Postlar filtri


1⃣7⃣ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


👑'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>  ስለ ንጉስ ቴዎድሮስ     🤴


🩸 ትንቢት የተነገረለትን ንጉስ የቴዎድሮስ የሚነሳበት አስደናቂና ምስጢራዊ ስፍራ

🩸 እውነት ትንቢት የተነገረለት ንጉስ ቴዎድሮስ ይመጣል ?

🩸 በፍካሬ ኢየሱስና በገድለ ፊቅጦር ስለ ትንቢታዊው ንጉስ ቴዎድሮስና ተጽፎ ይገኛል

🩸 የየረር ተራራ አስገራሚ ምስጢሮች

ለእነዚህ ጥያቂዎች መልስ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ

እዚህ ጋር ይጫኑ 'https://t.me/addlist/2CQ3e4ZJYT9hZGNk' rel='nofollow'>👇👇👇👇👇👇👇👇👇
➢ JOIN  ➢  JOIN  ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN  ➢  JOIN  ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN  ➢  JOIN  ➢ JOIN ➢JOIN
➢ JOIN  ➢  JOIN  ➢ JOIN ➢JOIN


ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት እና እምዬ ምኒልክ


ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት የውጫሌ ውል ፈርሶ ዳግማዊ ምኒልክ የክተት አዋጅ ሲያውጁ "ሞቴን ከምኒልክ ያስቀድመው!" ብለው ነበር የጎጃምን ሰራዊት አሰልፈው ዓድዋ የደረሱ። የአጼ ምኒልክ እና የንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ፍቅርና መተማመን በጣም ጥብቅ እንደነበር በታሪክ ተጽፏል፡፡ ሁለቱን መሪዎች ያቀራረባቸው እና አንድ ያደረጋቸው ደግሞ እርስ በእርስ ያካሄዱት የእምባቦ ጦርነት ነበር፡፡

የእምባቦ ጦርነት ዳግማዊ ምኒልክ ከመንገሳቸው በፊት ከጎጃሙ ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ጋር ባለመግባባት ያካሄዱት ጦርነት ነው፡፡ በጦርነቱ ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ቆስለው በንጉሥ ምኒልክ እጅ ይወድቃሉ፡፡ ምኒልክም የንጉሥ ተክለ ሀይማኖትን ቁስል ራሳቸው እያጠቡ አንድ ጥያቄ ንጉሡን ጠየቋቸው፡፡
“እኔን ብትይዘኝ ምን ታደርገኝ ነበር?”
“እገልህ ነበር!” በማለት ንጉሠ ተክለ ሀይማኖት ይመልሳሉ፡፡ ምኒልክም የንጉሡን ግልጽነት እያደነቁ ከህመማቸው እስኪያገግሙ በመንከባከብ ወደ ጎጃም ከሰራዊታቸው ጋር ይመልሷቸዋል፡፡

በዚህ የዳግማዊ ምኒልክ እንክብካቤ ልባቸው የተነካው ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት ምኒልክን "እምዬ" ብለው ስም አወጡላቸው። ከዚያ ጊዜ ጀምሮም ምኒልክ የእናትነት ርህራሄ ማሳየ በሆነው መጠሪያ "እምዬ ምኒልክ" ተብለው እየተጠሩ ዛሬን ደርሰዋል።

ጣሊያን ኢትዮጵያን በመውረሩ የክተት አዋጅ ሲታወጅ "ሞቴን ከምኒልክ ያስቀድመው!" ያሉትም ከዚህ መውደዳቸው የተነሳ እንደሆነ ይታወቃል፡፡

ንጉሥ ተክለ ሀይማኖት በዓድዋ ጦርነት ወቅት የዘመቻ ዋና የጦር መሪ እና የንጉሠ ነገሥቱ የቅርብ አማካሪ ነበሩ። በጦር መሪያቸው ራስ ወርቄ የሚመራው ሰራዊታቸውም በተሰለፈበት ግንባር ሁሉ ጣሊያንን ድባቅ በመምታት በዓድዋ ተራሮች ለተመዘገበው ድል ጉልህ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

✅ዓድዋ


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
🕊

" እነርሱ ... በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ።" [ ዕብ.፲፩፥፴፫ ]


"የካቲት ፳፫ ፲፰፻፹፰ ዓ.ም [march 1 1896] አነጋጉ ላይ በቤተክርስቲያኑ የነበረው ሁሉም ሰዉ ቅዱስ ቁርባንን ተቀበለ፡፡ ከዚያም አረንጓዴ ፣ ቢጫና ቀይ ቀለም ያለው ሰንደቅ ዓላማ በመስቀል ቅርፅ ተሰቀለ፡፡ የቆረብነውም ሁሉ ጎንበስ ብለን ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀገሪቱን ፤ ንጉሰ ነገሥቱን እና ኃይማኖቱን እንዲያስጠብቅና እንዲረዳን ለመንን፡፡ እንደ ነጋም ጦሩ ሁሉ የጦር መሳሪያውን ታጥቆ ወደ ውጊያ ገባ"

[ ከዳግማዊ ምኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ መፅሐፍ የተወሰደ ]


" እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ ፥ ጽድቅን አደረጉ ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ ፥ ከድካማቸው በረቱ ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ። [ ዕብ.፲፩፥፴፫ ]

- " አድዋ ባ'ፍ አይገባም "
- [ በገጣሚ አበባው መላኩ ]

         †               †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬


✝የክርስትና ስም ለምን አስፈለገ ?

❖የክርስትና ስም ለምን ያስፈልጋል?❖
ጥቂት የማንባል ሰዎች ከነ መሰየሙም የክርስትና ስማችንንም የማናስታውስ ልንኖር እንችላለን፡፡ የክርስትና ስም አንድ የሚጠመቅ ሰው በሚያጠምቀው ካህን የሚሰጠው ወይም የሚጸድቅለት ስያሜ ነው፡፡ ይህንን ስም ቤ/ክ ዝም ብላ ለህጻናቱ የምትለጥፍ የሚመስላቸው ሰዎች ቀላል አይደሉም፡፡ በጥምቀት ግዜ ቤ/ክን ልጆቿን ስትቀበል እንዲሁ አይደለም ተገቢ ስም አውጥታ ከመንፈስ ቅዱስ በጥምቀት ዳግመኛ ወልዳ ቅበዐ ሜሮን ቀብታ የሚንከባከብ የክርስትና አባት እናት ሰይማ በመስቀሉ ቃል አስገብታ ቅዱስ ስጋና ደሙን መግባ ነው፡፡ የክርስትና ስም መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና ክርስቲያናዊ ትውፊት አለው፡፡ ብዙ ነብያት እና ቅዱሳን ካላቸው መጠሪያ ሰም በተጨማሪ እራሱ አምላካችን አዳዲስ ስም ሲያወጣላቸው እናያለን ለምሳሌ፡-
አብራምን ☞ አብርሃም
ያዕቆብን ☞ እስራኤል
ስምዖንን ☞ ጴጥሮስ

ሳኦልን ☞ ጳውሎስ እያለ ሲጠራቸው ለምን በአዲስ ስም መጥራት እንደፈለገ አንዳች ነገር ልንገነዘብ ይገባል፡፡

✞ #ዓላማውስ_ምንድን_ነው?

1. #ቋሚ የቅዱሳን መታሰቢያ እንዲሆን፡- በት.ኢሳ 56:5 አምላክ ለቅዱሳን የማይጠፋ ስም እና የዘለዓለም መታሰቢያ እንደሰጣቸው እናነባለን፡፡ስለዚህ በተለያዩ ቅዱሳን ላይ የነበረውን ፀጋ እና በረከት ለመካፈልና እንዲሁም እንደነሱ የበረታን እንድንሆን በስማቸው እንሰየማለን የጌታችንንም ስሙን ዘርፍ በማድረግ እንዲሁ እንጠቀምበታለን፡፡

2. #ለተጠማቂውም በረከት እንዲሆንለት፡-
በምሳ 10:6 የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው ይላል፡፡ ስለዚህ በስማቸው በመሰየም ከላይ እንደገለጽነው መታሰቢያቸውን እና በረከታቸውን ለመካፈል ሲረዳን ይህን ጸጋ ለማግኘት በቅዱሳን ስም በመሰየም የክርስትና ስም ይወጣልናል፡፡

3. #መጠሪያ ስም ነው፡-
በቀድሞው ስርአት የክርስትና ስም ለሁልጊዜውም መጠሪያ ነበር፡፡ ከግራኝ መሐመድ መነሳት አስቀድሞ የነበሩ ምዕመናን በክርስትና ስማቸው ነበር የሚጠሩት፡፡ነገር ግን መከራው ሲበዛባቸው ከርስታቸው ላለመሰደድ ሲሉ ተለዋጭ ስም በማውጣት መጠቀም ጀመሩ ከዛን ግዜ ጀምሮ ይህ ነገር እየተስፋፋ መጥቶ ከነ ጭራሹ ለመለወጥ በቃ፡፡

በተጨማሪም
☞ -የማይገባ የክርስትና ስም
በአምላክ ስም በቀጥታ መጠራት አይገባም ለምሳሌ፡- አማኑኤል፣ኤልሻዳይ፣ኢየሱስ እነዚህ ስሞች ለሠው ልጆች መጠናችን ስላልሆኑ መጠቀም የለብንም፡፡ በዚህ ምትክ ገብረ አምላክ፣ሣህለ ሥላሴ፣ፍቅርተ ክርስቶስ ፣ዘአማኑኤል በማለት መሰየም ይቻላል።
☞-በቅዱሳንም ስም በቀጥታ ወይም ዘርፍ እየተደረገለት መሰየም ይቻላል፡፡
ለምሳሌ፡- ዘማርያም፣ዘሚካኤል፣አጸደ ማርያም፣ ተክለ ሐይማኖት ወዘተ...

#ከዚህ ስርዓት ከሚገኘው በረከት ተሳታፊዎች እንድንሆን አምላካችን እግዚአብሔር ለሁላችንም ይርዳን።
       ለተዋሕዶ ልጆች👇
               
@behle_abew
@behle_abew
@behle_abew


🌻አስኳላ online school 📖 dan repost
⭐️

ሰላም 🫡 እንደምን ናችሁ ይህ @Askuwala_Creative ነው። በዚህን ጊዜ አለማችን ወደ Digital💻 ነገሮች ፊቷን አዙራለች🌐 አመናቹም አላመናቹም Traditional things are going to be የድሮ ታሪክ🤷‍♂ So ከጊዜው ጋር መሄድ ደግሞ የእኛ ድርሻ ነው 😎 በዚህ ጊዜ ደግሞ Digital Skills🖥 are one of the leading service sectors የ Digital world📍 ተስእጦ ያለው Such like↔️

Graphics Designing 💻
Video editing 🎞
Content Creating 👾
Content Writing 🖌
Story telling 📝
Digital marketing 💵


ብቻ ምን አለፋቹ ከዚህም ያለፉ ብዙ Skills ያለው ሰው💻 በዚህን ጊዜ ተፈላጊ ነው🤝
እኛም ይህን በመገንዘብ እነዚህን Digital Skills በነፃ-Freely
እናንተን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል 🫡 ሳትዘገዩ ቶሎ ተቀላቀሉን🥰


⭐️Askuwala Creative😀💻📈

Unlock your creative potential!
🤜  We're here to help students like you to master the essential skills of the digital world. 🌐💻  Get ready to learn, grow, and create amazing things! 🤩

JOIN: @Askuwala_creative
share forward ለጓደኞችዎ
@Askuwala_Creative
@Askuwala_Creative
@Askuwala_Creative


የተዋሕዶ ፍሬዎች dan repost
ሰሞኑን በተነሳው በቅዱሳት ገድላትና ድርሳናት ዙሪያ እንዲሁም በጥንተ አብሶ ዙሪያ


፦ እስካሁን በተመለከትኩት ገድላት አያስፈልጉም መወገድ አለባቸው የሚል ንግግርም ጽሑፍም ከኦርቶዶክሳውያን አልሰማሁም። ምክንያቱም ገድላትና ድርሳናት የወንጌል ትርጉሞች ናቸው። የቅዱሳን ሕይወት የሚታይ የሚዳሰስ የወንጌልን ቃል በተግባር የሚያሳይ ነውና።

፪፦ ነገር ግን በአንዳንድ ገድላትና ድርሳናት ውስጥ በተለያዩ ምክንያቶች ብዙ ስሕተቶች ሊገኝባቸው ይችላል። ይህ እንዳይፈጠር የሊቃውንት ጉባኤያችን ጠንክሮ ማዕከላዊ የቅዱሳት መጻሕፍት ኅትመት ቢኖረውና በዚያ ቢታተሙ መልካም ነው። ብሔርን ከብሔር የሚያጣሉ፣ ጥላቻን የሚያስተላልፉ ሐሳቦች በግል በሚታተሙት ገድላት ይስተዋላል።

፫፦ ለምሳሌ ቡና ይጠጣል ወይስ አይጠጣም የሚለው ክርክር ምንጩ ገድልና ድርሳን ነው። ለምሳሌ እኔ ከአምስት የገድላትና የድርሳናት መጻሕፍት ቡና እንደማይጠጣ የሚገልጽ አግኝቻለሁ። በተማርኩባቸው ጉባኤ ቤቶችና በየትኛውም የመጻሕፍት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት ቡና አይጠጣም የሚለው ሐሳብ ተቀባይነት የለውም። ታዲያ ጉባኤ ቤቶች ይህንን ሐሳብ ቀጥታ የመቀበል ግዴታ አለባቸውን?

፬፦ ባለፈው መጋቤ ሐዲስ ኃይለ እግዚእ አሰፋ (የጠቅላይ ቤተክህነት የትምህርትና ሥልጠና ክፍል ኃላፊ) ማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት በነበረው ሥልጠና እንደማሳያ ብለው ብዙ የተአምረ ማርያም ቅጅዎችን እንዳዩ ገልጸውልን ነበር። እና በአንዱ የብራና ተአምረ ማርያም ቅጂ አጼ ቴዎድሮስን እጅግ በጣም አክፋፍቶ የሚገልጽ እንዳገኙ ገልጸውልን ነበር። አስተውሉ በአንዱ ቅጂ ነው የተገኘ እንጂ በሁሉ አይደለም። ትክክልነቱ ምን ያህል ነው? የሚለው ጥናት ይጠይቃል።

፭፦ ገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ላይ ዮሐንስ አሥር ጊዜ ከተለያዩ እናቶችና አባቶች እንደተወለደ የሚገልጽ አግኝቻለሁ። ዮሐንስ መጀመሪያ የተወለደ ከአዳምና ከሔዋን ሲሆን ስሙም ያን ጊዜ "ሔና" ነበረ ይላል። ከዚያ በየዘመናቱ እየተወለደና መጨረሻ ላይ ከዘካርያስና ከኤልሳቤጥ ተወለደ ይላል። ይህ በአንድ ወቅት ደብረ ሊባኖስ ገዳም ግጭት ፈጥሮ ነበር። በወቅቱ በገዳሙ የነበሩት የንታ ብሩክ ይህ መስተካከል አለበት ሲሉ አንዳንድ ከመጻሕፍት ሩቅ የነበሩ ሰዎች ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር ስለሌለ እንዳለ እንቀበላለን አሉ። ነገሩ ግን ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንጻር መመርመር አለበት። ይህ በአንዳንድ የገድለ ዮሐንስ መጥምቅ ቅጂዎች አይገኝም።

፮፦ ገድለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ላይ እስከ ዕለተ ምጽአት የጎጃም ሕዝብ ይቅር እንደማይባል ይገልጻል። በሌሎች ገድሎችና ድርሳኖች ለምሳሌ በገድለ አቡነ ሰላማ፣ በድርሳነ ኡራኤል፣ በገድለ ተከሥተ ብርሃን፣ በገድለ አቡነ ዜና ማርቆስ ደግሞ እስከ ዕለተ ምጽአት ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ብለው እግዚአብሔርን የሚያመልኩና እግዚአብሔርም የሚወዳቸው በሃይማኖታቸውና በምግባራቸው የተመሰከረላቸው የጎጃም ሰዎች ናቸው ይላል። እና የትኛውን እንቀበለው? መመርመር አለበት። ራእየ ማርያም ላይ ሻን*ቅላ ለዘለዓለም እንደማይጸድቅ የሚናገር አለ። በእውነት ይህን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት የተናገረችው? ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ጋር አይጋጭም?

፯፦ እንደዚህ እርስ በእርሱ የሚጋጩ ጉዳዮች ገድላት ላይና ድርሳናት ላይ ይስተዋላሉ። ይህ በተለያየ ምክንያት ነው። አንዳንድ መምህራን ሚሲዮናውያን ኢትዮጵያውያንን ለማለያየት ያስገቧቸው ናቸው ይላሉ። ይህ ሁሉ ቢሆንም ገድላትና ድርሳናት የሚታረሙት እየታረሙ በማዕከላዊነት በጠቅላይ ቤተክህነት ቢታተሙ እነዚህን ችግሮች መቅረፍ ይቻላል።

፰፦ በጥንተ አብሶ ዙሪያ ለምሳሌ ማኅበረ ቅዱሳን ባሳተመው ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በጻፉት መጽሐፍ የሰው ልጅ ከጥንተ አብሶ የሚላቀቅ ሲጠመቅ ነው ይላሉ። ሌሎች ደግሞ ጥንተ አብሶ በክርስቶስ መሰቀል ተወግዷል። ከዚህ በኋላ ሰው ቢኮነን እንኳ ራሱ በሠራው ኃጢአት እንጂ በጥንተ አብሶ አይደለም ይላሉ። (በጉባኤ ቤቶች ያለው አስተምህሮ ይህኛው ነው። በክርስቶስ መስቀል የውርስ ኃጢአት ጠፍቷል የሚል ነው። የእኔም አቋም ይህ ነው)። ጥንተ አብሶ የሚለው የግእዝ ቃል ሲሆን የበደል መጀመሪያ ማለት ነው። ይኸውም አዳምና ሔዋን የሠሩት በደል ነው። ይህ በደል ለአዳምና ለሔዋን ብቻ ይነገራል። የእነርሱ የበደል ውጤት (መርገም) ከእነርሱ ወደሚወለዱት ልጆች ተላልፏል። ይህን ውጤቱን የውርስ ኃጢአት እንለዋለን። ቅድስት ድንግል ማርያም የውርስ ኃጢአት የለባትም። ቀደሰ ማኅደሮ ልዑል እንዲል ከማኅፀን ጀምሮ ራሱ እግዚአብሔር ጠብቋታልና።

፱፦ በሚዲያ ዞር ዞር ስል ሕዝቤ ለሁለት ተቧድኖ ይቧቀሳል። በሁለቱም ወገን ያለው በእመቤታችን ንጽሕናና ቅድስና ይስማማል። ጠቡ በቃላት ያለመግባባት ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ሁሉም ጽንፍ ይዞ የአንዱ ደጋፊና የአንዱ ነቃፊ ሆኖ በየራሱ ትርጉም ክፉ ስም ይሰጣጣል እንጂ ቆም ብሎ አንዱ አንዱን ለማዳመጥ ጊዜ ቢሰጣጡ ተመሳሳይ አረዳድ ላይ ይደርሱ ነበር። አንዳንዱ ደግሞ ስለጉዳዩ የሚያውቀው ነገር የለም። ነገር ግን በደጋፊነትና በነቃፊነት ጎራ ይተራመሳል። የዚህ መፍትሔው ከፍ ያሉ ጉዳዮች ላይ ዝም ብሎ ማዳመጥ የተሻለ ነው።

፲፦ ወቅት እየጠበቁ የሚያከራክሩ ጉዳዮች አሁንም ብዙ አሉ። ለምሳሌ የልደት ጾም በዘመነ ዮሐንስ ህዳር 15 ይጀመራል ወይስ 14? ጥምቀት ሰኞ ሲውል ቅዳሜና እሑድ ይጾማል ወይስ እሑድ ብቻ የመሳሰሉ ጉዳዮች ይነሳሉ። (እነዚህን የጠቀስኳቸው ታዋቂ ስለሆኑ እንጂ ሌላም ቀኖናዊ ያልሆኑ ከፍ ያሉ ብዙ ጉዳዮች አሉ። ለጊዜው ከዚህ አልጠቅሳቸውም)። አሁን ዘመኑ የሚዲያ ስለሆነ ሁሉም የየራሱን አብነት እየያዘ ከሚወጋገዝ በማዕከላዊነት ሊቃውንት ተሰብስበው ወጥ የሆነ እይታ እንዲኖር ማድረግ ግድ ይላል። የሊቃውንት ጉባኤ ከዘመኑ መቅደም አለበት። EOTC Tv ከአሉባልታና ከጳጳሳት ውዳሴ ወጥቶ ዘመኑን የሚመጥንና ጥያቄዎችን ቀድሞ የመመለስ ሥራ ሊሠራ ይገባል።

ኦርቶዶክሳዊው መንገድ ጉዳይ ተኮር ነው። ክርስቶስ ኃጢአትን እንጂ ኃጢአተኛን አልጠላም ብሏል። ይህ ጉዳይን በጉዳይነቱ መሞገት እንደሚገባ ያስረዳናል። ሁሉም ሰው የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ከውስጥም ከውጭም ጠላቶች መጠበቅ አለበት። ሲጠብቅ ግን እውነትን መሠረት አድርጎ እንጂ በተሳሳተ ፍረጃ፣ ስምን በማጥፋት፣ በስድብ ሊሆን አይገባም።

© በትረ ማርያም አበባው
@yetewahedofera
@yetewahedofera
@yetewahedofera


🌻አስኳላ online school 📖 dan repost
⭐️

ሰላም 🫡 እንደምን ናችሁ ይህ @Askuwala_Creative ነው። በዚህን ጊዜ አለማችን ወደ Digital💻 ነገሮች ፊቷን አዙራለች🌐 አመናቹም አላመናቹም Traditional things are going to be የድሮ ታሪክ🤷‍♂ So ከጊዜው ጋር መሄድ ደግሞ የእኛ ድርሻ ነው 😎 በዚህ ጊዜ ደግሞ Digital Skills🖥 are one of the leading service sectors የ Digital world📍 ተስእጦ ያለው Such like↔️

Graphics Designing 💻
Video editing 🎞
Content Creating 👾
Content Writing 🖌
Story telling 📝
Digital marketing 💵


ብቻ ምን አለፋቹ ከዚህም ያለፉ ብዙ Skills ያለው ሰው💻 በዚህን ጊዜ ተፈላጊ ነው🤝
እኛም ይህን በመገንዘብ እነዚህን Digital Skills በነፃ-Freely
እናንተን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል 🫡 ሳትዘገዩ ቶሎ ተቀላቀሉን🥰


⭐️Askuwala Creative😀💻📈

Unlock your creative potential!
🤜  We're here to help students like you to master the essential skills of the digital world. 🌐💻  Get ready to learn, grow, and create amazing things! 🤩

JOIN: @Askuwala_creative
share forward ለጓደኞችዎ
@Askuwala_Creative
@Askuwala_Creative
@Askuwala_Creative


🌻አስኳላ online school 📖 dan repost
⭐️

ሰላም 🫡 እንደምን ናችሁ ይህ @Askuwala_Creative ነው። በዚህን ጊዜ አለማችን ወደ Digital💻 ነገሮች ፊቷን አዙራለች🌐 አመናቹም አላመናቹም Traditional things are going to be የድሮ ታሪክ🤷‍♂ So ከጊዜው ጋር መሄድ ደግሞ የእኛ ድርሻ ነው 😎 በዚህ ጊዜ ደግሞ Digital Skills🖥 are one of the leading service sectors የ Digital world📍 ተስእጦ ያለው Such like↔️

Graphics Designing 💻
Video editing 🎞
Content Creating 👾
Content Writing 🖌
Story telling 📝
Digital marketing 💵


ብቻ ምን አለፋቹ ከዚህም ያለፉ ብዙ Skills ያለው ሰው💻 በዚህን ጊዜ ተፈላጊ ነው🤝
እኛም ይህን በመገንዘብ እነዚህን Digital Skills በነፃ-Freely
እናንተን ለማስተማር ዝግጅታችንን ጨርሰናል 🫡 ሳትዘገዩ ቶሎ ተቀላቀሉን🥰


⭐️Askuwala Creative😀💻📈

Unlock your creative potential!
🤜  We're here to help students like you to master the essential skills of the digital world. 🌐💻  Get ready to learn, grow, and create amazing things! 🤩

JOIN: @Askuwala_creative
share forward ለጓደኞችዎ
@Askuwala_Creative
@Askuwala_Creative
@Askuwala_Creative


የዕለቱ ስንቅ

ተወዳጆች ሆይ! እስኪ ልጠይቃችሁ፦ አንድ ሰው የተጣራ ወርቅ ልሰጣችሁ እመጣለሁና የኾነ ቦታ ላይ ጠብቁኝ ቢላችሁ ምን ታደርጋላችሁ? ወደዚያ ቦታ ለመሔድ አስፈላጊ ነው የምትሉትን ኹሉ አታደርጉምን? ቀኑን ሙሉም ቢኾን ቁጭ ብላችሁ አትጠብቁምን? እግዚአብሔር እሰጣችኋለሁ ያላችሁ ግን አንዲት ወይም ዐሥር ወይም ሃያ ወይም መቶ ወይም አንድ ሺሕ ቅንጣት ወርቅ አይደለም፤ ወይም ምድርን ኹሉ አይደለም፡፡ ከዚህ ኹሉ የምትበልጠው መንግሥተ ሰማያት እንጂ፡፡ ከዚህ የሚበልጥ ስጦታ ታዲያ ምን አለ? ይህን ስጦታ ለማግኘት የማይደክሙ ሰዎችስ እንደምን ያሉ ምስኪናን ናቸው?

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

share
@yetewahedofera
@yetewahedofera
@yetewahedofera


​​#ቢያበሉኝ_ቢያጠጡኝ

ቢያበሉኝ ቢያጠጡኝ ፈትፍተዉ ቢያጎርሱኝ
ያሻኸዉን ዉሰድ ሁሉ የአንተ ነዉ ቢሉኝ
እኔስ እንደ ሥሟ የጣፈጠ አጣሁኝ
እኔስ እንደ ሥሟ የጣፈጠ አጣሁኝ /2/
አዝ...........
የእዚህ ዓለም ነገር ባዶ ሆኖብኛል
ዛሬ የበላሁት ነገ ይርበኛል
መራራው ሕይወቴ ጣፋጭ የሚሆነው
እመቤቴ ስሚኝ በአንቺ ጨዉነት ነዉ
አዛኝቷ ስሚኝ በአንቺ ጨዉነት ነው /2/
አዝ.......
አንቺ የሌለሽበት ማዕዴ ባዶ ነዉ
ሥምሽን ቃልጠራሁ ጣፋጭ መራራ ነዉ
በእጄ ከጨበጥኩት የመሶብ እንጀራ
ማርያም የሚለዉ ሥም ጣፋጭ ነዉ ሲበላ/2/
አዝ........
ተስፋ ያደረገ አንቺን በሕይወቱ
ስለሆንሽለት ነዉ ለተማሪ ራቱ
እኔም እልሻለሁ የኑሮ ጣዕሜ
ከሞት ወደ ሕይወት መሸጋገሪያዬ /2/


የዕለቱ ስንቅ

ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡

ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡

ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡

ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱን ልክ በእሳት ፊት እንደወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡
     
        ምክር ወተግሳጽ ዘቅዱስ ኤፍሬም

✨✨✨ሠናይ ዕለተ ሐሙስ ✨✨✨


አበው ስለ #እመቤታችን_ዕረፍት እንዲህ አሉ፦

"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ

"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ

"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ

(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)


+ከአእላፋት ማግስት+

Credit: ዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው (@yohannes_getachew1)

''ይሄን ስእል እያመለክሽ ነው ሳታገቢ የቆየሽው በጌታ በእየሱስ ስም መንፈስሽን ወጋሁት''

እናቴ ናት በጠዋት እንዲህ የምትለው። አሁንማ ገና እየደረሰ በመሆኑ፥ አእላፋት ዝማሬ ብቻ ሆኗል ወሬው እሱ ይረብሻታል።

ስለ እናቴ ትንሽ ላውራቹህ...

ኤልሳ ትባላለች። ሲበዛ ተጫዋች፥ ረጅም፥ በጣም ቀይ፥ ስትስቅ ጥርሷ የሚያምር፥ በዛ ላይ ዲምፕል ያላት ውብ ናት። አባቴ ደግሞ ሱራፌል ይባላል፤ ዲያቆን ነበር። በእርግጥ እኔ 16 አመቴ እያለ ነው የሞተው። ሰዎች ስለ እርሱ አውርተው አይጠግቡም። ሰው ቀና ብሎ የማያይ፥ ትንሽ ትልቁን አክባሪ፥ ጸሎተኛ ነበር ፤ መምህሩ ሲቀሩ እርሱ ነበር ጉባኤ ዘርግቶ የሚያስተምረው። ሁሉም ነበር የሚወደው። እኔን ራሱ ውዳሴ ማርያም፥ ዳዊት፥ ቅዳሴ፥ ሰዓታት አስተምሮብኛል። '

'ሰበኔ... ሴት ሆንሽብኝ እንጂ አንቺን ዲያቆን ነበር የማደርግሽ'' የሁል ጊዜ ንግግሩ ነበር።

እናቴ አባቴ በእግዚአብሔር ላይ ያለው መተማመን ይገርማታል። እኔ ልክ 15 አመት ሲሆነኝ አባቴ በጠና ታመመ። የሳንባ ካንሰር ያዘው። ከቤት መውጣት ከበደው፤ ቀኑን ሙሉ የሚያሳልፈው አልጋ ላይ መጽሐፈ መነኮሳትን እያነበበ ነበር። ትንሽ ህመሙ ባስ ሲልበት ደግሞ መጽሐፉን ደረቱ ላይ አድርጎ ለሰአታት መተንፈስ የከብደው ነበር። ከእርሱ ህመም በኋላ ቤታችን ውስጥ ሳቅ የሚባል ጠፋ። እናቴ ቀይ ፊቷን ማድያት ወረሰው።

.......የሆነ ማክሰኞ ቀን ጠዋት ላይ ''ኡኡኡኡኡኡኡኡ'' የሚል ጩኸት ከእንቅልፌ ቀሰቀሰኝ። እናቴ ነበረች። ብርድ ልብሱን ከራሴ ላይ በስርአት ሳላወልቅ ሮጥኩኝ። ኤልሲ አባቴን አቅፋ ፥-

"ጌታዬ ጉድ አታድረገኝ ባክህ ጉድ አታድርገኝ"

"እማ አባቴ ምን ሆነ?" ......እምባዬ ከየት እንደመጣ አላውቅም። ፊቴ ርሷል...

"የልጀነት ፍቅሬ ኧረ ተው" ትላለች።

"እማ አባቴ ምን ሆኗል?!"

"ጉድ አረከኝ! ብቻዬን ለማን ጥለከኝ! ኧረ ያላንተ አይሆንልኝም! ኧረ ጉዴ ኧረ ጉዴ ኧረ ጉዴ"

ጩኸታችንን የሰሙ ጎረቤቶቻችን ቤታችንን ሞሉት። በአንዴ ግማሹ ቲቪ ይሸፍናል፥ ግማሹ ስለ ድንኳን ያወራል......ራሴን ሳትኩ፤ ስነቃ ቀብር ሊሄዱ ህዝብ መጥቷል። ቤቱ ውጪው ግጥም ብሏል። ያ ሁሉ ህዝብ አንድ አባቴን አልሆን አለኝ.....

አባቴ ካረፈ ጊዜ ጀምሮ ቤታችን የማይቀሩ የማይቀሩ 3 ሰዎች ነበሩ። እነዚህ የእናቴ የስራ ባልደረቦች ታዲያ በመጡ ቁጥር ለእናቴ እንፀልይልሽ ብለዋት ነው የሚሄዱት፤ የሆነ ቀን ላይ ከታናናሾቼ ጋር ጸሎት እያደረግን "ከዛሬ ጀምሮ የዚህ ቤት ሃይማኖት ተቀይሯል!" አለችን።

"ወደምን?" አልን

"ጌታን ተቀብለናል! ነገ ትጠመቃላችሁ። አቁሙ አሁን!"

"እንዴ ኤልሲ! እኛ እኮ ልጅ እያለን ተጠምቀናል"

"አንቺ ልጅ! ተናገርኩ በቃ!"

"አልቀይርም! አባቴ ያስተማረኝ ያወረሰኝ ነው፤ አልቀይርም!" አልኩ።

ኤልሲም መልሳ "ነው? ከሆነ ከቤቴ ውጪ! እናንተም እንደዛ ነው?

ታናሽ እህቴም አዎ አለች።

"ውጡ! ችግር እና ረሃብ ሲፈራረቅባችሁ ትመጡ የለ!" አለችን በቁጣ።

ስልኬን አንስቼ ለአያቴ ደወልኩ። አያቴ ብቻዋን የምትኖር፥ በጣም ትልቅ ጊቢ ያላት፥ እሱ ላይ ወደ 20 ምናምን ቤት ሰርታ የምታከራይ ሴት ናት። ስደውል ኑ ኧረ ኑ አለች

......... እናቴ ሃይማኖቷን ቀየረች። ሁሉንም እኛ ክፍል የነበረ ስእለ አድኅኖ አውጥታ አቃጠለች። የአባቴን ግን ከበዳት። የእርሱን ዳዊት፥ የጸሎት መጻሕፍት፥ ሁሉን ነገሩን በአንድ ላይ አድርጋ አንድ ክፍል ውስጥ ቆለፈችበት። እኛም አያታችን ጋር መኖር ቀጠልን።

---------------------------------------------------

እናቴን ሃይማኖቷን ያስቀየሯት ሰዎች Theology እንድትማር አደረጉና ፓስተር ሆነች ።

ዛሬ...

"እሺ ባክሽ... አእላፋት ምናምን እያላችሁ ነው ደግሞ በነጭ ልብስ ጣኦት ልታመልኩ"

"ተይ እንጂ እማዬ... የማይሆን አትናገሪ። ለምን ዛሬ አብረን አንሄድም?"

"ማን? እኔ? ሆሆሆሆሆሆሆሆ... ሥራ አልፈታሁም"

"ምን ችግር አለው? ከደበረሽ ቶሎ እንወጣለን።"

"ቆይይይይይ እሄዳለው። የምሄደው ግን እንዴት ልክ እንዳልሆናችሁ ላሳይሽ ነው!"

ሁላችንም ለባብሰን ወጣን። በጊዜ ነበር የደረስነው፤ ቦሌ መድኃኔዓለም ሞልቷል። እንደምንም ብለን ፊት ተጠጋን። ዲያቆኑ "እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ" ይላል። ቁርጥ የአባቴን ድምፅ! ኤልሲ ደነገጠች። አባቴን ያየችው መስሏት ተንጠራርታ ፈለገችው፤ የለም። የሚፀየውን ጸሎት በግእዝም በአማርኛም ስታየው ቆየች። እምባዋ ይፈስ ጀመር። ጸሎቱ ተጠናቆ ነጫጭ የለበሱ ዘማሪያን መድረኩን ሞሉት። መዝሙር ቀጠለ። ቸሩ ሆይ የሚለው መዝሙር ዘማሪዎቹ መዘመር ጀመሩ። የአባቴ የሚወደው መዝሙር ነበር። የሲቃ ድምጽ አውጥታ አለቀሰች። አሳዘነችኝ ደስም አለኝ። መዝሙሩ አለቀ። በአባቶች ብራኬ ተጠናቀቀ። ኤልሲ ሙሉ ሰአት እያለቀሰች ነበር ።

"ኤልሲዬ በቃ አንቺ ሂጂ፥ እኛ እናስቀድሳለን።"

"ልምጣ?"

"የምርሽን ነው?"

"አዎ ልምጣ"

"ነይ" ድንጋጤዬ ያስታውቃል።

ማህሌቱ አልቆ፥ ቅዳሴው አልቆ፥ ቤት ገባን። እኛ ቤት ከመጣሁ 10 አመት አልፎኝ ነበር። ያው ነው፥ ምንም አልተቀየረም። እናቴ ሮጣ ጸሎት ቤት ገባች። ሁሉ ነገሩ አባቴን አባቴን ይላል። ትልቅ የእመቤታችን ምስለ ስዕል ፊት ወድቃ አለቀሰች።

"ሰበኔ አሁን ገባኝ! ልቤ ተሰብሬ ሲያገኙኝ ዓለም ገደል ስትሆንብኝ አግኝተውኝ ነው! ልጆቼ ይቅር በሉኝ! በጎደለኝ በኩል ሲቆሙ ወዳጆች መሰሉኝ ......"

ተቃቅፈን ተላቀስን። ምን ተረዳሁ መሰላችሁ? እግዚአብሔር ስራው Mysterious ነው። እንዲህ ነው ብለን Define የማይደረግ። ዛሬ ላይ ቤተሰቤ ሙሉ ሆኗል፤ እናቴም ወደ ክርስትና ለመመለስ ትምህርት ለመማር ከመምህሬ ጋር አገናኝቻለሁ። ከ 10 ዓመት ከብዙ ነገሮች በኋላ እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰማኝ። እጆቼን ከፍ አድርጌ እንዲህ ብዬ ጸለይኩ...

"የእኔን እምባ ያቆምክ እግዚአብሔር... እምባቸውን ለሚያወጡ ድረስ" ብዬ። "ሰላም ለናፈቁ ሁሉ ሰላም ስጥ። አባቴ የደከሙ ልቦችን አሳርፍ፥ ፈገግታን የናፈቁን ሁሉ ሳቅ አጥግብ፥ ለደስታ የተግደረደሩትን ሁሉ አላምዳቸው ...ባለቀሱበት ቦታ እንባቸውን አብስ። ሁሉን ቻይ ሆይ፥ የመዳናቸውን ቀን አታርቅ።"

ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው
ጥር 1 / 2017 ዓ.ም


#በጥምቀት_ዙሪያ_የሚነሱ_ጥያቄዎች_እና_መልሶቻቸው
#ጌታችን_ለምን_ተጠመቀ?
1. ምሥጢርን ለመግለጥ፡-
ጌታችን በፈለገ ዮርዳኖስ ሲጠመቅ ምስጢረ ሥላሴ ግልፅ ሆኗል፡፡ አብ በደመና “የምወደው የምወልደው ልጄ ይህ ነው” በማለቱ አብ የወልድ አባት መሆኑ ታወቀ፡፡ መንፈስ ቅዱስም የባሕርይ ሕይወቱ መሆኑን ሲያስረዳ በአምሳለ ርግብ በራሱ ላይ ተቀመጠ ወልድም በተለየ አካሉ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ ታየ፡፡ ስለዚህ ምሥጢርን ለመግለጥ ስንል የአንድነት የሦስትነት ምስጢር በጐላ ሁኔታ እንዲታወቅ ተጠመቀ ማለት ነው፡፡ /ማቴ. 3፥16/

2. ትንቢቱን ለመፈፀም፡-
በመዝሙር 46/47/፥16 ላይ “አቤቱ ውሆች አዩህ፣ ውሆችም አይተውህ ፈሩ ጥልቆች ተነዋወጡ ውሆችም ጮኹ፡፡” ተብሎ በቅዱስ ዳዊት የተነገረውን ትንቢት ለመፈፀም ተጠመቀ፡፡

3. አርአያ ሊሆነን፡-
ተጠምቆ እንድንጠመቅ አደረገን ሥርዓትን ሠራልን ቀድሞ በአርአያውና በአምሳሉ እንደፈጠረን አሁንም አርአያ ምሳሌ ሆነን፡፡ ለዚህም ነው ምሳሌን ከእኔ ተማሩ ያለን፡፡ /ማቴ 11፥29/ ለትምህርት ለአርአያ /ዮሐ. 13፥1-17/

4. የዕዳ ደብዳቤያችንን ለመደምሰስ፡-
አዳምና ሔዋን ፍዳው በፀናባቸው መከራው በበዛባቸው ጊዜ የሚያቃልልላቸው መስሏቸው ዲያብሎሰ ስመ
ግብርናችሁን ጽፋችሁ ስጡኝ ባላቸው ጊዜ አዳም ገብሩ ለዲያቢሎስ (አዳም የዲያብሎስ የወንድ አገልጋይ) ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ (ሔዋን የዲያብሎስ ሴት አገልጋይ) ብለው ጽፈው ሰጡት፡፡ ዲያብሎስም ይህንን ደብዳቤ አንዱን በሲኦል አንዱን በዮርዳኖስ አስቀመጠው፡፡ በዮርዳኖስ ያስቀመጠውን ጌታችን ሲጠመቅ እንደሰውነቱ ረግጦ ደምስሶታል፡፡ ይህንን ጽሕፈት ለመደምሰስ ነው ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው፡፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተፃፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው፡፡” ያለው ቆላ 2፥14

#ጌታችን_መች_ተጠመቀ?

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በ5531 ዓመተ ዓለም ዘመነ ሉቃስ ማክሰኞ ጥር 11 ቀን ከሌሊቱ በ10ኛው ሰዓት ነበር፡፡ ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 19 በተጠመቀም ጊዜ ዕድሜው 30 ዓመት ከ13 ቀን ነበር፡፡ /ሉቃ. 3፥23/

#ጌታችን_ስለምን_በ30_ዓመት_ተጠመቀ?
በብሉይ ኪዳን ሥርዓትና ልማድ ካህናት ለቤተ እግዚአብሔር ተልእኮ እና መንፈሳውያን አገልግሎቶች ከ30 ዓመት ዕድሜ በፊት አደባባይ አይወጡም ነበር፡፡ እጅግ አስፈላጊ እንኳ ቢሆን ከ20 እና 25 ዓመት አስቀድሞ ለአገልግሎት መሰየም ልማድ አልነበረም፡፡ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች በዕድሜና በዕውቀት የበሰሉ፣ በጠባይና በሥራ ልምድ የተፈተኑ ተልዕኳቸውን በብቃት ለመወጣት በተገልጋዩ ሕዝብ ዘንድ የተመሰከረላቸው መሆን ነበረባቸው፡፡ /ዘፀ. 4፥3፤1ዜና መዋ. 23፥24፤ 1ጢሞ.  3፥6-10/ ያንን ሥርዓት ለመፈጸም ጌታችን የተጠመቀውና ለትምህርተ ወንጌል የተገለጠው በ30 ዓመቱ ነበር፡፡

ዮሐንስ መጥምቅም የጌታን መምጣት ለማወጅ በዮርዳኖስ ይሁዳ ምድረ በዳዎች ወጥቶ የታየው ከ30 ዓመት ዕድሜው በኋላ ነው፡፡ ሌላው ዐቢይ ምክንያት የሰው ሁሉ መጀመሪያ አዳም የ30 ዓመት ጎልማሳ ሆኖ ተፈጥሮ በ40ኛ ቀን ተሰጥቶት ኋላም በኃጢአት ምክንያት ያስወሰደውን ልጅነት ለማስመለስ ነው፡፡

ክርስቶስ የተጠመቀው ክብር ሽቶ ሳይሆን የአብ የባሕርይ ልጅነቱን (የባሕርይ አምላክነቱን) ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ለማስመስከር፣ ውኃውን ለመቀደስ፣ የአዳምን ልጆች የእዳ ደብዳቤ ለመደምሰስና በስህተት የጠፋውን የልጅነት ክብር ለመመለስ ነው፡፡ ጌታ ተጠምቆ ከውኃው ከወጣ በኋላ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ በማረፍ አብ በደመና ‹‹ይህ ልጄ ነው›› ብሎ ሲመሰክርለት ምሥጢረ ሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በጉልህ ተረጋግጧል፡፡ /ማቴ. 3፥16/

#ጌታችን_በዮሐንስ_እጅ_ለምን_ተጠመቀ?

ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ሲሆን በአገልጋዩ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ይጠመቅ ዘንድ በፍጹም ትሕትና ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ይህንንም ያደረገልን አብነት ሊሆነን ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስን ‹‹መጥተህ አጥምቀኝ ›› ብሎት ቢሆን ኖሮ ነገ ነገሥታቱና መኳንንቱ ካህናቱን መጥታችሁ አጥምቁን ባሉ ነበር ስለዚህ እንዲህ እንዳይሆን ነው፡፡ ጌታችን ‹‹ጌታ ስሆን በባርያዬ እጅ እንደተጠመቅሁ እናንተም ወደ ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ በካህናት እጅ ተጠመቁ›› ሲል ነው፡፡

ጌታችን በዮርዳኖስ የተጠመቀው ልጅነትን የምታሰጥ ጥምቀትን ባርኮ ቀድሶ ሊሰጠን እንጂ ክብር እንዲሆነው አይደለም፡፡ ምክንያቱም፡- እርሱ እከብር አይል ክቡር እጸድቅ አይል ጻድቅ ነውና፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_ጌታችንን_በማን_ስም_አጠመቀው?

ጌታችን ዮሐንስን አጥምቀኝ ባለው ጊዜ "ሌላውን በአንተ ስም አጠምቃለሁ አንተን በማን ስም ላጥምቅህ? በአብ ስም እንዳላጠምቅህ አብ አባትህ ባንተ ሕልው ነው በወልድ ስም እንዳላጠምቅህ ወልድ አንተ ነህ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዳላጠምቅህ መንፈስ ቅዱስ ሕይወትህ ባንተ ሕልው ነው ታዲያ በማን ስም ላጥምቅህ?" ብሎ ቢጠይቀው ጌታም ‹‹እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለም ካህን ብርሃንን የምትገልጥ የአብ የባሕርይ ልጅ ሆይ ይቅር በለኝ›› ብለህ አጥምቀኝ አለው፡፡

#ዮሐንስ_ጌታን_ሲያጠምቀው_እጁን_ለምን_አልጫነበትም?
- ዮሐንስ በጥምቀት አከበረው /ልዕልና ሰጠው/ እንዳይባል፡፡
- መለኮትን በእጅ መንካት ስለማይቻል

#ጌታችን_ጥምቀቱን_ለምን_በዮርዳኖስ_አደረገው?
በኢየሩሳሌም አካባቢ ብዙ ወንዞች ኩሬዎችና ሐይቆች መኖራቸው የታወቀ ነው፡፡ ጌታ ጥምቀቱን በዮርዳኖስ ያደረገው ስለዚሁ አስቀድሞ የተነገረውን ትንቢት መፈጸሙን ለማረጋገጥ ነው፡፡ ‹‹ባሕር አይታ ሸሸች ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ›› /መዝ.113፥3/ ከዚህም ጋር ከላይ ምንጩ አንድ የሆነው ዮርዳኖስ ዝቅ ብሎ በደሴት ተከፍሎ እንደገና እንደሚገናኝ በግዝረት በቁልፈት (በመገዘርና ባለመገዘር) ተለያይተው የነበሩ ሕዝብና አሕዛብ መላው የአዳም ልጆች በጌታችን ጥምቀት አንድ መሆናቸውን የሚገልጽ ትርጉም አለው፡፡ እስራኤል ዮርዳኖስን ተሻግረው ምደረ ርስት ገብተዋል፡፡ ያመኑ የተጠመቁ ምዕመናንም በጥምቀት ገነት መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉ፡፡ ሌላው በዮርዳኖስ ተጥሎ የነበረውን የዕዳ ደብዳቤ ይደመስስልን ዘንድ /ቈላ. 2፥14/

#ጌታችን_ለምን_በውሃ_ተጠመቀ?
እግዚአብሔር አምላክ በዘመነ ኦሪት ሰብዐ ትካትን በንፍር ውሃ ፈርኦንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ካጠፋ በኋላ ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጂ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረ ለማጠየቅ በውሃ ተጠመቀ ( ዘፍ 7÷17፤ ዘጸ 14÷1-29)

አንድም ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ከገሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም ውሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ መልክዓ ሥላሴን የአምላክን ቸርነት ርህራሔ ታያላችሁ ሲል ነው፡፡

አንድም በማር በወተት ቢጠመቅ ኖሮ እነዚህ ለባለጸጎች እንጂ ለድሆች አይገኝም ውሃ ግን በሁሉ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ጥምቀት የታዘዘ ለሁሉ ነው ሲል ነው፡፡

አንድም ማርና ወተት ቢታጠብበት ያቆሽሻል እንጂ አያነጣም ውሃ ግን እድፍን ያስለቅቃል እናንተም በማየ ገቦ ብትጠመቁ ከኃጢአት ትጠራላችሁ ሲል ነው፡፡


"ዮርዳኖስ"
/መነባንብ/

አንቺ ሰፊ ባህር ዮርዳኖስ መስክሪ
የተጠመቀብሽ የአለም ፈጣሪ
ትንቢት መነገሩ በዳዊት ነብይ
ድምፅ በውኖች ነው ብሎ መመስከሩ
በውኖች ይታያል ብሎ መዘከሩ
በዩርዳኖስ መሸሽ ትልቁ ሚስጥር
የዩርዳኖስ ባህር አምላኩን ማክበሩ
በጥልቅ ውሃዎች ላይ ስልጣን አለው ሲሉ
አምላክን ማክበሩ ፈርቶ መንቀጥቀጡ
ሰዎች ሳይረዱ ወንዙ መረዳቱ
የዳዊት ትንቢት ትውልድ መዘንጋቱ
ምን ይባላል አሁን እውነትን መሣቱ
ሰው መዳኑን ንቆ እንዲህ መቅበዝበዙ
ዳዊት ለምን ሸሸ ብሎ  የጠየቀሽ
ባህረ ዮርዳኖስ ፈጣሪሽን አወቅሽ
ኧረ አንቺ ዮርዳኖስ ኢያሱየከፈለሽ
ሕዝበ እስራኤን በአንቺ ያሻገረብሽ
ከዕለቱ ክርስቶስ ውሃ ያጠጣብሽ
ኤልሳና ኤልያስ ደግሞ የቆሙብሽ
ለመጎናፀፍያ ከፍለው ያለፉብሽ
ንዕማር ሲጠመቅ ከለምጹየነፃብሽ
ሰው የሆነ ንጉስ ባንቺ ሲታይብሽ
ይህ ሁሉ ሲደረግ ትግሉ ሲሰምርብሽ
ዩሐንስ ሲያጠምቅ መድህን ሲመጣብሽ
እራሱን አዋርዶ ባንቺ ሲታይብሽ
ወልድ አምላክ በክብር ሲጠመቅ በውስጥሽ
እርጥበትሽ ሳይደርቅ እሳቱ ሳይፈጅሽ
ዮርዳኖስ ድንቅ ነው ጸንተሽ መገኘትሽ
ይመሰክር ጀመር ዩሐንስ ተረድቶ
የእግዚአብሔር በግ መጣ ይኽው ብሎ
እኔ አላውቀውም ጥንትም ነበር ደግም
አለ መስከር እውነት ተናገር
በእሳት የሚያጠምቅ ይመጣል እያለ
ታዲያ እንዲህ ሰዎች ሲጠመቁ
መድሐኒት ብቅ አለ ከወደ ጥምቀቱ
በዮሐንስ እጆች ሊጠመቅ ፈልጎ
ዩሐንስ አዘነ እጅግ ተፀፀተ
አምላከ ሰማይን እንዴት ላጥምቅ ብሎ
ፅድቅን ለመፈፀም ወዲህ መጣሁኝ
ብሎ ሲያስተምረው መድሐኒዓለም
ያጠምቀው ጀመረ በእሽታ መንፈስ
እየሱስ ሲጠመቅ በዮሐንስ እጅ
ሰማያት ተከፍተው ቃል ሲመጣለት
መንፈስ ቅዱስ መጥቶ በራሱ ላይ ሲያርፍ
የምወደው ልጄ ይህ ነው ስሙት
ተብሎ ሲነገር ከእግዚአብሔር አብ
የስላሴ ምስጢር በዮርዳኖስ ባህር
ተገልጾ ነበር የአንድነት ምስጢር
አንድነት ሶስትነት ያለመከፋፈል
ሰዎች ሲጠመቁ በስላሴ ስም
የእግዚአብሔር ልጅነት ያገኙ ነበር
ታዲያ ምን ይባላል የአሁኑ ትዕቢት
ስላሴ ምንድ ነው ብሎ መደንፋት
ኢየሱስ አንድ አካል ፍጡር ነው ማለት
ልበ ቆሻሻዎች የክርስቶስ ጠር
ጆረአቸው ተደፎኖ ልባቸው ቢዝል
በዮርዳኖስ ታይቷል የአንድነት ምስጢር
የወደደ ይምጣ የጠላ ይመለስ
አይከለስ እንደው የዮርዳኖስ እውነት
ከባህሮች ተመርጠሽ ዮርዳኖስ የታደልሽ ምስጢር ስላሴ የተገለፀብሽ
አንቺ ሰፊ ምድር ዮርዳኖስ መስክሪ
የተጠመቀብሽ የዓለም ፈጣሪ።
  ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

https://t.me/yetewahedofera


ብታነቡት አንድ ሥርዓት ትፈጽማላችሁ ታቃላችሁ 👍

ጾመ ገሃድ

ገሃድ ምንድን ነው?

ገሃድ የቃሉ ትርጉም መገለጥ፣ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ በ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና እንዲሁም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡(ማቴ 3፡13-17)

ይህን በማሰብ የምንጾመው ጾም “የገሃድ ጾም” ይባላል፡፡

በዚህ መሠረት የአሁን የገሃድ ጾም የራሱ አዋጅ አለው

ስንክሳር ዘጥር ፲ እንዲህ ብሎ ያዛል

ወለእመ ፡ ኮነ ፡ ዕለተ ፡ በይረሙን ፡ ዘውእቱ ፡ አስተርእዮ ፡ በዕለተ እሁድ አው፡በዕለተ፡ ሰንበተ አይሁድ፡ይጹሙ፡በእለተ ፡ ዓርብ ፡እምቅድሜሁ፡እስከ፡ምሴት፡በከመ ተናገርነ፡ ቅድመ ዳዕሙ ይትዓቀቡ፡እምነ፡በሊዕ፡ጥሉላተ።

ጥምቀት እሁድ ስለዋለ አስቀድመን አርብ እስከ 12 ሰአት ይጾማል። በዋዜማው ደሞ ቅዳሜ ከቅዳሴ በኃላ ምግብ መመገብ ይቻላል። ግን ጥሉላት አይበሉም።
ለምሳሌ  ሥጋ ፣ ወተትና የወተት ተዋጽኦ......

በረከት የምናገኝበት ጾም ያድርግልን!!!
@yetewahedofera
@yetewahedofera
@yetewahedofera


ዘንድሮ ከተራ ቅዳሜ ነው የሚውለው ፤ ጥምቀት ደሞ ገሀድ ጾም አለው

ጥያቄ ዘንድሮ እንዴት ነው ገሀድ ሚጾመው?

መልሳችሁን በ coment section ላይ ይላኩ ዋና ምላሹን በኋላ ይዘን እንመጣለን
@yetewahedofera
@yetewahedofera
@yetewahedofera


➢ ምን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ ❓

🔔• የምንሰጣቸው የማስታወቂያ አገልግሎቶች

┣➤ የ" ቻናል ማስታወቂያ "
┣➤ የ ዩቲዩብ ቻናል ማስታወቂያ
┣➤ ትሪትመንቶች እና
┣➤ ሌሎችም ሽያጮች ማስታወቂያ ያስተዋውቁ👍

በተመጣጣኝ ዋጋ
ለማስተዋወቅ ያናግሩን።

•➤አሁኑኑ ያናግሩን 👇

📩 •➤ 𝐈𝐧𝐛𝐨𝐱 𝐌𝐞
@fikreabe


በፈተና ወድቀህ እንደሆነ ፤ የኃጢአተኝነት(የጥፍተኝነት) ስሜት ከመጸለይ እንቅፋት እንዲሆንብህ አትፍቀድለት።
ንስሓ እስክገባ ብለህ መጸለይን ካቆምክ፤ መቼም ቢሆን ንስሓ አትገባም። ጸሎት ወደ እውነተኛ ንስሐ መግቢያ በር ናትና።

✍️ምክረ አበው🥰

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.