Ministry of Education Ethiopia


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Ta’lim


This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገለጸ፡፡
------------------------------------------------

የካቲት 25 /2017 ዓ.ም 10ኛው የአፍሪካ የትምህርት ቤት ምገባ ቀን በሐረሪ ብሔራዊ ክልል በሐረር ከተማ በሚገኘው ሞዴል አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከብሯል።

በክብረበዓሉ ላይ የተገኙት የሐረሪ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

አቶ ኦርዲን መርሃ-ግብሩ የመማር ማስተማር ሂደቱን ይበልጥ ውጤታማ በማድረግና የትምህርት ተሳትፎ እና ጥራትን ከማሳደግ ባለፈ የትምህርት ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ እንደሚያግዝም ጠቁመዋል።

አቶ ኦርዲን ጨምረውም የትምህርት ቤት ምገባ ከሚሰጠው ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አንጻር ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መርሃ-ግብር መሆኑን ጠቅሰው የመምህራንና የትምህርት አመራሮች የመማር ማስተማር ትኩረትን በማይቀንስ መልኩ ራሱን የቻለ አደረጃጀት ተፈጥሮለት ሊመራ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ከመርሃ-ግብሩ አንጻር በክልሉ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልጸዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ-ግብር በለውጡ መንግስት ትኩረት ተሰጥቶት ቀጣይነት ባለው መልኩ በስፋት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኝና ውጤት እያስመዘገበ ያለ መርሃ-ግብር መሆኑን ገልጸዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1B9oAaubEK/


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቤተ-ሙከራዎች ውስጥ የሚገኙት መጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ኬሚካሎች ቆጠራ በመካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ።
----------------------------------------------
በትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት መሪ ሥራ አስፈጽሚ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቤተ-ሙከራዎች ውስጥ የሚገኙት መጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈባቸው ኬሚካሎች ቆጠራ በመካሄድ ላይ መሆኑ ገልጿል፡፡

የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ጉዳዮች ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሃንዲሶ(ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንደገለጹት ሥራ ክፍሉ በ2017 ዓ.ም በአቅድ ከያዛቸው የሪፎርም ስራዎች መካከል አንዱ የምርምር ግብዓቶችንና ፋሲሊቲዎችን በማሻሻል የቤተ-ሙከራ ስታንዳርዳይዜሽንን እና አክሬዲቴሽን ስርዓትን መዘርጋት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚገኙ የኢንዱስትሪ፤ የምርምር እና የላብራቶሪ ኬሚካሎች አያያዝ፤ ክምችትና የማጓጓዝ ሂደትና የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን ኬሚካሎች የቆጠራ ሥራ ለመሥራት እንዲቻል ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አካዳሚክ ቴክኒካል ረዳት ባለሙያዎች ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ይህ ሥራ የሚሰራው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብቻ ሳይሆን በአቅራቢያቸው በሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ስር ባሉ ቤተ-ሙከራዎች ውስጥ የሚገኙትን ኬሚካሎች ምንጭ፣ አይነት፣ ደረጃ፣ መጠን እና ባህሪይ የማወቅ መረጃ የማሰባሰብ ሥራ እንደሚሰራም ሃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡


በደቡብ ምዕራብ ቀጣና የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ።
--------------------------------

(የካቲት 24/2017 ዓ.ም) በጅማ ከተማ አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው በደቡብ ምዕራብ ቀጣና ስር የተደለደሉ የጅማ ዞን ት/ቤቶች ስፖርት ሊግ ውድድር ተጠናቀቀ፡፡

በጅማ ዞን ስር የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ውድድር ፍጻሜውን ሲያገኝ በወንደች እግር ኳስ ሰቃ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ናዳ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የዋንጫ ተሸላሚ ሲሆን በወንዶች ቮሊ ቦል ደግሞ ቀርሱ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ስግሞ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን 3 ለ1 በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል፡፡

በሴቶች ቮሊ ቦል ዶዮ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት አሌ ትምህርት ቤትን 3 ለ 0 በማሸነፍ የዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡
በአትሌትክስ ስፖርት ብዙ ሜዳሊያዎችን የሰበሰበው ማና ወረዳ ትምህርት ቤቶች የአጠቃላይ አሸናፊ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል፡፡

ውድድሩም ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች ጎልተው የወጡበትና በየስፖርት ዓይነቱ ጥሩ ስፖርታዊ ክህሎት ያላቸው ተማሪዎች የታዩበት የውድድር መድረክ ሆኖ መጠናቀቁ ተገልጿል፡


በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ተገቢውን ሥነ-ምግባር የተከተሉና የህብረተሰቡን ችግሮ የሚፈቱ ሊሆኑ እንደሚገባ ተጠቆመ።
------------------------------------
(የካቲት 22/2017 ዓ.ም) በትምህርት ሚኒስቴር በጥናትና ምርምር ሥነ ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለመንግስትና ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሰጥቷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የምርምርና ማህበረሰብ ጉድኝት ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሰራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በሀገራችን የከፍተኛ ትምህርት ታሪክ በርካታ ጥናትና ምርምሮች ቢሰሩም ህብረተሰቡ ላይ ያመጡት ለውጥ ግን የሚጠበቀውን ያክል አይደለም ብለዋል።

እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የተለያዩ እርምጃዎች እየተወሰዱ እንዳልሂነም ገልጸዋል።

ጥራት ያለው ጥናት ለመስራትና ለሳይንስ ያለን እይታ እንዲጨምር የምንፈልግ ከሆነ በቅንጅት መስራት ያስፈልጋልም ብለዋል።

በዚህም የሚሰሩ ምርምሮች ተገቢውን ስነምግባር የተከተሉ፣ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ሊሆኑ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ እዮብ አየነው (ዶ/ር) በበኩላቸው ትምህርት ሚኒስቴር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተለያዩ ሪፍርሞችን ቀርፆ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ብለዋል።

በዚህም በመንግስትም ሆነ በግል ተቋማት የሚሰሩ ጥናትና ምርምሮች ከመመረቂያነት ባለፈ ጥራት ያላቸው ችግር ፈቺ እንዲሆኑ ለማድረግና ወጥ የሆነ አሰራር ሥርዓትን ለመከተል እንዲቻል ይህ ስልጠና መዘጋጀቱን ገልፀዋል።

በስልጠናው ከመንግስትና ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተወከሉ ምሁራን ተሳታፊ ሆነዋል።


ተማሪዎች ሰለስራ ቅጥርና ፈጠራ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ እየተሠራ ነው።
------------------------------------------
(የካቲት 22/2017 ዓ.ም) በቅርቡ በትምህርት ሚኒስቴር እና በኢንፎ ማይንድ ሶሊሽን መካከል የተፈረመውን የትብብር መግባቢያ ስምምነት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተከናውኗል።

የኢፊዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በትብብሩ ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት የስራ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ሚንስትር ዴኤታው በማያያዝም ዜጎች በሀገሪቱ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ከራሳቸው ባለፈ ለሀገራቸው አበርክቶ እንዲኖራቸው የትምህርት ዘርፉና ተባባሪ አካላት ሚናቸው የጎላ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሜጄና በበኩላቸው የትብብር ፕሮግራሙ ተማሪዎች በትምህርት ቆይታቸውም ይሁን ወደ ስራው አለም ሲቀላቀሉ የሚያስፈልጓቸውን ክህሎቶች እንዲገነቡ የሚያግዝ በመሆኑ የትምህርት ዘርፉ አስፈላጊውን ጥረትና ድጋፍ እንደሚያደርግ አብራርተዋል።

በዚህም በቀጣይ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ ቅጥርና ፈጠራ ማጎልበቻ ማዕከላት እንደሚገነቡ ገልጸዋል።

የኢንፎ ማይንድ ሶሊሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ የሱፍ ረጃ በበይነ መረብ ባስተላለፉት ቁልፍ መልዕክት የከፍተኛ ትምህርት ምሩቃን በስራ ቅጥርና ፈጠራ እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዬች ላይ ያላቸውን አቅም ለማጎልበት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ ተቋማቸው ሚናውን እንደሚወጣ አብራርተዋል።


የትብብር መርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ የሀገሪቱን የስራና ቅጥርና ፈጠራ ነባራዊ ሁኔታ የተመለከቱ ጥናቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።


በተለያዩ ክልሎች የመምህራንና የትምህርት አመራሮችን ብቃትና ተነሳሽነት ለማሳደግ ስልጠናዎች እየተሰጡ ነው።
---------------------------------------
የካቲት 22/ 2017 ዓ.ም በሁሉም ክልሎች በተመረጡ የስልጠና ማዕከላት እተሰጠ ያለው ስልጠና በስነ-ልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ፣ በስራና ተግባር ተኮር ትምህርት እና በአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርት ማስተማር ስነ ዘዴ ላይ ያተኮረ ነው፡፡

የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ ስልጠና ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት ችግሮች በነበሩባቸው አካባቢዎች ለሚያስተምሩ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች እየተሰጠ ያለው ስልጠና መምህራን ተግዳሮቶችን ተቋቁመው የማስተማርና ስራቸውን በአግባቡ መምራት እንዲችሉ እንደሚያግዝ ተናግረዋል፡፡ ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፤ https://www.facebook.com/share/p/1B5iVo18oY/


የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች 129ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከበሩ፡፡
-------------------------------------
የካቲት 21/2017 ዓ.ም) «ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ድል! » በሚል መሪ ቃል ዘንድሮ ለ129ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል የትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞችና አመራሮች በፓናል ውይይት አክብረዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመርሃ- ግብሩ ላይ በመገኘት ባስተላለፉት መልዕክት የአድዋ ድል የመላው ጥቁር ህዝቦች ድልና የነጻነት አርማ በመሆኑ የድሉን እሴቶችና ቱሩፋቶች ለይቻላል መንፈሰ ማጎለበቻነት በመጠቀም በያዝናቸው የሥራ ዘርፎች ላይ የሚጠበቅብንን ስኬት ማስመዘግብ እንደሚገባ ተናገግረዋል፡፡

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ጨምረውም የአድዋን ድል ከማክበርና ቱሩፋቶቹንም ከመጠቀም በተጨማሪ እኛ መሥራት ያለብንን የቤት ሥራ በወቅቱ በማከናወን የሀገራችን ልማት ማፋጠን ይኖርብናል ብለዋል።

በትምህርት ሚኒስቴር በአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ሃላፊ አቶ ኡመር ኢማም የውይይት መነሻ ያቀረቡ ሲሆን የህዝቦች አብሮ የመኖርና የመልማት እንዲሁም የሀገርን ሉዓላዊነትን የማስከበር ጉዳዮች ላይ ይህ ትውልድ ከቅድመ አያቶቹ ብዙ መማር እንደሚገባው አንስተዋል፡፡

አቶ ኡመር አክለውም የአድዋ ድል ቅድመ አያቶቻችን ብሄራቸው፣ ቋንቋቸው፣ ሀይማኖታቸው፣ባህላቸውና ሌሎች ልዩነቶቻቸው ሳይገድባቸው የሀገርን ሉዓላዊነትና አንድነት ያስከበሩ መሆኑን አብራርተው አሁን ያለው ትውልድ ከዚህ መማር እንደሚገባው ገለጸዋል።
======////======


የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ የማድረግ ሂደት የሁሉንም ባለድርሻዎች ድጋፍና ትብብር እንደሚጠይቅ ተጠቆመ፤
---------------------------------------
(የካቲት 18/2017 ዓ.ም) በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ራስ ገዝ አስተዳደር ስትራተጂክ እቅድ እና ሴኔት ህግ ለማዳበር የተዘጋጀ አውደ ጥናት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።

የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሹኔ አውደ ጥናቱን ሲከፍቱ እንደገለጹትት የዩኒቨርስቲዎችን የራስ ገዝ አስተዳደ ማስፋት የመንግስት አካላት ፣ የአካዳሚክ መሪዎች፣ የመምህራን ፣የተማሪዎችና የማህብረሰቡን ትብብር ይሻል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ራስ -ገዝነት የተቋማቱን ራስን በራስ የማስተዳደርና አካዳሚያዊ ነጻነትን በማረጋገጥ የትምህርት ጥራት ምርምርና ፈጠራን በውጤታማነትና በብቃት ለመፈጸም እንደሚያስችል ክቡር አቶ ኮራ ተናግረዋል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ።
https://www.facebook.com/share/p/167hNi9CW4/



9 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.