Postlar filtri


ለአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ሴት አመራሮች በስራ ፈጠራ(Entrepreneurship) ዙሪያ የአቅም ማጎልበቻ
ስልጠና ተሰጠ፡፡
---------
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ከብሄረሰብ አስተዳደሩ ሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ጋር በመተባበር ሴት አመራሮች ከአመራርነት ባለፈ በኢኮኖሚ የበቁ ሆነው ጎን ለጎን ስራ ፈጥረው መስራት እንዲችሉ የሚያግዝ የአቅም ማልበቻ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር መልካም አባተ
እንደገለጹት የዩኒቨርሲቲው በመማር ማስተማር፣ ምርምር ባሻገር ማህበረሰብ አግልግሎት በርካታ የአቅም ግንባታ
ስልጠናዎች መስጠቱን ገልጸው ይህ ስልጠና በዩኒቨርሲቲው አንዱ የትኩረት መስክ በሆነው ቱሪዝም፣ ስራ ፈጠራ እና ልማት ዙሪያ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር መልካም አያይዘውም ስልጠናው ሴት አመራሮች ለሚመሯቸው መስሪያ ቤቶች በስራ ፈጠራ የተሻለ ግንዘቤ ኖሯቸው ከአመራርነት ባለፈ በስራ ፈጠራም ብቁ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ ነው ነው ብለዋል፡፡

የስልጠናው አስተባበሪ እና ኮር አመራር የሆኑት ወ/ሮ ወይንሸት ነጋ እንደተናገሩት ስልጠናው ለአዊ ብሄረሰብ
አስተደዳር ሴት አመራሮች የመሪነት እና ስራ ፈጠራ አቅማቸውን ለማሳደግ የሚያግዝ መሆኑን ተናግረው
ዩኒቨርሲቲው ሴቶች በሁሉም መስክ እንዲበቁ ላደረገላቸው ድጋፍ አመስግነዋል፡፡ ወ/ሮ ወይንሸት አያይዘውም ብሄረሰብ አስተዳደሩ በቀጣይ በርካታ ስራዎችን በጋራ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02kn1HV3KCbFZgXiphevhWF5YgYSwSX3CkfcWwSfBzkiWGRJ8VeYPXHRpK7DA6TNX2l/




ማስታወቂያ

ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና እና ምዝገባ ቀናት የተራዘሙ መሆኑን ስለማሳወቅ

በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ መጋቢት 01/2017 መጠናቀቁ እና ፈተናው መጋቢት 05/2017 ከ3፡00 ጀምሮ እንደሚሰጥ መገለጹ ይታወሳል። ይሁን እንጂ በአንዳንድ ተፈታኞች ጥያቄ መሰረት ምዝገባው እስከ መጋቢት 04/2017 ዓ.ም እስከ ምሽቱ 12:00 የተራዘመ ሲሆን ፈተናው ደግሞ መጋቢት 12/2017 ከ3:00 ጀምሮ ይሰጣል።

በዚሁ መሰረት በተለያየ ምክንያት ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች ምዝገባችሁን ቀደም ሲል በተገለጸው ሊንክ በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ፈተናውን ከላይ በተጠቀሰው ቀንና ስዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት ተገኝታችሁ እንድትፈተኑ እናሳስባለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 30 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡

ትምህርት ሚኒስቴር


"ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁሉን አቀፍ ለውጥ በሴቶች ተሳትፎ ይረጋገጣል!" በሚል መሪቃል ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን ተከበረ።

ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን (march 8)በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ114ኛ፣ በኢትዮጵያ ለ49ኛ፣በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለ8ኛ ጊዜ በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል።

በፕሮግራሙ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ክንዴ ብርሃን (ዶ/ር)
ከዘንድሮው ዓለማቀፍ የሴቶች ቀን አመታዊ ክብረ በዓል መሪ ቃል የምንረዳው ዋና ቁም ነገር ሴቶች ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ሁለንተናዊ ለውጥ መምጣት ይቻል ዘንድ የሚጫወቱት አወንታዊ ሚና ላቅ ያለ
በመሆኑ በማንኛውም ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ የሴቶችን ተሳትፎ በማሳደግ በቤተሰብ፣በማህበረሰብና በሀገር ደረጃ ሁለንተናዊ ለውጥ እንዲመጣ ማስቻል የሁላችን ኃላፊነት አለብን ብለዋል።

ሴቶች እንደ አንድ የማህበረሰብ ክፍል ለቤተሰብ ለማህበረሰብ አና ለሃገር ሁለንተናዊ ለውጥና እድገት መምጣት ማበርከት ያለባቸውን አስተዋፅአ ማበርከት ይችሉ ዘንድ የሴቶችን ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማሳደግ ይገባናል ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል።
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid033mBxL591aAmxDgVA3juw6M3ciDnpasBWNZ8JzwDdohMp3SidyGWvcxmv5Ltnx45ml/?app=fbl




ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የሙያ ማሻሻያ ስልጠና ተሰጠ፡፡
--------------
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ ጋር በተባበር ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ዙሪያ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ለሚገኙ ለአየሁ ጓጉሳ እና ባንጃ ወረዳ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዳንኤል አዳነ (ረ/ፕሮፌሰር)ከዩኒቨርሲቲው የትኩረት መስኮች አንዱ ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መሆኑን ጠቅሰው ስልጠናው ከብሄረሰብ አስተዳደሩ ጤና መምሪያ ጋር በመተባበር ከማህበረሰቡ ጋር በቅርበት ለሚገናኙት የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የተዘጋጀ የሙያ ማሻሻያ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም ስልጠናው በዩኒቨርሲቲው የሙያ ማሻሻያ ማእከል (CPD) ውስጥ የተሠጠ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ዙሪያ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በቂ ዕውቀት እንዲኖራቸው በኮምፒውተር የታገዘ እና ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ CPD ማዕከል እስከ አሁን ከ110 በላይ በብሄረሰብ አስተዳደሩ ለሚገኙ ጤና ባለሙያዎች ስልጠና መሠጠቱንም ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ጤና መምሪያ የጤና ኤክስቴንሽን ትብብር ኦፊሰር የሆኑት ያረጋል መብራቱ በበኩላቸው ስልጠናው ለብሄረሰብ አስተዳደሩ የጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በስኳር፣ ቲቪ፣ኤች. አይ. ቪ እና መሰል በሽታዎች ዙሪያ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በኮምፒውተር የታገዘ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡
https://www.facebook.com/100069178971700/posts/pfbid02TkrW1RM3YE23AAmhQQX1bKXmrKLb8fBWwvuU4xHrHyAZwiBSxK18YgJD5nxie6w3l/?app=fbl


ማስታወቂያ

ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና ቀንን
ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ መሰረት ለመፈተን ያመለከታችሁ አመልካቾች ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
1. ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
2. ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
3. የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
4. የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር



8 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.