በትረማርያም አበባው Betremariam Abebaw


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


አቀድም አእኵቶቶ ለእግዚአብሔር

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


ብልጽግና ፈሪ ነው። ቦቅቧቃነቱ አሁን ካሉት የጠቅላይ ቤተክህነት ሰዎች ይከፋል። ለዚያም ነው ስሕተቱን ነቅሰው እንዲስተካከል የነገሩትን ጋዜጠኛዎች፣ የቤተክርስቲያን አባቶች፣ ፖለቲከኞች፣ ደራሲዎች እና ሌሎችንም እንዲታሰሩ ያደረገው። መሪዎቹ ለብዙዎች የኢትዮጵያውያን ሞት ተጠያቂ ናቸው። ወንጀለኞቹና መታሰር የሚገባቸው እነርሱ ናቸው። I hope በቅርብ ሁሉም የሥራቸውን ያገኛሉ።

ሁሉም ከጥቅመኝነት ወጥቶ እንደ ሕዝብ በማሰብ እኒህን የሕዝብ ነቀርሳዎች ከሥልጣን ማውረድ ይገባዋል።


ብልጽግና ፈሪ ነው። ቦቅቧቃነቱ አሁን በጠቅላይ ቤተ ክህነት ካሉ ሰዎች ይከፋል። ለዚያም ነው ስሕተቱን ነቅሰው እንዲስተካከል የነገሩትን ጋዜጠኛዎች፣ የቤተክርስቲያን አባቶች፣ ፖለቲከኞች፣ ደራሲዎች እና ሌሎችንም እንዲታሰሩ ያደረገው። መሪዎቹ ለብዙዎች የኢትዮጵያውያን ሞት ተጠያቂ ናቸው። ወንጀለኞቹና መታሰር የሚገባቸው እነርሱ ናቸው። I hope በቅርብ ሁሉም የሥራቸውን ያገኛሉ።

ሁሉም ከጥቅመኝነት ወጥቶ እንደ ሕዝብ በማሰብ እኒህን የሕዝብ ነቀርሳዎች ከሥልጣን ማውረድ ይገባዋል።


አንድ ቄስ ለጴንጤው ዐቢይ አሕመድ ወረብ ወረበለት። ድርጊቱ ስሕተት መሆኑን ስንናገር አንዳንድ ሰዎች ሥጋ ወደሙን የሚፈትትን ቄስ የፈለገ ቢያጠፋ ልንናገረው አይገባም ይላሉ። አንዲት ሴት የጌታን እግር በሽቱ ባጠበች ጊዜ ይሁዳ በብዙ ብር ተሽጦ ለነዳያን ይሆን ነበር አለ። ወንጌላዊው ዮሐንስ ይህንን ሲገልጽ ለነዳያን አስቦ ሳይሆን ይሁዳ ሌባ ስለነበር ነው ብሏል። እና ጳጳሳት፣ ቀሳውስት፣ መምህራን ፈርተው ከውሸት ጋር ተስማምተው ሲኖሩና ያን ጊዜ እነርሱን ደፈር ብለህ ስትናገር ለእነዚህ አካላት አዝነው ሳይሆን ራሳቸው እንደ ይሁዳ ሌባ ስለሆኑ ሲቃወሙ ታያለህ። ንስጥሮስን አትናገርብኝ ቢያንስ ሥጋውን ደሙን ይፈትት ነበር ከሚል ሰው ጋር መግባባት አይቻልም። የንስጥሮስን ክሕደት ሳይክድ በፊት ባደረገው ድርጊት መለካት አይገባም።

በቀድሞ ዘመን አንዳንድ መሪዎች አንዱን ወንድ ይሰልቡትና የቤተ-መንግሥት ሴቶች አጫዋች አድርገው ይሾሙት ነበር ይባላል። አሁንም መንግሥትን ተጠግተው ለቤተ መንግሥት ሴቶች ተረት ተረት እየተናገሩ እንዲያዝናኑ የተሾሙ ብዙ ስልቦች አሉ። በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር እንዳልደረሰ ለማስመሰል "ለቤተክርስቲያን ጥሩ ዘመን ነው" የሚሉ ስልቦች አሉ። ፈሪነት፣ ቦቅቧቃነት መልካም አይደለም። በተለይ ካህን ሲፈራ ያስቃል። ዘለዓለማዊ ሕይወት እንዳለ የሚሰብክ ቄስ በዚህ ምድር መኖርን ፈልጎ ከውሸት ጋር ተስማምቶ እንደማየት አስቂኝም አሳዝኝም ነገር የለም። በማንኛውም ጉዳይ ተስፋ አንቆርጥም። ካህን ትላንትን የሚያውቅ፣ ዛሬን የተረዳ፣ ነገን የሚያስብ መሆን አለበት። ለብር፣ ለሥልጣን፣ ለሆድ ብሎ እውነትን ደብቆ መኖር የለበትም። መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ ጉዳይ ካለ እንኳ በደስታ ራሱን መሥዋዕት ማድረግ አለበት።

© በትረማርያም አበባው


ሕዝቡ መፍትሔ እንዲሰጠው በተደጋጋሚ በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄዎቹን ሲጠይቅ ብልጽግናና የብልጽግና አክቲቪስቶች በሕዝቡ ይሳለቁ ነበር። ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በጊዜው እንዲሰጠው ገበሬው ጅራፍ ይዞ ሲጠይቅ በጉዳዩ የጅራፍ ፖለቲካ ብለው ተሳለቁበት። ከዚያ ሕዝቡ በሰላማዊ ሰልፍ መልኩ ጥያቄን መጠየቅ መፍትሔ እንደማያመጣ ሲረዳ የትጥቅ ትግል ማድረግ ጀመረ።

ከዚያ ብልጽግናና አክቲቪስቶቹ "በትጥቅ ትግል የሚፈታ" ችግር የለም እያሉ ማውራት ጀመሩ። በጣም አስቂኙ ደግሞ ከዚህ ቀደም ያሉትን ረስተው የሕዝቡን ጥያቄ እንመልሳለን ብለው ከማያልቅባቸው ውሸት ተናገሩ። ከዚህ በኋላ ብልጽግናን የሚያምን ትውልድ የለም። ምናልባት ከብልጽግና ጎን ቆመው ያሉትን ሰዎች እንኳ ብናጠናቸው በወንጀል የተዘፈቁ፣ በኮንዶሚኒየም የተታለሉ፣ ሕዝቡን ሲሰርቁ የኖሩ ሙሰኞችና ሌቦች ናቸው።

እኒህን አካላት ለመፋለም ብዙዎች ጫካ ገብተዋል። ምክንያቱም እንደ ብአዴን ጭቆናንና ኢፍትሐዊነትን ተቀብሎ ሺ ዓመት ከመኖር፣ ጭቆናንና ኢፍትሐዊነትን ተቃውሞ አንድ ቀን ኖሮ መሞት ይሻላል። ሰው መሞቱ ካልቀረ እውነትን ይዞ፣ ለእውነት ኖሮ መሞት ይገባዋል። ምክንያቱም ለትክክለኛ ነገር እየታገሉ መሞት ዘለዓለማዊ ሕይወትን ያሰጣልና ነው። ፖለቲከኛ ነገን አስቦ የሚናገር ነው መሆን የነበረበት። አሁን የምናያቸው ፖለቲከኞች ነን ባዮች ግን እንኳን ነገን ዛሬን አስበውንኳ አይናገሩም። እንኳን ሀገርን ቀበሌን የማስተዳደር አቅም የላቸውም።

© በትረማርያም አበባው




#PDF #PDF PDF PDF
ነገረ ክርስቶስን እስከ ክፍል 150 በፌስቡክ ገጼና በቴሌግራም ቻናሌ መመማራችን ይታወቃል። ይህ በፒዲኤፍ ተዘጋጅቶ በቴሌግራም ቻናሌ ስለተለቀቀ ገብታችሁ ማንበብ ትችላላችሁ።

ነገረ ክርስቶስ ከክፍል 150 እስከ ክፍል 300 ደግሞ ትንሽ አረፍ ብለን እንጀምራለን። ምንም እንኳ ያለንበት ጊዜ ብዙ ፈተናዎች ያለበት ቢሆንም ስለክርስቶስ መማር ጊዜን ይቀድሳል እንጂ አያሰለችምና መማር ማንበብ ተገቢ ነው።

የቴሌግራም ቻናሌ:- በትረማርያም አበባው
https://t.me/betremariyamabebaw ነው

ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፩ የተባለው ከክፍል 150 እስከ ክፍል 300 ደግሞ ክፍል ሁለት ስለሆነ ነው። እግዚአብሔር ከፈቀደልን ከክፍል 300 እስከ ክፍል 450 እያልን እንቀጥላለን።

© በትረማርያም አበባው


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፶
"ኢየሱስ መልሶ፦ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው" (ዮሐ. ፮፣፳፱)።

እግዚአብሔር የላከው የተባለ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እግዚአብሔር ሲል አብን፣ ወልድን፣ መንፈስ ቅዱስን ያመለክታል። "አንሰ ሶበ እቤ እግዚአብሔር እብል በእንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ" እኔ እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ ስለ አብ፣ ስለ ወልድ፣ ስለመንፈስ ቅዱስ እላለሁ እንዲል (ሃይማኖተ አበው)።

"የላከው" የሚለው ቃል "ሰው እንዲሆን ያደረገው" ተብሎ ይተረጎማል። ወልድን ሰው እንዲሆን ማድረግ ደግሞ የሦስቱም ሥራ ነው እንጂ ተለይቶ የአንዱ ብቻ አይደለም። በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን በአብም በመንፈስ ቅዱስም ማመን ነው። አብን፣ ወልድን፣ መንፈስ ቅዱስን የምናምነው እምነት አንድ እምነት ነው።

© በትረማርያም አበባው

የቴሌግራም ቻናሌ:- በትረማርያም አበባው ( Betremariam Abebaw)
https://t.me/betremariyamabebaw

የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፶፩ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፱
"ኢየሱስም እንጀራውን ያዘ፥ አመስግኖም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም ለተቀመጡት ሰዎች ሰጧቸው እንዲሁም ከዓሣው በፈለጉት መጠን" (ዮሐ. ፮፣፲፩)።

መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለእኛ አርዓያ ለመሆን እንጀራን ይዞ አመስግኖ ለደቀመዛሙርቱ ሰጥቷል። ለእኛ አርዓያ ለመሆን አመሰገነ እንጂ እርሱ ራሱ የምስጋና ባለቤት ነው። የሚመሰገነው እርሱ እኛን ለማስተማር አመሰገነ።

እኛም እርሱን አብነት አድርገን ምግብ ሲቀርብ አቡነ ዘበሰማያት ብለን እግዚአብሔርን አመስግነን ካህን ካለ ቆርሶ ይሰጠናል። አንድ ካህንና ብዙ ሰው ካለ ደግሞ ካህኑ ለዲያቆኑ ቆርሶ ይሰጠውና ዲያቆኑ ለሁሉ ያዳርሳል።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፶ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፰
"ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችኹ ነበር እርሱ ስለ እኔ ጽፏልና" (ዮሐ. ፭፣፵፮)።

አይሁድ የሙሴን ሕግ እንጠብቃለን ብለው ያስቡ ነበር። ነገር ግን የሙሴን ሕግ በትክክል ቢጠብቁ ኖሮ በኢየሱስ ክርስቶስ ያምኑ ነበረ። ምክንያቱም ለሙሴም ሕግን የሰጠው፣ ትንቢት ያናገረው እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና። የሙሴ ትንቢት ስለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነውና። ሙሴ ስለኢየሱስ ክርስቶስ ጽፏል።

"አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ መካከል ከወንድሞችህ እንደ እኔ ያለ ነቢይ ያስነሣልሃል ርሱንም ታደምጣለህ" ብሎ ለጊዜው ስለኢያሱ ፍጻሜው ግን ስለኢየሱስ ክርስቶስ ተናግሯል (ዘዳ. ፲፰፣፲፮)። ሙሴ እስራኤላውያንን ከአለት ውሃ አልፍቆ እንዳጠጣቸው ተነግሯል። ያ ዐለት ፍጻሜው ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ ጽፏል። "ወኰኵሕሰ ክርስቶስ ውእቱ" እንዲል። እና አይሁድ የሙሴን ሕግን ጠንቅቀው ቢያውቁ ኖሮ ክርስቶስን ባልተቃወሙት ነበር።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፱ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፯
"እኔ በአባቴ ስም መጥቻለኹ አልተቀበላችኹኝምም ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ ርሱን ትቀበሉታላችኹ" (ዮሐ. ፭፣፵፫)።

ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቴ ስም መጥቻለሁ ብሏል። በአባቴ ስም ብመጣ አልተቀበላችሁኝም ማለትም የባሕርይ አምላክ ነኝ ብየ ብመጣ አላመናችሁኝም ማለቱ ነው። ይኽውም አባቴ አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ መስክሮልኝ ብመጣ አላመናችሁኝም ማለቱ ነው። ሌላው ግን በራሱ ስም ቢመጣ ትቀበሉታላችሁ ማለቱ ወደፊት ሐሳዊ መሲሕ ራሱ ባወጣው ስም አምላክ ነኝ ብሎ ራሱ በራሱ መስክሮ ቢመጣ ታምኑበታላችሁ ማለቱ ነው።

ለሐሳዊ መሲሕ ሌላ ምስክር ሳይኖረው በራሱ ስም ብቻ መጥቶ ብዙውን በውሸት ያሳምናል። ለጌታ ግን አብ መስክሮለት፣ ዮሐንስ መጥምቅ መስክሮለት፣ ተአምራት መስክረውለት ቢመጣም ብዙዎች በእርሱ አለማመናቸውን ለመግለጽ እንዲህ አለ።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፶ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፮
"እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም እንደ ሰማኹ እፈርዳለኹ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና" (ዮሐ. ፭፣፴)።

ወልድ ከራሱ አንዳች ማድረግ አይችልም። ይህም ማለት አብ ልቡ ሆኖ፣ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋሱ ሆኖ በመገነዛዘብ ሥራውን ይሠራል እንጂ ብቻውን ምንም ማድረግ አይችልም ማለት ነው። ሦስቱ አካላት አንዱ ያለ አንዱ አይሠሩምና። የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻም ማለቱም ለእርሱ ከአብ የተለየ ፈቃድ እንደሌለው የሚያስረዳ ነው። የላከኝን ፈቃድ እሻለሁ ማለቱም የአብን ፈቃድ እሻለሁ ማለት ነው። ይህ ፈቃድ የእርሱም ፈቃድ ነውና።

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እንደመሆኑ ፍርዱ ቅን ነው። ፍርዱን ዘመን አይሽረውም። ምክንያቱም እርሱ ሲፈርድ ሁሉንም በምልዐት አውቆ ነው። የፍጡራን ፍርድ ግን ጉድለት አያጣውም። ምክንያቱም በውስን ዕውቀት የሚደረግ ስለሆነ ነው።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፯ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፭
"አብ በራሱ ሕይወት እንዳለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥታልና። የሰው ልጅም ስለ ሆነ ይፈርድ ዘንድ ሥልጣን ሰጠው" (ዮሐ. ፭፣፳፯-፳፰)።

ለአብ ሕይወትነት እንዳለውና ሕይወት የባሕርዩ እንደሆነ ለወልድም ሕይወትን ሰጠው። በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ መበላለጥ የለም። በክብር በሕይወት አንድ ናቸው። ክርስቶስ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ ብሏል። በሃይማኖተ አበውም አብ ሕይወት፣ ወልድ ሕይወት፣ መንፈስ ቅዱስ ሕይወት፣ አንድ ሕይወት ተብሎ የተገለጸው ይህኛው ሕይወትነት ነው። ይህኛው ሕይወትነት ግብረ ባሕርይ ነው። በከዊን ግን ሕይወትነት የመንፈስ ቅዱስ ብቻ ነው። ለወልድ ሰጠው ማለቱም ለወልድ መቀበል የሚስማማው ሆኖ አይደለም። ከተዋሕዶ በኋላ ሥጋ በቃል ርስት ወልድ ስለተባለ ስለ ሰውነቱ የተነገረ መሆኑን ማስተዋል ይገባል። ለዚህም ምስክሩ ቀጥሎ "እስመ ወልደ እግዚአብሔር ወልደ ዕጓለ እመሕያው ውእቱ" ተብሎ ተገልጿል። ተሰጠው የተባለ የሰው ልጅ ስለሆነ እንደሆነ ተነግሯል።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፮ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፬
"እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘለዓለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም" (ዮሐ. ፭፣፳፬)።

የኢየሱስ ክርስቶስን ቃል (ትምህርት) መስማትና በአብ ማመን የዘለዓለም ሕይወትን ያስገኛል። በነገራችን ላይ ሰው ሁሉ ዘለዓለማዊ ነው። ዘለዓለማዊነቱ ግን ሁለት ዓይነት ነው። ለኃጥእ ሰው ዘለዓለማዊ የስቃይ ዘመን አለው። ለጻድቅ ሰው ደግሞ ዘለዓለማዊ የደስታ ዘመን አለው።

ስለዚህ የዘለዓለም ሕይወት አለው ያለው የደስታውን ሕይወት ነው። በአብ ማመን ማለትም ወላዲ መሆኑን ማመን ማለት ነው። በተጨማሪም ወልድ ባሕርያዊ ልጁ መሆኑን ማመን ነው። ይህን ሳያምኑ ግን ዘለዓለማዊ ሕይወትን ማግኘት አይቻልም።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፭ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፫
"ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም" (ዮሐ. ፭፣፳፫)።

ወልድን የአብ ልጅ ነው ብሎ የማያከብር፣ የላከው አብንም ወላዲ ነው ብሎ አያከብረውም። አባት የሌለው ልጅ፣ ልጅ የሌለው አባት የለምና። ወልድን ማክበር ማለትም ትእዛዛቱን መጠበቅ ነው። ለሦስቱ አካላት ማለትም ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ የሚቀርበው ምስጋና አንድ ነው። አንዱን ማክበር ሌላውንም ማክበር መሆኑን መዘንጋት አይገባም። አብን ማመስገን ወልድን መንፈስ ቅዱስን ማመስገን ነው። ወልድን ማመስገን አብን መንፈስ ቅዱስን ማመስገን ነው። መንፈስ ቅዱስን ማመስገን አብን ወልድን ማመስገን ነው። በአንጻሩ አብን አለማክበር ወልድን መንፈስ ቅዱስን አለማክበር ነው። ወልድን አለማክበር አብን መንፈስ ቅዱስን አለማክበር ነው። መንፈስ ቅዱስን አለማክበር አብን ወልድን አለማክበር ነው። ወልድን የማያከብር የላከውን አብን አያከብርም የተባለው ለዚህ ነው። "የላከውን" የሚለው አገላለጽ ሰው እንዲሆን ያደረገውን ማለት ነው። ይኽውም ፈቃደ አብ ነው። እንዲህ ስላልን ግን የአብ ፈቃድ የወልድም የመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ስለሆነ ሰው እንዲሆን ማድረግም የሦስቱም አንዲት ፈቃድ መሆኗን እንገንዘብ።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፬ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፪
"ሰዎች ሁሉ አብን እንደሚያከብሩት ወልድን ያከብሩት ዘንድ፥ ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ አብ ባንድ ሰው ስንኳ አይፈርድም" (ዮሐ. ፭፣፳፪)።

አብ ምውታነ ሥጋን እንደሚያስነሳቸው ወልድም የወደደውን ያድነዋል። አብ በአንድ ሰውስ እንኳ አይፈርድም ሲል የመፍረድ ሥልጣን የለውም ማለት አይደለም። ፈታሒነት (በእውነት መፍረድ) የአብ የባሕርይ ገንዘቡ ነውና። ስለዚህ አብ በአንድ ሰውስ እንኳ አይፈርድም ማለቱ ተገልጾ ለሰው ታይቶ በማንም አይፈርድም ማለት ነው። ፍርድን ሁሉ ለወልድ ሰጠው እንጂ ማለትም በሥጋ ተገልጾ መፍረድን ለልጁ ገንዘብ አደረገለት ማለት ነው። በዚህ አግባብ ሰጪ ተደርጎ የቀረበውና ስሙ የተጠቀሰው አብ ቢሆንም በባሕርያዊ ሥራ የአንዱ ስም ቢጠቀስም ሁለቱም ስላሉበት ሥጋ አምላካዊ ፍርድን፣ አምላክነትን ገንዘብ ያደረገው በሦስቱም የአንድነት ሥልጣን መሆኑን ልብ ማድረግ ይገባል።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፫ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵፩
"ስለዚህ፥ ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህም አላቸው፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብ ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ ወልድ ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም ያ የሚያደርገውን ሁሉ ወልድ ደግሞ ይህን እንዲሁ ያደርጋልና። አብ ወልድን ይወዳልና፥ የሚያደርገውንም ሁሉ ያሳየዋል እናንተም ትደነቁ ዘንድ ከዚህ የሚበልጥ ሥራ ያሳየዋል። አብ ሙታንን እንደሚያነሣ ሕይወትም እንደሚሰጣቸው፥ እንዲሁ ወልድ ደግሞ ለሚወዳቸው ሕይወትን ይሰጣቸዋል" (ዮሐ. ፭፣፲፱-፳፩)።

ወልድ ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም ማለት ከራሱ ብቻ አንቅቶ ምንም ሥራ አይሠራም ማለት ነው። አብ ሲያደርግ ያየውን ያደርጋል እንጂ ማለትም አብ በህልውና የሠራውን ወልድም በህልውና ይሠራዋል ማለት ነው። ሙታንን የማስነሣት፣ ሕይወትን የመስጠት ሥልጣን የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት ሥራቸው ነው። በአንድነት ሥራቸው የአንዱ ስም ቢጠቀስም እንኳ አንዱ ብቻውን እንደሠራው ሊታሰብ አይገባም። የአንድነት ሥራቸው ስለሆነ የሦስቱም መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ወልድ ከራሱ ምንም ማድረግ አይችልም የተባለው ከራሱ ብቻ ምንም ማድረግ አይችልም ማለት ነው። ይኽውም ሥራውን ሁሉ የሚሠራው ሦስቱ አካላት በአንድ ባሕርይ ተገናዝበው እንደሆነ ለማስረዳት ነው።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፪ ይቀጥላል


ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵
"እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን፥ ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋራ አስተካክሎ፦ እግዚአብሔር አባቴ ነው ስለ አለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር" (ዮሐ. ፭፣፲፰)።

አይሁድ ትልቁ ችግራቸው ይህ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር መሆኑን ሲነግራቸውና አምላክነቱን በተለያዩ እግዚአብሔራዊ ሥራዎች እየገለጸላቸው እነርሱ ግን ላለመቀበል ኅሊናቸውን ይዘጉ ነበር። እርሱም አምላክ እንደመሆኑ "አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለኹ ብሎ መለሰላቸው" አለ (ዮሐ. ፭፣፲፯)። ይህን ሲሰሙ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካከለ ብለው ሊገድሉት ሳይቀር ይፈልጉ ነበር።

ሰውነቱን አይተው እግዚአብሔርነቱን ቢነግራቸው አልቀበልም አሉ። ሰውም አምላክም እንደሆነ ማወቅ ቢሳናቸው ሊገድሉት ፈለጉ። አሁንም ብዙዎች እግዚአብሔርነቱን ባለማመን ዕሩቅ ብእሲ (ሰው ብቻ) መስሏቸው ከነቢያት አንዱ ነው ብለው ይናገራሉ። እርሱው ጌታ እውነታውን ይግለጥላቸው።

© በትረማርያም አበባው


የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።

የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።

ክፍል ፻፵፩ ይቀጥላል


ኢየሱስ ክርስቶስ(1).pdf
2.0Mb
#PDF #PDF #PDF
#PDF #PDF #PDF
ከክፍል አንድ እስከ ክፍል መቶ የተማማርነውን ነገረ ክርስቶስ በፒዲኤፍ እነሆ። ከክፍል አንድ መቶ አንድ ጀምሮ እስከ ክፍል አንድ መቶ ኃምሳ ደግሞ ስንጨርስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ የምለቀው ይሆናል።





20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.