Postlar filtri




የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓልን ከተማሪዎች ጋር አከበሩ።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች የ2017 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓልን ከተማሪዎች ጋር በጋራ በድምቀት አክብረዋል።

የአስተዳደርና ልማት ም/ፕሬዝደንት ወሀቤ ብርሃን (ዶ/ር) የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለተማሪዎች በተዘጋጀው ልዩ የምሳ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልዋል።

መልካም የትንሳኤ በዓል!


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው ሠራተኞችና ተማሪዎች እንዲሁም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ  እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል!

መልካም የትንሳኤ በዓል!


እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

መልካም የስቅለት በዓል!
Telegram-https://t.me/injiuniversity
Website- https://www.inu.edu.et/
Facebook-https://www.facebook. Com/injibaruni
Email- injibarau@gmail.com
Institution Email -injibarauniversity@inu.edu.et
Twitter- (https://twitter.com/injibara_Inu/)
YouTube-https://www.youtube.com/c/injibarauniversity

Explore Your Creative Potential.


የትምህርት ሚኒስቴር ሱፐርቪዥን ቡድን የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲን ቁልፍ የአፈፃፀም አመላካቾች (KPIs) ትግበራ ላይ ግምገማ አካሄደ፡፡

የ2017 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቁልፍ አመላካቾች እና ተግባራት አፈጻጸም እና ክትትል ድጋፍ ቡድን በቁልፍ አፈጻጸም ጉዳዮች (KPIs) እና ተግባራት ላይ ከዩነቨርሲቲው የሴኔት አባላት፣ መምህራን፣ አስተዳደር ሰራተኞችና ተማሪዎች ጋር በቨርቹዋል ውይይት በማድረግ ግምገማ አካሂዷል፡፡

በውይይቱ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጋርዳቸው ወርቁ(ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው ከትምህርት ሚኒስትር ጋር በገባው የቁልፍ አፈጻጸም ጉዳዮች (KPIs) ስምምነት ውል መሰረት በመማር ማስተማር በምርምር፣በማህበረሰብ አገልግሎት፣ ምቹ የትምህርት ከባቢን ከመፍጠር እና የትምህርት ስርዓቱን ከማዘመን አኳያ እንዲሁም በመምህራንም ሆነ በተማሪዎች ተመራጭ ለማድረግ እየሰራ ያላቸውን ተግባራት ለገምጋሚ ቡድኑ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ዶ/ር ጋርዳቸው አያይዘውም ዩኒቨርሲቲው የተሰጠውን ተልዕኮ ለመፈጸም የጸጥታ ችግር፣ የመምህራን የኑሮ ውድነት ችግር እና አስፈላጊ ቁሳቁሶች እጥረት በከፍተኛ ሁኔታ ለሥራ ማነቆ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid0EQFPZeFiBpbQim5UQhW3iVYnk65mtcsBRRFiUoBaEUKhdvG6Fu9aMto8PJYqdhjyl/?app=fbl



6 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.