Christian tweet


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Inglizcha
Toifa: Telegram


በዚህ ቻናል በየቀኑ ለ
➜ #Profile_picture
➜ #Instagram_story
➜ #Facebook
➜ #Telegram_story
የሚሆኑ #መንፈሳዊ_ጥቅሶች እና #መፅሐፍ_ቅዱሳዊ መልእክቶችን (በአማርኛ እና ENGLISH) ወደእናንተ እናደርሳለን ቻናሉን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ 😊
ⒸSince 5-11-2015
Buy ads: https://telega.io/c/christian_tweet

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Inglizcha
Statistika
Postlar filtri


ኤፌሶን 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው፥
²¹ ለእርሱ በቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።

Ephesians 3 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ Now unto him that is able to do exceeding abundantly above all that we ask or think, according to the power that worketh in us,
²¹ Unto him be glory in the church by Christ Jesus throughout all ages, world without end. Amen.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


አሀሀ ሀሌሉያ....ሀሌሉያ....ሀሌሉያ...ሀሌሉያ እላለሁ ሀሌሉያ

@Christian_tweet


ወዶ አፍቅሮ ሲያስብ ሰው በልቡ
ይጠበብብኛል ለመግለፅ የውስጥ ሃሳቡ
ወደድኩኝ ባለበት ቅፅበት ጠላሁ ደግሞ ይልብኛል
ወረት ያለው ፍቅር ለእኔስ ግራ ገብቶኛል

አሃሃ ሰልችቶኛል ስተርከው የምድሩን
አሃሃ ግራ ይገባኛል ስዋደዱ ሲጣሉ
አሃሃ ምን አለ ሰዎች የላዩን ብትጽፉብኝ
አሃሃ የምድሩን ከማውራት መተረክ ብትገላግሉኘ
አሃሃ ጥሜ እንዲረካ የልቤ እንዲደርስ
አሃሃ እጅግ ደስ ይለኛል ቀለሜን ስለእርሱ ብጨርስ

አዝ፦ ብዕሬ እንኳን አንደበት ኖሮት ቢፈጠር
ኧረ ስንቱን ስንቱን ይናገር ነበር (2x)

It make a sence.

Sami T/Michael

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ኤፌሶን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።
³ በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን።
⁴ ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥
⁵ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥

Ephesians 2 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ And you hath he quickened, who were dead in trespasses and sins;
² Wherein in time past ye walked according to the course of this world, according to the prince of the power of the air, the spirit that now worketh in the children of disobedience:
³ Among whom also we all had our conversation in times past in the lusts of our flesh, fulfilling the desires of the flesh and of the mind; and were by nature the children of wrath, even as others.
⁴ But God, who is rich in mercy, for his great love wherewith he loved us,
⁵ Even when we were dead in sins, hath quickened us together with Christ, (by grace ye are saved;)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


“ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።”
— ዮሐንስ 10፥10

“The thief cometh not, but for to steal, and to kill, and to destroy: I am come that they might have life, and that they might have it more abundantly.”
— John 10:10 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


“ሳሙኤልም ነገሩን ሁሉ ነገረው፥ አንዳችም አልሸሸገውም። ዔሊም፦ እርሱ እግዚአብሔር ነው ደስ ያሰኘውን ያድርግ አለ።”
— 1ኛ ሳሙኤል 3፥18

“And Samuel told him every whit, and hid nothing from him. And he said, It is the LORD: let him do what seemeth him good.”
— 1 Samuel 3:18 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


መዝሙር 116
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ ነፍሴ ሆይ፥ ወደ ዕረፍትሽ ተመለሺ፥ እግዚአብሔር መልካም አድርጎልሻልና፤
⁸ ነፍሴን ከሞት፥ ዓይኔንም ከእንባ፥ እግሬንም ከመሰናከል አድኖአልና።

Psalms 116 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ Return unto thy rest, O my soul; for the LORD hath dealt bountifully with thee.
⁸ For thou hast delivered my soul from death, mine eyes from tears, and my feet from falling.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ሰቆ. 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።
²³ ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።


Lamentations 3 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² It is of the LORD'S mercies that we are not consumed, because his compassions fail not.
²³ They are new every morning: great is thy faithfulness.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


“አቤቱ፥ ለልቤ እንደ መከራዋ ብዛት ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።”
— መዝሙር 94፥19

“In the multitude of my thoughts within me thy comforts delight my soul.”
— Psalms 94:19 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


"ነፍሴ አንተን የሙጥኝ ብላለች፤ ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች።" መዝሙር 63:8


1ኛ ቆሮንቶስ 15
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵⁵ ሞት ሆይ፥ መውጊያህ የት አለ? ሲኦል ሆይ፥ ድል መንሣትህ የት አለ?
⁵⁶ የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤
⁵⁷ ነገር ግን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ድል መንሣትን ለሚሰጠን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።
⁵⁸ ስለዚህ፥ የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ ድካማችሁ በጌታ ከንቱ እንዳይሆን አውቃችኋልና የምትደላደሉ፥ የማትነቃነቁም፥ የጌታም ሥራ ሁልጊዜ የሚበዛላችሁ ሁኑ።

1 Corinthians 15 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵⁵ O death, where is thy sting? O grave, where is thy victory?
⁵⁶ The sting of death is sin; and the strength of sin is the law.
⁵⁷ But thanks be to God, which giveth us the victory through our Lord Jesus Christ.
⁵⁸ Therefore, my beloved brethren, be ye stedfast, unmoveable, always abounding in the work of the Lord, forasmuch as ye know that your labour is not in vain in the Lord.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


.     “He is not here: for he is risen,
as he said. Come, see the place
where the Lord lay.”
— Matthew 28፥6 (KJV)
             ✨ HAPPY EASTER ✨
               ▷@Christian_tweet


ሉቃስ 24
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ እነርሱም በዚህ ሲያመነቱ፥ እነሆ፥ ሁለት ሰዎች የሚያንጸባርቅ ልብስ ለብሰው ወደ እነርሱ ቀረቡ፤
⁵ ፈርተውም ፊታቸውን ወደ ምድር አቀርቅረው ሳሉ፥ እንዲህ አሉአቸው፦ ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።
⁶-⁷ የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ግድ ነው እያለ ገና በገሊላ ሳለ ለእናንተ እንደ ተናገረ አስቡ።


Luke 24 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ And it came to pass, as they were much perplexed thereabout, behold, two men stood by them in shining garments:
⁵ And as they were afraid, and bowed down their faces to the earth, they said unto them, Why seek ye the living among the dead?
⁶ He is not here, but is risen: remember how he spake unto you when he was yet in Galilee,
⁷ Saying, The Son of man must be delivered into the hands of sinful men, and be crucified, and the third day rise again.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ሉቃስ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁶ ደግሞም ምሳሌ እንዲህ ሲል ነገራቸው፦ የአዲስ ልብስ እራፊ ባረጀ ልብስ ላይ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱን ይቀደዋል ደግሞም አዲስ እራፊ ለአሮጌው አይስማማውም።
³⁷ ባረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን አዲሱ የወይን ጠጅ አቁማዳውን ያፈነዳል፥ እርሱም ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል።
³⁸ አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ማኖር ይገባል፥ ሁለቱም ይጠባበቃሉ።
³⁹ አሮጌ የወይን ጠጅ ሲጠጣ አዲሱን የሚሻ ማንም የለም፤ አሮጌው ይጣፍጣል ይላልና።

Luke 5 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁶ And he spake also a parable unto them; No man putteth a piece of a new garment upon an old; if otherwise, then both the new maketh a rent, and the piece that was taken out of the new agreeth not with the old.
³⁷ And no man putteth new wine into old bottles; else the new wine will burst the bottles, and be spilled, and the bottles shall perish.
³⁸ But new wine must be put into new bottles; and both are preserved.
³⁹ No man also having drunk old wine straightway desireth new: for he saith, The old is better.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


#የእርዳታ_ጥሪ

ቀና ልብ ላላችሁ ወገኖች በሙሉ  የወንድማችንን ነፍስ ከሞት እንታደግ🙏

ይህ ከላይ በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ወጣት ኤርምያስ ፍቅሬ ይባላል።

   ተወልዶ ያደገዉም በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣በሀድያ ዞን፣በፎንቆ ከተማ ስሆን፤ #ከልጅነቱም ጀምሮ ትሁትበስነ-ምግባሩ የታነፀበትምህርቱም ጎበዝና ለሌሎችም እንደ አራአያ የምታይ ወጣት ነዉ።

   የ2ተኛ ደረጃ ትምህርቱን በከፍተኛ ውጤት አጠናቆ በ2009ዓ.ም ወደ #ሀዋሳ_ዩንቨርስቲ በመግባት በቴክስታይል ኢንጅነርንግ(Textile Engineering) ት/ት ክፍል ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ተመርቆ #በሀዋሳ እንደስትርያል ፓርክ ውስጥ እየሰራ ባለበት ወቅት ድንገት ባጋጠመዉ የኩላሊት ህመም ምክንያት ስራውን አቋርጦ ህክምናዉን እየተከታተለ እያለ ህመሙ ብሶበት ሁለቱም ኩላሊቶቹ መስራት ስላቁመ ዶክተሮቹ በአፋጣኝ ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ የኩላሊት ንቅለ ተከላ እንዲደረግ ወስነዋል።

እናም ወደ ውጭ ሀገር ወስደን ለማሳከም የተጠየቅነዉ ብር ከአቅማችን በላይ በመሆኑ እናንተ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭም የምትኖሩ ደጋግ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እጃችሁን በመዘርጋት ወይም በምትችሉት ነገር ሁሉ ከጎናችን በመሆን ይህንን ወጣት ህይወት እንድትታደጉ ስንል እንማፀናለን🙏።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:-1000268155938
በአዋሽ ባንክ:- 013201523182800
ERMIAS FIKRE MESSELE

ለመደወልና ኤርምያስን ለማናገር ለምትፈልጉ
📞 0941414057
📞0920992184 ወይም
📞0939580869

የተቻላችሁን ብትረዱንና የወንድማችንን ህይወት በማትረፍ ትተባበሩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን🙏

ለምታደርጉልን ማንኛውም ቀና ትብብር እናመሰግናለን ፈጣሪ ጨምሮ ይስጥልን።

🙏ቻሌንጃችንን ለመቀላቀል👇

@Go_Fund1


“እግሮች እንዳይናወጡ አረማመዴን በመንገድህ አጽና።”
— መዝሙር 17፥5

“Hold up my goings in thy paths, that my footsteps slip not.”
— Psalms 17:5 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


ምሳሌ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ልጄ ሆይ፥ ወደ ጥበቤ አድምጥ፤ ጆሮህን ወደ ትምህርቴ መልስ፥
² ጥንቃቄን ትጠብቅ ዘንድ ከንፈሮችህም እውቀትን እንዲጠብቁ።


Proverbs 5 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ My son, attend unto my wisdom, and bow thine ear to my understanding:
² That thou mayest regard discretion, and that thy lips may keep knowledge.

@Christian_tweet
@Christian_tweet


'ዕብራውያን 9:25 - ሊቀ ካህናት የራሱ ያልሆነውን ደም ይዞ በየዓመቱ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን እንደሚገባ፣ ክርስቶስ ራሱን ብዙ ጊዜ መሥዋዕት ለማድረግ ወደ ሰማይ አልገባም።'


“ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም በእኔ የሚያምንም ሁልጊዜ ከቶ አይጠማም።”
— ዮሐንስ 6፥35


“And Jesus said unto them, I am the bread of life: he that cometh to me shall never hunger; and he that believeth on me shall never thirst.”
— John 6:35 (KJV)

@Christian_tweet
@Christian_tweet


መዝሙር 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ።
² ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል።
³ እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች፥ ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ፥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።
⁴ ክፉዎች እንዲህ አይደሉም፥ ነገር ግን ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ ናቸው።
⁵ ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ፥ ኃጢአተኞችም በጻድቃን ማኅበር አይቆሙም።
⁶ እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና፥ የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።


Psalms 1 (KJV)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ Blessed is the man that walketh not in the counsel of the ungodly, nor standeth in the way of sinners, nor sitteth in the seat of the scornful.
² But his delight is in the law of the LORD; and in his law doth he meditate day and night.
³ And he shall be like a tree planted by the rivers of water, that bringeth forth his fruit in his season; his leaf also shall not wither; and whatsoever he doeth shall prosper.
⁴ The ungodly are not so: but are like the chaff which the wind driveth away.
⁵ Therefore the ungodly shall not stand in the judgment, nor sinners in the congregation of the righteous.
⁶ For the LORD knoweth the way of the righteous: but the way of the ungodly shall perish.

@Christian_tweet
@Christian_tweet

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.