4-3-3 World News


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ይህ የእርሶ፣ የአንተ፣ የአንቺ፣ የእናንተ፣ የኛ የሁላችንም ድምጽ ነው! ለሃሳብ አስተያየት ለመስጠት @atsbaha12 ይጠቀሙ

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ዲቪ ደርሷቸው ፓስፖርት ማውጫ እና የኮቴ ገንዘብ ላጡት ቤተሰቦች በጎ እናድርግ!

(እጅግ አስቸኳይ ስለሆነ ሼር ሳታደርጉ አትለፉ!)

እኚህ እናት ጫርቱ ወርቁ ይባላሉ ከባለቤታቸው እና ከልጆቻቸው ጋር ዲቪ ደርሷቸው ፓስፖርት ማውጫ እና የኮቴ ገንዘብ አጥተው ሊቀሩ ነው።

ይህንን ቤተሰብ ማሳረፍ ትልቅ በጎነት ነውና የ 100ብር ቻሌንጅ አስጀምረናል

ደጋጎች "እንኳን ደስ አላችሁ" እያላችኋቸው የምትችሉትን እያደረጋችሁ ሌሎችም ለዚህ በጎ ተግባር እንዲነሳሱ ስኪሪን ሸት እያደጋችሁ ኮመንት ላይ አስቀምጡ። በሜሴንጀርም ልትልኩልን ትችላላችሁ።
ፓስፖርት በማውጣት ልትረዷቸው የምትችሉ ሰዎችም ካላችሁ በውስጥ መስመር ላኩልኝ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000528969937
ጫልቱ ወርቁ ሻንካ

(ሼር ማድረግም በጎነት ነውና ቢያንስ ለ10 ሰዎች አጋሩላቸው።)

@Ethionews433 @Ethionews433


የሴት ልጅ ግርዛት የበዛባቸው የዓለማችን ሀገራት

ምዕራብ አፍሪካዎቹ ጊኒ፣ ማሊ እና ሴራሊዮን በከፍተኛ መጠን የሴት ልጅ ግርዛት ከሚፈጸምባቸው የዓለማችን ሀገራት መካከል ዋነኞቹ ናቸው

ኢትዮጵያ የሴት ልጅ ግርዛት በብዛት ከሚፈጸምባቸው ሀገራት መካከል አንዷ ናት[አል አይን]

@Ethionews433
@Ethionews433


የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከደህንነት መረጃ ታገዱ

አሜሪካ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሆነው ያገለገሉ መሪዎች የሀገሪቱ ደህንነት መረጃዎች እንዲደርሳቸው የሚፈቅድ ህግ አላት

ጆ ባይደን ወደ ስልጣን ሲመጡ ዶናልድ ትራምፕ የሚታመን ሰው አይደለም በሚል መረጃው እንዳይደርሳቸው አግደዋቸው የነበረ ቢሆንም አሁን በተራቸው ታግደዋል

@Ethionews433 @Ethionews433


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በአርጀንቲና ቦነስ አይረስ የሚገኝ ወንዝ ቀለሙ "የደም "  መልክ በመያዙ እያነጋገረ ይገኛል

ይህ በጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች እና የቆዳ ፍብሪካዎች አካባቢ የሚገኘዉ የሳራንዲ ወንዝ ቀለሙ ወደ ደማቅ ቀይ መቀየሩን የሀገር ውስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። የውሃው ቀለም የተቀየረበትን መንስኤ ለማወቅ በስፍራው የሚገኙ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያዎች የውሃውን ናሙና ሰብሰበው የወሰዱ ሲሆን ፤ ባለሙያዎቹ ለውሀው መበከል መንስኤ የሆኑት የሆኑ አይነት "ተፈጥሮአዊ ውህዶች" ሊሆኑ ይችላሉ በማለት ጥርጣሬአቸውን አስቀምጠዋል።

@Ethionews433 @Ethionews433


በአሜሪካ አላስካ ግዛት ጠፍቶ የነበረው አውሮፕላን ስብርባሪው ተገኘ
**

በሀገረ አሜሪካ አላስካ ግዛት አብራሪውን ጨምሮ 10 ሰዎችን ይዞ ከአናክሌት ወደ ኖም እየተጓዘ ደብዛው የጠፋው አነስተኛ አውሮፕላን ስብርባሪው መገኘቱ ተገለጸ።

በአየር እና በምድር በተከናወነው የፍለጋ ስራ የአውሮፕላኑ ስብርባሪ ከአንኮሬጅ በ885 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ኖም አቅራቢያ መገኘቱም ነው የተገለፀው፡፡

የግዛቲቱ ባለሥልጣናት በአደጋው በሕይወት የተረፈ ሰው አለመኖሩን ጠቅሰው፤ የነብስ አድን ሰራተኞች የ3 ሰዎችን አስክሬን ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡

የአላስካ ገዥ ማይክ ዱንሌቪ በደረሰው አደጋ የተሰማቸውን ኀዘን ገልጸው፤ ለተጎጂ ቤተሰቦች መፅናናትን መመኘታቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

በአሜሪካ ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ይህ ሦስተኛው የአቪዬሽን አደጋ መሆኑ ተመላክቷል።

በቢታንያ ሲሳይ

@Ethionews433 @Ethionews433


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ

ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?


በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን  ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር  ትጠብቃላችው?

በራሳችው  አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን  ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?

ትራምፕ ይሄን የተናገሩት ሰሞኑን በዋሽንግተን ዋይት ሀውስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።

@Ethionews433
@Ethionews433

18k 1 133 856

የጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን መኪና በማስቆም በተደረገ እገታ አንድ ሰው መሞቱንና አራት ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኝ ተናገሩ። በሌላ አካባቢ ደግሞ የታገቱ 18 መንደኞችን የመንግሥት ኃይሎች ተታኩሰው ማስለቀቃቸው ተሰምቷል።

በዴሞክራቲክ ኮንጎ ጦር እና በሩዋንዳ ይደገፋል በሚባለው የM 23 አማጺዎች መካከል ውጊያው መባባሱ እየተነገረ ነው። ኮንጎ በሲቪሎች ላይ ለደረሰው ግድያ እና አስከፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የተመድ ሩዋንዳን ተጠያቂ ያድርግልኝ ብላለች።

አሸባብ ሰሜን ኬንያ ውስጥ ያገታቸውን የኬንያ ባለሥልጣናት ለመልቀቅ 53 ሺህ ዶላር በላይ ቤዛ ጠየቀ።

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት ICC ላይ የጣሉትን እገዳ በርካታ ሃገራት ተቃወሙ። ትራምፕ የICCን ንብረት በማገድ፤ ባለሥልጣናቱ፣ ሠራተኞቹ እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የጉዞ እገዳ ጥለዋል።(DW)

@Ethionews433 @Ethionews433


በአሜሪካ አላስካ ግዛት ደብዛው የጠፋው አውሮፕላን

10 ሰዎችን የጫነ አውሮፕላን በአሜሪካ አላስካ ግዛት መጥፋቱ ተገለፀ።

የቤሪንግ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ሴስና ካራቫን አውሮፕላን ከአሜሪካዋ አናላክሌት ወደ ኖም እያቀና ሳለ መጥፋቱ ነው የተገለፀው።

አውሮፕላኑ በጠፋበት ወቅት አብራሪውን ሳይጨምሮ 9 ሰዎችን ይዞ እንደነበረ ነው የተገለጸው።

የአየር መንገዱ ባለሙያዎች ከአብራሪው ጋር ለመጨረሻ ጊዜ ያደረጉት የመረጃ ልውውጥ አብራሪው የማረፊያ ቦታ እስኪስተካከል አየር ላይ ለመቆየት መወሰኑን ሲያሳውቅ ነው ተብሏል። ይህም ትናንት ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ነበር።

እስከ አሁን የጠፋውን አውሮፕላን ለማግኘት በአየር እና በምድር የፍለጋ ቡድን ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።

ቤሪንግ አየር መንገድ በአሜሪካዋ ምዕራብ አላስካ የሚገኙ 32 መንደሮችን ኖሜን ጨምሮ ከሶስት ዋና ማእከል ጋር የሚያገናኝ ነው።

@Ethionews433 @Ethionews433


በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገንዘብ በማጭበርበር የተከሰሰው የቱርክ የፋርም ባንክ መስራች መህመት አይዲን በ45 ሺህ 376 አመት ከ6 ወር እስራት ተቀጣ።

መህመት አይዲን ፋርም ባንክ በሚል በኦንላይን በመሰረተው ተቋም ስም ሰዎች በምናብ እንስሳትን እና ሰብሎችን እንዲገዙ በማድረግ ገንዘብ አጭበርብሯል ተብሏል።

“ቶሱንኩክ” በሚል ቅጽ ስሙ የሚታወቀው መሃመት አይዲን ፋርም ባንክ በሚል የማጭበርበሪያ ድርጅቱ በኩል ከ130 ሺህ ሰዎች ከ131 ቢሊየን የቱርክ ሊራ በላይ ገንዘብ ሰብስቧል ነው የተባለው።

አይዲን ገንዘቡን ከሰበሰበ በኋላ የተወሰነ ገንዘብ በመያዝ ከሀገር በ2018 ላይ ከሀገር የወጣ ቢሆንም፤ በፈረንቹ 2021 ላይ በብራዚል በቁጥጥር ስር ውሎ ለቱርክ ተላልፎ እንደተሰጠም ነው የተነገረው።

ፋርም ባንክ የኦንላይን የማጭበርበሪያ ጨዋታው በፈረንቹ 2016 ላይ ተከፍቶ በ2018 የተዘጋ ሲሆን፤ የክስ ሂደቱ ደግሞ በ2019 እንደተጀረም ነው የተነገረው።

አቃቤ ህግ መህመት አይዲን እና ወንድሙ ፋቲህ አይዲን ህገወጥ ድርጅት በማቋቋም እና በማስተዳደር፣ በማጭበርበር እና በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ከ75 ሺህ ዓመታት በላይ እስራት እንዲቀጡም ጠይቀው ነበር።

መህመት አይዲን ባሳለፍነው ሰኞ በዋለው ችሎች ላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ የተከራከረ ሲሆን፤ “ማንንም ለማታለል አላሰብኩም፣የማጭበርበር አላማ አልነበረኝም” ሲል ተናግሯል።

“ንብረቶቹን እንዳያንቀሳቀስ እግድ በመጣሉም ለተጎጂዎች ካሳ እንዳይከፍል እንዳደረገው” በመግለጽ፣ በተያዘው ገንዘብ ላይ የተጠራቀመው ወለድ የደረሰውን ጉዳቱን ሊሸፍን እንደሚችል ጠቁሟል።

የመህመት አይዲን ወንድም የሆነው ፋቲህ አይዲን እኔ የድርጅቱ መስራችም አባልም አይደለሁም፤ አብዛኞቹ ከሳሾ እኔን አያውቁኝም ስለዚህም በነጻ መለቀቅ አለብኝ ስሊ የእምት ክህደት ቃሉን ሰጥቷል።

የቱርክ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከተመለከተ በኋላ ብይን የሰጠ ሲሆን፤ በዚህም መህመት አይዲን እና ወንድሙ የሆነው ፋቲህ አይዲን እያንዳንዳቸው በ45 ሺህ 376 አመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

ከእስር በተጨማሪም የ496 ሚሊየን የቱርክ ሊራ የገንዘብ ቅጣትም ውሳኔም ያሳለፈ ሲሆን፤ ገንዘቡን በ24 ወራ ጊዝ ውስጥ እንዲከፍም ትእዛዝ ሰጥቷል።

@Ethionews433 @Ethionews433


አይኔ እየያ ሁለት ሰዎች ባላንስ አጥተው ወድቀዋል ብስራተ ገብርኤል አከባቢ 😪


ሰበር ዜና

ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ አሁን ተሰምቷል። የት ነው መነሻው የሚለውን እና ስንት ሬክተር ስኬል መሆኑን እናሳውቃለን።

@Ethionews433 @Ethionews433


የትራምፕ ማዕቀብ በአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ላይ ማዕቀብ መጣላቸው ተሰምቷል።

ፍርድ ቤቱ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚኒ ኔታንያሁ በጋዛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል በሚል የእስር ትዕዛዝ አውጥቶ የነበረ በመሆኑ ነው።

አለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት መሰረት አልባና ህጋዊ ያልሆነ ፍርድ በአሜሪካና በወዳጆቿ ላይ ሲያስተላልፍ ነበር ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።

ማዕቀቡ በICC ውስጥ የሚሰሩ ግለሰቦችና ቤተሰቦች ላይ የገንዘብና የቪዛ ክልከላን እንደሚያጠቃልል ተነግሯል ዘገባው የቢቢሲ ነው።

@Ethionews433 @Ethionews433


ትራንፕ በጋዛ ጉዳይ በግብጽ ላይ ተጽእኖ ለማሳደር የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እየተጠቀሙበት እንደሚገኙ ተገለጸ

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራንፕ የጋዛ ነዋሪዎችን ከአካባቢው በማስወጣት እንደ ግብጽ ባሉ የጎረቤት ሀገራት ለማስፈር ያቀረቡትን ሀሳብ ግብጽ እንድትቀበላቸው ለማድረግ የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እንደ መደለያ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝ ተገለጸ።

ባሳለፍነው ሳምንት የፕሬዝዳንተ ትራንፕ ከፍተኛ ባለስልጣናት በካይሮ ተገኝተው የጋዛ ነዋሪዎችን ከአከባቢው እንዲለቁ በማድረግ በግብጽ እና ሌሎች ሀገራት ለማስፈር ባቀረቡት እቅድ ዙሪያ መምከራቸው ተጠቁሟል።

የትራንፕ አስተዳደር ባለስልጣናት በግብጽ ላይ ተጽእኖ በማሳደር እቅዱን እንዲቀበሉት ለማድረግ የህዳሴ ግድብን ጉዳይ እንደ መደለያ ማቀረባቸውን ዘኒውአረብ ድረገጽ ምንጮቹን ዋቢ በማረግ ባቀረበው ዘገባ አመላክቷል።

የአሜሪካን ከፍተኛ ባለስልጣናት በካይሮ በነበራቸው ቆይታ ከግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ እና ከሀገሪቱ የደህንነት ቢሮ ሃላፊ ሃሰን ራሽድ ጋር “ግብጽ ከኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ውስጥ በገባችበት የህዳሴ ግድብ” እና "አወዛጋቢ በሆነው የጋዛ ነዋሪዎችን ማስለቀቅ” ዙሪያ መክረዋል ሲል ዘገባው አስታውቋል።

በህዳሴ ግድብ ዙሪያ በግብጽና በኢትዮጵያ መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት አሜሪካ ጣልቃ የምትገባው እና የምትሳተፈው ግብጽ በጋዛ ጉዳይ የትራንፕን እቅድ የምትቀበል ከሆነ ብቻ ነው በሚል የአሜሪካ ባለስልጣናት ጉዳዩን በቅድመ ሁኔታነት ማስቀመጣቸውን ምንጮቹን ዋቢ በማድረግ ዘገባው አመላክቷል።

የግብፅ ባለስልጣናት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ ጎረቤት ሀገራት የማስፈር ዕቅድ እንዳልተቀበሉትና "ሙሉ በሙሉ ውድቅ ማድረጋቸውን" ዘገባው አሰታውቋል።

ዘገባው የአዲስ ስታንዳርድ ነው።

@Ethionews433 @Ethionews433


ክብረ ወሰኑን ሰበሩት

የመቀሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መድህን
በ75 ዓመታቸው ወለዱ፦

ከዚህ ቀድም በ73 ዓመቷ ሕንዳዊ ተይዞ የነበረው
ክብረ ወሰንም በእጃቸው ማስገባት ችለዋል::

Via ሰግለለት ሾው

@Ethionews433 @Ethionews433


“ነፍሳችንን ቢያስከፍለን እንኳን ጋዛን አንለቅም”- የጋዛ ነዋሪዎች

በትራምፕ ውሳኔ የተገረሙ የጋዛ ነዋሪዎች “ከጋዛ አንወጣም” ሲሉ ተቃውሞዋቸውን ገልጸዋል። ትራምፕ በዋይት ኃውስ ከኔታንያሁ ጋር ሲመክሩ ጋዛን የመቆጣጠር እቅድ እንዳላቸው ተናግረዋል።

@Ethionews433 @Ethionews433


በ26 ጎማዎች የሚንቀሳቀሰው የዓለማችን ረጅሙ መኪና...

ባንድ ጊዜ 75 ሰዎችን የሚያጓጉዘው ይህ መኪና በዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ሰፍሯል

መኪናው ከትራንስፖርት ባለፈ የመዋኛ፣ አነስተኛ የጎልፍ ሜዳ እና አነስተኛ ሂልኮፕተር ማረፊያ ቦታ አለው ተብሏል(አል አይን)

@Ethionews433 @Ethionews433


ምክር ቤቱ በነገ ውሎው የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ሥርዓትን ለመደንገግ የተዘጋጀ ረቂቅ አዋጅን ጨምሮ የተለያዩ ሕጎችን መርምሮ ያፀድቃል
*****

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ በሚያካሂደው 18ኛ መደበኛ ስብሰባው የ17ኛ መደበኛ ስብሰባው ቃለ ጉባኤን መርምሮ እንደሚያፀድቅ የምክር ቤቱ መረጃ ያመለክታል።

በተጨማሪም፥ የፌዴራል የፍትህና የሕግ ኢንስቲትዩትን እንደገና ለማቋቋም የሚቀርብ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀረበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ በመርመር አዋጁን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

በተመሳሳይ ምክር ቤቱ የሲቪልና የቤተሰብ ምዝገባ እንዲሁም የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ሥርዓትን ለመደንገግ የተዘጋጁ ረቂቅ አዋጆችን አስመልክቶ የሚቀረብለትን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ አዋጆቹን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

@Ethionews433 @Ethionews433


ከፍተኛ ገንዘብ እያስከፈለ የሴቶችን መቀመጫ የሚያሳድግ አደገኛ መርፌ የሚወጋው ግለሰብ

ራሱን "የውበት አማካሪ" ሲል የሚጠራው 'የታዋቂ ሰዎች ዶክተር' ለደንበኞቹ አደገኛ የሆነ የኮስሜቲክስ መድኃነት በሕገ ወጥ መንገድ እንደሚሰጥ የቢቢሲ ምርመራ አጋለጠ።
ሪኪ ሶውየር የተባለው ግለሰብ 'ብራዚሊያን በት ሊፍት' (ቢቢኤል) የተባለውን የሴቶች የመቀመጫ መጠንን የሚያሳድግ መድኃኒት በመርፌ በመስጠት ይታወቃል።
ቢቢሲ አምስት ደንኞቹን ያናገረ ሲሆን፣ እኒህ ደንበኞች መርፌ ከተወጉ በኋላ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት ሆስፒታል የገቡ ናቸው። ሌሎች 30 ሴቶች ደግሞ ሴፕሲስ እና ኔክሮሲስ የተባሉ ከባድ የጤና እክሎች እንዳጋጠመቻው ቢቢሲ ተረድቷል።
አንዲት ሴት ግለሰቡ በሰጣት ሕክምና ምክንያት ያጋጠማትን ህመም እያስታወሰች "ከስቃዩ ሞት ይሻለኛል" ስትል መቀመጫን ለማሳደግ ያደረገችው "ሕክምና" ያስከተለባትን ስቃይ ጠቅሳለች።
በርካታ የብራዚል ባለሥጣናት ሶውዬር የተባለው ግለሰብ በአካካቢያቸው ይህንን የጤና ጠንቅ የሆነን ሕክምና እንዳይሰጥ አግደውታል።
ቢቢሲ በድብቅ የቀረፀው ቪድዮ ሰውዬው ትክክለኛ ባልሆነ የሕክምና መመሪያ አንቲባዮቲክስ (ፀረ ተህዋሲ መድኃኒት) ሲሰጥ ያሳያል። ይህን ማድረግ ወንጀል ነው። በተጨማሪም ግለሰቡ መድኃኒት ለማዘዝ የሚያስችው የሕክምና ፈቃድ ያለው አይደለም።
ቢቢሲ አድራሻውን ከኢንስታግራም ገፅ እንዳገኘ በመምሰል ቢቢኤል የተባለውን ሕክምና ለማግኘት 200 ፓውንድ ቀብድ ከፍሎ ቀርቦታል። የሕክምናው ሙሉ ዋጋ 1200 ፓውንድ ነው፤ ይህም በብር ሲሰላ ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።
ምንም እንኳ ይህ የሴቶችን መቀመጫ የሚያሳድገው ሕክምና "በሙያው የዳበረ ዕውቀት እና ልምድ ባላቸው ዶክተሮች" ይሰጣል ተብሎ ቢተዋወቅም፣ ክሊኒኩ ውስጥ አንድም ሰው አልነበረም። አነስተኛው ክሊኒክ የሚገኘው ምሥራቅ ለንደን ውስጥ ነው።
ግለሰቡ የቢቢሲን ሪፖርተር "ለምን 2000 ሺህ ፓወንድ ከፍለሽ 500 ሚሊ ሊትር አትወጊም" እያለ ሲጎተጉታት ይታያል። በኋላ ሪፖርተሯ መወጋት እንደማትፈልግ እና የምርመራ ሥራ ላይ እንደሆነች ስታሳውቀው እንድትወጣለት ጠይቆ በሩን ዘግቶታል።
የቢቢሲን ቪድዮ የመረመሩት የፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና ባለሙያው ዳልቪ ሁምዛህ ያዩት ነገር "እጅግ እንዳስደነገጣቸው" ተናግረው፤ ሰውዬው የሚፈፅመውን ነገር "በጣም አደገኛ ነው" ብለዋል።

@Ethionews433 @Ethionews433


በኢሎን መስክ ላይ እየደረሰ ያለው ተቃውሞ!

ትራምፕ ምርጫውን ማሸነፋቸውን ተከትሎ ሥልጣን ያገኙት ኢሎን መስክ ላይ አሜሪካውያኑ ተቃውሞ ማሰማታቸው የቀጠለ ሲሆን የአሜሪካ ዜጎች ሊይዙት የሚገባውን ሥልጣን እና ውሳኔ ኢሎን መስክ ላይ ወድቋል ሲሉ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል።

የተቃውሞ ድምጾቹም የሚከተሉት ናቸው፡፡

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዲመረጡ ኢሎን መስክ ከ250 ሚሊዮን ዶላር በላይ ድጋፍ አድርገዋል፡፡

ትራምፕም የአሜሪካን አስተዳደራዊ ቁልፍ ለኢሎን መስክ እና ለባዕለጸጋዎች አሳልፈው ሰጥተዋል ሲሉ ተቃዋሚዎቹ አንስተዋል፡፡

ዴሞክራሲ ምን ማለት እንደሆነ እኛ የአሜሪካ ዜጎች እናውቃለን ኢሎን መስክን ግን ማንም አልመረጣቸውም የሚሉ ወቀሳዎችም እየተሰነዘረባቸው ይገኛል፡፡

በአሜሪካ ታሪክ ተፈጽሞ የማያውቅ ነገር እየተከናወነ ነው ይህን ድርጊት እንቃወማለን ሲሉ በአደባባይ ተቃውሞአቸውን አሰምተዋል፡፡

በ-ፍቅረሚካኤል ዘየደ

@Ethionews433 @Ethionews433


በአዲስ አበባና አካባቢዋ ድሮን ያለ ፈቃድ ማብረር አይቻልም- አገልግሎቱ

በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውንም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡

አገልግሎቱ በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ የሚደረግ የድሮን እና ሌሎች በራሪ አካላት አጠቃቀምን በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል።

አገልግሎቱ በመግለጫው÷ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 1276/2014 በተሰጠው ስልጣን መሠረት የመሪዎችን፣ የቁልፍ መሠረተ-ልማቶችን እና ብሔራዊ ኩነቶችን ደኅንነት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለበት ብሏል።

ተቋሙ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት ጥቅም ላይ እየዋሉ የመጡ ድሮኖች እና መሰል ቴክኖሎጂ ወለድ መሣሪያዎች የሚፈጥሯቸውን ስጋቶች ለመከላከል የሚያስችል በቂ የቴክኖሎጂ እና የሰው ኃይል ዝግጅት ማድረጉንም ጠቅሷል፡፡

ሥራው ውጤታማ እንዲሆንም ለኅብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እና ጠንካራ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንደሚፈልግ ነው ያመላከተው፡፡

በተለይ ከመጪው የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ጋር ተያይዞ ቅንጅቱን ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ ማንኛውም አይነት ድሮን ያለ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መሥሪያ ቤት ፈቃድ ማስነሳትም ሆነ ማብረር እንደማይቻል አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

በሥራ ምክንያት ድሮኖች መጠቀም አስፈላጊ ከሆነ ጠያቂው አካል የበረራውን ዓላማ፣ የሚበርበትን ቦታ፣ የድሮኑን አይነት እና የሞዴል ቁጥር በመጥቀስ አስቀድሞ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱን መጠየቅ እና ፈቃድ ማግኘት እንደሚገባ  አስታውቋል፡፡

ይህ ሳይሆን ቀርቶ በዘፈቀደ የሚኒሱ እና የሚበሩ ድሮኖች ካሉ ተቋሙ አዲስ አበባንና ዙሪያዋን በጸረ-ድሮን ቴክኖሎጂ ያጠረ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በዚኅም ቴክኖሎጂዎች በመጠቀም በማንኛውም ጊዜ ድሮኖቹን ከአየር ላይ በመለየት፣ በመጥለፍ እና ወደ አስፈላጊው ቦታ በማሳረፍ እንዲሁም የድሮን አብራሪዎቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጠያቂነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጿል፡፡

ከሥራ ጋር በተያያዘ ድሮኖችን መጠቀም የሚፈልግ ማንኛውም አካል በ+251 983 00 02 98 እና +251 983 00 04 01 ስልክ ቁጥሮች በመደወል ተጨማሪ ማብራሪያ ማግኘት እንደሚችል በመግለጫው አሳስቧል።

@Ethionews433 @Ethionews433

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.