Orthodox Mezmur Channel


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


✞✞✞ Orthodox Mezmur Channel ✞✞✞

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ቆየት ያሉ እና አዳዲስ መዝሙሮችን ያገኛሉ።
@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All

ለማንኛውም ሀሳብ ፣ ጥቆማ ፣ አስተያየት
👇👇👇
@Orthodox_Mezmurs
@Orthodox_Mezmurs

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


ፍቅርህ ማረከኝ | ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

ፍቅርህ ማረከኝ በሕይወቴ በዘመኔ/2/
እግዚአብሔር ለእኔ መድኃኒቴ
ፍቅርህ ማረከኝ በህይወቴ በዘመኔ/2/
አዝ

ተገዝቻለሁ በወርቅ ደምህ
ዓለምን ትቼ ላገለግልህ
ሞትህ ህይወቴ ለእኔ ሆኖኛል
በአንተ መከራ ሸክሜ እርቋል
ለክብርህ ቆሜ እዘምራለሁ
እንደ አቅሜ አገንሃለሁ/2/
አዝ

ምድርና ሰማይ እልል ይበሉ
ምስጋና ለአንተ ይድረስ እያሉ
መሳይ የለህም ለቅድስናህ
አቀርባለሁኝ ለአንተ ምስጋና
ጣቴ በገና ይደረድራል
በቀን በሌሊት ያመስግናል/2/
አዝ

ክብርህን አይተው ጠላቶች ፈሩ
ለጌትነትህ ወድቀው ተገዙ
እንዲህ ነህ አምላክ እንዲህ ነህ ጌታ
ሁሉን በፍቅር የምትረታ
በአንተ ተመካሁ በፈጣሪያችን
አዳኝ በሆንከው በንጉሳችን/2/

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ቅድስት ሥላሴ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

ገፄን አማትቤ ልጀምር ውዳሴ
በትምህርተ መስቀል በስመ ሥላሴ
ይርቃል ከጎኔ ጠላት ዲያብሎስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አዝ

ከትቢያ ከአፈር አንስቶ የሰራኝ
በአፉም እስትንፋስ ሕይወትን ያደለኝ
የሥላሴ ሥራ ድንቅ ነው ጥበቡ
ከአይምሮ በላይ ነው የእግዚአብሔር ሃሳቡ
አዝ

እክሕደከ ሰይጣን ጠላቴን ክጃለውሁ
ለዚህም ምስክር ማርያም ናት ብያለሁ
በቤተክርስቲያ ቆሜ በመቅደሱ
ለቅድስት ሥላሴ ዘመርኩ ለንጉሡ
አዝ

አልነበረም ዘመን እርሱ ያልነበረበት
ዳግመኛም አይኖርም እርሱ ማይኖርበት
የሕይወቴ ጣዕም ክብሬ እና ሞገሴ
የማይሾሙት ንጉስ ዘላለም ሥላሴ
አዝ

ኪሩቤል ሱራፌል ኃይላት ሊቃናት
መናብርት ስልጣናት ቆመው በአንድነት
ያለአንዳች ዝምታ ይሉታል በክብር
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ምናል ብታስተምረኝ | ዘማሪት ሲስተር ሕይወት ተፈሪ

በክብር በሞገስ በመወደስ ፈንታ
መቀመጥ እንድችል ከመዋረድ ተርታ
ስድብን እየሰማሁ ያላንዳች ሁካታ
ለመቆም እንድችል ልቤ ሳይረታ
ምናል ብታስተምረኝ/2/ ብታስችለኝ ጌታ/2/
አዝ

ለኔም አስተምረኝ ባላጠፋት ጥፋት
በጸጋ መቀበል የአይሁድን ጥፋት
እንዴት እንደሚቻል ሳያጉረመርሙ
ንገረኝ ጌታዬ ይረዳኝ ትርጉሙ
ምናል ብታስተምረኝ/2/ ብታስችለኝ ጌታ/2/
አዝ

የመናቅን ጥበብ የውርደትን ዘዴ
እባክህ አስረዳኝ አስተምረኝ አንዴ
ብኤል ዜቡል ተብለህ ያልተበሳጨኸው
የሀጢያተኞች ወዳጅ መባል ያልጠላኸው
ጋኔን ይዞታልን የሰማህ በጸጋ
ለኔም አስተምረኝ /2/በቂም አልዋጋ/2/
አዝ

አልወጋ እባክህ በመራርነት ጦር
በቁጣ ጥላቻ ነፍሴ አትሰበር
እንዴት ነበር ያኔ የይሁዳን እግር
ዝቅ ብለህ ያጠብከው ስታውቅ ሁሉን ነገር
ለእኔም አስተምረኝ/2/ ብዙ ሳልናገር/2/
አዝ

በችንካር ተጣብቀህ ከመስቀሉ ጋራ
የደምህ ነጠብጣብ ገና ሳያባራ
አያውቁትምና የሚያደርጉትን
ይቅርታ የለመንክ ላጠጡህ ሐሞትን
ምናል ብታስተምረኝ/2/ እንዲህ ያለ ሕይወትን/2/
አዝ

አሁን ምንቸገረህ ብትሰጠኝ ለአንድ አፍታ
የትህትናን ቀሚስ የትዕግስትን ጉታ
እያየህ አይደል ወይ ነፍሴ እንዲ ተራቁታ
የመሰደብን ዘውድ የመናቅን ካባ
ምናለ ብትኖር/2/ ይህቺ ልቤ ደርባ/2/
አዝ

ትዕቢት ለተሞላው ላትንኩኝ ባይ ልቤ
ለክብሩ ለሚኖር ለኮርማው ሀሳቤ
ምናል ብትቀባው የትህትናን ሽቶ
እንደዚህ ከሚኖር ሸቶ ተበላሽቶ
ኧረ እኔስ አልቻልኩም አቅቶኛል በጣም
ስድብንም መቀበል ሀሜትንም ማጣጣም
ስተርከው እንጂ ስኖረው አቃተኝ
ይህን መራር ኑሮ አንተው ይዘህ ጋተኝ/2/

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ሥላሴ ትትረመም | ዘማሪ ዲያቆን ፍሬዘር ደሳለኝ

ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር
ሥላሴ ትትረመም ወትትነከር /2/
አዝ

ይገባል ምስጋና ይገባል ውዳሴ
ሁሉን ለፈጠረ ለቅድስት ሥላሴ
ከዘመናት በፊት ቀድሞ የነበረ
ፍጥረትን በሙሉ ለክብሩ ፈጠረ
አዝ

ልበል ሃሌ ሉያ ኪሩቤልን ልምሰል
በእግረ ምስጋና ያሬድን ልከተል
ላቅርብ ምስጋናውን ዘምስለ ሱራፌል
ውዳሴ ምስጋና ነውና ለልዑል
አዝ

በስም ሦስት ሲሆን እንዲሁም በአካል
በግብርም ሦስት ነው ያለመቀላቀል
ፍጥረትን በመፍጠር በአምላክነት
በባሕሪይ እና ደግሞም በመንግሥት
አንድ አምላክ ነው እንጂ አይባልም ሦስት
አዝ

በኪሩቤል ጀርባ ዙፋኑን ዘርግቶ
ክብሩን ጌትነቱን ከፍጥረት ለይቶ
ይኖራል ዘለዓለም በመንግሥቱ ጸንቶ/2/
አዝ

ይመስክር ዮርዳኖስ ይናገር ታቦር
የአምላክ ጌትነት የሥላሴን ክብር
ይኸው በዮርዳኖስ ወልድ ተገለጠ 
መንፈስ ቅዱስ ታየ አብም ቃሉን ሰጠ

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ባለውለታዬ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

ባለውለታዬ /2/ ከአመድ ያነሳኸኝ
ከትብያ ተጥዬ ተመስገን ጌታዬ
አዝ

በሩን ቢዘጋብኝ ስምኦን ጨክኖ
ዝቅ አድርጎ ቢያየኝ ከአይሁድ ጋር ሆኖ
እንድቀርብ ወደ እርሱ አዘዘ ጌታዬ
እግሩን አጥበዋለሁ ወድቄ በእንባዬ
አዝ

የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
መዓረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በየሱስ ክርስቶስ
አዝ

ድንጋይ የጨበጡ ፈራጆች ከበዉኝ
ነውሬን ዘርዝረው ጌታ ፊት አቆሙኝ
ፈረደችባቸው ሃጢያትም በነርሱ
በሰላም ሂድ ብሎ ምሮኛል ንጉሱ
አዝ

የማምነውን አምላክ አውቀዋለሁ እኔ
በሰራልኝ ስራ በእድሜ በዘመኔ
ፍቅሩን ተሸክሟል የልቤ ትከሻ
ልለየው አልችልም እስከመጨረሻ
አዝ

የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
መዓረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በየሱስ ክርስቶስ

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


እንግዲህ ምን ልበል | ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

እንግዲህ ምን ልበል
እንግዲህ ምን ላውራ
እጄን በአፌ አስጫነኝ
የአማኑኤል ስራ
አዝ

በሞት ጥላ ምድር ያሳለፈኝ መርቶ
ደግሞም ዛሬ አነሣኝ በልጁ ሞት ጠርቶ
ክብሬን ለማይረባ ነገር አልለውጥም
ከአመድ ስላነሳኝ ክብሩ ለዘለዓለም
አዝ

የሺሖርን ውኃ ለምን እጠጣለሁ
ፊቴን የማዞረው ምን አግኝቼበት ነው
ሁልጊዜ እየራራ ሳይዘነጋኝ ላፍታ
እኔ የዓይኑ ስስት እርሱ የኔ ርካታ
አዝ

ስለምን ሆምጣጣ ፍሬ አፈራ ብለህ
እኔ አልተነቀልኩም ስለፍጹም ፍቅርህ
ቢቀላ እንዳለላ ነጣ እንደባዘቶ
የተከፋው ልቤ ሄደ ተደስቶ
አዝ

ከወዜ ላይ ቀለብ ምናልባት ቢሰፍሩ
ወራቶቼ እንባን መከራን ቢያዘሩ
ልቤን ያስነከሰው ያ ቀን አለፈና
የበፍታዬን ኤፋድ ለበስኩ እንደገና

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ያላንተ ለኔ ማን ሊሆነኝ | ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

ያላንተ ለኔ ማን ሊሆነኝ
ጌታ ሆይ ፍቅርህ ልቤን ነካኝ
ህግህ ነበረ ያፌ መፍቻ
የማትቀየር አንተ ብቻ/2/
አዝ

አስተምርበት በመርከቤ
ቃልህን ብቻ ያድምጥ ልቤ
ቀኑም ቢገፋ ወደ ማታ
አሳው ታዘዘ ላንተ ጌታ
አዝ

ውዴ ልበልህ ሽልማቴ
ቤቴም ያንተ ነው ሰውነቴ
ደለደልክልኝ ያንን ጋራ
እንዳልሞት አርገኝ እንዳልፈራ
አዝ

ፀፀተኝ ዛሬ ያኛው ወራት
አንተን ሳላውቅህ የኖርኩበት
ፍቅር ነህ ለካ ማር ወለላ
ምን ህይወት አለ ካንተ ሌላ
አዝ

ቀፃፍያችንን ቀፅፈኸዋል
ያንን ጭንቁን ቀን አልፈነዋል
ነገም ያንተ ነው አዲሱ ቀን
እንዘምራለን ስትናፍቀን

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ስምሽን ለልጅ ልጅ እነግራለሁ | ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

ስምሽን ለልጅ ልጅ እነግራለሁ
እናቴ በምልጃሽ ሰው ሆኛለሁ
እመቤቴ ስልሽ ነይልኝ
ማዕበል ሳይነቅለኝ
አዝ

እመቤቴ ብዬ ስምሽን መጥራቴ
ቢራቆትብኝ ነው ባዶ ቢሆን ቤቴ
አይኖቼን ከእንባ ከለቅሶ ከልክይ
ልብሽ ይራራልኝ ወደኔ አዘንብይ
አዝ

ባህሩም ቢሞላ አምናለሁ በልጅሽ
አንገት አያስደፋም እናቴ ጸሎትሽ
ስምሽን ስጠራ እጆቼን ዘርግቼ
ቀስታቸውን ሁሉ ጣሉ ጠላቾቼ
አዝ

ሰላም አለኝ አሁን ይህንን አውቃለሁ
እጅግ ብዙ ነገር በአንቺ አግኝቻለሁ
ማድጋዬ ሞልቶ አለም ተመልክቷል
ምድረ በዳው ልቤ በጸሎትሽ ረክቶል
አዝ

ባህሩም ቢሞላ አምናለሁ በልጅሽ
አንገት አያስደፍም እናቴ ጸሎትሽ
ስምሽን ስጠራ እጆቼን ዘርግቼ
ቀስታቸውን ሁሉ ጣሉ ጠላቶቼ

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


የአንተ ሥራ | ሊቀ-መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

የአንተ ሥራ የአንተ ሥራ /2/
የአንተ ሥራ ለዓለም ይወራ
አዝ

በዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ አምስት
መጻጉዕ ተብሎ ተኝቶ ባራት
ዘመን ያስቆጠረ ሠላሳ ስምንት
ተነሳ ተባለ አገኘ ምህረት
አዝ

ሰውነቱ ደቆ እጅግ የታመመ/2/
በሱ ድንቅ ስራ አልጋ ተሸከመ/2/
አዝ

ወገን ያልነበረው ወድቆ የተረሳ/2/
ምህረት አገኘ እና በድንገት ተነሳ/2/
አዝ

ያዳነው ኢየሱስ መሆኑን ሲናገር
ያልተፈቀደውን ይሄው ሰንበት ሲሽር
አየነው ሰማነው አያሻም ምስክር
ብለው ተነሱበት በጠማማ ምክር

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ያዕቆብ ከቤርሳቤህ | ሊቀ-መዘምራን ይልማ ኃይሉ

ያዕቆብ ከቤርሳቤህ ወደካራን ሲሄድ
የለውም ነበረ አማካሪ ዘመድ
ፀሐይ ጠልቃ ነበር ከዛ እንደደረሰ
ከእራሱ በታች ድንጋይ ተንተራሰ
አዝ

ህልምንም አለመ ታላቁን እራእይ
መሠላል ተተክሎ ከምድር እስከ ሠማይ
ሲወጡ ሲወርዱ መላእክት በርሷ ላይ
እግዚአብሔርም ቆሞ ከላይ ከጫፏ ላይ
አዝ

ያባቶችህ አምላክ እኔ እግዚአብሔር ነኝ
ይህን ምድር ለእርስትህ እሰጥሀለውኝ
ዘርህ እንደ አሸዋ በምድር ይዘራል
በአራቱ ማእዘን ህዝብህም ይሆናል
አዝ

አበው በምሳሌ እንደ ተናገሩት
ከምድር እስከ ሰማይ አምላክ የዘረጋ
በላይዋ ተቀምጦ በግልፅ የታየባት
የያእቆብ መሰላል እመቤታችን ናት
አዝ

ሰማይና ምድር የሚታረቁባት
ወልድ እጓለመሕያው የተወለደበት
መላእክት ከሰማይ ባንድ የዘመሩላት
ታላቋ መሰላል እመቤታችን ናት

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ጥሩልኝ ዳዊትን | ዘማሪ አቤል ተስፋዬ

ጥሩልኝ ዳዊትን በገናውን ያምጣ
መንፈስ አስጨንቆት ሳኦል ስለመጣ /2/
አዝ

ምድር ግብሯን ትታ ሕግ እያፈረሰች
የሳኦልን መንገድ ስለ ተከተለች
ከህልም አለም ቅዠት እንድትረጋጋ
ያን ዳዊትን ጥሩት ይደርድር በገና
አዝ

የእርኩሰትን ሥራ ዓለም ስላበዛች
ያልተፈቀደውን ምርኮን ስለያዘች
በዝማሬው ጸጋ ፈውስን እንድታገኝ
ጥሩልኝ ዳዊትን በበገና ይቃኝ
አዝ

የአባቶቹን ትዕዛዝ መንገድ ስለሳተ
ፀያፍ የሆነውን ሕጉን ስለሻተ
ለንስሐ ደርሶ መንግስት እንዲቀና
ጥሩልኝ ያን ዳዊት ይደርድር በገና
አዝ

መለያየት በዝቶ ፍቅር ስለራቃት
ስላቀረቀረች መከራው ጸንቶባት
በጥልቁ ዝማሬ ምሕረትን እንድታይ
ዳዊት ይነሳና በበገና ይጸልይ
ዳዊት ይነሳና በበገና ትቃኝ

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ሥላሴን ከሰማይ እስጢፋኖስ አይቶ | ሊቀ-መዘምራን ይልማ ኃይሉ

ሥላሴን ከሰማይ እስጢፋኖስ አይቶ
ዓይኑ በመገረም ቀረ ተሰክቶ
የድንጋይ ናዳ ቢወርድበት እንኳ
ሥላሴን በማየት እረስቶታል ለካ
ስብሐት ለእግዚአብሔር
አዝ

የሰው ልጅ በቀኙ ተቀምጦ ነበር
እስጢፋኖስ ሲያየው በሚያስፈራ ክብር
ካህናተ ሰማይ ዙፋኑን ከበውት
ቅዱስ ቅዱስ ሲሉ ስብሐት ስብሐት
ስብሐት ለእግዚአብሔር
አዝ

ምሥጢረ ሥጋዌ ተገልጾለት በአካል
ሥጋው ቢታመምም ሐዘኑን ሽሮታል
ነፍሱ ከጸባኦት ስታመሰጥር
ድንጋይ ይለቅማሉ ያልታደሉ በምድር
ስብሐት ለእግዚአብሔር
አዝ

ለፈሪሳውያን ተሰውሮባቸው የሥላሴ ምሥጢር
ድንጋይ ሰበሰቡ ጻድቁን ለመውገር
እርሱ ግን ከሰማይ ፈጣሪውን አይቶ
ድንጋዩን እረሳው ህሊናው ተነክቶ
ስብሐት ለእግዚአብሔር
አዝ

የሰማዩ ሥርዓት ልዩ ስለነበር
ምንም አልመሰለው የድንጋዩ ክምር
የፍጥረታ ሁሉ ፈጣሪ ተገልጠው
ስቃዩን አስረሱት ህሊናውን ፍቀው
ስብሐት ለእግዚአብሔር
አዝ

ልባችሁ ጆሮአችሁ መቼ ተገረዘ
የጠነከረ ነው ለአምላክ ያልታዘዘ
መንፈስ ቅዱስን ትቃወማላችሁ
እንደገዛ ፍቃድ እየተመራችሁ
ስብሐት ለእግዚአብሔር

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


በስራዬ የት ይሆን መግቢያዬ | ሊቀ-መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

በሥራዬ የት ይሆን መግቢያዬ /4/
ጨነቀኝ ጠበበኝ/ከበደኝ/ ነፍሴ ወዲያልኝ /2/
አዝ

ተሸክሜ የኃጢአት ክምር /2/
ይመሻል ይነጋል በከንቱ ስዞር /2/
ገሰገሰ ቀኑ ጨለመብኝ /2/
ዋ ለነፍሴ ምንም ስንቅ አልያዝኩኝ /2/
አዝ

በድያለሁ ወዳንተ እጮሃለሁ
ይቅር በለኝ እማፀንሃለሁ
ችላ አትበለኝ ከፊትህ ቆሜአለሁ /2/
አዝ

አለፈብኝ በከንቱ ጊዜዬ /2/
እየጓጓሁ ለዚች ለሥጋዬ /2/
በንስሐ ሳላጥበው እድፌን /4/
ልትደርስ ነው ያች ፈተና ቀን /2/

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ለዚህም መልስ አለው | ዘማሪ ዲያቆን ናትናኤል ሳሙኤል

ለዚህም መልስ አለው
እግዚአብሔር መልስ አለው
ለተዘጋበት ሰው እግዚአብሔር በር አለው
ለልቤ ጥያቄ ውስጤን ላስጨነቀው
ይዘገያል እንጂ እግዚአብሔር መልስ አለው
አዝ

ከዚህ የበለጠ ፈተና አይቻለሁ
እግዚአብሔርን ይዤ ተሻግሬዋለሁ
አልቀሰቅሰውም ልጠፋ ነው ብዬ
ወጀቡን ያዘዋል ማዕበሉን ጌታዬ/2/
አዝ

እንኳን ከመከራ ያስመልጣል ከሞት
ካሳ ሆድ ሸሽጎ ያተርፋል ከመዓት
ይታመናል እርሱ ይታመናል ጌታ
እምነቴን ሊያየው ነው ማብዛቱ ዝምታ/2/
አዝ

አዲስ እየሆነ ቢከብድም ለጊዜው
ካሳለፍኩት ችግር አይበልጥም ይሄኛው
እጠይቀዋለው ደግሞ እንደትላንቱ
ትቶኛል አልልም አውጥቶኝ ከስንቱ/2/
አዝ

ተጨነኩኝ እንጂ መስሎኝ የማላልፈው
የዛሬው ለቅሶዬ ነገ ዝማሬዬ ነው
የማያልቀው ተስፋ ይመጣል አይቀርም
በጌታዬ ስራ አላጉረመረምም/2/

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ዘግይተህ አይደለም | ሊቀ ዲያቆናት ነብዩ ሳሙኤል

ዘግይተህ አይደለም እኔ ቸኩዬ ነው
በነጋ በጠባ ስምክን የማማርረው
የሚያስፈልገኝን አንተ ቀድመህ አውቀህ/2/
ሁሉንም በጊዜው ታደርግልኛለህ/2/
አዝ

መዝጊያ ምታ ይከፈታል
ስትጠይቅ ሁሉ ይሆናል
ብለህ ያልከኝ አለኝ ኪዳን
የማይሻር በየዘመን
ፈቃድህ ይደረግ አምላኬ አንተ ያልከው
አላማህ በእኔ ላይ አምናለሁ ፍቅር ነው
አዝ

ሰጥተኸኛል ድንቅ ውለታ
ልቤ ረስቶት ያን ስጦታ
ባህር ስትከፍል በአይኔ እያየሁ
እንዳላየ እሆናለሁ
ፈቃድህ ይደረግ አምላኬ አንተ ያልከው
አላማህ በእኔ ላይ አምናለሁ ፍቅር ነው
አዝ

መመኪያ ነህ ከአባት በላይ
የማትከዳ የማትለይ
ዛሬ ባይሆን ልጠይቀው
ጌታዬ ሆይ ለጥቅሜ ነው
ፈቃድህ ይደረግ አምላኬ አንተ ያልከው
አላማህ በእኔ ላይ አምናለሁ ፍቅር ነው
አዝ

ትሰማለህ ቸል ሳትል
ትሰጣለህ ሳትከለክል
የማትነፍገው ባለጸጋ
የገዛኸኝ በደም ዋጋ
ፈቃድህ ይደረግ አምላኬ አንተ ያልከው
አላማህ በእኔ ላይ አምናለሁ ፍቅር ነው

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ድንግል ሐረገወይን | የአእላፋት ዝማሬ

እንተ በምድር ሥረዊሃ ወበሰማይ አዕጹቂሃ /2/ ሐረገወይን /2/ ድንግል ሐረገወይን

ሥሮችዋ በምድር ጫፎችዋ በሰማይ የሆነ የወይን ሐረግ ድንግል ማርያም ናት

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


እመ አምላክ | ሊቀ-መዘምራን ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

እመ አምላክ /2/
አስቢኝ በሰርክ
አዝ

ሃዘኔ ጭንቀቴ በጣም በዛብኝ
ከልጅሽ አማልጅኝ አንቺው አስታርቂኝ
ከመንበሩ ቆመሽ ንገሪው ለልጅሽ
እናቱ ነሽና እሱ አያሳፍርሽ
አዝ

እኔ ኃጥያተኛው በደሌን አውቃለው
ምርኩዜ ነሽና እከተልሻለው
መንገዱ ጠፍቶብኝ የጽድቁ ጎዳና
መብራቱን አብሪልኝ እመጣለሁና
አዝ

መመገብ ይቅርብኝ አልራብምና
ስምሽን ስጠራ እጠግባለውና
አበው ሊቃውንቱ በአንቺ ይመካሉ
እመ አምላክ እያሉ ስምሽን ይጠራሉ
አዝ

ከገሃነም አውጭኝ ከዚያ ነበልባል
ከሲዖል ወድቄ እንዳልቃጠል
ያ የስቃይ ሃገር ባህሩ ያሰጥመኛል
አንቺ ከለመንሽው ልጅሽ ያዝንልኛል
አዝ

ወገን አታድርጊኝ ከሲዖል ከተማ
መድረሻ አያሳጣኝ የእሳቱ ጨለማ
አወድስሻለው በኤፍሬም ውዳሴ
ሁኝልኝ ጠበቃ አደራ ለነፍሴ
አዝ

እኔስ እፈራለው ምግባሬን ሳየው
ደካማው እምነቴ እየለየኝ ነው
አልረሳሽም ድንግል እማጸንሻለው
አማላጅነትሸ መድኅን ነው አውቃለው

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


በምሕረትህ ብዛት | ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት
እኔ ግን በይቅርታህ ብዛት
ወደ ቤትህ እገባለሁ
አመልክሃለው እዘምርልሃለሁ
አዝ

በሕይወቴ ዘመን አንዲት ነገር ሻትኩኝ
በቤትህ ተጥዬ መኖሬን መረጥኩኝ
ከኃጢአት ድንኳን የአንተን ደጅ ይሻላል
እረፍቴ ጌታዬ እቅፍህ ይሞቃል/2/
አዝ

የክብርህን ሥፍራ ማደርያ ወደድኩት
መቅደስህ ቀደሰኝ ዙፋኔን ጠላሁት
ከዚህች ለምለም ስፍራ ወዴት እወጣለሁ
የተሰበረ ልብ ይዤልህ እመጣለሁ
አዝ

በመከራዬ ቀን የተናገርኩትን
ከደጅህ መጥቼ ከንፈሮቼ ያሉትን
ስዕለቴን ልፈፅም ማልጄ እነሣለሁ
የአምልኮ መስዋዕቴን እሰዋልሃለው/2/
አዝ

እንደ ሰብአ ሰገል ይዤ ወርቅ ዕጣኔን
አምሃ አኮቴት መባዬን ከርቤዬን
ልቤን እየሰዋው እሰግድልሃለው
ኦሜጋ አልፋ ነህ እቀኝልሀለው

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


ይቅር ስላልከኝ | ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ

ይቅር ስላልከኝ ነው የእኔ መቆም
ደግሞ እንዳልፈርድ እርዳኝ/2/ በሰዎች ድካም
አዝ

ለዛሬ መድረሴ አይደል በጽድቄ
እያነሳኸኝ ነው አይተህ ውድቄ
በፈረድኩበት ፍርድ እንዳይፈረድ
አልሁን ፈሪሳዊ ወንድሜን ልውደድ
ጉዱፉን አልይ የወንድሜን በደል
አለ በእኔ ላይ ምሰሶን የሚያህል/2/
አዝ

ባታለብሰኝ ኖሮ ነውሬን ሸፍነህ
ባታቆመኝ ኖሮ በደሌን ከድነህ
በጠፋ ነበር ስም አጠራሬ
ድካሜ ብዙ ነው እንደ ራስ ፀጉሬ
ጉዱፉን አልይ የወንድሜን በደል
አለ በእኔ ላይ ምሰሶን የሚያህል/2/
አዝ

በምሕረትህ ብዛት ከቤትህ ልግባ
ዘወትር ላቅርብልህ የእንባዬን መባ
የውስጤን ማንነት ላንተ ልግለጥ
ለሰው አሳልፈህ ለማትሰጥ
ጉዱፉን አልይ የወንድሜን በደል
አለ በእኔ ላይ ምሰሶን የሚያህል/2/
አዝ

ዕለት ዕለት ግብሬ ኃጢአት መስራት ነው
አንተም ዕለት ዕለት እኔን መማር ነው
የበደለን መተው ያንተ ነውና
በወንድሜ መማር ቆሜ አልቅና
ጉዱፉን አልይ የወንድሜን በደል
አለ በእኔ ላይ ምሰሶን የሚያህል/2/

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All


በፍቅር ላዚምህ | ሊቀ-መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ

በፍቅር ላዚምህ ፍቅር ነህ ጌታዬ
በደም የገዛኸኝ ባለውለታዬ
በቃዬል ጎዳና እንዳልጓዝ እርዳኝ
በቀናው መንፈስህ ወደፅድቅህ ምራኝ
አዝ

በልቤ ትከሻ በቀል ተሸክሜ
ወንድሜን ጠልቼ ካንተ ፊት መቆሜ
ፃድቅ ቢያስመስለኝ በሰዎች እይታ
ጉዴን ስለምታውቅ እስራቴን ፍታ/2/
አዝ

ዙሪያውን ተከቦ በእሾህ ጥላቻ
ስብከቴ መዝሙሬ ሆኗል የቃል ብቻ
ማረኝና ይብቃኝ ለሀጢያት መዝመቱ
ፍቅር የሌለው ሰው ነው የከንቱ ከንቱ/2/
አዝ

አሸንፈህልኝ እኔ ግን ተሸነፍኩ
በእጅ የማልነካውን ለሰው እያሸከምኩ
በቃሌ ጠርቼ በግብሬ ረገምኩህ
በአስመሳይ ማንነት እየሸነገልኩህ/2/
አዝ

ዙሪያዉን ተከቦ በእሾህ ጥላቻ
ስብከቴ መዝሙሬ ሆኗል የቃል ብቻ
ማረኝና ይብቃኝ ለኃጢያት መዝመቱ
ፍቅር የሌለው ሰው ነው የከንቱ ከንቱ/2/

@Orthodox_Mezmur_For_All
@Orthodox_Mezmur_For_All

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.