የአዲስ አበባ ትራንስሚሽንና ዲስትሪቢዩሽን መልሶ ግንባታና አቅም ማሳደግ ፕሮጀክት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል
**************************
በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ በ50 ኪ.ሜ ራዲየስ ውስጥ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮች አቅም በማሳደግ ተጨማሪ የኃይል ፍላጎቶችን እንዲያስተናግድ ለማስቻልና የኃይል ብክነትን ለመቀነስ እንዲሁም መሰረተ ልማቱን ከአንድ ማዕከል ሆኖ ለመቆጣጠር የሚያስችለው ፕሮጀክት 87 ነጥብ 94 በመቶ ሥራው ተጠናቋል፡፡
ፕሮጀክቱ ረጅም ጊዜ ያገለገሉ የእንጨት ምሰሶዎችን በኮንክሪት መቀየርን ጨምሮ መስመሮቹን በተሻለ ጥራት በማደስ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኃይል ፍላጎት እንደሚያረካ እና ከመስመሮች እርጅና ጋር ተያይዞ የሚፈጠርን የኃይል መቆራረጥ በእጅጉ እንደሚቀንስ ይታመናል፡፡
እስካሁን 9 ሺህ 644 የእንጨት ምሰሶዎችን በኮንክሪት ምሰሶ ተቀይረው፤ 347 ነጥብ 39 ኪ.ሜ በቀላል ንክኪ ምክንያት ኃይል እንዳይቋረጥ የሚያደርጉ ሽፍን የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ ተከናውኗል፡፡
ለዝርዝር መረጃው 👉
http://www.eeu.gov.et/press-releases/detail/1156?lang=am