Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የጭሮ ሪጅን የስራ እንቅስቃሴ እና የደንበኛ አስተያየት!!


በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የሃይል አቅርቦት

ከሞጣ 230 ኪ.ቮ ኃይል ማካፋፈያ ጣቢያ ላይ በደረሰ የፓወር ትራንስፎርመር ብልሽት ምክንያት ሞጣ፣ ግንደወይን፣ መርጡለማሪያም፣ ፈለገ፣ ድጎ፣ ፈረ ስቤት፣ አስተሪዮ፣ ሰዴ ከተማ እና አካባቢያቸው ላይ ከትናንት 11፡00 ሰዓት ጀምሮ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል።

በተመሳሳይ በነጌሌ ቦረና ከፍተኛ የኃይል አስተላለፊያ መስመር 66 ኪ.ቮ ሃይል አስተላላፊ መስመር ላይ በደረሰ ብልሽት ምክንያት በነገሌ ቦረና ከተማ፣ ፋልቱ፣ ቢድሬ፣ ዋድራ እና ሀረቀሎ አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን ችግሩ ተፈቶ ወደ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁ በትህትና እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


የጅማ ሪጅን 3 የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ አደረገ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጅማ ሪጅን ባለፉት 9 ወራት ሶስት የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ አድርጓል።

የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ የሆኑት ቃቂ ፣ገንዲ ዳለቾ እና ሊሙ ካሳ ቀበሌዎች ሲሆኑ በቃቂ ቀበሌ የተዘረጋው 15 ኪሎ ሜትር መካከለኛ እና 9 ዝቅተኛ መስመሮችን እንዲሁም 1 ትራንፎርመር 220 ደንበኞችን የሚያስተናግድ ነው።

በተመሳሳይ ለገንዲ ዳለቾ ቀበሌ 8 ትራንስፎርመሮች የተተከሉ ሲሆን 900 ደኖበኞችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚችል ነው እንዲሁም ለሊሙ ካሳ ቀበሌ 5 ትራንስፎርመሮች ገጠማ በማድረግ 320 ደንበኞች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሆኗል።

ሪጅኑ በ9 ወራት ውስጥ 51 ኪ.ሜ የመካከለኛ እና 60 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመሮችን የዘረጋ ሲሆን የ14 ትራንስፎርመሮች ተከላም አድርጓል።

በዚህ በጀት አመት 3 ሺህ 200 የገጠር ቀበሌ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ እስካሁን 2 ሺህ 300 ደንበኞችን ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል፡፡

በአጠቃላይ ሪጅኑ በዚህ ዓመት 5 የገጠር ቀበሌዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዶ የሶስቱን ያጠናቀቀ ሲሆን የሁለት ቀሪ ሥራቸው 80 በመቶ የተጠናቀቀ መሆኑ ተጠቅሷል።

ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃችን ለማግኘት ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
[Facebook] http://www.facebook.com/EEUOfficial
[Telegram] https://t.me/eeuethiopia
[Website] http://www.eeu.gov.et
[YouTube] https://www.youtube.com/


በአዲስ አበባ፣ ሸገር እና ሐረሪ ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡፡
http://www.ethiopianelectricutility.gov.et/power-interruption?lang=am


ክቡራን ደንበኞቻችን የተቋረጠውን አገልግሎት በአጭር ጊዜ ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እያደረግን ነው

ካለፉት ሶስት ቀናት ጀምሮ ሲስተማችን ላይ ባጋጠመ ቴክኒካል ችግር ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎቻችን እንዲሁም የዲጂታል ክፍያ አማራጮች ላይ የአገልግሎት መቋረጥ ማጋጠሙን ማሳወቃችን ይታወሳል፡፡

ውድ ደንበኞቻችን ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል በድጋሚ ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ የተቋረጠውን አገልግሎት በአጭር ጊዜ ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እያደረግን መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

ክቡራን ደንበኞቻችን ያጋጠመንን ችግር በመረዳት የተቋረጠው አገልግሎት እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን የተለመደ ትብብራችሁን እየጠየቅን፤ ከክፍያ መዘግየት ጋር በተገናኘ የአገልግሎት መቋረጥ የማይኖር መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

6.7k 0 85 60 63

የሂርና ከተማ የመካከለኛ መስመሮች መልሶ ግንባታ እየተከናወነ ነው

በሒርና ከተማ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት የመካከለኛ መስመሮች የእንጨት ምሰሶዎች ሙሉ በሙሉ በኮንክሪት ምሶሶ የመቀየር ስራ እየተከናወነ ነው፡፡

በከተማዋ የሚገኙት የእንጨት ምሰሶዎች ከ40 ዓመት በላይ ያገለገሉና ያረጁ በመሆናቸው ለኃይል መቆራረጥ መንስኤ ሲሆኑ ቆይቷል፡፡

በመልሶ ግንባታው ከጭሮ ሰብስቴሽን እስከ ሂርና የተዘረጉት 600 የእንጨት ምሰሶዎች ወደ ኮንክሪት ምሰሶ ይቀየራሉ፤ ከጭሮ እስከ ሂርና 46 ኪ.ሜ፣ እስከ ዱባ ወረዳ ደግሞ 18 ኪ.ሜ በአጠቃላይ 64 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመሮች መልሶ ግንባታ ይከናወናል፡፡

የመልሶ ግንባታው ከሂርና ፊደር አገልግሎት የሚያገኙት ጡሎ ወረዳ፣ ሂርና ከተማ፣ ዱባ ወረዳ እና ግማሽ መስላ ወረዳ የኃይል አቅርቦት ያልተቆራረጠና ጥራት ያለው እንዲሆን ያስችላል፡፡

በአሁኑ ወቅት የኮንክሪት ምሰሶ ግዢ ተፈፅሞ የቁፋሮ ሥራ የተጀመረ ሲሆን በሁለት ወራት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዟል፡፡

በተመሳሳይ ለረዥም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን የገለምሶ ከተማ የእንጨት ምሶሶ ወደ ኮንክሪት ለመቀየር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡

መልሶ ግንባታው 37 ኪ.ሜ የሚያካልል እና ገለምሶ ከተማን፣ የኦዳቡልቱም ወረዳ ገጠር ቀበሌዎችን፣ የበአብሮ ወረዳ ገጠር ሳተላይቶች፣ የተሰወኑ የዳሮ ለቡ ቀበሌዎች ኃይል አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ የሚያግዝ ነው፡፡

ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃችን ለማግኘት ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
[Facebook] http://www.facebook.com/EEUOfficial
[Telegram] https://t.me/eeuethiopia
[Website] http://www.eeu.gov.et


በአዲስ አበባ፣ ጎንደርና ሐረሪ ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡፡
http://www.ethiopianelectricutility.gov.et/power-interruption?lang=am


በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የሃይል አቅርቦት

ከይርጋለም ሀይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ብሌ ሆራ ሀይል ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው የ 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል አስተላላፊ  መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት  ብሌ ሆራና አካባቢው ፣ ያቤሎና አካባቢው እንዲሁም ሞያሌና አካባቢው ላይ የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ መስመሩ ላይ ያጋጠመው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይልበኩል ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በጅማ ዞን ቀርሳ ወረዳ ቃቂ ቀበሌ የተከናወነ የመስመር ዝርጋታ !!




ሪጅኑ 7 ሺህ 631 አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ አደረገ

በኢትዮጵያ ኤሌክትክ አገልግሎት የባሌ ሮቤ ሪጅን ባለፉት 8 ወራት ውስጥ 7 ሺህ 631 ለሚሆኑ አዳዲስ ደንበኞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ በማድረግ የዕቅዱን 103.28% አሳክቷል፡፡

ሪጅኑ አዲስ ኃይል ፈልገው ከሚመጡት ደንበኞች ባሻገር ካለፈው ታህሳ ወር ጀምሮ አንድ ሠራተኛ በቀን አንድ ደንበኛ በሚል ንቅናቄ በተሰራ ስራ ከዕቅድ በላይ በመፈፀም ውጤታማ መሆን ችሏል፡፡

በሪጅኑ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ በማህበራት እና በራስ ኃይል በተሰራ የመልሶ ግንባታ ስራ 11.3 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር 18.98 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ስራ የተሰራ ሲሆን የ 11 ትራንስፎርመር አቅም ማሳደግ ስራ ተሰርቷል፡፡

በዚህም ከጃራ እስከ ዲንሳ ፣ከሮቤ -ጎሮ- ሶፍኡመር ፤ሮቤ ሪዲዮ ጣቢያ አካባቢ ፣ሮቤ ሼህ አብዱልመሊካ ሜዳ አካባቢ፣ አሊ ከተማ፣ሮቤ ኤግናን ካፌ እና የተባበሩት ፉድ ኮምፕሌክስ አካባቢ እና ሮቤ ዶንሳ ገበያ ይከሰት የነበረውን የኃይል መቆራረጥ መቀነስ ተችሏል፡፡

በተመሳሳይ 389.24 ኪ.ሜ የመካከለኛ መስመር 51.05 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር እንዲሁም 76 ትራንስፎርመር አቅም የማሳደግ ስራ ተከናውኗል፡፡

የመልሶ ግንባታ ስራው ሲጠናቀቅ በመልካ ዋከና-ሃቆ፤ ከራይቱ-ጊኒር፣ መልካ ዋከና-ዶዶላ፣ ሲናና 3 ፣ ከሃሮ-ሃረዋ፣ አጋርፋ ቲቪቲ ኮሌጅ፣ አለምገና ሂሱ-ሃስን ቤሪራ፣ ጎባ-ሃሮ-ድሎመና፣ ሮቤ ፣ አሊ፣ጎባ ደም ባንክ፣ አንጌቱ፣ ኪታታ፣ አዳባ እና ዶዶላ ከተማ አካባቢዎች ይስተዋል የነበረውን የኃይል መቆራረጥ ለመቀነስ ያስችላል ተብሏል፡፡

ሪጅኑ ባለፉት ስምንት ወራት የትራንስፎር መቃጠልን ለመቀነስ በተሰራ ስራ 27 ትራንስፎርመር አቅም በማሳደግ እና አጋዥ በማሰቅመጥ በትራንስፎርመሮች ላይ የሚደርሰውን መቃጠል ለመቀነስ መስራት ተችሏል፡፡

ሪጅኑ ለ117 ሺህ 432 ደንበኞች አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን 14 አገልግሎት መስጫ ማዕከላት እና 168 የሳተላይት ጣቢያዎች አሉት፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡፡
http://www.ethiopianelectricutility.gov.et/power-interruption?lang=am


ከ6 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በምእራብ ኦሞ ዞን ሜኒት ሻሻ ወረዳ የተገነባው እና ከ6 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የይርኒ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በዛሬው እለት ተመርቋል።

በምርቃት ሥነ ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት በውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢ/ር ሱልጣን ወሊ ኢነርጂ ለማንኛውም አይነት የልማት እንቅስቃሴ ዋነኛው ግብዓት በመሆኑ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶበት እየተሠራ መሆኑን ገልጸው የይርኒ የጸሐይ ኃይል ማመንጫ መገንባቱ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር አንጻር ቀላል የማይባል ሚና ያለው መሆኑን አንስተዋል።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥራ አስፈጻሚ ተወካይ እና የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ መላኩ ታዬ በበኩላቸው ለዜጎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማድረስ የመልሶ ግንባታ እና ማሻሻያ ሥራዎችን በመሥራት እንዲሁም ተጠቃሚ ያልሆኑ ዜጎች ደግሞ ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህም ከዋናው የኤሌክትሪክ መረብ ርቀው የሚገኙ የገጠር ከተሞች እና መንደሮችን የጸሐይ ኃይል ማመንጫ በመገንባት ተጠቃሚ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ገልጸው የይርኒ እነዚህ የጸሐይ ማመንጫ በመገንባቱ ከ 6 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ለአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም የጤና እና የትምህርት ተቋማት 24 ሰአት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ ተደርገዋል ብለዋል፡፡

የይርኒ ጸሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ ከ 60 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብ ብድር የተገነባ ሲሆን ነዋሪዎቹን ተጠቃሚ ለማድረግ 0.5 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ እና 2.4 ኪሎ ሜትር የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ እንዲሁም ባለ 100 እና 200 ኬ.ቪ.ኤ ትራንስፎርመሮች ተከላ ተከናውኗል፡፡

ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃችን ለማግኘት ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
[Facebook] http://www.facebook.com/EEUOfficial
[Telegram] https://t.me/eeuethiopia
[Website] http://www.eeu.gov.et
[YouTube] https://www.youtube.com/@EthiopianElectricUtility
[Tiwtter] https://x.com/EEUEthiopia
[TikTok] https://www.tiktok.com/@ethiopian.electri
[Whatsapp] https://web.whatsapp.com/
[EEU Customers Digital Support] https://t.me/EEUCustomersupport




Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የጅማ ከተማ ኮሪደር ልማት እና የማታ ገፅታ !!


ተጨማሪ የቅድመ-ክፍያ ካርድ መሙያ ቢሮ መከፈቱ ስለማስታወቅ

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደቡብ አዲስ አበባ ሪጅን ቁጥር 2 አገልግሎት መስጫ ማዕከል የቅድመ ከፍያ ተጠቃሚ ደንበኞችን እንግልት ለመቀነስና የበለጠ ወደ ደንበኞች ለመቅረብ ቦሌ ሚካኤል ልዩ ቦታው ታክሲ ተራ ማሕበር ፊት-ለፊት፣ ትራፊክ መብራቱ አካባቢ በሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ብሎክ ቁጥር 2 የቅድመ ክፍያ ካርድ መሙያ ተጨማሪ ቢሮ ክፍቷል፡፡

በመሆኑም የቅድመ-ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን በተጠቀሰው ቦታ በመሄድ ካርድ መሙላት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


⚠️ እንድታውቁት⚠️
ሲስተም ላይባጋጠም ብልሽት ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎቻችን እንዲሁም የዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ጨምሮ ከኢንተርኔት አገልግሎትጋር ተያያዥነት ያላቸው የድህረ ክፍያ አገልግሎቶች አገልግሎት መስጠት አቁመዋል፡፡

ውድ ደንበኞቻችን ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እየጠየቅን፤ ችግሩ ተፈትቶ የተቋረጠው አገልግሎት እስከሚመለስ ድረስ በአቅራቢያችሁ በሚገኙ ዲስትሪክቶች ወይም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎቻችን በአካል ወይም በቀጥታ ስልክ በመደወል ተገቢውን አገልግሎት ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

8.6k 0 120 33 9

በአዲስ አበባና ጎንደር ከተሞች የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውንቦታዎች ለማወቅ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፡፡
http://www.ethiopianelectricutility.gov.et/power-interruption?lang=am


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል

ከመንዲ -አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል አስተላለፊ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት በአሶሳ ፣ በባምባሲ፣ በኡራ፣ በአብራሃሞ፣ በሸርቆሌ፣ በመንጌ፣ በኩርሙክ፣ በሆሞሻ፣ በቶንጎ ፣በጊዳሚ፣ ቤጊ፣ ቆንዳላ፣  በኡንዱሉ፣ በብልድግሉ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው ተቋርጦ የነበረው  የኃይል አቅርቦት ተገናኝቷል።

የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የሃይል አቅርቦት

ከመንዲ -አሶሳ በተዘረጋው 132 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል አስተላለፊ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ከዛሬ 8፡10 ጀምሮ በአሶሳ ፣ በባምባሲ፣ በኡራ፣ በአብራሃሞ፣ በሸርቆሌ፣ በመንጌ፣ በኩርሙክ፣ በሆሞሻ፣ በቶንጎ ፣በጊዳሚ፣ ቤጊ፣ ቆንዳላ፣  በኡንዱሉ፣ በብልድግሉ ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ መስመሩ ላይ ያጋጠመው ችግር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይልበኩል ተፈትቶ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.