Postlar filtri


#NGAT

የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም (NGAT) አመልካቾች የመግቢያ ፈተና አርብ መጋቢት 5/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ ይሰጣል።

በመሆኑም በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት በመገኘት ፈተናውን መውሰድ የምትችሉ ሲሆን፤ ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡

ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡ የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑ ተጠቁሟል።

የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም እንደሚገለፅ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


ለባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የኦሪጅናል ዲግሪ አመልካቾች በሙሉ

ኦርጅናል ዲግሪ ለማሳተም የተያዘው ውል የሚጠናቀቀው በዚህ ወር በመሆኑ ከዛሬ ከዐ1/07/2017 ዓ.ም ጀምሮ #ላልተወሰነ ጊዜ የኦሪጅናል ማመልከቻ የማንቀበል መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡- አዲስ ውል እንደያዝን በማስታወቂያ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

(የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት)


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሰሜኑ ጦርነት በክልል የወደሙ ትምህርት ቤቶች አሁንም ሙሉ በሙሉ ተጠግነው ባለመጠናቀቃቸው በዛፍ ስር ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን የትግራይ ክልል አስታወቀ

የፌዴራል መንግስት፣ የአለም ጤና ድርጅት /WHO/ን ጨምሮ በውጪ ሃገራት ያሉ የትግራይ ተወላጆች የወደሙ ትምህርት ቤቶችን መልሶ ለመገንባት የበጀትና የቁሳቁስ ድጋፎችን እያደረጉ እንዳሉ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል፡፡

ይሁን እንጅ በጦርነቱ የወደሙት ትምህርት ቤቶች ቁጥራቸው በርካታ በመሆኑ ሙሉ በሙሉ ጠግኖ ማጠናቀቅ እንዳልተቻለ ለመናኸሪያ ሬዲዮ የገለፁት የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር አቶ ጣዕመ አረዶም ናቸው።

መሰረተ ልማቶቹን ጠግኖ ወደ ስራ ለማስገባት ጥረት ተደርጎ የተወሰኑት ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ቢደረግም፤ በተለይ በክልሉ ገጠራማ አካባቢ የመሰረተ ልማቱ ባለመጠገኑና የመጠለያ ካንፕ የነበሩ ትምህርት ቤቶች ባለመለቀቃቸው ተማሪዎች በዛፍ ጥላ ስር እንዲማሩ አስገድዷል ብለዋል፡፡

በመሆኑም አሁን ላይ በክልሉ ከ30 እስከ 40 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አለመመለሳቸውን ነው ያስታወቁት።

ከጦርነቱ በኋላ በስደትና መፈናቀል ምክንያት ወደ ትምህርት ገበታቸው ያልተመለሱ በርካቶች መሆናቸውን የሚገልፁት አቶ ጣዕመ፤ የምግብና የገንዘብ አቅም የሌላቸውም ቤተሰቦች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንደማይልኩ አስታውቀዋል፡፡

ተማሪዎቹን እና የትምህርት ተቋማቱን ለመደገፍ ሁሉም አካላት አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


#TVTI

በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በደረጃ 7 (2ኛ ዲግሪ) ለመማር ያመለከታችሁ በሙሉ ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመውሰድ ምዝገባው ዛሬ ይጠናቀቃል።

ምዝገባው ዛሬ ማታ 12፡00 ሰዓት ከመጠናቀቁ በፊት በ https://ngat.ethernet.edu.et/registration የመመዝገቢያ ሊንክ በኩል ምዝገባዎን ያድርጉ።

የመፈተኛ 'User Name' እና 'Password' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን፤ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈጸም ይጠበቅባችኋል፡፡

የመግቢያ ፈተናው በአቅራቢያችሁ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በቀጣይ በሚገለፅ ቀን ይሰጣል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


#Ad

TLA Academy

🌍 Welcome to Our Study Abroad Guidance 📚 
Travel with Us!

🇺🇸 USA 
🇮🇹 Italy 
🇦🇹 Austria 
🇵🇱 Poland 
🇷🇴 Romania 
🇨🇳 China 
🌍 And Other European Countries


Are you a student dreaming of studying abroad? 
Join our vibrant community for expert guidance and support!

▎What We Offer:

✨ Free Expert Guidance: Step-by-step assistance on university applications in worldwide.

📝 Personalized Support: Tips and templates for standout statements of purpose and motivation letters.

🎓 Scholarship Opportunities: Discover financial aid options and maximize your chances of securing funds.
I'm
🤝 Fraud Prevention: Learn about common scams to ensure safe decisions in your study abroad journey.

🌐 Networking: Connect with fellow students, share experiences, and build lasting relationships.

🚀 Resources  Workshops: Access webinars, articles, and QA sessions with international education experts.

Join us today and take the first step towards your dream of studying abroad! 
Let’s embark on this exciting journey together! 🌟

📩 Contact us: @mezmurhal 
🔗 Join us: https://t.me/guidescholar


ዛሬ ይጠናቀቃል!

ሀገር አቀፍ የ2017 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የአመልካቾች ምዝገባ ዛሬ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ማታ 12፡00 ሰዓት ያበቃል፡፡

በቀሩት ሰዓታት ምዝገባዎን ያድርጉ!

የመመዝገቢያ ሊንክ፦
https://ngat.ethernet.edu.et/registration

የመፈተኛ 'User Name' እና 'Password' በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን፤ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 750 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም ይጠበቅባችኋል፡፡

ፈተናው የሚሰጥበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


Unknown dan repost
Matric Study (Natural).apk
82.5Mb
📚 MATRIC STUDY APP(Only For Natural Science Students)

🎯 ለማትሪክ ጥናት ጀምረዋል? እነሆ ጉዞዎን ከኛጋ ይጀምሩ

🎯 በማትሪክ ስተዲ፣ የሚከተሉትን ያገኛሉ

✅ከ9-12ኛ ክፍል ያሉ ትምህርቶች ማስታወሻዎች(ኖቶች) በአጭርና፣ ለመረዳት ቀላል በሆነ መንገድ (በአዲሱ እና በነባሩ ስርዓተ ትምህርት)

✅ ያለፉ የማትሪክ ፈተናዎች ከዝርዝር ማብራሪያ ጋር 📖

✅ ፈጣን ክለሳ ለማረግና በልበ ሙሉነት ለማለፍ በሚረዳ መልኩ የተዘጋጀ!

📲 ማትሪክ ስተዲን አሁኑኑ ያውርዱ እና ትምህርትዎን ያሻሽሉ! 🚀 💡 የማትሪክ ስኬትዎ እዚህ ይጀምራል!


🔥🔥🔥 ከቤት ሆነው የትም መሄድ ሳይጠበቅቦት የሚሰሩበት እና በዶላር 💵💵💵 ተከፋይ የሚሆኑበት ምርጥ የስራ እድል www.CDIWork.com ይዞሎት መጥቷል።

ይህ ዕድል እንዳያመልጦ፤

💻 💰💵💸 💥

✨ ለበለጠ መረጃ  የማህበራዊ ሚዲያችንን ይቀላቀሉ። ✨
Telegram - https://t.me/CDIWork

ጉዞውን ዛሬ ይጀምሩ።
www.CDIWork.com


በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!

መንግሥት በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ትኩረት ሰጥቶ በመንቀሳቀስ በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሕንድ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በማይናማር በእገታ ሥር ቆይተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ ወደ ሀገራቸው መግባታቸው ተገልጿል።

#EBC
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


44A+ እና 40A+ ያሳኩት ተመራቂዎች 👏

ከደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ዛሬ የተመረቁት ተማሪ አስማማው እና ተማሪ ቤዛዊት ከ40 በላይ A+ በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚዎች ሆነዋል።

የማርኬቲንግ ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተመራቂው ተማሪ አስማማው ሽፈራው CGPA 4.00 እና 44A+ በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

የሳይኮሎጂ ትምህርት ክፍል ተመራቂዋ ቤዛዊት ጌቱ CGPA 4.00 እና 40A+ በማምጣት በሁለተኝነት የዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች።

ሁለቱም ተመራቂዎች ጊዜያቸውን በአግባቡ ለትምህርታቸው ብቻ በመስጠታቸውና ጠንክረው በመስራታቸው ለዚህ ውጤት መብቃታቸውን ገልፀዋል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


#Ad

TLA Academy

🌍 Welcome to Our Study Abroad Guidance 📚 
Travel with Us!

🇺🇸 USA 
🇮🇹 Italy 
🇦🇹 Austria 
🇵🇱 Poland 
🇷🇴 Romania 
🇨🇳 China 
🌍 And Other European Countries


Are you a student dreaming of studying abroad? 
Join our vibrant community for expert guidance and support!

▎What We Offer:

✨ Free Expert Guidance: Step-by-step assistance on university applications in worldwide.

📝 Personalized Support: Tips and templates for standout statements of purpose and motivation letters.

🎓 Scholarship Opportunities: Discover financial aid options and maximize your chances of securing funds.
I'm
🤝 Fraud Prevention: Learn about common scams to ensure safe decisions in your study abroad journey.

🌐 Networking: Connect with fellow students, share experiences, and build lasting relationships.

🚀 Resources  Workshops: Access webinars, articles, and QA sessions with international education experts.

Join us today and take the first step towards your dream of studying abroad! 
Let’s embark on this exciting journey together! 🌟

📩 Contact us: @mezmurhal 
🔗 Join us: https://t.me/guidescholar


ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ 800 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና 2ኛ ዲግሪ ያስተማራቸውን 1 ሺህ 811 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስማረ መለሰ (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት እንዳሉት÷ዩኒቨርሲቲው ሀገር በቀል እውቀትን በመጠቀም በተለያዩ ዘርፎች የልሕቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ ነው፡፡

ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ፕሬዚዳንቱ ÷ ተመራቂዎች የቀሰሙትን ዕውቀትና ያካበቱትን ክህሎት ተጠቅመው ሀገራዊ ድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል።

ዩኒቨርሲቲው ለ17ኛ ጊዜ ካስመረቃቸው ተማሪዎች ውስጥ 46ቱ በ2ኛ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆኑ÷ከአጠቃላይ ተመራቂዎች 527 የሚሆኑት ደግሞ ሴቶች መሆናቸው ተመላክቷል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዲግሪ መርሀ- ግብር ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ጀመረ


የጠዳ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የዲግሪ መርሀ- ግብር ጅማሮ ማብሰሪያ እና ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ የምስጋና መርሀ-ግብር በዛሬው እለት ማለትም የካቲት 29/2017ዓ.ም በኦሎምፒክ ሆቴል ተካሂዷል።

ኮሌጁ በአማራ ክልል ጤና ቢሮ ሥር ከ1971 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት አርባ ስድስት ዓመታት መካከለኛ የጤና ባለሙያዎችን ሲያፈራ የቆየ አንጋፋ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሲሆን ፣የጤና ትምህርት መስኮች በማስተማር በርካታ ባለሙያዎችን አፍርቷል።

በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በዲግሪ መርሀ-ግብር ለማስተማር እውቅና አግኝቶ ተማሪዎችን ማስተማር ጀምሯል።

በዛሬው እለት በተደረገውም የዲግሪ መርሀ-ግብር ማብሰሪያ እና የምስጋና ፕሮግራም ኮሌጁ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ላደረገው አስተዋጽኦ እውቅና ሰጥቶታል።

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ ተልዕኮውን እንዲወጣ በሰው ኋይል ስልጠናና በተለያዩ ድጋፎች በአጋርነት ሲሰራ ቆይቷል።

ኮሌጁ በዲግሪ መርሀ- ግብር ማስተማር በመጀመሩ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ደስታቸውን ገልፀዋል። በቀጣይም ኮሌጁ በጤናው ዘርፍ ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት በሚያደርገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው በትብብር የሚሰራ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


Unknown dan repost
Matric Study (Natural).apk
82.5Mb
📚 MATRIC STUDY APP(Only For Natural Science Students)

🎯 ለማትሪክ ጥናት ጀምረዋል? እነሆ ጉዞዎን ከኛጋ ይጀምሩ

🎯 በማትሪክ ስተዲ፣ የሚከተሉትን ያገኛሉ

✅ከ9-12ኛ ክፍል ያሉ ትምህርቶች ማስታወሻዎች(ኖቶች) በአጭርና፣ ለመረዳት ቀላል በሆነ መንገድ (በአዲሱ እና በነባሩ ስርዓተ ትምህርት)

✅ ያለፉ የማትሪክ ፈተናዎች ከዝርዝር ማብራሪያ ጋር 📖

✅ ፈጣን ክለሳ ለማረግና በልበ ሙሉነት ለማለፍ በሚረዳ መልኩ የተዘጋጀ!

📲 ማትሪክ ስተዲን አሁኑኑ ያውርዱ እና ትምህርትዎን ያሻሽሉ! 🚀 💡 የማትሪክ ስኬትዎ እዚህ ይጀምራል!


ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ያሠለጠናቸውን ተማሪዎችን አስመረቀ።

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሠለጠናቸውን 560 የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎችን አስመርቋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ የአማራ ክልል ፕላን እና ልማት ቢሮ አማካሪ ሙሉቀን አዳነ (ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ አማካሪ ግዛት አብዩ፣ የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ፣ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት አስማማው ዘገዬ (ዶ.ር) ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የተማሪ ወላጆች፤ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት አስማማው ዘገዬ (ዶ.ር) በተለያዩ ችግሮች ውስጥ አልፈው ለምርቃት የበቁ ተማሪዎችን፣ የተማሪ ወላጆችን እና የዩኒቨርሲቲውን መምህራን እና ሠራተኞችን አንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

ተመራቂ ተማሪዎቹ በርካታ ችግሮች ሳይበግሯቸው ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ለምርቃት የበቁ በመኾናቸው የፅናት ተምሳሌት ናቸው ነው ያሉት።

ወደፊትም ችግሮችን የመቋቋም ልምዳቸውን፤ በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው ያገኙትን ዕውቀትን እና ክህሎት ተጠቅመው ለወላጆቻቸው፣ ለማኅበረሰባቸው እና ለሀገራቸው የሚጠቅም ሥራ እንዲሠሩ አሳስበዋል።

የአማራ ክልል ፕላን እና ልማት ቢሮ አማካሪ እና የምርቃቱ የክብር እንግዳ ሙሉቀን አዳነ (ዶ.ር) ዕውቀት እና ክህሎት ይዘው ለምርቃት የበቁ ተማሪዎች ሀገራቸውን የሚያሻግር ሥራ ሊሠሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ተመራቂዎች በዕውቀታቸው፣ በክህሎታቸው እና ጉልበታቸው ሀገራቸውን እንዲያገለግሉም አሳስበዋል።

በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በስሜት ሳይኾን በስሌት እንዲሠሩ የሚያስችላቸውን ዕውቀት አግኝተዋል ነው ያሉት። ተመራቂዎች ለሀገራቸው የችግሮች መፍትሔ እንጅ የችግሮች ምንጭ መኾን እንደማይኖርባቸው አስገንዝበዋል።

የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ
እንደ ሀገር የተጀመረውን የልህቀት እና የልዕልና ጉዞ ለማሳካት ትምህርት አይነተኛ ሚና አለው ብለዋል።

ለዚህም በዕውቀት እና በክህሎት የበቃ ዜጋ ለመፍጠር መንግሥት ትምህርት ላይ በትኩረት እየሠራ ነው ብለዋል።

የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች በቀጣይ በተማሩት ሙያ ለሀገር እና ለወገን የሚጠቅም ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ በየትምህርት መስኩ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎች የዋንጫ፣ የሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በዩኒቨርሲቲው በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ የትምህርት መስክ በከፍተኛ ውጤት የዋንጫ ተሸላሚ የኾነው ተመራቂ ታምሩ ተውቦ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በተለያዩ ችግሮች ቢፈተንም በፅናት ለውጤት እና ለምርቃት መብቃቱን ተናግሯል።

በቀጣይ በተማረበት ሙያ ሀገሩን እና ወገኑን ለማገልገል ዝግጁ መኾኑን ገልጿል።

ሌላኛዋ የሥነ ሕይወት ትምህርት ክፍል ተመራቂ ቤተልሔም አበባው ከሴት ተማሪዎች ከፍተኛ ነጥብ በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ኾናለች።

ተመራቂዋ በርካታ ችግሮችን ማለፋቸውን አንስታለች። ትምህርቷ በሽልማት በመጠናቀቁም ደስተኛ እንዳደረጋት ገልጻለች።

በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ ያገኘችውን ዕውቀት እና ክህሎት ተጠቅማ ሥራ ጠባቂ ሳይኾን ሥራ ፈጣሪ ኾና ወገኗን እና ሀገሯን ለማገልገል ዝግጁ መኾኗንም ተናግራለች።

©️አሚኮ
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news



18 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.