Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


كناشة ابن منور

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣3️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 65፣ ሐዲሥ ቁ. 103


ዑምደቱል አሕካም ደርስ
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 65፣ ሐዲሥ ቁ. 103


ቋንቋችን በቁርኣን አቀራራችን ላይ ተፅእኖ እንዳያሳድርብን
~
ቋንቋዎች በአካባቢና በዘመን መለያየት የተነሳ ልዩነቶችን ያንፀባርቃሉ። ዐረብኛን እንደ ምሳሌ ብንወስድ በተለያዩ ሃገራት የተለያዩ ዘዬዎች አሉ። አንዳንዶቹ ለኛ ቀርቶ ለዐረቦቹም የሚከብዱ ናቸው። የሆነ ቦታ አንድ ግብፃዊ ያወራኛል። እኔ ከአንዳንድ ቃላት በስተቀር የሚያወራው አልገባኝም። የሌላ ሃገር ዐረብ ቦታው ላይ ነበርና ሁኔታዬን የተረዳ መሰለኝ " የተናገረው ገብቶሃል?" አለኝ። "አልገባኝም" አልኩት። አጠቃላይ የሚናገራቸው እንደሚከብዱኝ ነገርኩት። "እኛም እነሱ ስላስተማሩን ነው ቋንቋቸውን የለመድነው" አለኝ። እንዲያውም የሚገርም ገጠመኝ ነገረኝ። ልጁን ትምህርት ቤት እንዳስገባው ጥቂት ቀን ከሄደ በኋላ "ከዚህ በኋላ እዚያ ትምህርት ቤት አልሄድም። በዐረብኛ ሳይሆን በእንግሊዝኛ ነው የሚያስተምሩት። እኔ እየገባኝ አይደለም አለኝ። ለህጃቸው (ዘያቸው) እንግዳ ስለሆነበት ነበር እንደዚያ ያለው" አለኝ።

ወደ ራሳችን ስመልሰው በየቋንቋው አካባቢን መሰረት ያደረገ ሰፊ የዘዬ ልዩነት አለ። አንዳንዴ ታዲያ ቋንቋችን ወይም ዘያችን የቁርኣን አቀራራችን ላይ ተፅእኖ ሊኖረው ይችላል። ለምሳሌ ያክል
* ሀምዛ (أ) እና ዐይን (ع)፣
* ሓእ (ح)፣ ኻእ (خ) እና ሃእ (هـ) ፣
* ዛል (ذ) እና ዛይ (ز)
ወዘተ በቋንቋ ተፅእኖ ምክንያት ብዙ ሰው ያለ ልዩነት አደባልቆ ያወጣቸዋል። خير ለማለት ከይር ወይም ሀይር የሚለው ብዙ ነው። {غَیۡرِ ٱلۡمَغۡضُوبِ عَلَیۡهِمۡ وَلَا ٱلضَّاۤلِّینَ} ለማለት "ገይሪል መግዱቢ አለይሂም ወለድዷልሊን" የሚለው ብዙ ነው። 0ረብኛ ደግሞ ጥልቅ የድምፅ አጠቃቀም አለው። ثم፣ سم እና صم አንድ አማርኛ ተናጋሪ በአንድ ድምፅ ሊያወጣቸው ይችላል። ሶስቱም ቃላት ግን የተለያየ ድምፅ እና የተለያየ ትርጉም ነው ያላቸው። እነዚህ ቀላል የሚመስሉ ነገሮች ቁርኣን አቀራራችን ላይ በትክክል ካልተማርን ትርጉም በሚቀይር መልኩ ግድፈት እንድንፈፅም ሊያደርጉን ይችላሉ። ሁለት አካባቢዎችን እንደምሳሌ ልጥቀስ። አዲስ አበባ እና ወሎ።

1. አዲስ አበባ፦

በአብዛኛው የሃገራችን ህዝብ ዘንድ የዐረብኛዋ ض ድምፅ የለችም። (ሁሉም ያላልኩት ለምሳሌ ዐፋር እና ምስራቁ የወሎ ክፍል አነጋገር ላይ ይሄ ድምፅ እንዳለ ስለማውቅ ነው።)
እና ይሄ ድምፅ (ض) የሌላቸው ተናጋሪዎች { وَوَجَدَكَ ضَاۤلࣰّا فَهَدَىٰ } የሚለውን "... ዳለን ... " ብለው ቢያነቡት ትርጉም የሚቀይር ግድፈት ነው። ضر እና در የተለያየ ድምፅ ያላቸው የተለያዩ ቃላት ናቸው። ትርጉማቸውም ፍፁም የተለያየ ነው። በተመሳሳይ
ضال እና دال
ضرس እና درس
ضرب እና درب
እያልን ብንዘረዝር ብዙ ድምጻቸውም ትርጉማቸውም የሚለያዩ ቃላትን ማየት እንችላለን። ضን በትክክል የማያወጣ ሰው እነዚህን ቃላት ትርጉም በሚቀይር መልኩ ነው የሚያወጣቸው።
ይሄ ክፍተት የአዲስ አበባ ልጆች ላይ በሰፊው ይታያል። ልጆች ቁርኣን ሲቀሩ ይቸገራሉ። ከዱዓቶች ራሱ እንዲህ አይነት ግድፈቶች የሚታዩባቸው አሉ። {سَنَشُدُّ عَضُدَكَ بِأَخِیكَ} የሚለውን የቁርኣን አንቀፅ "0ዱደከ" እያሉ የሚቀሩ አሉ። {أَنقَضَ ظَهۡرَكَ} የሚለውን "አንቀደ ..." ብሎ መቅራት ስህተት ነው። አዲስ አበባን በቅርብ ስለሚገጥመኝ በምሳሌነት አነሳሁት እንጂ ችግሩ ሌሎችም ጋር ይኖራል።

2. ወሎ፦

የወሎ አማርኛ የቃላት ሃብቱ ስፋት አለው። እጅግ በርካታ ቃላት ከዐረብኛ እና ከኦሮምኛ አስገብቷል። ከሌሎችም አጎራባች ቋንቋዎች በስሱም ቢሆን ይዋዋሳል። ቁልምጫዎቹ፣ ስሜትን (ፍቅርን፣ መቆርቆርን፣ ሃዘንን፣ ...) ገላጭ የሆኑ ለየት ያሉ ቅላፄዎቹ ለቋንቋው ተጨማሪ ውበት ናቸው።

እዚህ ላይ ማንሳት የፈልግኩት ግን ከቁርኣን ጋር በተያያያዘ የተለመደው የ "ዴ" ድምፅ ተፅእኖን ነው። የወሎው አማርኛ ዘዬ ላይ "ደ"ን "ዴ"፣ "ድ"ን ደግሞ "ዲ" አድርጎ ወይም ወደዚያ አቅርቦ ማውጣት የተለመደ ነው። ችግር የሚሆነው ይሄ የአነጋገር 'ስታይል' ወደ ቁርኣን አቀራር ሲመጣ ነው።
* ከላይ ያቀረብኳትን ኣያ {وَوَجَدَكَ ضَاۤلࣰّا فَهَدَىٰ} ብንወስድ አንድ ሰው "ወወጀዴከ ... ፈሀዲያ" ብሎ ቢቀራ ልክ አይሆንም። "ወወጀደከ ... ፈሀዳ" መሆን አለበት። {عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰۤ} የሚለውን "ዐብዴን ኢዛ ሶልላ" ብሎ ቢቀራው ልክ አይደለም።
* እንዲሁም {قُلۡ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ} የሚለውን "... አሐዲ" በሚል፣ {وَمَاۤ أَدۡرَاكَ} የሚለው "ወማ አዲራከ" በሚል መቅራት ስህተት ነው።
ተመሳሳይ ሁኔታዎች በጣም ብዙ ናቸው። ይሄ መታረም ያለበት ነው።

በሌላ በኩል አንዳንዶች ይህንን በመሸሽ ሌላ ግድፈት እያመጡ ነው። "ዴ" እና "ዲ" እኮ የራሳቸው ቦታ አላቸው። ስህተት የሚሆነው ያልቦታቸው ሲውሉ ነው። በቦታቸው አለመጠቀም ሌላ ስህተት ነው። "እንዴት ነህ?" ለማለት "እንደት ነህ?"፣ "አዲስ" ለማለት "አድስ"፣ "ወልዲያ" ለማለት "ወልድያ" ይላሉ። ተመሳሳይ ቅርፅ ያላቸው ብዙ ስህተቶች አሉ። የትም ቦታ "ዴ" እና "ዲ" ላለመጠቀም ይጠነቀቃሉ። ይሄ ስህተት ነው። በርእሴ እንደጠቆምኩት የኔ ትኩረት ከቁርኣን አነባበብ ጋር ያሉ ግድፈቶችን ማስታወስ ነው። ስለዚህ አንድ ሰው {وَٱلۡعَـٰدِیَـٰتِ ضَبۡحࣰا} የሚለውን "ወልዓድያቲ " ብሎ ከቀራ ስህተት ነው። ትክክለኛው "ወልዓዲያቲ " ነውና።

አዲስ አበባንና ወሎ ለማሳያ መዘዝኩ እንጂ በየቋንቋ የተለያዩ የተለመዱ ግድፈቶች አሉና ትኩረት እንስጣቸው። አላማዬ ቁርኣንን በትክክል እንድንማር እና በአቀራራችን ላይ ቋንቋችን ተፅእኖ እንዳያሳድርብን ማስታወስ ነው። ተጅዊድን በጥልቀት እንደተማረ ሰው ባንሆን እንኳ ቢያንስ ትርጉም በሚቀይር መልኩ እያዛነፍን እንዳንቀራ መጠንቀቅ ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


“በተውሒድ ላይ ያዘጋጀው ኪታቡ ትልቅ ጥራዝ ነው። እሱ እራሱ የአላህን 'ሱራ' በተመለከተ የመጣውን ሐዲሥ በርግጥም ከቀጥተኛ መልእክቱ አዙሯል (ተእዊል አድርጓል)። እንግዲያው አንዳንድ የአላህ መገለጫዎችን ተእዊል ያደረጉ ሰዎችንም ዑዝር ይስጥ። ቀደምቶች በተእዊል ውስጥ አልገቡም። ይልቁንም በቀጥታ አምነዋል። ከተእዊልም ተቆጥበዋል። የዚህን እውቀት (ሐቂቃውን) ወደ አላህና መልእክተኛው አስጠግተዋል። ኢማኑ ትክክለኛ፣ ሐቅን ለመከተል የሚያልም የሆነን ሁሉ በኢጅቲሃዱ በተሳሳተ ቁጥር ገደል የምንከተውና በቢድዐ የምንፈርጀው ቢሆን ኖሮ ከአኢማዎች ውስጥ የሚተርፍልን በቀለለ ነበር። አላህ ሁሉንም በችሮታውና በቸርነቱ ይዘንላቸው።” [አሲየር፡ 14/37-376]

ከዚህ የዘሀቢ ተግባር የምንረዳው ምንድነው? ኢብኑ ኹዘይማ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን ማፅደቅ ግዴታ እንደሆነ መናገራቸውን አስረግጠዋል። ነገር ግን በዚህ ላይ የተሳሳቱ ሰዎችን በተመለከተ ኢብኑ ኹዘይማ በሄዱበት ርቀት (ማ^ክ^ፈ^ር) እንደማይገባ እየገለፁ ነው። የአላህን መገለጫዎች ተእዊል አድርጎ የተረዳ ሁሉ በዚህ መልኩ ቢያዝ ኖሮ እራሳቸው ኢብኑ ኹዘይማም አይተርፉም ነበር እያሉን ነው። ለዚህም ሐዲሠ ሱራን ተእዊል ማድረጋቸውን አነሱ።

3. አልባኒይ ረሒመሁላህ፦

ቢድዐ ላይ የወደቀ ሁሉ በሙብተዲዕነት ሊፈረጅ እንደማይገባ የተናገሩበት ብዙ ነው። ለሌላ ጊዜ በሰፊው መመለሴ ባይቀርም ለጊዜው አንድ ሁለት ንግግሮቻቸውን ልጥቀስ፡-
إذا كان هذا المخالف يخالف نصا أولا: لا يجوز اتباعه، وثانيا لا نبدع القائل بخلاف النص وإن كنا نقول إن قوله بدعة، وأنا أفرق بين أن تقول فلان وقع في الكف.ر وفلان كف.ر، وكذلك فلان وقع في البدعة وفلان مبت.دع، فأقول فلان مبت.دع مش معناه وقع في بدعة، وهو مَن شأنه أنه يبتدع، لأن مبت.دع اسم فاعل، هذا كما إذا قلنا فلان عادل ليس لأنه عدل مرة في حياته، فأخذ هذا اسم الفاعل، القصد أن المجتهد قد يقع في البدعة–ولا شك-لكن لا ألومه بها ولا أطلق عليه اسم مبت.دع، هذا فيما إذا خالف نصا
“ይሄ ተፃራሪ፡ በቅድሚያ መረጃን የሚፃረር ከሆነ ሊከተሉት አይፈቀድም። ሁለተኛ ከመረጃ ተቃርሮ የተናገረውን ንግግሩን ‘ቢድዐ ነው’ ብንልም ተናጋሪውን ሙብተዲዕ አናደርግም። እኔ ‘እከሌ ክህደት ላይ ወድቋል’ በማለትና ‘እከሌ ከ^ፍ^ሯ^ል’ በማለት መካከል እለያለሁ። ‘እከሌ ቢድዐ ላይ ወደቀ’ በማለትና ‘እከሌ ሙብ^ተዲዕ ነው’ በማለትም ላይ እንዲሁ። እናም እንዲህ እላለሁ፦ እከሌ ሙብ^ተዲዕ ነው ማለት ቢድዐ ላይ ወድቋል ማለት አይደልም ትርጉሙ። ይልቁንም ቢድዐ የሚያራምድ ማለት ነው። ምክንያቱም ሙብ^ተዲዕ የሚለው ቃል አድራጊ ነው። ይሄ ማለት ልክ ፍትሃዊው እከሌ እንደማለት ነው። ይሄ ግን በህይወቱ አንዴ በፍትህ ስለፈረደ ይህንን ስም ይዟል ማለት አይደለም። ዋናው ነገር ሙጅተሂድ የሆነ ሰው ያለ ጥርጥር ቢድዐ ላይ ሊወድቅ ይችላል። ነገር ግን በሷ አልወቅሰውም። ሙብ^ተዲዕ የሚል ስምም አልለጥፍበትም። ይሄ እንግዲህ ቀጥተኛ መረጃ ሲፃረር ነው።” [ሲልሲለቱል ሁዳ ወኑር፡ 850]

ወንድሜ ሆይ! ንግግሮቻቸውን በደንብ አጢነህ እራስህን ገምግም። በተሳሳተ መልኩ ቀጥተኛ መረጃ በተፃረረ ላይ ይህንን ካሉ በኢጅቲሃድ ጉዳዮች የተሳሳተስ ላይ ምን የሚሉ ይመስልሃል?!
አሁንም ከአልባኒ ጋር እንቀጥል፦
“አንድ መሰረቱ የአህሉ ሱና መሰረት የሆነ፣ በዚያም ላይ የሚጓዝ የሆነ፣ ከሱና ሰዎች በመከላከልና መንገዳቸውን በማገልገልም የሚታወቅ የሆነ ሰው አልፎ አልፎ አንዳንድ የመንሃጅ ስህተቶች ቢንፀባረቁበት፡
* ከሱ ማስጠንቀቅ ነው የሚገባው? ወይስ
* ስህተቶቹን ግልፅ ማድረግ ነው የሚገባው?” ተብለው ሲጠየቁ እንዲህ ነበር የመለሱት፡-
“መልሱ ሁለተኛው ነው እንጂ የመጀመሪያው አይደለም።” (ስህተቶቹ ግልፅ ይደረጋሉ እንጂ ከሱ ማስጠንቀቅ አይገባም።) [ሲልሲለቱል ሁዳ ወኑር ካሴት ቁ. 751]

4. ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ፦

አንድ ሱናን መንገዱ ያደረገ ሰው የዐቂዳ ስህተት ብናገኝበት በቀጥታ በቢድዐ ፈርጀን ከሱና እናስወጣዋለን? ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን በንዲህ አይነት ጉዳይ ላይ ምን እንደሚሉ እንመልከት፡-
وأما الخطأ في العقيدة: فإن كان خطأ مخالفًا لطريق السلف، فهو ضلال بلا شك ولكن لا يحكم على صاحبه بالضلال حتى تقوم عليه الحجة، فإذا قامت عليه الحجة، وأصر على خطئه وضلاله، كان مبت.دعًا فيما خالف فيه الحق، وإن كان سلفيًّا فيما سواه
“የዐቂዳ ስህተትን በተመለከተ ለመልካም ቀደምቶች መንገድ ተፃራሪ የሆነ ስህተት ከሆነ እሱ ያለጥርጥር ጥመት ነው። ነገር ግን ባለዚህ ጥፋት መረጃ እስከሚቀርብበት ድረስ በጥመት አይፈረጅም። መረጃ ቀርቦበት በስህተቱና በጥመቱ ላይ የሚፀና ከሆነ ግን ሐቅን በጣሰበት ጉዳይ ሙብ^ተዲዕ ሆኗል። ከዚያ ውጭ ባለው ሰለፊ ቢሆንም።” [ኪታቡል ዒልም፡ 135]
ፅሁፌ ስለረዘመ የሌሎች ዓሊሞችን ንግግር አላካተትኩም። የምፅፈው በጉዳዩ ላይ የዑለማዎቹ አካሄድ ምን እንደሚመስል ማወቅ ለሚፈልጉ ጥቆማ ለመስጠት ያክል ነው። እርምት ያለው ካለ ከስር በአደብ ሃሳብ መለዋወጥ ይቻላል።
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 24/2013)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


የመንሃጅ ስህተት የታየበት/ ቢድዐ ላይ የወደቀ ሁሉ ከሱና ይወጣል ወይ?
~
ባለፈው ጥፋቶች ከክብደታቸው አንፃር እኩል እንዳልሆኑ ስለሆነም በኢጅቲሃዳዊ ጉዳዮ ሰዎችን ከሱና ማስወጣት እንደማይፈቀድ በመግለፅ የተወሰኑ ዑለማዎችን ንግግሮች አጣቅሼ ነበር። ዛሬ ማንሳት የፈለግኩት ደግሞ ስህተቶቹ መንሃጅ ነክ ቢሆኑ እንኳ ከሱና ለማስወጣት መቻኮል እንደማይገባ ማስታወስ ነው። በሱና የሚታወቅ ሰው እንዲህ አይነት ስህተቶች ስለታዩበት ግራ ቀኝ ሳይታይ በቢድዐ አይፈረጅም። የዑለማዎችን ንግግር እጠቅሳለሁ፦

1. ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ፦
وَقَدْ اجْتَهَدَ فِي طَلَبِهِ فَعَجَزَ عَنْهُ فَلَا يُعَاقَبُ وَقَدْ يَفْعَلُ بَعْضَ مَا أُمِرَ بِهِ فَيَكُونُ لَهُ أَجْرٌ عَلَى اجْتِهَادِهِ وَخَطَؤُهُ الَّذِي ضَلَّ فِيهِ عَنْ حَقِيقَةِ الْأَمْرِ مَغْفُورٌ لَهُ. وَكَثِيرٌ مِنْ مُجْتَهِدِي السَّلَفِ وَالْخَلَفِ قَدْ قَالُوا وَفَعَلُوا مَا هُوَ بِدْعَةٌ وَلَمْ يَعْلَمُوا أَنَّهُ بِدْعَةٌ إمَّا لِأَحَادِيثَ ضَعِيفَةٍ ظَنُّوهَا صَحِيحَةً وَإِمَّا لِآيَاتِ فَهِمُوا مِنْهَا مَا لَمْ يُرَدْ مِنْهَا وَإِمَّا لِرَأْيٍ رَأَوْهُ وَفِي الْمَسْأَلَةِ نُصُوصٌ لَمْ تَبْلُغْهُمْ.
“በርግጥም ሐቅን ፈልጎ ጥሮ ስላልደረሰበት አይቀጣም። ምናልባት ከታዘዘበት ከፊሉን ይሰራና በጥረቱ ምንዳ ይኖረዋል። ከትክክለኛው ጉዳይ ፈር የለቀቀበት ስህተቱ ይማርለታል። ከቀደምቶቹም ይሁን ከኋለኞቹ ብዙ ሙጅተሂዶች ቢድዐ መሆኑን ሳያውቁ በእርግጥም ቢድዐ የሆነን ነገር ተናግረዋል፣ ፈፅመዋልም። ይህም የሆነው ወይ ትክክለኛ መስለዋቸው ደካማ ሐዲሦችን ይዘው ነው። ወይ ደግሞ ትክክለኛ ያልሆነን መልእክት (በተሳሳተ መልኩ) ከ(ቁርኣን) አንቀፆች ተረድተው ነው። ወይ ደግሞ መረጃዎች ሳይደርሷቸው በጉዳዩ ላይ የራሳቸውን እይታ ተንተርሰው ነው።” [አልመጅሙዕ፡ 19/191]

አሁንም ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ይላሉ፡-
وَمِثْلُ هَؤُلَاءِ إذَا لَمْ يَجْعَلُوا مَا ابْتَدَعُوهُ قَوْلًا يُفَارِقُونَ بِهِ جَمَاعَةَ الْمُسْلِمِينَ؛ يُوَالُونَ عَلَيْهِ وَيُعَادُونَ؛ كَانَ مِنْ نَوْعِ الْخَطَأِ. وَاَللَّهُ سُبْحَانَهُ وَتَعَالَى يَغْفِرُ لِلْمُؤْمِنِينَ خَطَأَهُمْ فِي مِثْلِ ذَلِكَ. وَلِهَذَا وَقَعَ فِي مِثْلِ هَذَا كَثِيرٌ مِنْ سَلَفِ الْأُمَّةِ وَأَئِمَّتِهَا: لَهُمْ مَقَالَاتٌ قَالُوهَا بِاجْتِهَادِ وَهِيَ تُخَالِفُ مَا ثَبَتَ فِي الْكِتَابِ وَالسُّنَّةِ
“የነዚህ አምሳያ የሆነው የፈጠሩትን ነገር በሱ ሳቢያ የሚወዳጁበትና የሚጠሉበት፣ ከሙስሊሞች ህብረት የሚገነጠሉበት ንግግር ካላደረጉት እንደ ስህተት ነው የሚቆጠረው። የጠራውና የላቀው አላህ በዚህ አምሳያ ላይ ያሉ ስህተቶችን ለአማኞች ይምራልና። ለዚህም ነው ከመልካም ቀደምቶችና ምሁራን ውስጥ ብዙዎች ይህን በሚመስሉ ጥፋቶች ላይ የወደቁት። በኢጅቲሃድ የተናገሯቸው ከቁርኣንና ከሱና ጋር የሚፃረሩ ንግግሮች አሏቸው።” [አልመጅሙዕ፡ 3/349]

ልብ በል! ከሰለፍም ከኸለፍም ሳያስቡት ቢድዐ የፈፀሙ/ የተናገሩ አሉ እያሉ ነው። ሰለፎች ቢድዐ ላይ ብርቱ አስጠንቃቂዎች ነበሩ ማለት በተናጠል ከቢድዐ ፍፁሞች ነበሩ ማለት አይደለም። ከነቢያት ውጭ የሰው ልጅ በሙሉ ሰለፎቹን ጨምሮ ተሳሳች ነው። የአህለ ሱናን አቋም የሚከተል፣ ለሱና የሚለፋና ተቆርቋሪ የሆነ ሰው በሚታዩበት አንዳንድ ስህተቶች ገደል አይከተትም። ባይሆን ስህተት ከማንም ቢመጣ ይጣላል። እንጂ የተከበረ፣ የታወቀ፣ ዑዝር የሚሰጠው ስለሆነ ብቻ የተናገረው ሁሉ ሐቅ ይሆናል ማለት አይደለም።

2. አዘሀቢይ ረሒመሁላህ፦

አልኢማም ሙሐመድ ብኑ ነስር አልመርወዚ ረሒመሁላህ ከታላላቅ የኢስላም ሊቃውንት ናቸው። ከኢማን ጋር በተያያዘ ብዙዎች ያልወደዱት አሻሚ ቃል ይናገራሉ። በዚህ የተነሳ የዘመናቸው ዑለማዎች አኮረፏቸው። የኹራሳንና የዒራቅ ሊቃውንትም ተቃረኗቸው። ኢማሙ ዘሀቢ ረሒመሁላህ በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጠልቆ መግባት እንደማያስፈልግ ገልፀው ከዚያም ትክክለኛውን እይታ አፍታተው ካስቀመጡ በኋላ እንዲህ ሲሉ ቁልፍ መልእክት አስተላለፉ፡-
وَلَوْ أَنَّا كلَّمَا أَخْطَأَ إِمَامٌ فِي اجْتِهَادِهِ فِي آحَادِ المَسَائِلِ خَطَأً مَغْفُوراً لَهُ، قُمْنَا عَلَيْهِ، وَبدَّعْنَاهُ، وَهَجَرْنَاهُ، لَمَا سَلِمَ مَعَنَا لَا ابْنَ نَصْرٍ، ‌وَلَا ‌ابْنَ ‌مَنْدَةَ، وَلَا مَنْ هُوَ أَكْبَرُ مِنْهُمَا، وَاللهُ هُوَ هَادِي الخَلْقِ إِلَى الحَقِّ، وَهُوَ أَرحمُ الرَّاحمِينَ، فَنَعُوذُ بِاللهِ مِنَ الهوَى وَالفظَاظَةِ
“አንድ ኢማም በነጠላ ጉዳዮች ይቅር የሚባልበት የሆነን ስህተት በኢጅቲሃዱ በተሳሳተ ቁጥር ተነስተን በቢድዐ የምንፈርጀውና የምናኮርፈው ቢሆን ኖሮ ከኛ ጋር ኢብኑ ነስርም፣ ኢብኑ መንዳህም አይተርፉም ነበር። ኧረ ከነሱ የበለጠም አይተርፍም። ፍጡርን ወደ ሐቅ የሚመራው አላህ ነው። እሱ ከአዛኞች ሁሉ አዛኝ ነው። ከስሜትና ከክፉ አመል በአላህ እንጠበቃለን።” [አሲየር፡ 14/39-40]
ምን እያሉ እንደሆነ ገብቶሃል? ከነዚያ ታላላቆች በኩል መርወዚ ላይ የተወሰደውን እርምጃ በአደብ እያረሙ፣ ለሌሎች ወሳኝ ትምህርት እያስተላለፉ ነው። ነገሮችን በዚህ መልኩ ብንይዝ ኖሮ እንኳን መርወዚ ከሳቸው የሚበልጡ ታላላቆችም አይተርፉም ነበር እያሉ ነው። እየውልህ ወንድሜ! ይሄ ጥንቃቄ ከዘሀቢ ጋር የተቀበረ አይደለም። ዛሬም ይሰራል። ማንም ላንቃው እስከሚበጠስ ቢጮህ ከኋላው እንዲያሰልፍህ አትፈቀድለት። የምትገባው ከራስህ ቀብር ነው።

ልጨምር፡ ኢብኑ ኹዘይማህ ረሒመሁላህ የአላህን ከዐርሹ በላይ መሆን ያላፀደቁ ሰዎችን አክ^ፍ^ረው ተናግረዋል። ዘሀቢ የኢብኑ ኹዘይማን ክብርና ደረጃ ከገለፁ በኋላ እንዲህ ይላሉ፦
وَكِتَابُه فِي (التَّوحيدِ) مُجَلَّدٌ كَبِيْرٌ، وَقَدْ تَأَوَّلَ فِي ذَلِكَ حَدِيْثَ الصُّورَةِ. فَلْيَعْذُر مَنْ تَأَوَّلَ بَعْضَ الصِّفَاتِ، وَأَمَّا السَّلَفُ، فَمَا خَاضُوا فِي التَّأْوِيْلِ، بَلْ آمَنُوا وَكَفُّوا، وَفَوَّضُوا عِلمَ ذَلِكَ إِلَى اللهِ وَرَسُوْلِه، وَلَوْ أَنَّ كُلَّ مَنْ أَخْطَأَ فِي اجْتِهَادِهِ - مَعَ صِحَّةِ إِيْمَانِهِ، وَتَوَخِّيْهِ لاتِّبَاعِ الحَقِّ - أَهْدَرْنَاهُ، وَبَدَّعنَاهُ، لَقَلَّ مَنْ يَسلَمُ مِنَ الأَئِمَّةِ مَعَنَا، رَحِمَ اللهُ الجَمِيْعَ بِمَنِّهِ وَكَرَمِهِ




ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣2⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 59፣ ሐዲሥ ቁ. 93


ዑምደቱል አሕካም ደርስ
~
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 59፣ ሐዲሥ ቁ. 93


አነስ ብኑ ማሊክ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ እንዲህ አሉ፦
(( دَخَلَ عَلَيْنَا النَّبِيُّ ﷺ فَقَالَ عِنْدَنَا فَعَرِقَ، وَجَاءَتْ أُمِّي بِقَارُورَةٍ فَجَعَلَتْ تَسْلِتُ الْعَرَقَ فِيهَا، فَاسْتَيْقَظَ النَّبِيُّ ﷺ فَقَالَ : يَا أُمَّ سُلَيْمٍ، مَا هَذَا الَّذِي تَصْنَعِينَ
قَالَتْ : هَذَا عَرَقُكَ نَجْعَلُهُ فِي طِيبِنَا، وَهُوَ مِنْ أَطْيَبِ الطِّيبِ ))
"ነብያችን ﷺ እኛ ዘንድ ቀለል ያለ የቀትር ሰዓት እንቅልፍ ተኙና አላባቸው። እናቴ ጠርሙስ አመጣችና እየጠረገች ጨመረች። ነብያችን ﷺ ነቁ እና 'ኡሙ ሱለይም ሆይ! ምንድነው እየሰራሽ ያለሽው' አሏት።
እሷም፡ 'ይሄ ላብህ ነው። በሽቷችን ላይ እናደርገዋለን። እሱ ምርጥ ከሆኑት ሽቶዎች ውስጥ ነው።'"
📚 አልቡኻሪይ እና ሙስሊም የተስማሙበት ዘገባ ነው። [6281፣ 2331]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣1️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 53፣ ሐዲሥ ቁ. 81


ግንኙነት ያልተፈፀመበት ኒካሕ
~
አንድ ሰው አንዲትን ሴት ኒካሕ አድርጎ ካገባ በኋላ ነገር ግን በመሃላቸው ግንኙነት ሳይፈፀም ከፈታት ፤ ለምሳሌ የተለያየ ሃገር እየኖሩ ኒካሕ ከታሰረ በኋላ ሳይገናኙ ፍቺ ቢፈፅም ዒዳ የለባትም። ምክንያቱም አላህ እንዲህ ብሏልና፦
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آَمَنُوا إِذَا نَكَحْتُمُ الْمُؤْمِنَاتِ ثُمَّ طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِنْ قَبْلِ أَنْ تَمَسُّوهُنَّ فَمَا لَكُمْ عَلَيْهِنَّ مِنْ عِدَّةٍ تَعْتَدُّونَهَا فَمَتِّعُوهُنَّ وَسَرِّحُوهُنَّ سَرَاحًا جَمِيلًا
{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ምእምናትን ባገባችሁና ከዚያም ሳትነኳቸው በፊት በፈታችኋቸው ጊዜ ለእናንተ በእነርሱ ላይ የምትቆጥሯት ዒዳ ምንም የላችሁም፡፡ አጣቅሟቸውም፤ (ጉርሻ ስጧቸው)፡፡ መልካም ማሰናበትንም አሰናብቷቸው፡፡} [አል አሕዛብ፡ 49]
* ይሄ ጉዳይ የዑለማእ ኢጅማዕ ያለበት ነው።

ማሳሰቢያ፦

* ዳግም ማግባት ከፈለገ መስፈርቱን ያሟላ አዲስ ኒካሕ ማሰር እንጂ እንዲሁ መልሻለሁ ብሎ መመለስ አይችልም።
* ለመመለስ ሌላ አግብታ መፈታቷ ሸርጥ አይደለም። ሌላ አግብታ የተፈታች ባይሆንም ማግባት ይችላል። ነገር ግን የባለፈው ፍቺ አንድ ተብሎ ይቆጠራል። ስለዚህ ሁለት ኒካሕ ነው የሚቀረው ማለት ነው።
.
በፍቺ ሳይሆን በሞት ከተለየ ግን የዒዳው ብይን ይለያል። ማለትም ኒካሕ ታስሮ ግንኙነት ሳይፈፀም በፊት ባል ከሞተ አራት ወር ከ 10 ቀን ዒዳ ትቆጥራለች። ከንብረቱም ትወርሳለች። ሙሉ መህሯንም ትወስዳለች። የመህሯ መጠን ቀድሞ ያልተወሰነ ከሆነ የአምሳያዎቿ መህር ታሰቦ ይሰጣታል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
• ዑምደቱል አሕካም
• ክፍል:- 1️⃣0️⃣
• የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• የሚሰጥበት ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 49፣ ሐዲሥ ቁ. 72


የደርስ ማስታወቂያ
~
• ኪታቡ፦ ዑምደቱል አሕካም
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 53፣ ሐዲሥ ቁ. 81


✨ كتاب جديد ✨

📚 [ الحق ليس محصورًا في المذاهب الأربعة ]

📎 الرد إغلاق متعصبة المذاهب لباب الاجتهاد، وبيان تناقضهم
📎 من أسباب بُعد المذهبيين عن تدريس الفقه بالدليل
📎 مناقشة رسالة (الرد على من اتبع غير المذاهب الأربعة) لابن رجب
📎 أقوال المذاهب الأربعة ليست أقوال أئمتها
📎 بطلان القول بإلزام اتباع أحد المذاهب الأربعة، وكلام أئمة العصر في ذلك

📥 [https://www.islamancient.com/ar/?p=36825]

✍🏻 د. عبدالعزيز بن ريس الريس


عَنْ عَائِشَةَ رضي الله عنها - في ذكرها لصفة صلاته صلى الله عليه وسلم - أنها قَالَتْ: "وَكَانَ يَنْهَى عَنْ عُقْبَةِ الشَّيْطَانِ".
رواه مسلم في "صحيحه" (498)


የደርስ ማስታወቂያ
~
• ኪታቡ፦ ዑምደቱል አሕካም
• ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://t.me/IbnuMunewor/6880?single
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 49፣ ሐዲሥ ቁ. 72


የወሎን ሙስሊምና የጥምቀትን በዓል ምን አገናኘው⁉️

የቦሩ ሙስሊሞች ታቦት ቢሸኙ ኑሮ ይታረዱ ነበርን⁉️

እረ ረረ ሸህ አያሌው ከበደ!

ያገሬ ዑለሞች ዱዓቶች እረ እሪ በሉ እረ ጩሁ እረ ተናገሩ እረ ኮስተር በሉ ውይ ውይ ውይ!!

https://t.me/abumuazhusenedris


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
አይሁድ ወታደር ፍልስጤማዊ ህፃን ላይ የሚያደርገውን ተመልከቱ።
~
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ደርስ
~
* መንሀጁ ሳሊኪን
* ክፍል:- 4️⃣4️⃣
* የሚሰጥበት ቦታ፦ የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ ሑዘይፋህ መስጂድ
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ረፋድ ላይ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ማሳሰቢያ፦
የፖስቱ ዋና ማጠንጠኛ የዲን አስተማሪዎች ፖለቲካ ውስጥ መግባታቸው ጉዳት እንዳለው መጠቆም ነው። ያልተፃፈ እንዳታነቡ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.