🌹#አባ_ሕርያቆስ 🌹
☞ወር በገባ በ2 የእመቤታችን ወዳጅ የቅዳሴ ማርያም ደራሲ የአባ ሕርያቆስ ወርሐዊ መታሰቢያው ነው፡፡ ሕርያቆስ ማለት ኅሩይ ረቂቅ ፀሓይ ብርሃን ማለት ነው፡፡ሀገሩ በብህንሳ ነው፡፡ በ10'000 መነኮሳት ላይ ተሹሟል፡፡ግብረ ገብ ነውናሥርዐት ያጸናባቸዋል፡፡ ነገር ግን ያልተማረ ነውና ይንቁታል፡፡ እሱ ግን እንደ ጠሉኝልጥላቸው እንደ ናቁኝ ልናቃቸው ሳይል በፍቅር በትሕትና ጸንቶ ያስተምራቸውጀመረ፡
፡
☞ከዕለታት አንድ ቀን በምን ምክንያት እንሻረው ብለው መከሩ፡፡ ቅዳሴ ቀድሰኽ
አቁረበን ብለን የሚያስቸግር ቅዳሴ ሰጥተን በዚህ ምክንያት እንሽረዋለን ብለው
ወሰኑ፡፡
☞እሱ ግን እንደ ቅዱስ ኤፍሬም የእመቤቴ ምስጋና እንደ ባሕር አሸዋ በዝቶልኝ
እንደ ልብስ ለብሼው እንደ ምግብ ተመግቤዎ እንደ ውሃ ጠጥቼው እያለ ይመኝ
ነበርና ሥርዐቱን ጨርሶ ፍሬ ቅዳሴ ሲደርስ ከሊቃውንት የሚያስቸግር እያሉ
ሲያወጡ ሲያወርዱ ጉሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ ብሎ ወይእዜኒ ንስብሖ እስከ
ሚለው ድረስ ሰተት አድርጎ ተናግሮታል፡፡
☞የሚጠሉትና የሚንቁት የነገሩትን አከናውኖ መናገር የማይችል ዛሬስ እንግዳ
ድርሰት እደርሳለኹ ብሎ እንዳገኘ ይቀባጥራል ብለው አቃለሉበት፡፡
☞የሚወዱትና የሚያከብሩት ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ ካልኾነ ከዕሩቅ ብእሲ
እንዲኽ ያለ ምስጢር አይገኝም በማለት ጽፈው ደጉሰው ከውሃ ቢጥሉትብራናው
ሳይፋቅ ከእሳትቢጥሉት ሳይቃጠል ወጣ፡፡ ከሕሙማን ላይ ቢጥሉት ድውይ
ፈወሰ፡፡ የበለጠ ደግሞ ሙት አስነሳ፡፡
☞ይህስ ደግ ድርሰት ነው ብለው ከቅዳሴ ድረስት መካከል 14ኛ አድርገው
ጠርዘውታል፡፡፡፡
☞አባ ሕርያቆስ ተሹሞ ሳለ ብዙ ድርሰት ብዘ ተግሣፅ ጽፏል፡፡ ከብዙም ቅዳሴ
ማርያምና ላሐ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡
☞እመቤታችን ቅዱስ ኤፍሬምን ከሶርያ አንተ ውዳሴዬን አባ ሕርያቆስን ከብሕንሳ በደመና ነጥቃ አንተ ቅዳሴን ንገሩት ብላ ቅዱስ ያሬድ በዜማ ደረሶላቸዋል፡፡
☞የቅዱስ አባ ሕርያቆስ ድርሰት የሆነው ከ14
ቅዳሴ አንዱ የሆነው" ቅዳሴ ማርያም" ብለው ሰየሙት፡፡
☞(ከመድብለ ታሪክ መጻሐፍ የተወሰደ)
☞ለአባ ሕርያቆስ፤ለቅዱስ ኤፍሬም፤ለቅዱስ ያሬድ፤ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
የተመነች ለእኛም ትለመነን፡፡ ማስተዋሉን ታድለን፡
☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc