ebstv worldwide📡️


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


Welcome to EBS TV WORLDWIDE Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates. Don’t forget to share it with your friends.
@ebstvworldwidebot
@EbswhatsnewBot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri




🇪🇹🥈🏅ትውልደ ኢትዮጵያዊው ታዳጊ ተመራማሪ ሄመን በቀለ አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚያሸልመውን የዜይድ አዋርድ 2025 አሸናፊ ሆኗል፡፡

🇪🇹🥈🏅በአሜሪካ ነዋሪ የሆነው የ15 ዓመቱ ታዳጊ የቆዳ ካንሰር ህመሞችን ለመከላከልና ለማከም የሚችል ሳሙና በመፍጠሩ ነው ተሸላሚ መሆን የቻለው፡፡

🇪🇹🥈🏅ከታዳጊው በተጨማሪ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞትሊ እንዲሁም ዎርልድ ሴንትራል ኪችን የተሰኘው ድርጅት የዜይድ አዋርድ 2025 ተሸልመዋል፡፡

🇪🇹🥈🏅በፈረንጆቹ 2010 ዓመት በአዲስ አበባ የተወለደው ሔመን በቀለ 4 ዓመት ሲሞላው ቤተሰቦቹ ኑሮአቸውን ወደ አሜሪካ ማዞራቸውን ተከትሎ እድገቱን በሀገር አሜሪካ አድርጓል፡፡

🇪🇹🥈🏅አሁን ላይ የ15 ዓመት ታዳጊ የሆነው ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት ሄመን ከህጻንነቱ ጀምሮ ለሳይንሳዊ ሙከራዎች ልዩ ፍቅር እንደነበረውና በተለይም ወደ ትምህርት ቤት ከገባ በኋላ አብዛኛው ጊዜውን በቤተ ሙከራ ውስጥ ማሳለፍ እንደሚያስደስተው ከታይም መጽሄት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ተናግሯል፡፡   መረጃውን ያደረሰን ብሩክ አስቀናው ነው፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም ፦ https://t.me/ebstvnews
ዩቲዩብ፡-https://www.youtube.com/@ebstvWorldwide/featured
ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/profile.php?id=61569783971786
ቲክቶክ:-https://www.tiktok.com/@ebstv.tv?is_from_webapp=1&sender_device=pc
ድህረ ገጽ፡- https://ebstv.tv
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN


የጥር 29/2017 ዓ.ም የከሰአት ዓበይት የዓለም ዜናዎች

🇮🇱እስራኤል በፍልስጤም ጋዛ ያሉ ስደተኞችን ለማስወጣት በአሜሪካው መሪ ዶናልድ ትራምፕ የቀረበውን ጥሪ ለማስፈጸም ዝግጅት መጀመሯ ተነግሯል።

🇺🇸የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ እስራኤል በጋዛ እያካሄደች ያለውን ጦርነት ስታጠናቅቅ ጋዛን ለአሜሪካ ታስረክባለች ሲሉ አነጋጋሪ አስተያየት መስጠታቸው ተሰምቷል።

🇺🇦የዩክሬኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንድሪ ሲቢሃ ከድህረ ጦርነት በኋላ የዩክሬን መልሶ ግንባታን ለማካሄድ ለጋሽ ሀገራት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረቡ።

🇺🇸በቅርቡ አሜሪካንን ከአለም የጤና ድርጅት አባልነት ያስወጣው የትራምፕ አስተዳደር የጤና ድርጅቱ ማሻሻያ የሚያደርግ እና አሜሪካዊ ባለስልጣን የድርጅቱ ሀላፊ አድርጎ የሚሾም ከሆነ አሜሪካንን መልሶ ለመቀላቀል እያጤነ ነው ተባለ።

🌍የአፍሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያ ማእከል አፍሪካ ሲዲሲ የአሜሪካ ድጋፍ የሚቆም ከሆነ በአህጉሪቱ ከ2 እስከ4 ሚሊዮን ሰዎች ለሞት ሊዳርጉ ይችላል ሲል አስጠነቀቀ።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

ያማረ ምሽት ተመኘንላችሁ !

የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
ቴሌግራም ፦
https://t.me/ebstvnews
ዩቲዩብ፡-https://www.youtube.com/@ebstvWorldwide/featured
ፌስቡክ፡-https://web.facebook.com/profile.php?id=61569783971786


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የእኩለ ቀን 7፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_

🕊🕊በትግራይ ክልል በህወሃት አመራሮች መካከል ያለው ልዩነት ያሳሰባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዳግም ጦርነትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።

❇️▶️የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ግብር ከፋዮች የጣራና ግርግዳ ግብር እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት ድረስ ከፍለው እንዲያጠናቅቁ ሲል ጥሪውን አስተላለፈ፡፡

🇺🇸👉በኢትዮጵያ የተቋረጠው የአሜሪካ የተራድኦ ድርጅት ድጋፍ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የኤች አይቪ ኤድስ ህሙማን የድጋፍ አገልግሎት አደጋ ላይ እንዲወድቅ ማድርጉን የመንግስታቱ ድርጅት አስታወቀ፡፡

💠🉐የአሜሪካ የረድኤት ድርጅት ወይም ዩኤስኤይድ ድጋፍ በአለም ደረጃ መቋረጥ በኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበራት ስራቸውን የሚያስተጓጉል አደጋ ነው እናም ያሳስበኛል ሲል የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ገለጸ፡፡

🕊🏳️የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሀን ምክር ቤት ከመገናኛ ብዙሀንና ከዘርፉ ባለሙያዎች ያሰባሰባቸውን የሀገራዊ ምክክር አጀንዳዎች ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስረክቧል።

📚📚የአማራ ክልል በገጠመው የጸጥታ ችግር ምክንያት ከ4 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ወጭ መሆናቸው ሲገለጽ በመማር ላይ ያሉ ተማሪዎች ከአንድ ሚሊዮን በላይ መኾናቸውንም ተጠቆመ።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

መልካም ቀን!

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉
https://t.me/ebstvnews

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews








የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም የእኩለ ቀን 7፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_

🇪🇹🇰🇪ኢትዮጵያና ኬንያ የደህንነትና የጸጥታ ተቋማት በሁለቱ ሀገራት ድንበር አካባቢ በሚንቀሳቀሰው የሸኔ ታጣቂ ላይ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ማካሄድ መጀመራቸውን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።

❇️የጤና ሚኒስቴር በሲዲሲና ዩኤስኤይድ ድጋፍ የተቀጠሩ ከ5 ሺህ በላይ ስራተኞችን ውል እንዲቋረጥ መመሪያ ሰጠ።

▶️በ4 ኪሎ ሲገነባ የነበረው የምድር ዉስጥ የእግረኞች መንገድ ተጠናቆ ለህብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ተገለጸ፡፡

🛣ከአዲስ አበባ በተለያዩ መስመሮች የሚወጡ 4 አዳዲስ የፍጥነት መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ይገኛል፡፡

🇷🇺🌍ሩስያ ከአፍሪካ ጋር ያላትን ስትራቴጂክ ትብብር ያጠናክራል ያለችውን የአፍሪካ የትብብር ቢሮ (Department for African Partnership) በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሥር ከፍታ ሥራ ጀመረች።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

መልካም ቀን!

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉
https://t.me/ebstvnews
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN


የጥር 28/2017 ዓ.ም የረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች

🇮🇱እስራኤልና የፍልስጤሙ የሀማስ ቡድን የተኩስ አቁም ስምምነት ለመድረስ የሚያስችል ውይይት በኳታር መዲና ዶሀ መቀጠላቸው ተሰምቷል።

🇺🇸የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው አሜሪካ ጋዛን ጠቅልላ መያዝ እንደምትፈልግ ተናገሩ።

🇺🇸የአሜሪካው መሪ ትራምፕ የፍልስጤሙ ጋዛ መልሶ ግንባታው እስኪካሄድ ድረስ ፍልስጤማዊያን ነዋሪዎች ከጋዛ ውጭ ባሉ የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት እንዲሰፍሩ ሀሳብ አቀረቡ።

🇺🇸የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ሀገራቸው አሜሪካ ከመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ም/ቤት እንድትወጣ የሚያስችል ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ላይ ፈረሙ።

🇸🇪በአውሮፓዊቷ ስዊድን አንድ ታጣቂ በአንድ ት/ቤት ላይ በከፈተው የተኩስ እሩምታ በትንሹ 11 ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews






Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ምስጡ ይበልጥ ያስፈራኛል🤣😂 /ዞሮ መውጫዬ/
ዛሬ ምሽት 3፡00 ሰአት ይጠብቁን!

#Zoro_Mewchaye
#EBS


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ሰዓት የአለም ዋና ዋና  ዜናዎች፡_

🇪🇹ሉሲ ወይም ድንቅ ነሽ እና ሰላም የተባሉት ዕድሜ ጠገቦቹ የሰው ልጆች ቅሪተ አካላት በቼክ ሪፐብሊክ ብሔራዊ ሙዚዬም ለዕይታ ሊቀርቡ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

🇺🇸የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (USAID) ዋና ቢሮ ሰራተኞች ከዛሬ ጀምሮ በቤታቸው እንዲቆዩ ትእዛዝ መተላለፉን ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ነው፡፡

🇪🇹🇰🇪የኢትዮጵያና ኬንያ የደኅንነትና የጸጥታ ተቋማት የሸኔ ታጣቂ ላይ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ማካሄድ መጀመራቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ::

✅ኢትዮጵያ የአፍሪካ የቴክኖሎጂ ጥናቶች ማዕከል የአስተዳደር ምክር ቤት አባል ሆነች፡፡

🇪🇹🇸🇸 ኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን የቪዛ ችግሮችን ለመቅረፍ ተስማሙ፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

ያማረ ምሽት ተመኘንላችሁ !

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉
https://t.me/ebstvnews

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም የእኩለ ቀን 7፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና  ዜናዎች፡_

✅ጠ/ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) የትግራይ ሊሂቃን የህዝቡን አንድነት በሚያረጋግጥ መልኩ ልዩነቶቻቸውን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ፡፡

✅እንደ  ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ መረጃ ኢትዮጵያና ሩሲያ በራሳቸው ገንዘብ ግብይት ለመፈጸም የሚያስችላቸው ስምምነት ላይ ደርሰዋል አለ፡፡

✅ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ እዳ በመክፈል ረገድ መሻሻል ማሳየቷን የዓለም ገንዘብ ድርጅት አስታወቀ።

✅ኢትዮጵያ ከ91 ሺሕ በላይ የዝርያ ናሙናዎችን በዘረመል ባንክ በማስቀመጥ ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኗ የኢትዮጵያ ብዝኃ ሕይወት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

✅የቀድሞ ታጣቂዎችና ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት ሂደት ክተጠበቀው ጊዜ በላይ ዘግይቶ መጀመሩን የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

ሰናይ ከሰዓት!

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉 https://t.me/ebstvnews

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የጥር 27 የረፋድ አበይት የዓለም ዜናዎች

🇨🇳ቻይና ከአሜሪካ በሚገቡ የተፈጥሮ ጋዝ ምርቶች ላይ የ15 በመቶ እና ማሽነሪዎች ላይ ደግሞ የ10 በመቶ ቀረጥ መጣሏን ይፋ አደረገች።

🇺🇸የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ዛሬ በዋይት ሀውስ ምክክር እንደሚያካሂዱ ተነገረ።

🇺🇸የአሜሪካ የተራድኦ ድርጅት “ዩኤስኤይድ” በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር ሊጠቃለል መሆኑ ተሰምቷል።

🇨🇩በዲሞክራቲክ ኮንጎ ምስራቃዊ ክፍል የሚንቀሳቀሱት አማፅያን የሰብዓዊ ድጋፍ መስጫ ያሉትን የተኩስ አቁም አወጁ።

🇿🇦የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሚኒስቴር ጌውዲ ማንታሽ አሜሪካ በሀገራችን ላይ ማዕቀብ የምትጥል ከሆነ ወደ አሜሪካ የሚሄደውን ማዕድን እናቆማለን ሲሉ አስጠነቀቁ።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews




የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና  ዜናዎች፡_

❇️እናት ፓርቲ የጣርያና ግርግዳ ግብርን በተመለከተ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ቢሮ ላይ የመሰረተው ክስ በፍርድ ቤት ተቀባይነት አግኝቶ ህጋዊነት የለውም ተብሎ ስለተወሰነ በቀጣይ የአፈጻጸም መዝገብ ለመክፈት እየተዘጋጀሁ ነው ብሏል፡፡

👉ቢሊየነሩ ኤሎን መስክ በየዓመቱ እስከ 70 ቢሊዮን ዶላር በጀት በአሜሪካ መንግስት የሚመደብለትን የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት “ዩኤስኤድ” እስከወዲያኛው እንደሚዘጋ ከትራምፕ ጋር መስማማቱን በኤክስ ገጹ ገለጸ፡፡

❇️የአዲስ_አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር በተለያዩ አካባቢዎች በዘፈቀደ የሚደረጉ ሐይማኖታዊ ስብከቶችን ለማስተካከል እና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት መመሪያ እያዘጋጀሁ ነው አለ፡፡

🏦የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ ከ1 ነጥብ 4 ትሪሊየን ብር በላይ መድረሱን አስታወቀ፡፡

❇️የምግብ ዘይት ወደ ሀገር ቤት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳወቀ።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

መልካም ምሽ!

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉 https://t.me/ebstvnews

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የጥር 26/2017 ዓ.ም አበይት የዓለም ዜናዎች

🇺🇸የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአውሮፓ ህብረት ሀገራት ላይ ቀረጥ እንደሚጥሉ ተናገሩ።

🇺🇸የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ቻይና በፓናማ የንግድ መተላለፊያ ቦይ ላይ ያላትን ተፅዕኖ ፓናማ እንድታስቀር አሳሰቡ።

🇨🇦ካናዳ ከአሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ25 በመቶ ቀረጥ መጣሏን የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ቱሩዶ ተናገሩ።

🌍የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም የትራምፕ አስተዳደር አሜሪካ ከዓለም የጤና ድርጅት እንድትወጣ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዲተው ሀገራት ግፊት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረቡ።

🇺🇳የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዩክሬን በሱድዛ አዳሪ ትምህርት ቤት ላይ ያካሄደችውን ጥቃት እንዲያወግዝ ሩሲያ ጠየቀች።

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉
https://t.me/ebstvnews
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም የእኩለ ቀን 7፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_

👉ገዥው የብልጽግና ፓርቲ ለ3 ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ባለ ስምንት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት አጠናቀቀ፡፡

👉የትግራይ ጊዚያው አስተዳደር የክልሉን ሰላም ለማጠናከር ያስችላል ያለውን የጊዜያዊ አስተዳደሩ፣የፖለቲካ ፓርቲ፣የሲቪክ ማህበራት እና የፀጥታ አመራር አባላትን ያቀፈ አማካሪ ምክር ቤት አቋቋመ፡፡

👉የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም በኢትዮጵያ ከሁለት አመታት በፊት በባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረውን የብድር ጣሪያ በመጭው መስከረም እንደሚያነሳ አዲስ ባወጣው ሪፖርቱ አሳወቀ፡፡

👉የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ባለፉት 3 ወራት ከ17 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎች የተሀድሶ ስልጠና ወስደው ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ መደረጉን አሳወቀ፡፡

👉13 ታጋቾችን ከእገታ ማስለቀቁን የጭልጋ ወረዳ ሰላም እና ደህንነት ጽሐፈት ቤት አስታወቀ፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"

ቆንጆ ቀን ተመኘንላችሁ !

ትክክለኛውን የኢቢኤስ አዲስ ነገር የቴሌግራም ገፅ ለመወዳጀት ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👉
https://t.me/ebstvnews
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.