Postlar filtri


በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1166?lang=am


ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብዎን በቀላሉ፣ የትም ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው ከዚህ በፊት በሚከፍሉበት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ካሻዎ በቴሌ ብር፣ በሲቢኢ ብር፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአዋሽ ብር ፕሮ ወይም በኤም ፔሳ በኩል ይፈፅሙ፡፡

ፍጆታዎ በስልክዎ! ዘመናዊ የክፍያ አማራጭ በመምረጥ ኑሮዎን ያቅሉ!

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የኃይል አቅረቦት ተቋርጧል

በነቀምቴ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንሰፎርመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት በነቀምቴ ከተማና አካባቢው፣ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ በኢትዮ ቴሌኮም ዋና ጣቢያ፣ በአርጆ አዉራጃ ከተማ እና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በኃይል ማከፋፈያ ትራንሰፎርመሩ ላይ የተፈጠረው ብልሽት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በኩል ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


#የጨረታ ማስታወቂያ


የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በግንባታ ላይ በሚገኘው የቴክኖለጂ ልህቀት ማዕከል የሚገኝ ድንጋይን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ ተጫራቾች ማስታወቂው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡


#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


ለግንባታ ሥራ የተነሱ ዜጎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሊሆኑ ነው

በአዳማ ከተማ ቁጥር 2 የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ሲከናወን የተነሱ አራት መቶ አባወራዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ሊደረጉ መሆኑን የአዳማ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጠሃ አህመድ ገለፁ፡፡

የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያገኙት በአዳማ ከተማ አስተዳደር በቶሌ እና ዋጩ ለፋ ቀበሌዎች የሚገኙ ነዋሪዎች መሆናቸውን ጠቅሰው በአሁኑ ሰዓት የመስመር ዝርጋታ ስራ እየተጠናቀቀ ነው ብለዋል፡፡

በተከናወነው ሥራ 17 ነጥብ 5 የዝቅተኛ እና 3 ነጥብ 5 የመካከለኛ ቮልቴጅ የኤሌክትሪክ ሽቦ መዘርጋቱን ተናግረዋል፡፡

አክለውም 3 ባለ 200 ኪ.ቮ.አ እና አንድ ባለ አንድ መቶ ኪ.ቮ.አ ትራንስፎርመር መተከሉን ጠቅሰው ነዋሪዎቹ እስከ የካቲት ወር አጋማሽ ኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ይሆናሉ ብለዋል፡፡

የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ዝርጋታውን ለማከናወን 24 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገ ሲሆን ወጪውም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሸፈኑን አብራርተዋል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-
http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1164?lang=am


የሥራ ማስታወቂያ

9.1k 0 155 26 59

ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት የሚዳርግ መሆኑን ያውቃሉ? እንግዲያውስ እንንገርዎ!! ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳብ በወቅቱ አለመፈፀም ለተጠራቀመ የፍጆታ ሂሳብና ቅጣት ይዳርጋል፡፡ ስለሆነም ውድ የድህረ ክፍያ አገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን ወርሃዊ የኤሌክትሪክ ፍጆታ ሂሳባችሁን በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በወቅቱ እንድትፈፅሙ እናሳስባለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


የመታር ሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት የመስመር ዝርጋታ 98 በመቶ ደረሰ

በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን ዋንተዋ ወረዳ መታር ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የመታር ሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክት የመስመር ዝርጋታ ሥራ 98 በመቶ ማድረስ ተችሏል፡፡

በፕሮጀክቱ 2.1 ኪ.ሜ የመካከለኛ፣ 17 ኪ.ሜ የዝቅተኛ መስመር ዝርጋታ እና የ4 ትራንስፎርመር ተከላ ስራ የተከናወነ ሲሆን የሶላር ሚኒግሪድ ግንባታ አጠቃላይ ግንባታ 40 በመቶ ደርሷል፡፡

እየተጠናቀቀ የሚገኘው የመስመር ዝርጋታ 20 ሚሊየን ብር በጀት የተመደበለት ሲሆን ለኃይል ማመነጫ ግንባታው ደግሞ 532 ሺህ 682.74 ዶላር እና 7 ሚሊየን 231 ሺህ 714 ብር በጀት ተይዞለታል፡፡

የፕሮጀክቱ ግንባታ እየተከናወነ የሚገኘው ሲ.ኢ.ቲ እና ኤን.አር በተባሉ ሁለት የቻይና ኮንትራክተሮች አማካኝነት ሲሆን ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ እስከ 250 ኪሎ ዋት ኃይል የሚያመነጭ ይሆናል፡፡

የፀሐይ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ለማብቃት ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኙ የጤና ተቋማት፣ የእርሻ ማዕከላት፣ ትምህርት ቤቶች፣ ወፍጮ ቤቶች፣ የውሃ ተቋማትና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በመኖሪያ ቤት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዴት በቁጠባ መጠቀም ይቻላል?

የመብራት አምፖሎች አጠቃቀም

• ቀን ቀን መብራት አለማብራት፤ በቀን ክፍለ ጊዜ የፀሐይ ብርሃንን መጠቀም፤
• በማንኛውም ጊዜ ክፍላችንን ለቀን ስንወጣ በመብራት ላይ ያሉ መብራቶችን ማጥፋት፤
• ከኢንካንድሰንት አምፖሎች ይልቅ የኤልኢዲ አምፖሎችን መጠቀም፤
• ፍሎረሰንት አምፑል ከተባላሸ ባላስቱን መንቀል ወይም መጠገን ምክንያቱም ባላስት ከሚመጣው ሀይል እስከ 30% የሚሆነውን ስለሚያባክን፤
• ከማግኔቲክ ባላስት ይልቅ ኤሌክትሮኒክ ባላስት ፍሎረሰንት አምፖል በመጠቀም የሚባክን ሀይል መቀነስ፤
• የአምፖሎችን ፅዳት መከታተል፤

የፍሪጅ አጠቃቀም

• ፍሪጅ የሚገቡ ምግቦች ትኩስ መሆን የለባቸውም፤
• የፍሪጅ ጋስኬት በደምብ መዘጋቱን ማረጋገጥ፤
• ከማብሰያ ምድጃዎች እና ከግርግዳ ጋር አለማስጠጋት
• ቀጥታ ፀሐይ ከሚያስገቡ መስኮቶች ወይም በሮች ፊት ለፊት አለማስቀመጥ፤
• ቴርሞስታቱን ትክክለኛው ቁጥር ላይ ማድረግ (medium range)፤
• በረዶ ከያዘ ቶሎ ማስወገድ፤
• ከሚፈለገው የቅዝቃዜ መጠን በላይ አለማቀዝቀዝ፤
• ማቀዝቀዣዎች በተቻለ መጠን ሙሉ ሆነው እንዲያቀዘቅዙ ማድረግ፤
• የማቀዝቀዣዎችን በር በተደጋጋሚ አለመክፈትና በትክክል መዘጋቱን ማረጋገጥ፤

ለምጣዶችና ምድጃዎች

• የማይክሮዌቭ ኦቭን ማብሰያዎችን መጠቀም፤
• ምግብ በሚያበስሉበት ወቅት ማብሰያውን በትክክል መዝጋትና ቶሎ ቶሎ አለመክፈት፤
• ምግብ ሲያበስሉ 5 ደቂቃ ቀደም ብለው ምድጃውን ማጥፋት፤ ምድጃው በያዘው ሙቀት ቀሪውን ማብሰል ስለሚቻል፤
• ምግብ ለማብሰል ሲዘጋጁ ምድጃውን ለማጋል ከ5 ደቂቃ ላነሰ ጊዜ ብቻ ያብሩ፤

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

7.1k 0 70 27 29

የአዲስ አበባ ትራንስሚሽንና ዲስትሪቢዩሽን መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
**************************
በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ በ50 ኪ.ሜ ራዲየስ ውስጥ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮች አቅም በማሳደግ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎቶችን እንዲያስተናግድ ለማስቻልና የኃይል ብክነትን ለመቀነስ እንዲሁም መሰረተ ልማቱን ከአንድ ማዕከል ሆኖ ለመቆጣጠር የሚያስችለው ፕሮጀክት 87 ነጥብ 94 በመቶ ሥራው ተጠናቋል፡፡

ፕሮጀክቱ ረጅም ጊዜ ያገለገሉ የእንጨት ምሰሶዎችን በኮንክሪት መቀየርን ጨምሮ መስመሮቹን በተሻለ ጥራት በማደስ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኃይል ፍላጎት እንደሚያረካ እና ከመስመሮች እርጅና ጋር ተያይዞ የሚፈጠርን የኃይል መቆራረጥ በእጅጉ እንደሚቀንስ ይታመናል፡፡

እስካሁን 9 ሺህ 644 የእንጨት ምሰሶዎችን በኮንክሪት ምሰሶ ተቀይረው፤ 347 ነጥብ 39 ኪ.ሜ በቀላል ንክኪ ምክንያት ኃይል እንዳይቋረጥ የሚያደርጉ ሽፍን የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ ተከናውኗል፡፡

ለዝርዝር መረጃው 👉 http://www.eeu.gov.et/press-releases/detail/1156?lang=am


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1159?lang=am


ተቋርጦ የነበረው የኃይል አቅርቦት ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል።


ከፍተኛ የኃይል አስተላለፊያ መስመር 66kv ኮሶበር እና ቻግኒ መከከል  በተፈጠረ ብልሽት ምክንያት ቻጊኒን ጨምሮ በመተከል  ዞን፣ በግ/በለስ ከተማ ፣በማንዱራ ፣ በፖዌ፣ በዲባጤ፣ በቡለን፣በደ/ዘይት፣ በዳንጉር፣ወረዳዎችና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጠው የነበረ በ20/05/2017 ዓ .ም 7:50  ጥገና ተጠናቀው  ወደ አገልግሎቱን ተመልሷል።

የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት ለጠበቃችሁን ክቡራን ደንበኞቻችን ከልብ እናመሰግናለን ።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በኃይል አስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት የተቋረጠ የኃይል አቅረቦት

ከኮሶበር -ቻግኒ በተዘረጋው 66 ኪ.ቮልት ኃይል አስተላለፊያ መስመር ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት ቻግኒን ጨምሮ በመተከል ዞን፣ በግ/በለስ ከተማ፣ በማንዱራ፣ በፖዌ፣ በዲባጠ፣ በቡለን፣ በደ/ዘይት፣ በዳንጉርና አካባቢዎቻቸው የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡

ስለሆነም በኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ የተፈጠረው ብልሽት ተጠግኖ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ ክቡራን ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


የመስመሮች መልሶ ግንባታ - ለአስተማማኝ የኃይል አቅርቦት

አስተማማኝ የሆነ የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ዘመኑ ያፈራቸውንና ውጤታማ የሆኑ አዳዲስ አሰራሮችን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችንና ሌሎች የኃይል አማራጮችን ስራ ላይ ማዋል ያስፈልጋል፡፡

በዚህ መሰረት እያደገ የመጣውን የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማርካት በተቋሙ ከፍተኛ ስራ ተከናውኗል፤ እየተከናወነም ይገኛል፡፡

በተለይ በአገልግሎት ጥራት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች እየተከናወኑ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ማሻሻያና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ከስር የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ!
http://www.eeu.gov.et/publication/detail/1153?lang=am


ለኢንዱስትሪ ፓርኮች ተጨማሪ ኃይል ሊሰጥ ነው

ለአዳማ እና ሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ከአንድ ወር በአነሰ ጊዜ ውስጥ ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ሊሰጡ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአዳማና የሐዋሳ ሪጅኖች አስታውቀዋል፡፡

ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ ኃይል ለመስጠት 766 የኮንክሪት ምሰሶ ተከላ እና 42 ኪሜ የመካከለኛ ቮልቴጅ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ የተጠናቀቀ ሲሆን 8 ኪ.ሜ በቀጣይ አንድ ወር ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡

ለኢንዱስትሪ ፓርኩ የሚዘረጋው የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ቀድሞ ሲያገኝ ከነበረው 20 ሜጋ ዋት በተጨማሪ በ40 ሜጋ ዋት ኃይል ሊያገኝ የሚያስችለው ነው ተብሏል፡፡

ለአዳማ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚደረገው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ወደ ሥራ ይገባል ተብሏል፡፡

በተመሳሳይ ለሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመስጠት የ20 ነጥብ 8 የመሬት ውስጥ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ስራ ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁ ታውቋል፡፡

ፓርኩ ኃይል ለማቅረብ የቀረው ሥራ ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ማሰራጫ መስመር የማገናኘት እንደሆነ የታወቀ ሲሆን ለዚህ የሚያግዙ 19 ምሰሶዎች በማጓጓዝ ላይ ይገኛል ተብሏል፡፡

የሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከአንድ ወር በአነሰ ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ጥረት የሚደረግ መሆኑ ከአገኘነው መረጃ ተረድተናል፡፡

የኢንዱስትሪ ፓርክ ተጨማሪ መሰረተ-ልማት ለመዘርጋት ያስፈለገው የኃይል መቆራረጥ ለማስቀረት ታሳቢ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡

በተጨማሪም የቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ 21 ኪሎ ሜትር የመሬት ውስጥ የቀጥታ መስመር ለመዘርጋት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በተፈፀመ የስርቆት ወንጀል ከ6 መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት ጉዳት ደረሰ

በቢሾፍቱ ከተማ ቦሮ ሆራ አርሰዴ ወረዳ በተለምዶ ሽንብራ ሜዳ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ለውኃ አገልግሎት በሚሰጥ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት 672 ሺህ ብር የሚገመት ጉዳት ደርሷል፡፡

ወንጀለኞቹ የከፍተኛ ኃይል መስመር 5 ምሶሶዎችን በመጋዝ በመቁረጥ ጉዳት ያደረሱ ሲሆን የወንጀሉ ፈፃሚዎች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ለማድረግ ከህግ አካላት ጋር ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

በአሁኑ ወቅት በአካባቢው ተቋርጦ የነበረውን የሃይል አቅርቦት ለመመለስ መስመሩን በአዲስ የመቀየር ስራ ተከናወኗል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት በአካባቢው የሚፈፀመው የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ስርቆት ለኃይል መቆራረጥ ምክንያት እየሆነ ይገኛል፡፡

በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ ስርቆት የሚፈፅም ማንኛውም አካል በቴሌ ኮሚኒኬሽንና የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት አውታሮች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 464/97 መሰረት ከ5 ዓመት እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት የሚቀጣ ይሆናል፡፡

በመሆኑም ተቋሙ ከሚወስደው ህጋዊ እርምጃ ባሻገር ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ የሆነ የህዝብ ሀብት የፈሰሰባቸውን የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ሁልግዜ በንቃት በመጠበቅ የዜግነት ኃላፊነታቸው ሊወጡ ይገባል፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት


በአዲስ አበባ ከተማ የቅድመ ጥገና ሥራ ለማከናወን ሲባል በዕቅድ ኃይል የሚቋረጥባቸውን ቦታዎች ለማየት ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡-http://www.eeu.gov.et/power-interruption/detail/1151?lang=am


በማህበር የተደራጁ ነዋሪዎች ያቀረቡት የኃይል ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ ነው

የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ወጪ ከፍለው ሲጠባበቁ የነበሩ ሦስት ማኅበሮች በቀጣይ ሳምንት ውስጥ ያቀረቡት የኃይል ጥያቄ ምላሽ ሊያገኝ መሆኑን የባህር-ዳር ሪጅን ቁጥር 3 አገልግሎት መስጫ ማዕከል ሥራ አስኪያጅ አቶ አዲሱ ፈረደ አስታወቁ፡፡

ማኅበራቱ በዘነዘልማ ከተማ በመቶ ካሬ ሜትር ተደራጅተው በኤቢሲ ገመድ፣ በትራንስፎርመር እና በምሶሶ እጥረት ለአምስት ወራት ሲጠባበቁ የቆዩ ናቸው ብለዋል፡፡

በአጠቃላይ በዘንዘለማ መንደር በሦስት ማኅበራት ተደራጅተው አዲስ ሃይል ሲጠባበቁ የነበሩ 497 ነዋሪዎች መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ በሚቀጥለው ሳምንት 8 ሺህ 9 መቶ ሜትር የኤቢሲ ኬብል በማሟላት የማህበራቱ የሃይል ጥያቄ ምላሽ እንደሚያገኝ አስታውቀዋል፡፡

በማዕከሉ የዘንዘልማ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ለማድረግ የአንድ ኪሎ ሜትር የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ የተደረገ ሲሆን 14 ምሰሶ መተከሉንም ተናግረዋል፡፡

ስራ አስኪያጁ አክለውም 2 ሺህ ሜትር ኤ.ቢ.ሲ የኤሌክትሪክ ሽቦ በቄስ እሸቴ ስም ለተደራጁ 127 አባወራዎች ተዘርግቷል ብለዋል፡፡

በቄስ እሸቴ ስር ለተደራጁ ማኅበራት ቀሪ 1 ሺህ 500 ሜትር ኤቢሲ የኤሌክትሪክ ሽቦ እስከ ሰኞ የአቅርቦት ችግሩ ተቀርፎ ኤሌክትሪክ የሚያገኙ ይሆናል፡፡

በአቶ ኑርልኝ ስም የተደራጁት ማኅበራት በቀጣይ ማክሰኞ ኤሌክትሪክ እንደሚያገኙ ተገልፆ በአቶ መእረ ስም ለተደራጀው ማኅበር ደግሞ ትራንስፎርመር ለማቅረብ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.