EBSTV NEWS


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.
https://t.me/ebstvworldwide
Inbox - @EbswhatsnewBot

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ዛሬ የካቲት 16 የሚደረጉ ጨዋታዎች

⚽በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ
09:30  ኤቨርተን ከ ማንችስተር ዩናይትድ
12:00  አርሰናል ከ ዌስትሀም
12:00 በርንማውዝ ከ ወልቭስ
12:00 ፉልሃም ከ ክርስታል ፓላስ
12:00 ኢፕስዊች ከ ቶተንሀም
12:00 ሳውዝሃፕተን ከ ብራይተን
02:30 አስቶን ቪላ ከ ቼልሲ

⚽በስፖኒሽ ላሊጋ
10:00  አላቬስ ከ ኢስፓኞል
12:15  ራዮ ቫልካኖ ከ ቪያሪያል
02:30 ቫሌንሺያ ከ አትሌቲኮ ማድሪድ
05:00 ላስ ፓልማስ ከ ባርሴሎና 

⚽በጣሊያን ሴሪኣ
09:00  ፓርማ ከ ቦሎኛ
11:00  ቬንዚያ ከ ላዚዮ
02:00  ቶሪኖ ከ ኤሲ ሚላን
04:45  ኢንተር ከ ጀኖዋ

⚽በጀርመን ቦንደስሊጋ
11:30 ሞንቼግላድባህ ከ ኦግስበርግ
11:30  ሆልስታይን ኪል ከ ባየር ሌቨርኩሰን
11:30 ሜንዝ ከ ሴንት ፓውሊ
11:30 ወልፍስበርግ ከ ቦኩም
02:30  ዶርትሙንድ ከ ዩኒየን በርሊን

⚽በፈረንሳይ ሊግ ኣ
01:00  ሊል ከ ሞናኮ
03:00  ሴንት ኢቴን ከ አንገርስ
04:45  አግዥሬ ከ ማርሴ

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


🇪🇹🛬የኢትዮጵያ አየር መንገድ “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ዕውቅና መቀዳጀቱ ተገልጿል።

🇪🇹🛬አየር መንገዱ ይሄን ሽልማት የተቀዳጀው በኬንያ ናይሮቢ በተካሄደው የ2025 ዓ.ም  የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት ልሕቀት ሽልማት መርሐግብር “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ነው።

🇪🇹🛬ከዚህ በተጨማሪም “የአፍሪካ ምርጥ የካርጎ አገልግሎት ኤርፖርት” እና “ፈጣን ዕድገት እያስመዘገበ ያለ የዓመቱ የካርጎ አገልግሎት አየር መንገድ” በመባል ተደራራቢ ዕውቅና እና ሽልማት እንደተቸረው ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የየካቲት 14 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_

❇️👉የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ለተቀበሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት መስጠቱን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጽህፈት ቤት ገለጸ።

❇️👉ማንኛውም መስፈርቱን የሚያሟሉ ዜጎች ፓስፖርት ለማግኘት ሲጠይቁ ሳይንገላቱ ማግኘት እንዲችሉ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እንዲደግፋቸው ርዕሰ ብሄር ታዬ አጸቀስላሴ መልእክታቸውን አስተላለፉ፡፡

❇️👉ኢትዮጵያ 2ኛውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ስርዓት ጉባዔ በመጭው ሀምሌ ወር ለማስተናገድ ዝግጁ ነኝ አለች፡፡

❇️👉በአንድ ጊዜ 16 በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ሃይል መሙላት የሚያስችል የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተገንብቶ ሥራ መጀመሩ ተገለጸ።

❇️👉በመንግስትና በግል ድርጅቶች አጋርነት ስምንት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በኢትዮጵያ ሊገነባ መሆኑ ተሰማ፡፡

❇️👉ሩሲያ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገውን ጥረት እደግፋለሁ አለች፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ዩቲዩብ፡-
https://www.youtube.com/@ebstvWorldwide/featured


⚽️የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ለ2026 የሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያ ዙር  ጨዋታቸውን በኡጋንዳ አቻቸው ተሸንፈዋል።

⚽️ካምፓላ በሚገኘው ሀምዝ ስቴዲየም  የኡጋንዳ አቻቸውን የገጠሙት ሉሲዎቹ የጨዋታው መጠናቀቂያ ደቂቃዎች ላይ ዛይናህ ናሙሌሜ እና ፋዚላ ኢክዋፑት ባስቆጠሯቸው  ግቦች 2-0 በሆነ ውጤት ተረትተዋል።

⚽️ወደ ካምፓላ 30 የልኡክ ቡድን አባላቶቻቸውን በመያዝ የተጓዙት የሴቶች ብሄራዊ ቡድን አባላቱ በነገው ዕለት ወደ አዲስ አበባ የሚመለሱም ይሆናል።

⚽️በአሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ የሚመራው ብሔራዊ ቡድኑ ወደ መጨረሻው ዙር ማጣሪያ ለማለፍ በቀጣይ ሶስት እና ከዚያ በላይ ግብ አስቆጠሮ ግብ ሳያስተናግድ ማሸነፍ ይጠበቅበታል።

⚽️ቡድኑ እሁድ ልምምዱን የሚጀምር ሲሆን  ሁለተኛ የመልስ ጨዋታውን ረቡዕ የካቲት 19 በ9 ሰዓት  ከኡጋንዳ አቻው ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ያከናውናል።

⚽️የኢትዮጵያ የሴቶች ብሄራዊ ቡድን አባላት ይህንን ዙር በደርሶ መልስ አሸንፈው ወደ ሁለተኛው ዙር ማጣሪያ  የሚያልፉ ከሆ ከታንዛንያ እና ኢኳቶሪያል ጊኒ አሸናፊ ጋር ጨዋታቸውን የሚያከናውኑ ይሆናል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የየካቲት 14/2017 ዓ.ም የከሰአት ዓበይት የዓለም ዜናዎች!

🎯የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ የትራምፕ አስተዳደር የፀጥታ ዋስትና ለዩክሬን እስካልሰጠ ድረስ የሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት እንደማይቆም ተናገሩ።

🎯የበለፀጉት የቡድን 7 ሀገራት ባወጡት የጋራ መግለጫ ሩሲያን ወራሪ ሀገር ብለዉ ከመጥራት እንዲቆጠቡ ስትል አሜሪካ ተቃውሞ ማሰማቷ ተሰማ።

🎯 የተወሰኑ የአሜሪካ የኮንግረስ አባላት የአሜሪካን ብሄራዊ ጥቅም ይጋፋሉ ካሉት የመንግስታቱ ድርጅት አባልነት አሜሪካ እንድትወጣ ጠየቁ።

🎯የአረብ ሀገራት መሪዎች በጋዛ መልሶ ግንባታ እቅድ ዙሪያ ዛሬ በሳኡዲ አረቢያ መዲና ሪያድ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

🎯የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ በብሪክስ ሀገራት ላይ የሚጣል ቀረጥ ሀገራቱን ይጎዳል ሲሉ ተናገሩ።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበር ከፖላንድ አገር የመጡና ለመጪው አንድ ሳምንት በኢትዮጵያ ነጻ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ የህክምና ቡድኖችን በዛሬው እለት ተቀብሏል፡፡

ከአውሮፓዊቷ አገር ፖላንድ የመጡት እነዚሁ የሃኪሞች ስብስብ በዛው አገር ላለፉት 36 ዓመታት የህክምና አገልግሎት ሲሰጡ በነበሩት ትውልደ ኢትዮጵያዊ ሃኪም ብዙአየው መንገሻ አስተባባሪነት ከዚህ ቀደም በሶስት ዙር ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የአይን ህክምናን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን መስጠታቸው ተነግሯል፡፡

በዚሁ ለአራተኛ ጊዜ በሚሰጡት ህክምና ደግሞ በጦርነት ወቅት ጉዳት ለደረሰባቸው የሰራዊት አባላት ህክምናን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን እንደሚሰጡ ሲገለጽ፤አለርት ሆስፒታልን ጨምሮ በተለያዩ የመንግስት ህክምና ተቋማትም አገልግሎት እንደሚሰጡ ተመልክቷል ፡፡

የህክምና ቡድኑ የአከርካሪ አጥንት ህክምናን ጨምሮ በዋናነት በአገር ውስጥ ህክምና ለመስጠት አዳጋች የሆኑ ቀዶ ህክምናዎችን ያደርጋል የተባለ ሲሆን፤ከህክምናው ጎን ለጎን የእውቀት ሽግግርና የቁሳቁስ ድጋፍም ያደርጋል ተብሏል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የየካቲት 14 2017 ዓ.ም የእኩለ 7፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_

🇪🇹 ኢትዮጵያ በጆሃንስበርግ እየተካሄደ በሚገኘው የቡድን 20 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የአፍሪካውያን የልማት ጥረት ድጋፍ እንዲያገኝ ከአባል ሀገራቱ ጋር በትብብር እንደምትሠራ ገለጸች፡፡

❇️👉በኢትዮጵያ ለመጪው አንድ ሳምንት የጦር ሃይሎች ሆስፒታልን ጨምሮ በተለያዩ ሆስፒታሎች ነጻ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ልዑክ ከአገረ ፖላንድ በዛሬው እለት በኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበር አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

❇️👉የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት በአይነቱ ልዩ የሆነ አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርትን በዛሬው እለት ይፋ አደረገ፡፡

❇️👉በኢፌዴሪ አየር ኃይል ተሰርታ “ፀሃይ - 2” የሚል ስም የተሰጣት የስልጠና አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማከናወኗ ተነገረ፡፡

❇️👉የመጀመሪያ ዙር የተቀናጀ የልጅነት ልምሻ ወይም (ፖሊዮ) መከላከያ ክትባት ዘመቻ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች በዛሬው እለት መሰጠት ጀምሯል።

❇️👉በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የህፃናት አንጎልና ህብለ ሰረሰር ቀዶ ህክምና የልህቀት ማዕከል በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ተገልጿል።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ዩቲዩብ፡-
https://www.youtube.com/@ebstvWorldwide/featured


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
🇪🇹🛫በኢትዮጵያ አየር ኃይል የተሰራችው "ፀሃይ - 2" የስልጠና አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማከናወን መቻሏን የአየር ኃይል አስታወቋል፡፡ እኛም የሙከራ ሂደቷን በተንቀሳቃሽ ምስል ልናሳያችሁ ወደድን፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


⚽️በ2026 ሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ አንደኛ ዙር የመጀመርያ ጨዋታ ዛሬ ከቀኑ አስር ሰአት ኢትዮጵያ ዩጋንዳን ካምፖላ ላይ ትገጥማለች።

⚽️ጨዋታው በካምፓላ ሀምዝ ስታዲየም ይደረጋል

ድል ለኢትዮጵያ 🇪🇹

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የየካቲት 14/2017 ዓ.ም የረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች

🎯የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ትራምፕ አሜሪካ የዩክሬንን “ሬር ኧርዝ” የተባሉ ማዕድናት ተጠቃሚ በምትሆንበት ዙሪያ የኪዬቭ መንግስት ወደ ድርድር እንዲመጣ መጠየቃቸውን ተናገሩ።

🎯ሩሲያና ዩክሬን በፈረንጆቹ 2025 የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈራረሙ እንደሚችሉ አንድ የዩክሬን የደህንነት ባለስልጣን ተናገሩ።

🎯ፈረንሳይ ወታደሮቿን ከምዕራብ አፍሪካዊቷ ኮትዲቯር ማስወጣቷን አስታወቀች።

🎯የቡድን 20 አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ በደቡብ አፍሪካዋ ጆሀንስበርግ ከተማ እየተካሄደ መሆኑ ተነገረ።

🎯የትራምፕ አስተዳደር ከቻይና ጋር አዲስ የኒውክለር ስምምነት መፈራረም እንደሚፈልግ ተሰማ።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


❇️👉በአገልግሎት ተቋሙ በተለያዩ የሥራ ሃላፊነቶች ላይ በርከት ላሉ ዓመታት ሲያገለግሉ የቆዩት ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ተቋሙን በዋና ስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የቆዩትን ሽፈራው ተሊላ (ኢ/ር) በመተካት ተቋሙን በዋና ስራ አስፈጻሚነት እንዲመሩ መመደባቸውን ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


🇪🇹🛫በኢትዮጵያ አየር ኃይል የተሰራችው ፀሃይ - 2 የስልጠና አውሮፕላን የመጀመሪያ የሙከራ በረራዋን በስኬት ማከናወን መቻሏን የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ ኮሎኔል መሰረት ጌታቸው ገልፀዋል፡፡

🇪🇹🛫ፀሃይ -2 አውሮፕላን ለበረራ ማሰልጠኛ እና ለሌሎች አገልግሎት መዋል የምትችል መሆኑን ያስታወቁት ኮሎኔሉ የተሰጣትን ግዳጅ በብቃት መፈፀም የሚያስችላትን የዘመኑን የአቭዬሽን ቴክኖሎጂ መታጠቋንም አብራርተዋል፡፡

🇪🇹🛫የአውሮፕላኗ ስኬታማ የሙከራ በረራ አየር ኃይሉ የደረሰበትን የከፍታ ጉዞ ጠቋሚ ነው ያሉት ምክትል አዛዡ በቀጣይነትም ወደ ምርት ሂደት ለመሸጋገር ፋብሪካውን የማደራጀት ፣የመፈተሻ እቃዎችን የማሟላት እና የሙያተኞችን አቅም የማጎልበት ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡

🇪🇹🛫የትራንስፖርት አውሮፕላን ስኳድሮን አዛዥና አብራሪ እንዲሁም የፀሃይ -2 የሙከራ በረራን በስኬት ያካሄዱት ሻለቃ ፍቃዱ ደምሴ በበኩላቸው አውሮፕላኗ አለም የደረሰበትን የአውሮፕላን ቴክኖሎጂ የታጠቀች የበረራ አቅሟም አስተማማኝ፤ ተቋሙ ለያዘው ራዕይ ጉልህ አስተዋፅዖ የምታበረክት መሆኗን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመለክታል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


❇️👉የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርትን ይፋ አደረገ ፡፡

❇️👉ይህ አዲሱ ፓስፖርት ደህንነቱ የተጠበቀ እና በሀገር ዉስጥ የሚመረት ሲሆን ፣ የደህንነት ደረጃው ከቀድሞው ፓስፖርት በ300 እጥፍ ይበልጣል ተብሏል፡፡

❇️👉ፓስፖርቱ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘዉ የለሚ ኢንደስትሪያል ፓርክ የሚመረት ሲሆን ጥራቱ አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስለመሆኑም ተነግሯል፡፡

❇️👉በተጨማሪም ፣ በፓስፖርቱ ገፆች ላይ የሀገር ገፅታ የሚያስተዋዉቁ የኢትዮጵያ መለያዎች እንደተካተቱበትም ለማወቅ ተችሏል፡፡

❇️👉 አዲሱ የኤሌክትሮኒክስ ፓስፖርት የግለሰቡን ባዮግራፊክ መረጃ ብቻ ሳይሆን የጣት አሻራውንም የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ ይዟል ተብሏል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ምርቴን በእጥፍ አሳድጋለሁ ብሏል።

የናይጀሪያው ኩባንያ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን ኢንቨስትመንት ለማስፋት ማቀዱን አስታውቋል፡፡
ኩባንያው ከዚህ ቀደም የተሠማራበትን የሲሚንቶ የማምረት አቅሙን በእጥፍ የማሳደግና ከዚህም ባለፈ በኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ ለመሰማራትም ፍላጎት አለኝ ብሏል፡፡
ዝርዝሩን ለመከታተል ሊንኩን ይጫኑ👇
https://youtu.be/0v6PvfYlpvU


የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 41 ግዙፍ ሀገራዊ  የቢዝነስ ኩባንያዎችን እያስተዳደረ ይገኛል፡ ፡ኩባንያዎቹ  ከኪሳራ ወደ አትራፊነት የማሸጋገር ሃላፊነት ያለው ተቋም ነው፡፡ ከ2014 ጀምሮ በአዲስ መልክ ሥራ የጀመረ ሲሆን ባለፉት በንግድ ህግ እንዲተዳደሩ አድርጓል፡፡

በቀጣይም በኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ነዋይ ገበያ እንዲሳተፉ ከወዲሁ ሥራዎችን እየሠራ ሲሆን ከውጭ ከሚገቡ ድርጅቶች ጋር ተቀዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡
በእነዚህና ሌሎችም ጉዳዮችም ከድርጅቱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ከሆኑት መልዕክት ሳህሉ ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡
ዝርዝሩን ለመከታተል ሊንኩን ይጫኑ👇
https://youtu.be/nDudRH0H3mo


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የየካቲት 13 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_

❇️👉የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል መንግስትና ፋኖና ለማደራደር ሃላፊነት ወስዷል የተባለው መረጃ ሃሰተኛ ነው አለ፡፡

❇️👉የትምህርት ሚኒስቴር 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበይነ መረብ እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታወቀ፡

❇️👉የአዲስ አበባ ፖሊስ ባለፈው ጥር ወር ብቻ ለዕይታ ግልፅ ያልሆነ ሰሌዳ ለጥፈው በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ላይ በተደረገ ቁጥጥር ከ2 ሺ 1 መቶ በላይ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃ ወስጃለሁ አለ፡፡

❇️👉የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በፎረንሲክ ምርመራ ከ358 ሰነዶች ውስጥ 73 በመቶዎቹ ሀሰተኛ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

❇️👉የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ በከተማዋ የተደራጁ ከ6 ሺ በላይ ዕድሮች ህጋዊ ምዝገባ አካሂደው እውቅና ማግኘታቸውን አስታወቀ።

❇️👉በአዲስ አበባ በመብራት ችግር ምክንያት ለፀጥታ ስጋት የሆኑ 174 የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና 197 የመንገድ ዳር አካባቢዎችን በመለየት የመፍትሄ ማስፈፀሚያ እቅድ መዘጋጀቱ ተነገረ።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ዩቲዩብ፡-https://www.youtube.com/@ebstvWorldwide/featured

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


❇️👉በአዲስ አበባ በመብራት ችግር ምክንያት ለፀጥታ ስጋት የሆኑ 174 የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና 197 የመንገድ ዳር አካባቢዎችን በመለየት የመፍትሄ ማስፈፀሚያ እቅድ ስለመዘጋጀቱ ተነግሯል።

❇️👉ይህን ያለው የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ የወንጀል ምጣኔ ከባለፈው አመት አንፃር 33 በመቶ ቅናሽ ቢያሳይም የምሽት ላይ ዝርፊያዎች ግን እየተበራከቱ መሆኑን አሳውቋል።

❇️👉ለዚህ ሲባል የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ ሀይል አገልግሎትን ጨምሮ 5 አስፈፃሚ አካላት የተካተቱበት እቅድ ተዘጋጅቷል ያለው ቢሮው እነዚህ ለወንጀል ምቹ የሆኑ የውስጥ ለውስጥና የመንገድ ዳር አካባቢዎች መብራት እንዲያገኙ ይሰራል ነው ያለው።

❇️👉የመንገድ ዳር መብራት የተዘረጋላቸው ነገር ግን ብርሀን የሌላቸው የመንገድ ዳር መብራቶች በርካታ ናቸው ያለው ቢሮው ይህን ለማስተካከል እንደሚሰራና ህብረተሰቡም ግቢውና አካባቢው ላይ መብራት እንዲያኖር እንደሚደረግ ጠቁሟል።

❇️👉ኮልፌ ክፍለከተማ የማይሰሩ መብራቶች በብዛት ያሉበትና ወንጀልም የተበራከተበት ቀዳሚ ክፍለከተማ ነው ያለው ቢሮው ልደታምና ለሚ ኩራም እንዲሁም አራዳና ቦሌ ክፍለከተማም ይህ ስራ በዋነኝነት የሚተገበርባቸው 5 ክፍለ ከተሞች ይሆናሉ ብሏል።

❇️👉ተመሳሳይ ችግር ያለባቸው ናቸው። ለሚ ኩራ ከመንገድ ዳር መብራት ይልቅ የውስጥለውስጡ ይበዛል። አራዳና ቦሌም የቸወሰነ ችግር አለባቸው።

❇️👉ህብረተሰቡ ለአካባቢው የሚያበራቸው የደጅ አምፓሎች ስታንዳርድ እንደሚወጣላቸውና ከስታንዳርድ ውጪ የሆኑ የደጅ አምፓሎችን መጠቀም እንደሚከለከል የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ ሀይል አሳውቋል።

❇️👉በከተማዋ ባሉ 5246 ብሎኮች ውስጥ ወብራቶችን ወደደጅ የማውጣት ውይይት በ15 ቀናት ውስጥ ከህ ብረተሰቡ ጋር እንዲካሄድ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ለክፍለከተሞቹ ትእዛዝ ሰጥቷል።

መረጃውን ያደረሰን ሪፖርተራችን አቤል አበበ ነው፡፡
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews




❇️👉በመዲናዋ አዲስ አበባ የሚገኙ ከ6 ሺ በላይ ዕድሮች ህጋዊ ምዝገባ አካሂደው እውቅና ማግኘታቸው ተነገረ፡፡

❇️👉የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ በከተማዋ የተደራጁ ከ6 ሺ በላይ ዕድሮች ህጋዊ ምዝገባ አካሂደው እውቅና ማግኘታቸውን አስታውቋል።

❇️👉በአዲስ አበባ ከተማ ከ7 ሺህ በላይ ዕድሮች እንደሚገኙ የጠቆመው የሴቶች፣ ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ እስከ መጪው ሰኔ 30 ቀን 2017 ድረስ ያልተመዘገቡ እድሮች ምዝገባ እንዲያከናውኑ ጥሪ አቅርቧል፡፡

❇️👉ቢሮው በእድሮች ምዝገባና እድሳት መመሪያ ዙሪያ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ የመንግስት ተቋማት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ዛሬ አካሂዷል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.