበር።
የጨበጣትን ክላሽ መሬት አስቀመጠ በደረት ትጥቁ ከያዛቸው ሁለት ቦንቦች በተጨማሪ ሁለት ቦንቦች ከጓደኞቹ ተቀብሎ በተኩሱ መካከል እየተፈተለከ ጠንካራ ምሽግ በያዙ 3 የጠላት ብሬኖች ላይ የያዛቸውን ቦንቦች አንድ በአንድ ጣለ ማዶ የሚሰማው የብሬን ተኩስ ቀጥ አሉ ጠላትም ግራ ተጋባ የሚያየውንም አላመነም በብሬን ምድብተኞችን ቀይሮ ማክቤል ምሽጉን ተቆጣጥሯል።
የወገን ኃይል ፊታውራሪያቸው የሰራውን ገድል አስጠብቀው በወኔ የጠላትን ሰራዊት ያደባዩት ጀመር ሁኔታዎች ተቀያየሩ "የማክቤል 4(አራት) ቦንቦች" የጠላትን አሰላለፍ ምስቅልቅሉን አወጡት በየ ተራራው የተሰቀለው ጠላት ተናደ፣ እንደ ዝንጀሮ ተንበርክኮ ሲወርድ ልዩ ትዕይንት ነው የሚሉት ጀግኖቹ ምርተር፣ብሬን፣ስናይፕር፣ክላሽ፣ጥይት፣ በየ ሜዳው ጥሎ ፊቱን ባዞረበት ፈረጠጠ በዚህ መሀል የስናን አባ ጅሜ ብርጌድ ታህሳስ 24 አስደናቂ ፈፀመ ጠላትን እየተከተለ በጥይት ለቃቅሟቸዋል።
ክላሽ በየ ሜዳው ወድቋል፣አስክሬኖች በየ ቋጥኙ፣በየ ሸጡ ተጋድመዋል፣ማነቆ በር፣መስተዋት ፣ሳር ቅጠሉ፣የአርሶአደሩ ማሳ በጠላት ደም ጨቀዩ ፣እልህ አስጨራሹ የመጨረሻው ተጋድሎ በማክቤል አራት ቦንቦች ታግዞ የአብይ አህመድ ሰራዊትን አባ ጅሜ ብርጌድ አመድ አደረገ የቆሙት ተዘረሩ ፣የሚተኩስቱ በድን ሆኑ፣ የሚሮጡት በአፍንጫቸው ተደፉ ፣ቦቅቧቆች በጀግኖች ምድር ድንጋ ተንተርሰው፣ ሳር ግጠው፣ ቅጠል ጨብጠው ተገኙ፣ ነበልባሎች በጠላት አስክሬን ላይ በኩራት ሲረማመዱ ከመካከላቸው እንቅፋት የመታው እንኳ አንድም የለም።




የአማራ ፋኖ በጎጃም የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክፍለ ጦር የአብራጂት ብርጌድ አፈና ለማድረግ በሶስት አቅጣጫ የመጣውን የወራሪው አቢይ አሐመድ ሰራዊት ከንጋቱ 12:00-10:00ሰዓት ኮርክ ከተማ ላይ ቁም ስቅሉን ሲያሳየው ውሏል።ይኸ ውጊያ ከፍተኛ ፍጥጫ የተደረገበት ሲሆን የአገዛዙ ሰራዊት ከ 35 በላይ አስከሬን እና 14 ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ተመልሷል። ክፉኛ በመመታቱ የተበሳጨው ጠላት ከተማዋ ላይ የፋኖስ ቤተሰቦችን እና የታጋዮችን ቤት እና ንብረት አውድሞ ወጥቷል።
ድል ለአማራ ፋኖ!! ፋኖ ያሸንፋል!!
ፋኖ መ/ር እንደሰው ታምሩ የሐዲስ ዓለማየሁ 7ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) የምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር እና ኮር2 ታጠቅ ክፍለጦር አሃዶች በጋራ በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ አንጦ ጨፌ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ፡፡

ዛሬ ጥር 27/2017 ዓ.ም በተደረገው ተጋድሎ የባለሽርጡ ክፍለጦር ሜካናይዝድ ክፍል 100% ኢላማዉን የጠበቀ የሞርታር ጥቃት በመፈፀም  የፋሽቱን ስርዓት ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት የብልፅግና ሆድ አደር ካድሬ እንዲሁም ሆድ አደር ሚሊሻ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ሰርቷል::

በዚህም የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት መርሳ ከተማ ሆድ አደር አድማ ብተና እና ሚሊሻዎችን ለተሻለ ግዳጅ በሚል ጫካ ላይ ስብሰባ ጠርቶ የተሳሳተ ቅስቀሳ ፅንፈኛው ስለተዳከመ የቀጠናውን ሰላም መመለስና አካባቢውን ተረከቡ በሚል በመድረክ ሲደሰኩር የባለሽርጡ ሜካናይዝ ክፍል ወደ ስብሰባው ባስወነጨፈው የሞርተር ጥቃት የስርዐቱን ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ሆድ አደር ሚሊሻዎችና አድማ ብተና ሀይልን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ያሰቡትንም መድረክ ሳያሳኩ ስብሰባውን የበተኑት ሲሆን የሜካናይዝድ አጃቢ ሻለቃ በአንጦ ጨፌ የመጣውን ጨፍጫፊ ሀይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ወደ መጣበት እንዲመለስ አድርጎታል::   

የታጠቅ ክፍለጦር አሃዶች ዙፋን አቦ ቀበሌ በመነሳት ከላይ ወደታች አጋምሳ እና ወረላሎን ማለትም ከመርሳ ከተማ ደቡባዊዩን አቅጣጫ አድማ ብተናና ሚሊሻ የሰፈረበትን ምሺግ በመስበር በርካታ ጠላት ሲደመስሱና ሲያቆስሉ ጠላት ነፍስ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጧል::

የባለሽርጡን እና ታጠቅን በትር መቋቋም ያቃተዉ የባንዳ ጥርቅም የግለሰብን ሀብትና ንብረት እየዘረፈ፣ እያወደመና የዘወትር ልምዱ የሆነዉን ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ ሞርታር ጥቃት በመፈፀም ሶስት ገበሬዎችን ሲገድል በተመሳሳይ ከግለሰብ ቤት ላይ በተወረወረ ሞርተር ሁለት እናቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን እነዚህ እናቶች አሁን በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ጥር 27/2017 ዓ.ም




ሰበር ዜና !

አቸፈር ወንድዬ

አገዛዙ እራሱ በራሱ ተጨራረሰ ሰዉ በላዉ ስርዓት ከሊበን በመነሳት ወደ ይስማላ አቅንቶ የነበረ ሲሆን በአማራ ፋኖ በጎጃም አገዉ ምድር ክፍለ ጦር የቢትወደድ አያሌዉ መኮነንን ብርጌድ አቤ ጉበኛ ሻለቃ በደፈጣ ሲለበለብ ከተማዉ ላይ የግለሰብን ቲወታ መኪና በማናለብኝነት ነጥቀዉ መበያዝ የወረዳዉ አስተዳደር
ፀጥታ ሃላፊ ኑሬ እንደ ባንዳነት መኪና ማሽከርከር ቀላል የመሰለዉ ጅላንፎ መኪናዋን በመያዝ ከላይ ሰዉ በመያዝ ከይስማላ ወደ ሊበን እግሬ አዉጭኝ ብሎ ሲፈረጥጥ መኪናዋ ተገልብጣ ወዲያዉኑ 3 ሰዉ የሞተ ሲሆን የአስተዳደር ፀጥታ ሃላፊዉ ኑሬ እና የሚሊሻ ጽ/ቤት ሃላፊዉ ግርማ የተባለ ጅላንፎ ክፋኛ ቆስለዉ ወደ ሊበን ሆስፒታል የገቡ ሲሆን ሌሎችም ቁስለኞች መኖራቸዉን አረጋግጠናል

ባንዳ ገና ብዙ ነገር ይጠብቅሻል

የብርጌዱ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ይበልጣል የዉነቱ ጀግናዉ


🔥ሰልጣኝ የአባት አርበኞች ተመረቁ‼️

የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለጦር ልጅ ስዩም ብርጌድ ከእንሳሮ ወረዳ ከሶስት ቀበሌወች በፍላጎት ወደ ትግሉ የተቀላቀሉ አባት አርበኞችን አሰልጥኖ አስመረቀ።

የአማራን ህዝብ የህልውና ትግል መቀላቀል አለብን ብለው ከእንሳሮ ወረዳ ሶስት ቀበሌወች ማለትም የትኖራና ቦለድ ቀበሌ፣ ቀንና ሞልታንባ ቀበሌ እንዲሁም ካራምባና ጥቁርዱር ቀበሌወች ውስጥ የተውጣጡ በርካታ አባት አርበኞችን በአካል ብቃት ፣ በወታደራዊ ሳይንስና በፖለቲካ አሰልጥኖ  የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ የብርጌዱ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌወች በተገኙበት ተመርቀዋል።

ተመራቂ አባት አርበኞች የብልፅግናው ስርአት የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት የተሰለፈ ስለሆነ ሁላችንም በአንድነት መንፈስ በመተባበር ይህን የበሰበሰ ስርአት በማክሰም ህዝባችንን የሚመጥን ስርአት መትከል አለብን ሲሉ ተደምጠዋል።

©የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል።




ህዝባዊ ውይይት በደባይ ጥላትገን ወረዳ🙏

ጥር 27/2017ዓም

የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር በደባይ ጥላትገን ወረዳ ከሚገኜው ደበይ ጮቄ ብረጌድ አመራርና አባላት ጋር ከአንድ ሳምንት በላይ የፈጄ  ውይይት አካሂዶል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የፖለቲካ መኮነኖች እና የ8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አመራሮች በደባይ ጥላትገን ወረዳ ናብራ ከተማ፣ደብር እየሱስ ከተማና የዳማ ቀበሌዎች ላይ በመገኜት ከብርጌዱ አመራሮች የሻለቃ አመራሮች የፋኖ አባላት በየቀበሌው የሚገኙ ግዚአዊ አስተዳዳሪዎችን እንዲሁም በትግሉ የግል መሳሪያ ይዘው ይታገሉ የነበሩ የህብርተሰብ ክፍሎች በመሰብሰብ ሰፋ ያለ ህዝባዊ ውይይት አድርገዋል።

በደባይ ጥላትገን ወረዳ ሳምንታትን በፈጄው ህዝባዊ ውይይት በማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ፣እንደ ክፍለ ጦር ጠንካራ ወታደራዊ ጦር ስለመገንባት፣ማህበራዊ የፍትህ አሰጣጥ ችግሮችን፣የህዝብ አስተዳደር፣የፋይናስ ስረዓት ደንብ መምሪያ፣ በተመለከተ እንደ አማራ ፋኖ በጎጃም በወጡት መመሪያዎችና ደንቦች እንዲሁም የአማራን ህዝብ የተደቀነበትን የህልውና ትግል ነፃ ለማውጣት ጥልቅ ውይይት ሲያካሂድ ሰንብቶል።

በመጨረሻም የአማራ ፋኖ በጎጃም የሚያወጣቸውን ህግና መመሪያዎች በአግባቡ ለመተግበር የብርጌድ የስራ አፈፃፀም ገምግሞ በወታደራዊ ዝግጁነቱን እንዲሁም በብረጌዱ የአመራር ማሟላትና 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር እና ደበይ ጮቄ ብርጌድ ውስጥ የሚገጥሙ ችግሮችን ለመፍታት በርካታ ሀሳቦች ተነስተው ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዶ በድረጅቱ የመጡ መምሪያዎች እና ደንቦችን እንዲተገበሩ እና በተቋሙ ህግ ጥሰው የተገኙ ግለሰቦችን በተቋሙ በህግ እንዲጠየቁ በማድረግ የስራ አቅጣጫዎች በመስጠት ውይይቱ በሰላም ተጠናቋል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፌ Fano Yibeltal Getie Mitiku

አዲስ ትውልድ!አዲስ ተስፋ!አዲስ አስተሳሰብ! ለአማራ ህዝብ!



17 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.