ከፍተኛ ገንዘብ እያስከፈለ የሴቶችን መቀመጫ የሚያሳድግ አደገኛ መርፌ የሚወጋው ግለሰብ
ራሱን "የውበት አማካሪ" ሲል የሚጠራው 'የታዋቂ ሰዎች ዶክተር' ለደንበኞቹ አደገኛ የሆነ የኮስሜቲክስ መድኃነት በሕገ ወጥ መንገድ እንደሚሰጥ የቢቢሲ ምርመራ አጋለጠ።
ሪኪ ሶውየር የተባለው ግለሰብ 'ብራዚሊያን በት ሊፍት' (ቢቢኤል) የተባለውን የሴቶች የመቀመጫ መጠንን የሚያሳድግ መድኃኒት በመርፌ በመስጠት ይታወቃል።
ቢቢሲ አምስት ደንኞቹን ያናገረ ሲሆን፣ እኒህ ደንበኞች መርፌ ከተወጉ በኋላ ባጋጠማቸው ህመም ምክንያት ሆስፒታል የገቡ ናቸው። ሌሎች 30 ሴቶች ደግሞ ሴፕሲስ እና ኔክሮሲስ የተባሉ ከባድ የጤና እክሎች እንዳጋጠመቻው ቢቢሲ ተረድቷል።
አንዲት ሴት ግለሰቡ በሰጣት ሕክምና ምክንያት ያጋጠማትን ህመም እያስታወሰች "ከስቃዩ ሞት ይሻለኛል" ስትል መቀመጫን ለማሳደግ ያደረገችው "ሕክምና" ያስከተለባትን ስቃይ ጠቅሳለች።
በርካታ የብራዚል ባለሥጣናት ሶውዬር የተባለው ግለሰብ በአካካቢያቸው ይህንን የጤና ጠንቅ የሆነን ሕክምና እንዳይሰጥ አግደውታል።
ቢቢሲ በድብቅ የቀረፀው ቪድዮ ሰውዬው ትክክለኛ ባልሆነ የሕክምና መመሪያ አንቲባዮቲክስ (ፀረ ተህዋሲ መድኃኒት) ሲሰጥ ያሳያል። ይህን ማድረግ ወንጀል ነው። በተጨማሪም ግለሰቡ መድኃኒት ለማዘዝ የሚያስችው የሕክምና ፈቃድ ያለው አይደለም።
ቢቢሲ አድራሻውን ከኢንስታግራም ገፅ እንዳገኘ በመምሰል ቢቢኤል የተባለውን ሕክምና ለማግኘት 200 ፓውንድ ቀብድ ከፍሎ ቀርቦታል። የሕክምናው ሙሉ ዋጋ 1200 ፓውንድ ነው፤ ይህም በብር ሲሰላ ከ1.9 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።
ምንም እንኳ ይህ የሴቶችን መቀመጫ የሚያሳድገው ሕክምና "በሙያው የዳበረ ዕውቀት እና ልምድ ባላቸው ዶክተሮች" ይሰጣል ተብሎ ቢተዋወቅም፣ ክሊኒኩ ውስጥ አንድም ሰው አልነበረም። አነስተኛው ክሊኒክ የሚገኘው ምሥራቅ ለንደን ውስጥ ነው።
ግለሰቡ የቢቢሲን ሪፖርተር "ለምን 2000 ሺህ ፓወንድ ከፍለሽ 500 ሚሊ ሊትር አትወጊም" እያለ ሲጎተጉታት ይታያል። በኋላ ሪፖርተሯ መወጋት እንደማትፈልግ እና የምርመራ ሥራ ላይ እንደሆነች ስታሳውቀው እንድትወጣለት ጠይቆ በሩን ዘግቶታል።
የቢቢሲን ቪድዮ የመረመሩት የፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና ባለሙያው ዳልቪ ሁምዛህ ያዩት ነገር "እጅግ እንዳስደነገጣቸው" ተናግረው፤ ሰውዬው የሚፈፅመውን ነገር "በጣም አደገኛ ነው" ብለዋል።
@Ethionews433 @Ethionews433