FBC (Fana Broadcasting Corporate)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


This is FBC's official Telegram channel.
For more updates please visit www.fanabc.com

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ከ2011 ዓ.ም ማህደር ለትውስታ


ቢያንስ አንድ ቢሊየን መራጮች የሚሳተፉበት የህንድ ምርጫ መካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አንድ ቢሊየን ያህል ህንዳውያን ድምፅ ይሰጡበታል ተብሎ የሚጠበቀው የህንድ ጠቅላላ ምርጫ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በቢሊየን የሚቆጠሩ ድምፅ ሰጭዎችን በማስተናገድ በዓለም ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዘው የህንድ ምርጫ በፈረንጆቹ ሰኔ 1 ቀን 2024 ፍፃሜውን እንደሚያገኝ ተገልጿል፡፡ በምርጫው ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ለሶስተኛ ጊዜ ለማሸነፍ እየተወዳደሩ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን…

https://www.fanabc.com/archives/242936


ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በኬኒያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ህልፈት የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኬኒያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጀኔራል ፍራንሲስ ኦሞንዲ ኦጎላን ህልፈተ-ሕይወት በማስመልከት የኃዘን መግለጫ አስተላልፈዋል። ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ በሃዘን መግለጫቸው፤ ጀኔራል ፍራንሲስ ኦሞንዲ ኦጎላ ለሀገራቸውና ለቀጣናው ሠላምና ደህንነት መረጋገጥ የነበራቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደነበር አስታውቀዋል። እሳቸውና ሌሎች ከፍተኛ…

https://www.fanabc.com/archives/242925


በተሻሻለው የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲ ዙሪያ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በተሻሻለው የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲ ዙሪያ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡ በውይይት መድረኩ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበልን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡ መድረኩ የተሻሻለው የአምራች ኢንዱስትሪ ፖሊሲ የሚያመጣቸው ሀገራዊ ፋይዳዎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ አቶ መላኩ አለበል÷ ፖሊሲው በግሉ ዘርፍ የሚመራ፣…

https://www.fanabc.com/archives/242919


ከአልሸባብ ጋር ተቀላቅለው የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ ነበር የተባሉ እስከ 12 ዓመት በሚደርስ እስራት ተቀጡ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአልሸባብ የሽብር ቡድን ጋር ተቀላቅለው የሽብር ተግባር ሲፈጽሙ ነበር የተባሉ ስምንት ግለሰቦች እስከ 12 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ተቀጡ። በሁለት መዝገብ የተከሳሾችን ጉዳይ ተመልክቶና ማስረጃ መርምሮ የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ድሬዳዋ ምድብ 4ኛ ወንጀል ጅግጅጋ ተዘዋዋሪ ችሎት ነው። የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው ተከሳሾች ሀሰን…

https://www.fanabc.com/archives/242916


በመዲናዋ የብክለት መከላከል ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የብክለት መከላከል ንቅናቄ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡

የንቅናቄ መድረኩ 'ብክለት ይብቃ ውበት ይንቃ' በሚል መሪ ሃሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡

በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።


በማንዴላ መታሰቢያ ዋንጫ የቦክስ ውድድር ም/ሳጅን ሮማን አሰፋ ተጋጣሚዋን በበቃኝ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው የማንዴላ መታሰቢያ ዋንጫ የቦክስ ውድድር ምክትል ሳጅን ሮማን አሰፋ ተጋጣሚዋን በበቃኝ አሸነፈች፡፡ ትናንት ምሽት ሀገሯን የወከለችው የአዲስ አበባ ፖሊሷ ምክትል ሳጅን ሮማን አሰፋ በ54 ኪሎ ግራም የናሚቢያ ተጋጣሚዋን በመጀመሪያው ዙር በበቃኝ አሸንፋለች፡፡ ውድድሩ እስከ ሚያዝያ 13 ቀን 2016 ዓ.ም…

https://www.fanabc.com/archives/242908


የስኳር ህመም አይነቶች እና ምልክቶች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የስኳር ህመም በደም ውስጥ የስኳር መጠን ከሚገባው በላይ ሆኖ በሚገኝበት ሰዓት የሚከሰት ተላላፊ ያልሆነ የህመም አይነት ነው። በዋናነት አራት የስኳር ህመም አይነቶች አሉ፤ እነርሱም አይነት አንድ፣ አይነት ሁለት፣ በእርግዝና ወቅት የሚከሰትና በሌሎች ተዛማች ህመሞች የሚመጣ የስኳር ህመም ናቸው። ከነዚህ ውስጥ ሁለቱ (አይነት አንድ፣ አይነት ሁለት)…

https://www.fanabc.com/archives/242856


በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የተመራው ልዑክ ከዓለም ባንክና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ከፍተኛ ሃላፊዎች ጋር ተወያየ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የተመራው ልዑካን ቡድን ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ከፍተኛ ሃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ ልዑኩ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ በተጨማሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱን፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎችን ያካተተ ነው…

https://www.fanabc.com/archives/242900






በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ500 ሚሊየን ብር የተገነባ የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ሥራ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሽ ዞን በ500 ሚሊየን ብር የተገነባው የዮ ሆልዲንግ ዘመናዊ የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ኩባንያ ምርት ማምረት ጀምሯል። ኩባንያው የስራ እንቅስቃሴውን አስመልክቶ ለክልሉ ከፍተኛ የአመራር አባላትና እና ለባለድርሻ አካላት ዛሬ በአሶሳ የማስተዋወቂያ መርሐ ግብር አካሂዷል። የኩባንያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም ታደሰ በወቅቱ÷በ500 ሚሊየን…

https://www.fanabc.com/archives/242887


አቶ አረጋ ከበደ የክልሉን ዘመናዊ የመንገድ ሥራዎች አፈጻጸም ተመለከቱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ እና ሌሎች የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በባሕር ዳር ከተማ የሚገነቡትን የዘመናዊ የመንገድ ሥራዎች አፈጻጸም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ከልደታ በማርዳ እብነ በረድ ፋብሪካ አቋርጦ ወደ ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የሚዘልቀው ዘመናዊ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የምልከታቸው ትኩረት ነበር። ርዕሰ መሥተዳድር…

https://www.fanabc.com/archives/242880


የኬንያ መከላከያ ሃይል ዋና አዛዥ በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸው አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኬንያ መከላከያ ሃይል ዋና አዛዥ ጄኔራል ፍራንሲስ ኦጎላ በሄሊኮፕተር አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል፡፡

የኬኒያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ አደጋውን ተከትሎ አስቸኳይ ስብሰባ መጥራታቸውን የኬኒያ ቴሌቪዥን ዘግቧል፡፡


ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ዞን አምስት የእጅ ኳስ ውድድርን ከግንቦት 4 ጀምሮ ታስተናግዳለች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ ዞን አምስት የእጅ ኳስ ውድድርን ከግንቦት 4 ጀምሮ እንደምታስተናግድ ተገለፀ፡፡ በአለም የእጅ ኳስ ፌዴሬሽን እና በአፍሪካ የእጅ ኳስ ፌዴሬሽን በጣምራ የሚዘጋጀው ውድድሩ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ከግንቦት 4 እስከ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል ተብሏል። ኢትዮጵያ፣ ቡሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣…

https://www.fanabc.com/archives/242861


ዓየር መንገዱ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ የሚያደርገውን ሣምንታዊ በረራ አሳደገ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ዓየር መንገዱ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ የሚያደርገውን ሣምንታዊ በረራ ማሳደጉን አስታወቀ፡፡

ዓየር መንገዱ ወደ ሩዋንዳ ኪጋሊ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ 12 እንደነበር አስታውሷል፡፡

ሆኖም ከሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚያደርገውን ሳምንታዊ በረራ ወደ 18 ከፍ እንደሚያደርግ በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታወቀ፡፡


በጂዳና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከጉዞ ሰነድና ፓስፖርት ጋር በተያያዘ ያለባቸውን ችግር ለመቅረፍ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጂዳና አካባቢዋ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከጉዞ ሰነድና ፓስፖርት ጋር በተያያዘ ያለባቸውን ችግር ለመቅረፍ ከአካባቢው ኮሚዩኒቲ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሄደ፡፡ በኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የተመራ ልዑክ ከተለያዩ ግዛቶች ከተውጣጡ የኢትዮጵያ ኮሙዩኒቲ አመራሮች ጋር ተወያይቷል። በጂዳ የኢፌዴሪ ቆንስል ከሚሸፍናቸው ሰባት ግዛቶች የተውጣጡ የኢትዮጵያ ዜጎች ተወካዮች…

https://www.fanabc.com/archives/242866


ኤሌክትሪክ የማከፋፈል ስራ ዐቢይ አካል እንደመሆኑ ዘርፉ ሙሉ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል -ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኤሌክትሪክ የማከፋፈል ስራ ዐቢይ አካል እንደመሆኑ ዘርፉ ሙሉ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥራ እና ክህሎት፣ መከላከያ፣ ማዕድን፣ ኢንዱስትሪ እና ኢኖቬሽን ሚኒስትሮች ጋር በመሆን በኢንዱስትሪዎች ጉብኝት አካሂደዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው÷ ሀገር በቀል ኩባንያዎች ከፍተኛ ኃይል አስተላላፊ እና የኤሌትሪክ ገመዶችን በማምረት በሀይል አቅርቦት እና ቴሌኮም ኢንደስትሪ መሳተፋቸው እጅግ አበረታች ነው ብለዋል።

ኤሌክትሪክ የማከፋፈል ስራ ዐቢይ አካል እንደመሆኑ ዘርፉ ሙሉ ድጋፍ ሊደረግለት ይገባልም... https://www.fanabc.com/archives/242862


ኢትዮጵያና ኖርዌይ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን የበለጠ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ኖርዌይ ያላቸውን ዘርፍ ብዙ የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገለጹ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቴን ክሪስተንሰን ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በልማት ትብብር፣ በዘላቂ ሰላም ግንባታ፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እና ለመቋቋም በሚከናወኑ ሥራዎች፣ በውሃ ሀብት አስተዳደር እና ድንበር ተሻጋሪ…

https://www.fanabc.com/archives/242845


የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል የብሪክስ አባል ሀገራት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቴክኖሎጂ እድገትን ተከትሎ እየጨመረ የመጣውን የሳይበር ጥቃት ለመከላከል የብሪክስ አባል ሀገራት በትብብርና በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ተጠቆመ። 10ኛው የብሪክስ የ“ወርኪንግ ግሩፕ” ስብሰባ ሁሉም የብሪስክስ አባል ሀገራት የዘርፉ ሃላፊዎች በተገኙበት ከሚያዝያ 16 እስከ 17 በሩሲያ ሞስኮ ተካሂዷል፡፡ በጉባኤዉ ላይ ኢትዮጵያን በመወከል በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና…

https://www.fanabc.com/archives/242846

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.