Postlar filtri


❤️ "Message (ergaa) Jaalalaa jaalallee keetiif erguuf rakkataa jirta taanaan asitti bu'i!",... See More

            👇👇👇👇
     👉✨See More✨👈
     👉✨See More ✨👈
             👆👆👆👆


❤️ Ergaalee jaalalaa 100,... See More


መዝሙር (MEZMUR) E4J dan repost
ዝማሬ በዘማሪት ማዕረግ

@e4jesus

https://t.me/e4jsong
@e4jsong

ኢትዮጵያን ለኢየሱስ


Mesay Birhanu @ Kingdom Sound Worship Night 2025 ' Anten Bicha Sasib ' Original Song By Dagmawi Tilahun

@revealjesus


ሰሞኑን “ሰማያዊ አመለካከት” በተሰኘው ርእስ ስር የተማርናቸውን አምስት ክፍሎች ተግባራዊ ለማድረግ እንዲመቻችሁ የሚከተሉትን የግል ጥሞና ጥያቄዎችን ትቼላችኋለሁ፡፡

1. ሰማያዊ የአስተሳሰብ ዘይቤን ከማዳበር አንጻር በሕይወቴ ምን ለውጥ ለማምጣት አሰብኩ?

2. ሰማያዊ የንግግር ዘይቤን ከማዳበር አንጻር በሕይወቴ ምን ለውጥ ለማምጣት አሰብኩ?

3. ሰማያዊ የሕይወት ዘይቤን ከማዳበር አንጻር በሕይወቴ ምን ለውጥ ለማምጣት አሰብኩ?

4. ሰማያዊ የውጊያ ዘይቤን ከማዳበር አንጻር በሕይወቴ ምን ለውጥ ለማምጣት አሰብኩ?

5. ሰማያዊ የጥበብ ዘይቤን ከማዳበር አንጻር በሕይወቴ ምን ለውጥ ለማምጣት አሰብኩ?


የግል ሕልማችሁ ጉዳይ

(“የተደራጀ ሕይወት” ከተሰኘው ሰሞኑን ከታተመው አዲስ የዶ/ር ኢዮብ መጽሐፍ የተወሰደ)

የተደራጀ ሕይወት ከመኖር አንጻር ሕልማችን ላይ የመስራታችንን አስፈላጊነት ትኩረት ሰጥተን እንመለከታለን፡፡ በቅድሚያ ግን “የግል ሕልም” ስንል ትርጉሙ ምን ማለት እንደሆነ በመስማማት እንጀምር፡፡

“የግል ሕልም ማለት በተለያዩ የግል ሕይወታችን ዘርፎች ስኬታማ እና ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ለመኖር የሚያስችሉንን መርሆች በመከተል የልህቀት ከፍታ ውስጥ የሚከቱንን ሁኔታዎች መገንባት ማለት ነው፡፡”

በዚህ ትርጉም መሰረት በሕልም ላይ ስለመስራት ማሰብ ማለት የራስን ሕይወት መገንባትና ማሻሻል ማለት ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ፣ ራእይ የሰውን ሕይወት የመገንባትን፣ የማሳደግንና የመለወጥን ሁኔታ ሲነካ፣ ሕልም ደግሞ የራስን ሕይወት የመገንባትን፣ የማሳደግንና የመለወጥን ሁኔታ ይነካል፡፡

ይህ ሕልም ብለን የምንጠራው ጉዳይ የራሳችንን ሁለንተናዊ ሕይወት ከማሳደግ ጋር የሚገናኝ ልምምድ ሲሆን፣ ሁኔታው እንዲሁ በሃሳባችን የፈጠርነውን ነገር ሁሉ እንደሚሆን በጭፍንነት የማሰብ ጉዳይ ሳይሆን ተግባራዊ ሂደትን ተከትሎ ስኬታማ ሕይወት ውስጥ የመግባት ጉዳይ ነው፡፡

ሕልሞቻችን ቅዠት ሆነው እንዳይቀሩ መውሰድ ከሚገቡን ወሳኝ እርምጃዎች መካከል የሚከተሉትን ቀላል መርሆች ማስታወስና መለማመድ ይጠቅናል፡፡

1.  አልመው - እያንዳንዱ ታላቅ ስኬት የሚጀምረው በአንድ ሰው አእምሮ ውስጥ ሲፈጠር ነው።

2.  እመነው - ሕልም ጋር የሚደረሰው ያለምነውን ሕልም ልንደርስበት እንደምንችል በማመን ነው፡፡

3.  እየው - ሕልማችንን በገሃዱ አለም ከማየታችን በፊት በአይነ-ህሊናችን ማየት አስፈላጊ ነው፡፡

4.  አጋራው - ሕልማችንን በውስጣችን አምቀን ከምንይዝ ይልቅ ለተገቢ ሰዎች ማጋራት ወደ ስኬት ያስጠጋናል፡፡

5.  አቅደው - ያለምነውና አምነን በውስጠ-ህሊናችን ያየነውን ሕልም በእቅድ ደረጃ ማውረድ አለብን፡፡

6.  ስራው - ሕልማችንን ካመንነውና ካቀድነው በኋላ ወደ እንቅስቃሴ መግባት ይኖረብናል፡፡

7.  አጣጥመው - በሕልም ተጀምሮ ጠንክሮ በመስራት እጃችን የገባውን ውጤት ማጣጣምና መደሰት ያስፈልጋል፡፡

መጽሐፉን በቅናሽ ለማግኘት በ 0947930369


      @revealjesus




👉ዛሬ ስለአንድ ነገር አፅንኦት ሰተን እንመለከታለን። እሱም ስለ መንፈሳዊ ልባችን ነው ሁላችንም ልቦናችንን ልንመዝን አስፈላጊ ነው ምክንያቱም ክርስቶስ በምሳሌው ይነግረናል ልብ ምን ያህል ለ መንፈሳዊ እድገትን እና ፍሬ ለማፍራት መሰረት እንደ ሆነ።

👉ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ከመፅሀፍ ቅዱሳችን (ሉቃስ 8፥4-15) ይህ ክፍል የሚያወራው የዘሪውን ምሳሌ ነው። ምሳሌውም 2 ነገሮች ላይ ትኩረት አድርጔል እስቲ እንመልከት።

📌1ኛ= ዘር ሲል  የሚወክለው የእግዚአብሔርን ቃል ነው( ሉቃስ 8፥11) ልንመለከት እንችላለን ይህ ዘር አንድ ሆኖ ሳለ ካረፈበት መሬት የተነሳ ግን የተለያየ ፍሬ ሲያፈራ እንመልከት።
📌2ኛ መሬት (ዘሩ የወደቀበት ስፍራ) እሱ የልባችን ምሳሌ ነው ።


(ዕብራውያን 1፥1-2) ላይ ሲናገር ይህ የእግዚአብሔር ቃል በተለያየ ሁኔታ ለአባቶች ፤ እንዲሁም አሁን በአዲስ ኪዳን በልጁ በክርስቶስ ለእኛ ተናገረን እንደሚል ቃሉ ከመነገር ካልተከለከለ እንዴት ልባችንን ከቃሉ ጋር አስማምተን ፍሬ እናፈራ ይሆን?
በዚህ ምሳሌ ላይ 4 አይነት ስፍራዎችን እናያለን።
👉1ኛ "መንገድ ዳር "ተብሎ የተገለፀ የልብ አይነት ያላቸው ሰዎች በ (ሉቃስ8፥12)እንደተገለፀው ቃሉን የሚሰሙ ነገር ግን አምነው እንዳይድኑ ድያብሎስ ቃሉን ከልባቸው የሚወስድባቸው።
👉2ኛ "አለታማ"ቃሉን የሚሰሙ ነገር ግን በፈተና ወቅት የሚክዱ ናቸው።
👉3ኛ "በእሾህ መካከል ያለ መሬት"ቃሉን የሚሰሙ ነገር ግን ምቾት እና የለተለት ሩጫ እንዳያፈሩ ያነቃቸው ናቸው።
👉4ኛ"መልካም መሬት" ቃሉን በመልካም እና በበጐ ልብ ቃሉን የሚሰሙ ብቻ ሳይሆን ፀንተው የሚጠብቁ ናቸው። በመሆኑም መቶ እጥፍ ያፈራሉ።ስለዚህ ሁላችንም እራሳችንን እንጠይቅ የእኛ ልብ የቱን ይመስል ይሆን?


👉በስተመጨረሻም ስለ መንፈሳዊ ፍሬ እና ስለ ልባችንን ስናስብ ምን ላይ እናተኩር ለሚለው የሚከተለው እንይ።
📌1ኛ የእግዚአብሔርን ቃል በማወቃችን (በመስማታችንና በማንበባችን) ብቻ አንደገፍ ምክንያቱም ባየነው ምሳሌ ላይ ሁሉም የሚሰሙ ስለነበሩ በመስማት ላይ እምነትን እና ከራስ ጋር ማዋሀድን(ማሰላሰልን) ይጠይቃል።
📌2ኛ(ያዕቆብ 1፥12) በፈተና የሚፀና ሰው የተባረከ ነው ። እንደሚል ምን ያህል ከመከራችን በላይ ቃሉን እናምናለን እንደገፈዋለን? ፅናት ታማኝነት ስለሆነ አጥብቀን ልንይዘው ይገባል።
📌3ኛ መልካም ልብ፣ በጐ ህሊና ሊኖረን ይገባል።ለበለጠ( 1ጢሞ1፥19) እንመልከት።
📌4ኛ በምቾትና በድሎት ማነቆ ስር እንዳንሆን ልንጠነቀቅ ይገባናል ለስጋችን እንደምንጨነቅ እንደዚያው ለመንፈሳዊ ህይወታችን ልንጨነቅ ይገባናል በመጠን መኖርን እራሳችንን እናስለምድ።እንግዳ ነንና!




Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


ሰማያዊ የሕይወት ዘይቤ

“ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋ ልትኖሩ በቀረላችሁ ዘመን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ” (1ጴጥ. 4፡1)፡፡

እስከዛሬ የኖርነውን ሕይወት መለስ ብለን ስንመለከት ምናልባት እንደቃሉ ያልሆኑ ልምምዶቻችን እናስታውስ ይሆናል፡፡ ያለፈው ልምምዳችን ያም ሆነ ይህ፣ በቀረልን ዘመን የሰውን ምኞት ተወት በማድረግ እንደ ጌታ ፈቃድ የምንኖርበት የሕይወት ዘይቤ እንድንይዝ ቃሉ ያበረታታናል፡፡ እንደ ቃሉ ስናስብና እንደ ቃሉ ስንናገር እንደቃሉ ወደሆነ የሕይወት ዘይቤ አንድ እርምጃ እንደተጠጋን ማስታወስ አለብን፡፡ ለዚህ አይቱ ሰማያዊ የሕይወት ዘይቤ ምሳ የሚሆኑን ብዙ ምስክሮች አሉን፡፡

“ኖኅ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ” (ዘፍ. 6:9)፣ “ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔርጋር አደረገ” (ዘፍ. 5:22)፡፡ ኢያሱም ቢሆን፣ “በምትሄድበትም ሁሉ እንዲሳካልህ፣ ወደ ቀኝም ወደ ግራም አትበል” (ኢያ. 1፡7) የሚለውን ቃል ሰምቶ ልቡን ያበረታ ሰው ነበር፡፡

እነዚህና ሌሎች እንደመና የከበቡን ምስክሮች የተውልንን ፈለግ በመከተል ሰማያዊውን የሕይወት ዘይቤ ለማዳበር ዋነኛው ጉዳይ ምርጫ ይባላል፡፡ የትኛውን የሕይወት ዘይቤ እንመርጣለን? የሚከተሉትን ምርጫዎቻችንን እንመልከት፡፡

1. እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የመመላለስ ምርጫ

“በመንፈስ ተመላለሱ” (ገላ. 5፡16)፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ይህን ቃል የተናገረበት አውድ የስጋን ስራ የመፈጸምንና እኛ የምንፈልገውን ሳይሆን ጌታ የሚፈልገውን ነገር የማድረግን እውታ ያካተተ ነው፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ በትእዛዝ መልክ ተቀምጦ ለእኛ ምርጫ የተተወ እንደሆነ ቃሉ ይጠቁመናል፡፡ እርስ በርስ የሚቀዋወሙትን የመንፈስና የስጋ አሳብ በመለየት ለመንፈስ አሳብ መወገን በመንፈስ እንድንመላለስ በርን ይከፍትልናል፡፡

2. እንደ ሰው ልማድ የመመላለስ ምርጫ

“ቅናትና ክርክር ስለሚገኝባችሁ ሥጋውያን መሆናችሁ አይደላችሁምን? እንደ ሰው ልማድስ አትመላለሱምን?” (1ቆሮ. 3፡3)፡፡

ዙሪያችንን እንመለክተው፡፡ በስራና በማሕበራዊ መስኮቻችን የሚገኙ የዚህ አለም ሰዎች ያላቸውን የሕይወት ዘይቤ እናጢነው፡፡ የቅንአቱ፣ የክርክሩ፣ የዘረኝነቱ፣ የክፋቱ … ዘይቤ ከእኛ የተሰወረ አይደለም፡፡ ቃሉ በግለጽ የሚያስተምረን እንደነሱ እንዳንመላለስ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን በእኛም ሳይቀር እነዚህ የሰው ልማዶች ብቅ ሲሉ እናያቸዋለን፡፡ ዛሬ ግን በመንፈስ የመመላለስን ምርጫ መውሰድ እንችላለን፡፡

3. እንደ ጠላት ፈቃድ የመመላለስምርጫ

“በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው” (ኤፌ. 2:1)፡፡

ሐዋርያው ጳውሎስ ከላይ በተጠቀሰው ሃሳብ ላይ ራሱን በመጨመርና እርሱም የዚያ አይነት ሕይወት ተሳታፊ መሆኑን ካመነ በኋላ “ነገርግንበምሕረቱባለጠጋየሆነእግዚአብሔር … በክርስቶስሕያዋንአደረገን” በማለት በጸጋው ጉልበት አዲስ የሕይወት ዘይቤን መምረጡን ይጠቁመናል፡፡ እዚህም ጋር ምርጫው የእኛ ነው፡፡ ክፉው ሹክ እንዳይለንና ወደ ክፉ እንዳይመራን የመንፈስን መንገድ የመምረጥ ጸጋው ተሰጥቶናል፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ሰማያዊ የውጊያ ዘይቤ”

Dr. Eyob


ሰማያዊ የሕይወት ዘይቤ


HTIS መንፈሳዊው ሰው.png
209.3Kb
HTIS_Chap1.pdf
110.7Kb
HTIS_Chap2.pdf
1.5Mb
HTIS_Chap3.pdf
2.0Mb
HTIS_Chap4.pdf
211.5Kb
መንፈሳዊው ሰው፤ በሉዊስ ስፔሪ ሼፈር፤ ትርጕም ዘላለም መንግሥቱ

@revealjesud


አዝ፦ የእግዚአብሔር እጅ የያዘው ነገር
እንዳይወድቅ አይፈራ እንዳይጠፋ አይፈራ
ከጥላው ሥር ያረፈው ሰው
ዘለዓለሙ አያሰጋው (2x)

አባትዬ የእኔ ወዳጅ (2x)
ኑሮዬ በአንተ እጅ (2x)
አባትዬ የእኔ ከለላ ከለላዬ
በጥላህ ሥር ነው ማደሪያዬ (2x)

በእናቴ ማህፀን ደምሳለ ሆኜ አጥንቶቼም ሳይዋደዱ
አንተው ታውቀው ነበር እንዲህ እንዲሆን የሕይወቴ አካሄዱ
ደግሞ እስከ አሳለፍከኝ በቸርነትህ የትላንቱኑ ጨለማ
ለነገውስ ቢሆን ለምን አላምንም ሕይወቴ በእጅህ ነውና

ተውኩት ሁሉንም ለአንተ ተውኩት
ተይ ነፍሴ እኔ አላውቅም ብዬ እንዳልኩት
ይሁን ያልከው የፀና ለመሆኑ
ምስክር ነው ሰማይ የለም አገር መሆኑ

አዝ፦ የእግዚአብሔር እጅ የያዘው ነገር
እንዳይወድቅ አይፈራ እንዳይጠፋ አይፈራ
ከጥላው ሥር ያረፈው ሰው
ዘለዓለሙ አያሰጋው (2x)

አባትዬ የእኔ ወዳጅ (2x)
ኑሮዬ በአንተ እጅ (2x)
አባትዬ የእኔ ከለላ ከለላዬ
በጥላህ ሥር ነው ማደሪያዬ (2x)

ክብርን የምትገልፅበት ደካማ ሰው ስትፈልግ አገኘኸኝ
እንጂማ በእራሴ እንኳን በአንተ በሰውም ዓይን የማልሞላ ነኝ
ገና በወደድከኝ በንጋት አየሁ ብልስ ምን እልሃለሁ
አንተ ነህ ደጀኔ ተባረክልኝ ከትከሻህ የሚያወርደኝ ማነው

አልጥልሽ አልተውሽ እያልክ
ልፌ ስትደግፈኝ እንደዋልክ
አይቼህ መንፈሴ ረካ
አትተወኝም አትረሳኝም ለካ
አዬ አትረሳኝም ለካ

አትተወኝም በቃ አትረሳኝም በቃ
አሄ አትረሳኝም በቃ
አትተወኝም በቃ አትለቀኝም በቃ
አሄ አትለቀኝም በቃ (2x)


በሰላሙ ብዛት ቀለለ ችግሩ
አደገ ቁመቴ እያለ ነገሩ
ቀረ መዋከቤ በጠራኸኝ ሳርፍ
ተምራልኝ ነፍሴ አንተ ላይ ማራገፍ

ድምጿ ተቀየረ ተለወጠ ቃሏ
እዬዬን በእሰየው የአንተ በመሆኗ
እህህን በእልልታ ለምኑን በአሜን
ስለወጥከው እየሱስ እንካ ዘላለሜን
እዬዬን በእሰየው የአንተ በመሆኗ
እህህን በእልልታ ለምኑን በአሜን
ለቀየርከው እየሱስ እንካ ዘላለሜን

ተባረክ እልሃለሁኝ/8

ተንበርክኬ አሸነፍኩኝ
እጅ ሰጥቼ ድል ነሳሁኝ
በጩኸቴ መዳን ሆነ
አበሳዬ ተከደነ
ተከትዬህ ከፊት ቀደምኩ
ያንተን ብዬ ከምን ጎደልኩ
ስፈልግህ ጽኑ እግሮቼ ሃይሌ ሆነኸኝ ተሟጋቼ

በመጨነቅ ስርዐትን
በመማጸን መጓደድን
በር በመዝጋት ክፉን ማምለጥ
እርዳኝ ብዬ ሁሉን መብለጥ
ከአንተ ሰምቶ የውስጥ ውበት
አቤት ብዬህ አለኝ ማለት
ከአንተ ዘግኖ ሞልቶ ማዳር
ሆኖልኛል ስምህ ይክበር

ስኬቴ በአንተ መታመኔ
ከፍታዬ እግርህ ስር መሆኔ
ውበቴ አንተን መጠጋቴ
ድምቀቴ ምህረትህ ነው ለኔ
ስኬቴ በአንተ መታመኔ
ከፍታዬ እግርህ ስር መሆኔ
ውበቴ አንተን መጠጋቴ
ድምቀቴ ምህረትህ ነው ለኔ

አሃ ሃሌሉያ/4 እላለው ሃሌሉያ

በማለዳ ሃሌሉያ በቀርት ሃሌሉያ
በምሽት ሃሌሉያ በሌሊት ሃሌሉያ
ሁሉ አንዳለ ሆኖ ሃሌሉያ
ሳይቀየር ሃሌሉያ
እላለው ሃሌሉያ

አሃ ሃ ሃ ሃሌሉያ/2
ኦሆ ኦሆ ኦሆ ሃሌሉያ
አሃ ሃ ሃ ሃሌሉያ/3
ኦሆ ኦሆ ኦሆ ሃሌሉያ
አሃ ሃ ሃ ሃሌሉያ
ኦሆ ኦሆ ኦሆ ሃሌሉያ

የኔ ሕይወት መዝሙር ቢሆንም እንዲህ ነው የሚሆነው 🥹❤️


ሰማያዊ የንግግር ዘይቤ

“መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያይተን መንፈስ በሚያስተምረን ቃል ይህን ደግሞ እንናገራለን”(1ቆሮ. 2፡13)፡፡

“ንግግር” በአስተሳሰብና በተግባር መካከል ልክ እንደሳንዲዊች ተጣብቆ የሚገኝ ነገር ነው፡፡ ንግግር አሳብን ሲከተል፣ በተራው ደግሞ ተግባርን ያስከትላል፡፡ ሰው ፈጠነም ዘገየም ሲያሰላስል የከረመውን በአንደበቱ ማውጣቱ አይቀርም፣ “በልብ ውስጥ የሞላውን አንደበት ይናገረዋልና” (ማቴ. 12፡34)፡፡

ይህ ሁኔታ እያደገ ሲሄድ ወደ ተግባር መለወጡ አይቀርም፡፡ በውስጡ የሞላው ሰማያዊው ከሆነ በአንደበቱ ያንኑ ሲናገር፣ በውስጡ ያለው ምድራዊው ከሆነ ደግሞ ምድራዊውን ይናገራል፡፡ ስለዚህ ንግግራችን የአስተሳሰባችን ነጸብራቅ ነው፡፡

ሰማያዊ የንግግር ዘይቤ ማለት ከምድራዊና ከተራ ንግግር የወጣና እንደ ቃሉ የሆነ ንግግር ማዳበር ማለት ነው፡፡ ይህ የንግግር ዘይቤ በሶስት ጎኑ ትኩረት ሊጠውና መስመር ውስጥ ሊገባ ይገባል፡፡

1. ለእግዚአብሔር የምናገረው

“በዚህ ሁሉ፣ ኢዮብ አልበደለም፤ በእግዚአብሔርም ላይ ክፉ አልተናገረም” (ኢዮ. 1:22)፡፡

አንዳንድ ጊዜ ሁኔታዎች እንደጠበቅናቸው አልሄድ ሲሉን ወይም ያልጠበቅናቸው ሁኔታዎች ሲጋፈጡን በጌታ ላይ የማጉረምረምና የእርሱን ባህሪያት የማይወክሉ ንግግሮች ከአንደበታችን እናወጣለን፡፡ ይህ ሁኔታ ለውስጥ ሰውነታችን ጥንካሬና በውጪ ላለው ምስክርነታችንን በእጅጉ የሚጎዳ ጉዳይ ነው፡፡ ለሰዎች ስለእግዚአብሔር የምንናገራቸውና ለእግዚአብሔር ለራሱ የምንናገራቸው ንግግሮች ወሳኝ ናቸው፡፡ “ስለዚህ ዘወትር የምስጋናን መሥዋዕት ይኸውም ለስሙ የሚመስክሩ የከንፈሮችን ፍሬ በኢየሱስ አማካይነት ለእግዚአብሔር እናቅርብ” (ዕብ. 13፡15)፡፡

2. ለሰው የምናገረው

“ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ” (ኤፌ. 4፡29)፡፡

ይህ የብዙዎች ፈተና ነው፡፡ በየእለት ኑሯችን አንዳንድ ሰዎች የሚያሳዩትን ባህሪ ስንመለከትና ሁኔታው ሲነካን፣ ለሰዎቹ “የሚገባቸውን” ክፉ ቃላት ለማውጣት ይቃጣናል፡፡ ማስታወስ ግን ያለብን አንድ ቃላቶቹ ለሰዎቹ ተገባቸውም አልተገባቸውም፣ ከእኛ አንደበት ግን ሊወጡ የሚገባቸው ቃላት እንደሆኑ አምኖ መቀበል አስፈላጊ ነው፡፡ መላእክት እንኳን ከዲያቢሎስ ጋር ሲከራከሩ ጌታ ይገስጽህ ከማለት ካለፈ የስድብ ቃል ራሳቸውን ይጠብቁ ነበር፡፡

3. ለራሴ የምናገረው

“ብላቴና ነኝ አትበል” (ኤር. 1፡7)፡፡

ለራሳችንና በራሳችንን የምንናገራቸው ነገሮች በራሳችን ላይ ያለንን አመለካከት ጠቋሚ ናቸው፡፡ ጊዜያዊው ድካማችንና የተቃወሰው ስሜታችን ከሚነግረን ተቃራኒን በራሳችን ላይ መናገር አስፈላጊ እውነታ ነው፡፡ ምክንያቱም የጊዜው ሁኔታችን በክርስቶስ የተሰጠንን ስፍራ ስለማይወክል ማለት ነው፡፡ ስለዚህም፣ ሁኔታዬ የሚነገረኝን ሳይሆን ጌታ ያለኝንና ያሰበልኝን መናገር ታላቅ የብርታት ምንጭ ነው፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “ሰማያዊ የሕይወት ዘይቤ”

Dr. Eyob Mamo


ሰማያዊ የንግግር ዘይቤ


ሰማያዊ አመለካከት

ባለፈው ፖስቴ፣ “የታደሰ አእምሮ” በሚል ርእስ ስር ትምህርት እንደምጀምር በመግለጽ መግቢያውን ሰጥቻችኋለሁ፡፡ ባለፈው የሰጠኋችሁ note በ pdf በመሆኑ እንዳስቸገራችሁ ብዙዎቻችሁ በገለጸችሁት መሰረት ጽሑፉን ብቻ አሰፍራለችኋለሁ፡፡

የዚህን ትምህርት የመጀመሪያ ክፍል፣ “ሰማያዊ አመለካከት” የተሰኘ ሲሆን፣ በዚህ ክፍል የምንመለከታቸው አምስቱ ሃሳቦች የሚከተሉት ናቸው፡፡ 

“ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው” (ዮሐ. 3፡31)፡፡

አንድ ሰው በምድራዊው ሃሳብና አመለካከት ብቻ ሲጠመድ የሚናገረውም ሆነ የሚተገብረው ምድራዊውን ነው፤ ፍሬውም እንዲሁ፡፡

ሰማያዊው አመለካከት ሁል ጊዜ ከምድራዊው እንደላቀ ይኖራል፡፡ ራሱ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎናል፡- “ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለነው” (ኢሳ. 55፡9)፡፡

“ከሰማያዊው ጥሪ ተካፋዮች” (ዕብ. 3፡1) ሆነን ሳለን በምድራዊው አሳብ ተይዘንን እንዳንቀር የታደሰ አእምሮ ያስፈልገናል፡፡

በምድር ካለው ተራ ነገር ለመውጣት ደግሞ የላቀውን ሰማያዊ አመለካከት ማዳበር የግድ ነው፡፡ የታደሰ አመለካከት የሚጀምረው ምድራዊውን ሃሳብ በመጸየፍና ሰማያዊውን ሃሳብ በማስተናገድ ነው፡፡

ይህንን ለማድረግ ደግሞ ቃሉ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን እንደሚል ጠለቅ ብለን መመልከት ይገባናል፡፡

የዚህ ክፍል አላማ አንድ አማኝ ስለ ሰማያዊ አመለካከት ሊያውቃቸው የሚገባውን መሰረታዊ እውነታዎች መግለጽ ነው፡፡ በዚህ ክፍል ውስጥ የምናጠናቸው

አምስት ዋና ዋና እውነታዎች የሚከተሉት ናቸው፡-


1.  ሰማያዊ የአስተሳሰብ ዘይቤ
“በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም” (ቆላ 3፡1)፡፡

2.  ሰማያዊ የንግግር ዘይቤ
“መንፈሳዊውን ነገር ከመንፈሳዊው ነገር ጋር አስተያይተን መንፈስ በሚያስተምረን ቃል  ይህን ደግሞ እንናገራለን” (1ቆሮ. 2፡13)፡፡

3.  ሰማያዊ የሕይወት ዘይቤ
“ከእንግዲህ ወዲህ በሥጋ ልትኖሩ በቀረላችሁ ዘመን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንጂ እንደ ሰው ምኞት እንዳትኖሩ” (1ጴጥ. 4፡1)፡፡

4.  ሰማያዊ የውጊያ ዘይቤ
“በሰው ልማድ ምንም እንኳ የምንመላለስ ብንሆን፥ እንደ ሰው ልማድ አንዋጋም” (2ቆሮ. 10፡3)፡፡

5.  ሰማያዊ የጥበብ ዘይቤ
“ላይኛይቱ ጥበብ ግን በመጀመሪያ ንጽሕት ናት፥ በኋላም ታራቂ፥ ገር፥ እሺ ባይ ምሕረትና በጎ ፍሬ የሞላባት፥ ጥርጥርና ግብዝነት የሌለባት ናት” (ያዕ. 3፡17)፡፡

የመጀመሪያውን ሃሳብ (ሰማያዊ የአስተሳሰብ ዘይቤ) ነገ ጠዋት ጠብቁ፡፡

የጌታን በረከት ተመኘሁላችሁ!


@revealjesus


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


For more join us 👇☺️ @shoppinggeni

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.