ነገረ ክርስቶስ ክፍል ፻፵
"እንግዲህ ሰንበትን ስለ ሻረ ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን፥ ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋራ አስተካክሎ፦ እግዚአብሔር አባቴ ነው ስለ አለ፥ ስለዚህ አይሁድ ሊገድሉት አብዝተው ይፈልጉት ነበር" (ዮሐ. ፭፣፲፰)።
አይሁድ ትልቁ ችግራቸው ይህ ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር መሆኑን ሲነግራቸውና አምላክነቱን በተለያዩ እግዚአብሔራዊ ሥራዎች እየገለጸላቸው እነርሱ ግን ላለመቀበል ኅሊናቸውን ይዘጉ ነበር። እርሱም አምላክ እንደመሆኑ "አባቴ እስከ ዛሬ ይሠራል እኔም ደግሞ እሠራለኹ ብሎ መለሰላቸው" አለ (ዮሐ. ፭፣፲፯)። ይህን ሲሰሙ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካከለ ብለው ሊገድሉት ሳይቀር ይፈልጉ ነበር።
ሰውነቱን አይተው እግዚአብሔርነቱን ቢነግራቸው አልቀበልም አሉ። ሰውም አምላክም እንደሆነ ማወቅ ቢሳናቸው ሊገድሉት ፈለጉ። አሁንም ብዙዎች እግዚአብሔርነቱን ባለማመን ዕሩቅ ብእሲ (ሰው ብቻ) መስሏቸው ከነቢያት አንዱ ነው ብለው ይናገራሉ። እርሱው ጌታ እውነታውን ይግለጥላቸው።
© በትረማርያም አበባው
የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf' rel='nofollow'>
https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
ክፍል ፻፵፩ ይቀጥላል