Farankaa - ፈረንካ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


The primary goal of this page is to enhance the financial literacy of Ethiopians by offering valuable insights on investment, banking, insurance, capital markets, and taxation.

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ህዝብህን (የምትመራቸውን) መታደግ የማትችል ከሆነ፣ መሪ ነኝ ብለህ አታስብ።


እጅግ ምርጡ ኢንቨስትመንት ፣ በራስ ላይ የሚደረግ ኢንቨስትመንት ነው።




Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ለመላው የFeysel and associates ሰራተኞች፣ ፓርትነሮች እና ለደንበቻችን በሙሉ ተቋማችን PKF Ethiopia በሚል ስያሜ የዓለም አቀፉ የPKF Global አባል ድርጅት በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ!

የPKF አባል በመሆናችን የተሻሻሉ አሰራሮችና ቴክኖሎጂዎችን ለመተግበር እድል ከፋች በመሆኑ የኦዲት፣ የታክስ እና የማማከር አገልግሎቶችን የምትሹ ደንበኞች በሙሉ አብራችሁን እንድትሰሩ እንጋብዛለን።

#PKF #Ethiopia #Growth #New #Beginning!




እንኳን አደረሳችሁ!


ኑ አብረን እንሳቅ! (እያረርን ከመሳቅ ውጪስ ምን አማራጭ አለን?!)

የሐረሪ ክልል በክልሉ ሊያከናውን ላሰበው የኮሪደር ልማት እያንዳንዱ በከተማው ውስጥ ያለ የባንክ ቅርንጫፍ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ 2,000,000 ብር እንዲያዋጣ ደብዳቤ ላከ።

ቅርንጫፎች እንዲህ አይነቱ ውሳኔ የሚወሰነው በየባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ስለሆነ ደብዳቤውን ወደዛ ልኮ ውሳኔ መጠባበቅ ያዘ።

ይሄንና ጥያቄዬ አልተከበረም ያለው ቆፍጣናው የሐረሪ ክልል በሐረር ከተማ እየዞረ የህዝብ ገንዘብ በአደራ ያስቀመጡ ቅርንጫፍ ባንኮች ላይ "ታሽጓል!" የሚል ማስጠንቀቂያ ለጥፎ ዘጋ!

በመሠረቱ ክልሉ ከቅርንጫፍ ባንኮቹ ላይ የሠራተኛ ደሞዝ ግብር ከመሰብሰብ የዘለለ መብት አልነበረውም። ያው ሀገሩ ኢትዮጵያ ነውና፣ ህግ አውጪው በዝቷልና የሆነው ሆነ።


የፕላስቲክ ፌስታል መጠቀም የሚከለክለዉን ረቂቅ ህግ እንድምታ..
                       ***
ኢትዮጵያ የፕላስቲክ ፌስታል መጠቀም የሚከለክለዉን ህግ ለተወካዮች ምክር ቤት አቅርባለች።ረቂቅ ህጉ የፕላስቲክ ፌስታል ማምረትንና መጠቀም የሚከለክል ሲሆን...

⚖ የፕላስቲክ ከረጢት የተጠቀመ ወይም ለመጠቀም ይዞ የተገኘ ማንኛውም ሰው ከ5,000 ብር እስከ 10,000 ብር ይቀጣል።

⚖ የፕላስቲክ ከረጢት አምርቶ ወይም ወደ ሀገር ውስጥ አስገብቶ ለገበያ ማቅረብ፣ ለንግድ ዓላማ ማከማቸት ከ50 ሺህ ብር እስከ መቶ ሺህ ብር ያስቀጣል። ከዚህ በተጨማሪም ከአምስት አመት የማይበልጥ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።

የህጉ መጽደቅ ምን እንድምታ ይኖረዋል?

ረቂቅ ህጉ የአከባቢ አየር ብክለትን ለመቆጣጠር የወጣ እና አካባቢያዊ ቀጣይነትን/ Sustainability ለማረጋገጥ ያለመ ቢሆንም የህጉ መጽደቅ...

🧑‍🚀  በፕላስቲክ ፌስታል ፋብሪካ ዉስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ በሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ሥራ ያሳጣል።

⚙ ከእዚህ ቀደም ሚሊዮኖችን ኢንቨስት በማድረግ የተገዙ ማሽኖች ተለዋጭ የማምረት አቅም ከሌላቸው በቀር ከጥቅም ውጪ ይሆናሉ።

🏭 እኒህን ማሽኖች ከባንክ በመበደር የገዙ አምራቾች የባንክ እዳውን ለመክፈል ስለሚያቅታቸው ብድሮቻቸው ይበላሻሉ አሊያም nonperforming loan ይሆናሉ፣ ይሄ ደግሞ በተለይ እነዚህን ማሽኖች በብድር እንዲገዛ ፋይናንስ ያደረጉ እና በመያዣነት የያዙ ባንኮች ማሽኖቹን መሸጥ ስለማይችሉ ለኪሳራ ይዳረጋሉ።

Picture credit: OpenAI




ይሄንን ተቀበል...

ሁልጊዜ ፍጹም ልትሆን እንደማትችል፣ ህይወት ሁሌም በፈተና የተሞላች መሆኗን እንዲሁም አንዳንዴ ሰዎች ሊያበሳጩህ እንደሚችሉ አምነህ ተቀበል። መቀበል ሰላምን የማሸነፊያ የመጀመሪያው እርምጃ ነው።

መልካም ሳምንት!


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ትላንት ይፋ ባደረገው፣ ሁለተኛው የፋይናንሺያል ስቴቢሊቲ ሪፖርት መሠረት የባንኮች operational risk ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመሩንና ከአመት በፊት በአጠቃላይ ከባንክ ዘርፉ ላይ የተሰረቀው የገንዘብ መጠን 1 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ይኸው ገንዘብ ወደ 1.3 ቢሊዮን ብር ከፍ ማለቱን፣ እንዲሁም በስርቆቱ 28 ባንኮች (ሁሉም ሊባል በሚችል መልኩ) መጎዳታቸውን ገልጿል።

በእነዚህ ስርቆቶች እና ማጭበርበሮች ውስጥ የባንኮች የውስጥ ሰራተኞች ጭምር የተሳተፋበት ሲሆን ስርቆቶቹ በዋናነት ሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን፣ ሀሰተኛ ቼክ፣ ሀሰተኛ የባንክ ጋራንቲን፣ የተሰረቁ የኤቲኤም ካርዶችን፣ ሀሰተኛ የስልክ ጥሪዎችንና መልእክቶችን በመጠቀም የተከናወኑ መሆናቸውን ብሔራዊ ባንኩ የገለጸ ሲሆን ባንኮች ከጊዜ ወደ ጊዜ የፋይናንስ አካታችነትን ለማሳካት በሚተገብሯቸው የቴክኖሎጂ ውጤቶች ምክንያት ስጋቱ እየጨመረ እንደሚሄድ የገለጸ ሲሆን ባንኮች እኒህን ስጋቶች ለመቀነስ ፖሊሲና ስትራቴጂ ቀይሰው እንዲሰሩ አሳስቧል።




የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሁለተኛ የፋይናንሺያል ስቴቢሊቲ ሪፖርት።👇




በኢትዮጵያ እየተቋቋመ ስላለው የተመሰከረላቸው የሒሳብ ባለሙያዎች /Charted Public Accountants/ ኢንስቲትዩት ምንነትና አስፈላጊነት፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እየተቋቋመ ስለሚገኘው ኢንቨስትመንት ባንኪንግ ምንነትና ፋይዳ እንዲሁም የሰው ኃይል ላይ ሊደረግ ስለሚገባው ኢንቨስትመንት/Human Capital Development/ መረጃ ከፈለጉ የሚከተለውን ያዳምጡ...

https://youtu.be/ZFxxY89vqf8?si=N4pJm9Y17tTwV2Qs


ሌሎች ሰዎች እንዲወዱህ ብለህ እውነተኛ ማንነትህን አትቀይር፣ እራስህን ሆነህ ተገኝና ትክክለኛ ሰዎች ይወድዱሀል።




የቁሳዊ ነገሮች ዋጋ የሚታወቀው በእጃችሁ ሳይገቡ በፊት ሲሆን፣ የሰው ልጆች ዋጋ ደግሞ የሚታወቀው ካጣችኋቸው በኋላ ነው!

መልካም ቀን፣ መልካም ሳምንት!


"መልሶችህ እውቀትህን የሚያሳዩ ሲሆን፣ ጥያቄዎችህ ደግሞ እሳቤህን ያመላክታሉ።"

መልካም ቀን ይሁንላችሁ!


ከአስር ባሎች መካከል ዘጠኙ "ሚስቶች ሁልጊዜ ትክክል ናቸው" ማለታቸውን አንድ ጥናት አረጋገጠ።

አስረኛው ባል (ሚስቶች ሁልጊዜ ትክክል አይደሉም ያለው) ጥናቱ ከተደረገ በኋላ እምጥ ይግባ ስምጥ ይግባ አልታወቀም።

የት ሄዶ ይሆን ወገን?

መልካም የእረፍት ቀናት!

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.