ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ ቻናል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማንና ቀኖናን ትውፊትን እንዲሁም አስተምሮን የጠበቁ የተለያዩ የሚያስተምሩ ነገሮች ይለቀቁበታ፡፡ በተጨማሪ በ youtube #subscribe በማድረግ አገለግሎቱን ይደግፉ።
‹‹ከትውልዱ ማን አስተዋለ››
ት.ኢሳ 58÷3
https://youtu.be/csxxAMGtC4I
ለመቀላቀል
http://t.me/ortodoxtewahedo

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri




ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስንት መልእክታትን ጽፏል ?




ይድረስ ለእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ★

★ እናንተ ቤት የምትለኩሱትን እሳት እንዴት ታዩታላቹ ?

★ሼር በማድረግ አድርሷቸው ★

ሰሞኑን በቲክቶክ ፕላቶ ፎርም በእስልምናና በክርስትና መጻሕፍት ዙሪያ በሚወያዩ ወጣቶች የተነሱ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ ከሙስሊም ወገኖች ለምን ተጠየቅን በሚል ግልፍተኝነት ጉዳዩን ከቲክቶክ ወደ ተቋማዊ ጉዳይ ከፍ አድርገውታል እኛ ዝምያልነው የቲክቶክ ጉዳይ ነው ብለን ነበር።እናንተ በተቋም ደረጃ ካመጣችሁት እኛም ጥያቄ አለን።

‎አንዳንድ ኢስላም ወንድሞችና ኡዝታዞች ክርስትናን በኢስላሞች ዘንድ የተጠላ ለማድረግ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖችን ወደ እስልምና ለመውሰድ በርካታ ክብረ ነክ መፅሐፍትን ጽፈዋል፣ እየፃፉም ይገኛሉ።

‎ክርስትናን ከእስልምና እያነጻፀሩ እጅግ በሚያስነውር መልኩ ከሚጽፉትና የክርስቶስን አምላክነት ከሚፃረሩት መካከል ቀዳሚዎቹ ቀመር ሁሴንና ኡዝታዝ አቡ ሃይደር ይጠቀሳሉ። አቡ ሃይደር "ላለመደናገር ማመሳከር" በሚል መጽሐፉ ክርስትናን በማጥላላት፣ ክርስቶስን ፍጡር በማድረግ ነውረኛ ጽሑፍ ፅፏል። በየዩቲዩብ የሚናገረው ፀባ ጫሪ ንግግሩና ደም አፋሳሽ የሽብር መልዕክቱ በስፋት ተሰራጭቷል።

‎ሸይኽ ሐሰን ታጁ "ሰይፉን ፍለጋ" እና "የኀመረ-ኖህ ቅጥፈት በእስልምና እውነት" የሚሉ ድርሰቶችን በመፃፍ በክርስትናውና እስልምናው መካከል ልዩነቶች እንዲሰፉና መከባበር እንዲያከትምለት የድርሻውን አበርክቷል። አሁንም ድረስ ለስሙ አምባሳደር ተብሎ ተቀምጦ ከፍተኛ የሽብር ተግባራትን ውስጥ ለውስጥ እንደሚሰራ ተደርሶበታል።የመንግስትን ፓሊስ ከማስፈጸምና ሃገራዊ ሥራዎችን ከመሥራት ይልቅ ጽንፈኝነት በማባባስና የሽብር ወላፈን በማቀጣጠል የተጠመደ መሰሪ ሰው በመሆኑ መንግሥት እርምጃ ውሳኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል።

‎ዶ/ር እንድሪስ የተባለ ሰውም የቁራኑ ኢሳና የመጽሐፍ ቅዱሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የተለያዩ ቢሆኑም "ኢየሱስ የኢስላም ነቢይ" የሚል ክብረ ነክ መፅሀፍ አሳትሞ አሰራጭቷል። በክርስቲያኖችና በሙስሊሞች መካከል ከፍተኛ ፀብ፣ጥላቻ፣አምቧጓሮ እንዲፈጠር አድርጓል።

‎አሁን ላይ በክርስቲያኖችና ኢስላሞች መካከል ሰፋፊ የመለያያ አጥሮች በማስቀመጥና ከፍተኛ የጥላቻ መርዝ በመርጨት የሚታወቀው አህመዲን ጀበልም "303 ጥያቄዎች ለክርስቲያኖች" የሚል ድርሰት ፅፎ ተገቢው መልስ ተሰጥቶታል። ዋሂድ እና ኤልያህ እንዲሁም ሰልማን የተባሉ አክቲቪስቶችም የየራሳቸውን መጽሐፍ ፃፉ ርካሽ የሆኑ ቃላትን በመጠቀም ከፍተኛ ደም አፋሳሽ ቅስቀሳዎችን አደረጉ ።

‎እኒህ ከላይ የጠቀስናቸው ግለሰቦችና መጻሕፍት ክርስትናን ለማጥላላት፣ክርስቲያኖች ላይ ግድያ ለማምጣት የተጻፉና የሰበኩ ናቸው። በስብከት ደረጃ ደግሞ እጅግ ብዙ ኡዝታዞችንና አክቲቪስቶችን መጠቃቀስ ይቻላል። ለዓመታት ደም ደም የሚል ንግግሮችንና ፀባ ጫሪ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ ቆይተዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ክርስቲያኖች በመጽሐፍትም በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችም ለተነሱ ጥያቄዎች በራሳቸው ድንበር ላይ ሆነው በቂ ምላሽና ማብራሪያ ከመስጠት በስተቀር እስልምናን የሚነካ አንዳች ነገር አልተናገሩም።

‎ አክራሪዎች የፃፏቸው መጽሐፍትም ሆኑ ድርሰቶች በሙስሊሞችና በሌላው እምነት ዙሪያ ያስገኙት ጥቅም የለም። ይልቁንም የመለያያ ድልድይ ሰሩ እንጂ። በሁለቱም ዘንድ የነበረው ጥላቻ እጅግ እንዲያይል እና ሁሉም ራሱን ከመከላከል ወጥቶ ወደ ማጥቃት እንዲሸጋገር በር ከፍቷል።

‎አክራሪ ፀሐፍት ያስገኙት ጥቅም ቢኖር ክርስቲያኖች እምነታቸው ላይ እንዲጣበቁና እንዲያውቁ ብቻ ነው። ሃይማኖት ለማስለወጥ የተፃፉ የጥላቻ መጽሐፍት ሃይማኖትን አጥብቆ የሚይዝ ወጣት እንዲፈጠር፣ ሞጋችና ሌላውን ጠያቂ ክርስቲያን እንዲበዛ አድርገዋል።

‎የራሳቸውን እምነት በቅጡ ተርጉመው ያላስተማሩ አክራሪያን የማያውቁትንና በአግባቡ ያልተረዱትን መጽሐፍ ቅዱስ ሚሊየን ጊዜ ለማብራራት ሞክረው አልተሳካላቸውም። ክርስትናን ለቆ ኢስላም የሆነም በታሪክ አጋጣሚ አላገኙም።በገንዘብ እየተደለሉ ኑሮን ለማሸነፍ ሃይማኖቴን ለወጥኩ የሚሉት እነርሱ የድራማ ተዋናዮች ስለሆኑ በንቀት እናልፈዋለን።

‎አሁን ለፈተፈቱት ጉዳይ በልካቸው እየተሰፈረ ሲመለስላቸው እሪታና ዋይታ፣ ሰላማዊ ሰልፍና ዛቻ ጀመሩ። ምን ጠብቀው ኖሯል? ድሮ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ! ድንበር ዘለልነት የመጨረሻ ጣጣው ይህ ነው።

ሙስሊሞች አንድ እውነት ተረዱ ዘመኑ የዕውቀትና የመረጃ ዘመን ነው ወጣቱ ትውልድ ቁርዐኑንም ሆነ ሐዲሳቱን በሚገባው ቋንቋ እየተረጎመ መመርምር የሚችልበት ዘመን ላይ ነው ያለነው።ከራሳቹ መጽሐፍ ለምትጠየቁት ጥያቂ በቂና አሳማኝ መልስ መስጠት እንጂ ኡኡኡ ያዙኝ ልቀቁኝ የሚለው የሜዳ ላይ ጩኸት ጥያቄዎችን አያሳቆምም ትውልዱ ከእንግዲህ በአረብኛ ብቻ የተጻፈ ጽሑፍ አይቶ አሜን ብሎ አይቀመጥም በየቋንቋው ስለተተረጎሙ እያንዳንዱን መጽሐፍት እያራገፈ መጠየቁን ይቀጥላል።አንድ ግለሰብ ላይ ስትዘምቱ ሺዎች ተፈጥረው እንደሚያድሩ ዕወቁ።

ሼርና ታግ አድርጉላቸው

#followers

#highlight

👉 ለመቀላቀል

  @ortodoxtewahedo




የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የጥቃት ዓላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እንዲቆሙ ምእመናን ጠየቁ !

መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)

በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዒላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እና መልእክቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ እና መንግስትም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ቲኤምሲ ያነጋገራቸው ምእመናን ገልጸዋል።

ማናቸውም ቤተ እምነቶች መብቶቻቸው እንዲከበር እንደሚፈልጉትና የሃይማኖታቸውን አስተምህሮ በነጻነት ማስተላለፍ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪ ምእመናኑ በተመሳሳይም ሁሉም ቤተ እምነቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት እና አስተምህሮ ባከበረ መልኩ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነጻነታቸውን ተጠቅመው በማናቸውም መልኩ ሃይማኖታቸውን ማራመድ ሕገ መኖግስታዊ መብታቸው ቢሆንም የሌላውን እምነት ማንቋሸሽ፣ ማኮሰስ እና ማጥላላት ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እና ግጭት ቀስቃሽና ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ባለፉት ጊዜያት ከአንዳንድ ቤተ እምነት ተከታዮች ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ቅዱሳን፣ ስለ ንዋያተ ቅድሳት ብሎም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በምታስተምቸው ትምህርቶች ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች ሲተላለፉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።

በተለይም መዋቅራዊ ድጋፍ እየተሰጠው በሚመስል መልኩ የጥላቻ ንግግሮች ተባብሰው መቀጠላቸው እና ይኸው ጥላቻም በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ብቻ ሳይሆን በሜንስትሪም እና በመጽሐፍትም ጭምር ሲካሄድ መቆየቱ እና እየተካሄደ መሆኑ በርካታ ምእመናንን ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑ ተመላክቶአል።

መንግስት እነዚህን የጥላቻ አራማጆች እና ጸረ ሃይማኖት ግለሰቦችን በሕግ አግባብ እንዲጠይቅም ምእመናን ጥሪ አቅርበዋል።


💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕

[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛


🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧


መልካም ዜና ለአእላፍት ዝማሬ ቤተሰቦች ❤️‍🔥

የአእላፍት ዝማሬ መዝሙሮችን በነፃ የምታገኙበት አዲስ ቻናል ተገኝቷል፣ በቀላሉ ቻናሉን ለማግኘት 👇


የዐቢይ ጾም ጉዞ
           ክፍል 1  
Size:-103.3MB
Length:-1:51:39

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

👉 ለመቀላቀል

  @ortodoxtewahedo


እውነት ለመናገር እፎይን የጠራው ከአንደ አመት በፊት የስልጤ ሰማዕታት ደም ነው ። እኔ ደግሞ እፎይን በተከታታል ለ3 ወራት የሰራቸውን የንጽጽር ትምርት አይቻለው ብዙዎቹ ከበድ ያሉ እና መልስ የሚሰጥ ሰው መጥፋቱን አይቻለሁ አሁን ደግሞ በዛቻና በለመዱት መልኩ ዝም ለማስባል እየጣሩ ነው
በንጽጽር የሚሰሩትን ሁሉ እግዚአብሔር ይጠብቅልን 😍

👉 ለመቀላቀል

  @ortodoxtewahedo


👉 ለመቀላቀል

  @ortodoxtewahedo


ጠያቂው ተጠየቅ እንጂ…!

"…ክርስቶስ ማነው…? በሚል 303 ጥያቄዎች አሉኝ ብሎ እሱ በማያምንበት ለእኔ ግን ጌታዬ አምላኬና መድኃኒቴ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ጥያቄ አቅርቧል። በመጽሐፍ መልክም አሳትሟል። መልካም መብቱ ነው። አሕመዲን ጀበል በጌታ ላይ ተሳልቋል፣ በምስጢረ ሥላሴ ላይ አሹፏል፣ ቀልዷል ብለን ሰልፍ አልወጣንም። ይገደልም አላልንም።

"…አሕመዲን ጀበል በኢየሱስ ክርስቶስ ስለማያምን የፈለገውን የመጻፍ መብት አለው ከተባለ እፎይም ሆነ እኔ ስለማላምንበት ስለ መሀመድ ብጽፍ ለምን ትናደዳለህ? አንተ የእኔን በመናቅህ ዝም እንዳልኩህ እኔም የአንተን ስንቅ ዝም ማለት ነው እኮ ያለብህ። አንተ የእኔን ድንበር አልፈህ ለማዋረድ ስትሞክር እኔ በድንበሬ ላይ ቆሜ የአንተን ባዋርድ ለምንድነው ጎረቤት ሁላ እስኪረበሽ የምትንጫጫው። አንተ "ለነቢይህ" ፍቅር፣ አክብሮት፣ ውዴታ አለኝ ካልክ እኔ ለአምላኬና ለመድኃኒቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ ምንም ዓይነት ፍቅር፣ መስዋዕትነት የማልከፍል ይመስልሃል?

"…ንጽጽር ብለህ ያለ አቅምህ መጽሐፍ ቅዱስ ትንተና የጀመርከው አንተው ራስህ ነህ። አንተ የማታውቀውን መጽሐፍ ቅዱስ ገልጠህ ስትዳክር ዝም ብለን ቆይተን፣ መልስም ከዚያው ከመጽሐፍ ቅዱስ ስንሰጥህ ከርመን፣ አይ ቆይ እስኪ ለምን ደግሞ ከቁርዓኑና ከሐዲሱ መልስ አንጠይቃቸውም ብለን ስንነሣ ቆንጨራ ይዞ መፎከር ምን የሚሉት ነው? ወይ አስቀድሞ አለመፎከር፣ አቅምን ዐውቆ መኖርም ጥሩ ነው። ግጠመኝ ካልክ በኋላ አንተ በእኔ መጽሐፍ ቅዱስ ልትሞግተኝ ስትመጣ፣ እኔ ደግሞ በአንተው ቁርዓን ልሞግትህ ስነሣ የምን መነጫነጭ ነው?

"…በመስታወት ቤት የሚኖር ሰው የድንጋይ ውርወራ ጠብ ውስጥ ፈጽሞ አይገባም። ባለጊዜ ነን ተብሎ እንደ ሕጻን በልቅሶ፣ በጩኸት ፍላጎትን ለማሳካት መሯሯጥ ያስገምታል።

👉 ለመቀላቀል

  @ortodoxtewahedo




ካንቲባ አዳነች "ለመዘመር !" አልፈራችም እምነቷን ለመመስከር ወደኃላ አላለችም ፤ ምነው መምህር ስብከትህን ተውከው አገልግሎትህን ገፋኸው ፤ ባለስልጣን ሆኖ እኮ ኦርቶዶክስ መሆን ይቻላል።

ሌላ ምሳሌ ልስጥህ ቀዳማዊ እመቤትም "ዝማሬ !" አሳትማለች።ምነው እምነትህን ለመመስከር ወደኃላ አልክ።

እባክህ ለቤተክርስቲያን አገልግላት ፤ ንዋያቶችዋ ሲደፈሩ ዝም አትበል።

👉 ለመቀላቀል

  @ortodoxtewahedo


ፈጽሞ አትጨነቁ
             
Size:-123.5MB
Length:-1:41:49

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

👉 ለመቀላቀል

@ortodoxtewahedo


"ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው።"

#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

@ortodoxtewahedo


👉ምስባክ፦ “እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፡፡ ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፡፡ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡” ትርጉም “የቤትህ ቅንዓት በልቶኛልና፥ የሚሰድቡህም ስድብ በለዬ ወድቆአልና፡፡ ሰውነቴን በጾም አደከምኋት፡፡ (መዝ.፷፰፥፱)

በምሕረቱ ይታደገን፤ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፤ አሜን

"ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው።"

#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

@ortodoxtewahedo


#ምኵራብ

👉 የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት እንኳን አደረሳችሁ

“ቦአ ኢየሱስ ምኵራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት፤ አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት፤ እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኵራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤ የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው።” (ጾመ ድጓ)

በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሦስተኛውን የዐቢይ ጾም ሳምንት “ምኵራብ” ይባላል። ቀጥተኛ ፍቺው “ኮረብታ፣ ተራራ የሚያህል ታላቅ ሕንጻ፣ ሰቀላ መሰል አዳራሽ” ሲሆን፣ የአይሁድ መካነ ጸሎት ወይም ቤተ መቅደስ በመሆን ያገለግል ነበር። በብሉይ ኪዳን አይሁድ ቤተ መቅደስ ነበራቸው፡፡

ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተ መቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡን ወደ ባቢሎን አፈለሰ፤(፪ኛነገ.፳፬-፳፭፣ኤር.፬፥፯:፣፴፱፥፩-፲፣፶፪፥፩-፴) ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሠሩ ነበር፡፡ በዚያን ዘመን ቢያንስ ዐሥር አባ ወራዎች/የቤተ ሰብ ኃላፊዎች/ በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመሥራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ (Talmud Mishnah, Responsa literature, Jewish Encyclopedia, Academic Scholarly Works.) ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ግን ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ በሐዲስ ኪዳንም ለሐዋርያት በብዛት የስብከት ዓውደ ምሕረቶች ሆነው አገልግለዋል።

👉ምኵራበ አይሁድ በውስጡ የብራና የሕግ እና የነቢያት መጻሐፍት ይገኛሉ፡፡ ምእመኑ እንዲሰማቸው ከፍ ባለ መድረክ ላይ በመሆን መምህራንና ካህናት ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም ያስተምሩ ነበር። የምኵራብ ሹማምንት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሊቀጡ ሥልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር፣ በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትእዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡

በሰንበት ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስቦ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፣ ስብከትና ቡራኬ በመቀበል አምልኮታቸውን ይፈጽሙ ነበር፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምኵራብ ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ሉቃስ በወንጌሉ ”ወዳደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሣ” እንዳለ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ፣ መማር፣ መመርመር፣መተርጎም፣ጉባኤ መሥራት አዘውትረው የሚፈጽሙት ተግባር እንደነበር ያስረዳል።(ሉቃ.፬፡፥፲፮)

ነገር ግን በምኵራብ ሰዎች ለተለያየ ዓላማ ይሰበሰቡ ነበር፡፡

👉፩. አማናዊ እረኛ ነው ብለው፦ ወልድ ዋሕድ ብለው ሲጠብቁት የነበረው ተስፋ “ደረሰልን፤ ወረደ፤ ተወለደ፤ የዓለም መድኃኒት እርሱ ነው” ብለው አዳኝነቱን አምነው ይከተሉታል። “ነዋ በግዑ ለእግዚብሔር ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም፤ የዓለሙን ኃጢአት የሚያስተሰርይ የእግዚብሔር በግ መሆኑን አውቀው የሚከተሉት አሉ። ”በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል” እንዲል። (ዮሐ.፲፥፬)

👉፪. የቃሉን ትምህርት የእጁን ተአምራት ሽተው፦ ከደዌ ለመፈወስ ይሰበሰባሉ፤ ልብሱን ዳሰው፣ ወድቀው ሰግደው፣ ጥላውን ተጋርደው፣ በእጁ ተዳሰው የሚፈወሱ ነበሩ። (ማር. ፭፥፳፪ እስከ ፍጻሜ)። ጌታችን በዕለተ ሰንበት ሕዝብ በተሰበሰበበት በምኵራብ እንደሚያስተምር ያስረዳናል፤ ”ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፤…ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ፡፡” (ማር.፮፥፩) “ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር።” (ማቴ.፲፫፥፶፬)

👉፫. ምግበ-ሥጋ ፈልገው ደም ግባቱን አይተው:- ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከምኵራብ ጉባኤ ትምህርት በኋላ ጥቂቱን አበርክቶ እልፉን ይመግብ ስለነበር ጉባኤውን ይታደማሉ። ክርስቲያኖች እግዚአብሔርን የምናመልከው ምግበ ሥጋ ስለሰጠን አይደለም። እርሱንማ ለሕዝብም ለአሕዛብም ሳይሰስት የሚመግብ መጋቤ ዓለማት ነው። ክርስቲያን በመብል አይገመትም። “እንግዲህ በመብልም ቢሆን÷ በመጠጥም ቢሆን÷ በልዩ ልዩ በዓላትም ቢሆን÷ በመባቻም ቢሆን÷ በሰንበትም ቢሆን የሚነቅፋችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፡፡” እንዲል፡፡ (ቆላ. ፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ)

👉፬. ለክስ የሚቀርቡ አሉ፦ ከቃሉ ግድፈት ከትምህርቱ ስሕተት የሚፈልጉ ሰቃለያን አይሁድ፣ ሊቃነ ካህናት አምላክነቱን የሚጠራጠሩ አይሁድ የሸንጎውን ጌታ ለሸንጎ ፍርድ ሊያቀርቡት ከግር በግር ይከተሉት ነበር። “ወጸቢሖ ተጋብኡ ሊቃነ ካህናት ወጸሐፍት ወሊቃናተ ሕዝብ ወወሰድዎ ውስተ ዐውዶሙ። ወይቤልዎ እመ አንተሁ ክርስቶስ ንግረነ ገሃደ ወይቤሎሙ እመኒ አይዳእኩክሙ ኢተአምኑኒ፡፡ በነጋም ጊዜ፥ የካህናት አለቆች፥ ጻፎችና የሕዝቡ ሽማግሌዎች ተሰብስበው ወደ ሸንጎአቸው ወሰዱት፡፡ “አንተ ክርስቶስ እንደ ሆንህ በግልጥ ንገረን” አሉት፡፡እርሱም እንዲህ አላቸው፥ “ብነግራችሁም አታምኑኝም” እንዲል፡፡ (ሉቃ. ፳፪፥፷፮፣ ማቴ.፳፮፥፶፱)

ዛሬም በአማናዊቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥጋዊ ነገር ብቻ ገዝፎባቸው ቤተ መቅደሱን ለንግድ፣ ንዋያተ ቅድሳትን ለትርፍ ብቻ አሳልፈው የሚሸጡ፣ የሚለውጡ፣ ለክስ የሚፋጠኑ ከምኵራብ ያልወጡ የበጎችን እረኛ አሳልፈው የሚሰጡ አዋልደ ይሁዳ እንዳሉ ግልጽ ነው። “ወረከበ በምኵራብ እለ ይሠይጡ አልህምተ ወአባግዐ ወአርጋበ …፤ በመቅደስም በሬዎችን፣ ላሞችን፣ በጎችን፣ ርግቦችን፣ የሚሸጡትን አገኘ …፤ “ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት፤ ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል” እያለም የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡፡ (ዮሐ.፪፥፲፮፣ማቴ.፳፩፥፲፫)

👉በምኵራብ ይሸጡ፣ ይለውጡ የነበሩትን የገሠፀበት፣ ቤተ መቅደስን የከብት መንጃ የወርቅ መነገጃ ያደረጉ ሰዎችን ከእነ ሸቀጣቸው ከቤተ መቅደስ ያስወጣበት፣ ቤተ መቅደስ የእግዚአብሔር ማደሪያ፣ የመሥዋዕቱ መክበሪያ፣ የጸሎት ሥፍራ ምስካበ ቅዱሳን መሆኗን ያስተማረበት ዕለት ነው። ቃሉ በዚያን ዘመን ተነግሮ ብቻ ያለፈ አይደለም፤ ለእኛ የተነገረን መሆኑን አውቀን የባለቤቱ ጅራፍ ሳይገርፈን ልንመለስ ይገባል። “የገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎችንም በሬዎችንም ከመቅደስ አወጣቸው፥ የለዋጮችንም ገንዘብ አፈሰሰ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡” (ዮሐ.፪፥፲፬)

ከሚመጣው ጅራፍ ለመዳን እምነት ከተግባር ይዞ መገኘት ያስፈልጋል።” ወንድሞቻችን ሆይ÷ እምነት አለኝ፤ ምግባር ግን የለኝም የሚል ሰው ቢኖር÷ ምን ይጠቅመዋል? በውኑ እምነቱ ልታድነው ትችላለችን? ከወንድሞቻችን÷ ወይም ከእኅቶቻችን÷ የታረዙ ወይም የዕለት ምግብ ያጡ ቢኖሩ÷ ከእናንተም አንዱ …እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው።” እንዳለ። (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)

የዕለቱ መዝሙር (ከጾመ ድጓ)፦ ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት፤ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤

መልእክታት፦(ቆላ.፪፥፲፮ እስከ ፍጻሜ) (ያዕ.፪፥፲፬ እስከ ፍጻሜ)
ወንጌል፦ (ዮሐ.፪፥፲፪-እስከ ፍጻሜ)
(የሐዋ.፲፥፩-፰)


ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ dan repost
."ሆዳችሁ ጠግቦ ከምታቀርቡት አንድ መቶ ጸሎትና ተራራ ከሚያርድ ድምጻችሁ ይልቅ በጾም ውስጥ ሆናችሁ የምታቀርቡት አንድ ጸሎት ተሰሚነት አለው።"

#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

@ortodoxtewahedo


ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ dan repost
“የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።”

— ኤፌሶን 6፥17

@ortodoxtewahedo

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.