በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባሉት አስተዳደራዊ ጕዳዮች ላይ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ መግለጫ ሰጠ።
ጥቅምት ፲፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባሉት አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ከተቋቋመበት ማግስት ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ መሠረት በማድረግ አያሌ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን በመግለጽ ለኢኦተቤ ቴቪ (#EOTCTV) መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የመግለጫውን ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ! አሜን!
በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ የተስጠ መግለጫ ።
ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባሉት አስተዳደራዊ ጕዳዮች ላይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ከተቋቋመበት ማግሥት ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስን መመሪያ መሠረት በማድረግ አያሌ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።
የዚህ የማጣራት ሥራ በጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ጀምሮ የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳኗር ልማት ድርጅትን አካቶ ፧ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እና በሥሩ ያሉ አድባራትና ገዳማት ላይ ያለውን የአሠራር ክፍተት የመጨረሻ እልባት እንዲሰጥ ያስችል ዘንድ የቀረቡ ጕዳዮች ያላቸውን አግባብነት መመልከት ሲሆን በዋነኝነት ግን የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ችግሮቿን መፍታት ስለሆነ ታላቀ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መሆኑ ታምኖበታል፡፡
በዚህም መሠረት አጣሪ ኮሚቴው ጠቅላላ የማጣራት ሂደቱን በሦስት ዋና ክፍሎች በመክፈል እየተገበረ የሚገኝ ሲሆን በዚህም መሠረት ክፍል አንድ
1. አጣሪ ኮሚቴው አዘጋጅቶ በአጸደቀው የሥራ መመሪያ መሠረት ጽ/ቤት አዋቅሮ እና የጽ/ቤት ሥራ አስፈጻሚዎችን መድቧል፡፡
2. መደበኛ የስብሰባ ጊዜያትን ወስኗል፣ የኮሚቴውን የሥራ ማጣቀሻ ዝርዝር እቅድ እና የሥራ መመሪያውን አዘጋጅቶ
በቋሚ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለማጣራት ሥራው አስፈላጊ የሆኑትን ቅድመ ዝግጅቶች በማሟላት ወኗ ሥራ 7ብቷል፡፡
3. በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት የማጣራት ሥራ የ ሚ ካ ሔ ድ ባ ቸ ውን ተቋ ማ ት ን በ መ ለ የ ት ና ሊመለከታቸው በሚገባው ጕዳዮች ዙሪያ ጥልቅ ምልከታ በማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራውን አጠናቋል።
4. የማጣራት ሥራው የታለመለትን ውጤት በማምጣት ረ7ኗ ያለውን ችግር ነቅሶ በማውጣትና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት አስተዳደራዊ የሥራ ዘርፎችን አይቷል፡፡ የሚጣሩ
5. በጥናት ተለይተው ለተቀመጡት አምስት የሥራ ዘርፎች በእያንዳንዳቸው የዘርፏን ሞያ መሠረት ባደረ7 መልኩ ድጋፍ ሰጭ ባለሞያዎችን አቋቁሞ የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር ሥራ አስጀምሯል፡፡
6. በማጣራት ሂደቱ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትን የማሳተፍ ቅድመ ሁኔታዎችን በመለየት እና የሥራ ዝርዝርበማዘጋጀት በቋሚ ሲኖዶስ መመሪያ ሰጭነት የቅሬታ መረጃዎችን እና ማስረጃዎችን በተለያዩ የመረጃ መስጫ ዘዴዎች ለማቅረብ እንዲቻል በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት መደበኛ ቢሮ በመክፈትና ቋሚ ሠራተኞችን በመመዷብ ሥራውን እያከናወነ ይገኛል ።
ከፍል ሁለት
1. በአጣሪ ኮሚቴውና የየዘርፉ ድጋፍ ሰጭ ባለሞያዎች ጋርየሥራ ዝርዝር እቅድ መሠረት ኮሚቴው በቀጣይከሚመለከታቸው የአስተዳዳራር አካላት ጋር የገጽ ለገጽ
ማስረጃ የማረጋጋጥ እና ለማጣራት ሥራው አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ውደደት የማካሄድ ሥራ ያከናውናል።
2. ቀሬታዎችን የመስማትና የቅሬታ ሰነዶችን የመቀበል ደፋዊ ሥራውን የጀመረ በመሆኑ አስፈላጊ በሆኑ እና መፍትሔ በሚሹ ጕዳዮች ላይ ሁሉ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች አና ከማጣራት ሥራው ጋር በተያያዘ ለሚቀርቡ መረጃዎች እና ማስረጃዎች በሩ ክፍት መሆኑን ያስታውቃል፡፡
3. አጣሪ ኮሚቴውና የየዘርፏ ድጋፍ ሰጭ ባለሞያዎች ጋርበሚኖረው የገጽ ለገጽ ውደደት ፣ የሰነዶች ምርመራ እና ማስረጃዎች የማጣራት ሥራ ማብራሪያ እና ምላሽ በሚፈልግበት አግባብ በድጋሚ ጕዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መረጃውን የማረጋገጥ ሥራ ያከናውናል፡፡
ክፍል ሦስት
1. በንጽ ለገጽ ውደደቶች፣ በመረጃ ማሰባሰብ እና ማጠናቀርሂደቶች እንዲሁም አሁን እየተከናወኑ ባሉ አስተዳደር ተኮርነባራዊ ኩነቶች ዙሪያ የማጠቃለያ ውደደት ኮሚቴው ከድጋፍ ሰጪ የዘርፍ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ያከናውናል።
2. የመረጃ ትንተና እና የማጣራት ሥራው ማጠቃለያ ሰነድ ይደራጃል።
3. የማጣራት ሰነዱ በግኝቱ፣ በሂደቱ እና በዘላቂ መፍትሔው ላይ የሚያተኩር ይዘት ኖሮት መረጃ እና ማስረጃዎችን ከህትመት እንዲሁም ምስል ወድምጽ ጋር በአባሪነት በማካተት ይጠናቀቃል፡፡
4. በስተመጨረሻም በማጣራት ሥራው የተገኘውን ውጤት በቋሚ ሲኖዶስ በኩል አጀንዳ አስይዞ ለምልዓተ ጉባኤ ያቀርባል።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ።
➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕➕
☎️ ለበለጠ መረጃ 👉 +251985585858
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo 🇪🇹 "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 🇪🇹
📡 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥
📱 የዲጂታል ሚዲያ ገጾች💻
ለመረጃ 📞 +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2
https://youtu.be/Wqgq1KebrOo➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=