Postlar filtri


☝️አንድ የፀሎት ርዕስ => #ነብሳት
☝️የዛሬው የፀሎት ርዕስ => በ
#ፓኪስታን ለሚገኙ ላልተደረሱ #ሰዪድ ነብሳት

✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️✝️
- - - - - - - - - - - - - - - - - -
“ውሃ ባሕርን እንደሚሸፍን ሁሉ፣ #ምድርም_የእግዚአብሔርን_ክብር_በማወቅ_ትሞላለችና።”
ዕንባቆም 2:14
- - - - - - - - - - - - - - - - - -

#Pray_for_sayyid ☪️🕋
#Pray_for_sayyid☪️🕋
#Pray_for_sayyid ☪️🕋


ተልእኳችን ማለዳ
መጋቢት 6- 2017

ረመዷን ጾም ቀን -15-
የመጸሐፍ ቅዱስ ምንባብ፡- ዩሐንስ ወንጌል 14፡ 6

ኢየሱስም፡— እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።


ብዙ ሰዎች ሲሞቱ ወደ መንግሥተ ሰማያት መሄድ እንደሚፈልጉ ይናገራሉ—ገነት የዘላለም መዳረሻቸው ተስፋ ነው። ነገር ግን ብዙዎቹ ተመሳሳይ ሰዎች ወደ መንግሥተ ሰማይ የሚወስደው መንገድ እንደ ጎግል ካርታ ነው ብለው ያምናሉ - እዚያ ለመድረስ ብዙ መንገዶች አሉ እና እርስዎ የመረጡትን ለመምረጥ ነፃ ነዎት። ይሁን እንጂ በዮሐንስ 14፡6 ላይ ኢየሱስ “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ። በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። በሌላ አነጋገር፣ ወደ ዘላለማዊ ሕይወት በሚወስደው መንገድ ላይ ምንም አማራጮች የሉም ብቸኛው አማራጭ አንድ አለ እርሱም ኢየሱስ ነው።

ኢየሱስ ይህን ግልጽ በሆነ መንገድ የተናገረዉ አንዳንድ ግራ በሚያጋቡ ጊዜያት ነዉ። በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 13 ላይ፣ ኢየሱስ ከመሰቀሉ በፊት በነበረው ምሽት ለደቀ መዛሙርቱ ከመካከላቸው አንዱ አሳልፎ እንደሚሰጠው (ዮሐንስ 13፡21)፣ ሊተዋቸው እንደሆነ (ዮሐንስ 13፡33) እና ጴጥሮስ እንደሚክደው ነገራቸው (ዮሐንስ 13፡38)። ደቀ መዛሙርቱ ሕይወታቸውን ያዋሉበት ነገር ሁሉ በዙሪያቸው እየፈራረሰ ሲሄድ ምን ያህል የጠፉ፣ ግራ የተጋቡ እና ተስፋ ቢስ እንደሆኑ መገመት እችላለሁ።
እንግዲያው ኢየሱስ በጽሑፋችን ላይ የተናገረው ሐሳብ ምን ያህል አጽናኝ ሊሆን እንደሚችል አስቡ! ኢየሱስ ታላቅ ፍርሃታቸውን ለማቃለል ወሳኝ ማረጋገጫ ሰጥቷቸዋል—መለያየታቸው ጊዜያዊ ነው፣ እንደገና መገናኘታቸው ዘላለማዊ ይሆናል፣ እና እሱ፣ ኢየሱስ እነሱን ለማግኘት ተመልሶ ይመጣል፡-

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን በዳግም ምጽአቱ (በትንሳኤው ብቻ ሳይሆን በዳግም ምጽአቱ 1) እና ዘላለማዊ መገናኘታቸውን ካጽናና በኋላ፣ ግራ መጋባትን የሚያቃልልባቸውን ቃላት ተናግሯል፡- እኔ የምሄድበትን ብቻ ሳይሆን ወደምሄድበት ቦታ መድረሻ መንገዱንም ታውቃላችሁ። የጠፉ አልነበሩም፣ የሚተውም አይሆኑም ነበር ከዚያም ሲያልፍ መንገዱን ያውቁ ነበር።

ዛሬ በዓለማችን የሚገኙ ሙስሊሞች እንዲህ ይጸልያሉ፤ አላህ ሆይ በዚህ ቀን የትሁታንን ታዛዥነት ስጠኝ፤ በትሑታን ንስሃ ደረቴን አስፋ፤ በአንተ ደህንነት የፈሪዎች መጠጊያ የሆንክ ሆይ! ወደ እግዚአብሔር የሚያደርሰውን ብቸኛውን መንገድ ልጁን ኢየሱስን በማመን፤ በልጁ በኩል የሐጢያትን ይቅርታ ያገኙ ዘንድ እግዚአብሔር ይገናኛቸው ዘንድ እንጸልይ፡፡


🔹ብዙ ጊዜ የአብዛኞቻችን ችግር የሚሆነው በትንሽ ነገር የምንረካ ነን ። በትንሽ ፀሎት ፡ በትንሽ ቃል ማንበብ ፡ ትንሽ በሆነ እግዚአብሔርን መፈለግ ቶሎ እንጠግባለን ትንሽ ፈልገን ብዙ እንደደከምን ይሰማናል ግን ያ ልክ ያልሆነ ርሀብ ነው ።

🔹መንፈስ ቅዱስ ዕለት ዕለት በሆነ ርሀብ እና ጥማት የሚፈለግ እና የሚናፈቅ ነው ። አንድ ጊዜ አግኝተን የምንረካው ሳይሆን እያገኘነው የሚናፍቀን ከመንፈሱ እያረካን የሚጠማን ነው።

✨መንፈስቅዱስ የእውነት ርሀባችንን ይፈውሰው ።🙏🙏




REVEAL JESUS dan repost
ትልቅ ራእይ አለኝ!

ሰዎች ላይ መልካም ተፅእኖን ለመፍጠር እና ራእያችሁን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስፈልጋችሁ ብዙ ብር፣ የብዙ ሰው ድጋፍ፣ ትልቅ እውቅና፣ እና የመሳሰሉት ነገሮች ብቻ አይደሉም እነዚህና መሰል ሁኔታዎች በጊዜያቸው አስፈላጊ መሆናቸውን የማይካድ ሀቅ ነው ይሁን እንጂ የመነሻው ነጥብ ግን እሱ አይደለም፡፡ እነዚህን “ትልልቅ” ነገሮች ይዘው ከትንሽነትና ከተራ አመለካት ያልወጡ ጊዜያቸውንና ያላቸውን ትልቅ ነገር በከንቱ የሚያባክኑ ብዙዎች አሉ፡፡

ትልልቅ ክንዋኔዎች የሚጀመሩት በትልቅ ልብና በትንንሽ ተግባራዊ እርመጃዎች ነው ትልቅ አስቡና በትንሹ ጅምሩት ፍጥነታችሁን እየጨመራችሁ በየለቱ ለትልቁ ሀሳባችሁ ተራመዱ ያኔ አንድ ቀን ካሰባችሁበት ደርሳችሁ ራሳችሁን ታገኙታላችሁ::

ቅዱስ ቃሉም ጅማሬህ ታናሽ ቢሆንም እንኳ ፍጻሜህ እጅግ ይበዛል እዮብ 8-7 ይለናል ትንንሽ ነገሮችን ትልቅ የሚያደርጋቸው የትልቅ ልብ አመለካከት እና ቀጣይነት ያላቸው ትንንሽ እርምጃዎች ናቸው::

ለዚህም ነው ከትንሽ መጀመር የማልፈራው እስከቀጠልኩ ድረስ ትልቅ መሆኔ እንደማይቀር እና ትልቅነት ከትንሽ የመጀመር እና በትጋት የመቀጠል ውጤት መሆኑን በሚገባ አውቃለሁ::

@revealjesus


እንዴት እንሙት? እንዴት እንኑር?

በምድር ላይ ረጅም ዕድሜ አልኖረም፤ የኖረበት ጥቂት ዕድሜ ግን እስከ ዛሬ ያላባራ የለውጥ፣ የተሐድሶ፣ የፍስሓ፣ የጸጋ ሞገድ አስነሥቷል። ‘ከኖርኩ አይቀር እንደ እርሱ ልኑር’ የሚያሰኝ ትርጉም ያለው ሕይወት ኖረ። ኢየሱስ ክርስቶስ እንዴት እንደሚኖር ብቻ ሳይሆን እንዴት እንደሚሞትም አሳየን። ከኑሮው ለመቅዳት የምንሻማ ሁሉ ከሞቱም ለመማር ብንዘጋጅ እጅግ እንጠቀማለን።

እውነቱን ለመናገር መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመሞት የመጣ ነዋሪ ነበር። “በሥጋና በደም የተካፈለው” (ሰው ሆኖ የተወለደው) በሞቱ አማካይነት በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን ዲያብሎስን ለመሻር ነው። እና በመሞት አሸነፈው፤ በንጹሕ ሞት ድል ነሣው፤ ታይቶ በማይታወቅ ዐይነት መሥዋዕታዊ ሞት ሞትንና አለቃውን ቀጣቸው። ቅርንጫፉን በመቁረጥ ሳይሆን፣ የሞትን ሥሩን በጥሶ አመከነው። የሞት መነሻ ሥሩ ኀጢአት ነበረና የኀጢአትን ሰንኮፍ ሲነቅል ሞት ተልፈሰፈሰ። የእግዚአብሔር ስም ይመስገን። ይህ ሟች ልዩ ሟች ነው። ማንም ይሞታል በኀጢአቱ፣ በአዳምነቱ፤ ይህኛው ግን ያለ ኀጢአት ሞቶ ኀጢአተኛኞች ሟቾችን አጸደቀ። አቤት ጥበቡ!

ይህስ ይሁን፣ ታዲያ ትምህርቱ ምንድን ነው? ከአሟሟቱ ምን እንማራለን?

የወንጌላቱ ትራኬ በሕይወት ታሪክ አጻጻፍ ደንብ ሲቃኝ አድልዎ ያሳያል። ስለ ሕይወቱ፣ ስለ አገልግሎቱ፣ ስለ ትምህርቱ፣ ከጻፉት ጋር በማይመጣጠን መንገድ ስለ ሞቱ የጻፉት ይበልጣል። ምናልባት የመጽሐፋቸውን እርቦ ያህል የጻፉት ስለዚህ ሰው የመጨረሻ ሳምንት ሳይሆን አይቀርም። በከንቱ አላደረጉትም፤ ሞቱ ግዙፍ ሞት ነበርና።

የመጀመሪያው ትምህርት
ኢየሱስ ክርስቶስ ኑሮው የተለካ ዐጭር ጊዜ እንደ ነበረ ዐውቆ፣ ይህንኑ እየተናገረ፣ በዚሁ ዕይታ ይኖር የነበረ ሰው ነበር። በታላቅ መረጋጋት ውስጥ ሆኖ እያለ አንዳች የተልእኮ ጥድፊያ ደግሞ ይጎተጉተው እንደ ነበር ያስታውቃል። “…ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር እቆያለሁ፤ ወደ ላከኝም እሄዳለሁ። ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም…” ዮሐ 7፥33-34፤ “ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል” (ዮሐ 9፥4)፤ ለመሞት ተዘጋጅቶ በተልእኮ ልቡና ውስጥ ይኖር ነበር።

የእኛስ እድሜ ልክ የለሽ ነው እንዴ? ‘ሌሎች ሊሞቱ ይችላሉ፤ እኔ እንኳ ሳልቆይ አልቀርም’ ማለት ከፍተኛ ሽንገላ አይደለምን? የሞትን እውነታ ገፋ ገፋ ማድረግ ሰብአዊ ጨዋታ ሳይሆን አይቀርም። የምር ስንነጋገር ግን ይህን ዐረፍተ ነገር እንኳ አንብበን ሳንጨርስ ሕይወት ልትቋረጥ እንደምትችል አንዘነጋውም። እንግዲያው አንዱ የጌታ ትምህርት ሕይወት ጥቂት ጊዜ ታይቶ እንደሚጠፋ እንፋሎት መሆኑን ተገንዝቦ በተልእኮ ልቡና እንዲሁም በሥራ ትጋት መኖር ነው። ሕይወት ከቸሩ ጌታ የተሰጠችን ጥሪት ናት። ሙዐለ ሕይወት ትርፋማ እንዲሆን ሳንጨነቅ፣ በብርቱ ትጋት እንድንሠራ ያሻል።

ሁለተኛው ትምህርት
ጌታችን ሞትን እንደ ክብር መሸጋገሪያ መንገድ አድርጎ የቆጠረበት አተያይ ነው። የሞቱ ጊዜ ደረሰ ማለት ለጌታችን የክብሩ ጊዜ ደረሰ የማለት ያህል ነበር። አሟሟቱ ላይ ላዩን ሲያዩት የታላቅ ውርደት ይመስል ነበር። በሐሰተኛ ምስክሮች ተከስሶ፣ በቅርብ ጓደኞቹ ተከድቶ፣ አጠገቡ በነበረ ተማሪው በገንዘብ ተሸጦ፣ በወታደሮች ጥፊና ድብደባ፣ በጅራፍ ግርፊያና በስላቅ እየተነዳ፣ እርቃኑን በእንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ፣ ዐላፊ አግዳሚ እያላገጠበት የሞተውን ሞት እንዴት ነው የክብር መንገድ የሚለው?

ነገሩ እንዲህ ነው፤ መሬት ሲሳለቅበት ሰማይ ያጨበጭብለት ነበር፤ ጲላጦስ እንዲሰቀል ሲፈርድበት አባቱ ትንሣኤውን ያዘጋጅለት ነበር፤ ብቻውን ቀርቶ እየጮኸ ሲሞት ለአእላፍ አማኞቹ የሰማይ በር ያስከፍት ነበር። ሞቱ ታላቅ ዐላማ ስለ ነበረው ጻድቅ አምላክ ያከበረው ሞት ነበረ። አባቱን እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ታዝዞ፣ የሰውን ልጅ እስከ መጨረሻው ድረስ ወድዶ ስለ ሞተ ታላቅ ክብር ተጎናጸፈ። “… በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር ያለ ልክ ከፍ ከፍ አደረገው” ብሎ ይለናል ሐዋርያው ጳውሎስ (ፊል 2፥9)። እንግዲያው ለእኛ ለምናምነው ሁሉ የመታዘዝና የፍቅር አርኣያ ሆነልን፤ የክብርን መንገድ አሳየን። እና እኛ ከመሞታችን በፊት በዚህ በጠረገልን መንገድ ስንጓዝ፣ በሕመም ብንሞት፣ በአደጋ፣ በእርጅና በሌላ በማናቸውም “አሰቃቂ” ይሁን “ለስላሳ” አሟሟት ብንሞት ግሥገሳችን ወደ ክብር እንደ ሆነ እንድናስብ ያሻል። ‘ጎሽ፤ አንተ ታማኝ ባሪያ እንኳን ደኅና መጣህ!’ ወደሚለን ቸር አባት እየቀረብን መሆናችንን እናስብ።

ሦስተኛ ትምህርት
ኢየሱስ ክርስቶስ የሞቱን እውነት አስቀድሞ ቢረዳም እጅ አጣጥፎ፣ ጉልበቱን ኮርትሞ በሰቀቀንና በድንጋጤ ሞትን አልተጠባበቀም። እስከ መጨረሻ ትንፋሹ ሕቅታ ድረስ በጎ እየሠራ፣ የያዙትን ወታደሮች እየፈወሰ፣ ለሰቀሉት ምሕረት እየለመነ፣ ከአባቱ ጋር በጸሎት እየተነጋገረ “ተፈጸመ” ብሎ ነፍሱን ሰጠ።

እስክንሞት ድረስ ቦዝዘን እንዳንቀመጥ፣ ከበጎ ሥራ እንዳንታክት፣ ከጸሎት እንዳናፈገፍግ፣ ‘ወይኔ ጉዴ’ እያልን በሰቀቀን እንዳናልቅ አስተማረን። እያንዳንዷን ሰዓት በዘላለም መዝገብ ውስጥ የሚገባ የሰላምና የፍቅር ዘር እየዘራን እንሙት (ያው መሞታችን አይቀርም ብዬ ነው)። የምንወድዳቸውን በጣም እንውደዳቸው፤ ለሚጠሉን እንጸልይላቸው፤ ለአገርና ለሕዝብ መልካሙን ሁሉ እንመኝ፤ እንናገር፤ እንባርክ። እንደዚያ ሀኬተኛ ባሪያ መክሊታችንን ቀብረን የቁጥጥሩን ቀን በድንጋጤ አንጠብቅ። በተሰጠን ትንሽ ትንፋሽ እንኳ በመክሊታችን እየነገድን እንሙት።

አራተኛ ትምህርት
ለሞቱ ቀን ተማሪዎችን እያዘጋጃቸው ሳለ፣ ጌታችን ከደቀ መዛሙርቱ ጋር መዝሙር ዘመረ (ማቴ 26፥30)። ምን እንደ ዘመሩ ባይጻፍልንም፣ የእኔ ግምት የፋሲካ ሰሞን ስለ ነበረ እስራኤል ከግብፅ ባርነት ነጻ የወጣበትን፣ የእግዚአብሔርን ትድግናና ግርማ የሚናገር የነጻነትና የምስጋና መዝሙር ሳይሆን አይቀርም። በሞት ሰሞን መዝሙር አልተከለከለም። የሚሠራውን የሚያውቀውና የፍጥረት ሁሉ ገዥ የሆነውን፣ የነፍስ ሁሉ ባለቤት የሆነውን ጌታ እያመሰገንነው እንሙት። ሮበርት ፍሮስት ስመጥር አሜሪካዊ ባለ ቅኔ ነበረ። እንጨት አጥር ላይ ቆማ በጧት የምትዘምር ወፍ፣ ሥራ በፈታ አንድ ልጅ በተወረወረ ድንጋይ ተመትታ ጸጥ ስትል አዝኖ እንዲህ አለ፦

There must be some wrong;
in silencing any song!
መዝሙር የሚያዳፍን ዜማ የሚከለክል፣
ጤና ሰው አይደለም ሠርቷል ትልቅ በደል!

ሌላም ብዙ ትምህርት አለው። ለምሳሌ፣ በመስቀል ላይ እየሞተ ሳለ ስለ ወላጅ እናቱ አስቦ ለዮሐንስ ዐደራ መስጠቱ ትልቅ የኀላፊነት አብነት ነው።

የመጨረሻው እራት ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ሲበላ፣ ህብስቱንና ወይኑን ሲሰጣቸው “በእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ጋር አዲሷን ወይን እስክንጠጣ ከዚህ በኋላ አልጠጣውም” ማለቱ የትንሣኤንና የዳግም ምፅዐቱን ተስፋ የሚያለመልም የተረጋጋ ንግግር ነው። ከዚህ ሕይወት በኋላ ሌላ የከበረ ሕይወት አለ፤ ይህንን እየተናገረ የሞተ ሰው ነበረ።

ሁሉን ትምህርት ዘርዝረን አንጨርስም …

ነገር ግን ይህ አስገራሚ ሞት የሞተው ትሑቱ ኢየሱስ የገሃነም ኀይሎች ሊቋቋሙት በማይችሉት ታላቅ ኀይል ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። በእርሱ የምናምን የሁላችንን ዕንባ የሚያብስ፣ ነፍሳችንን የሚመልስ፣ የመጽናናት ብሥራት ሰጠን። እና ወዳጆቼ እንደ ጳውሎስ፣ “ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ሞትም ጥቅም ነው” የማለት ጸጋ ያድለን።


Nigussie Bulcha

@revealjesus


ከታንኳው ውረዱ

ከአገልጋይ ብሩክ ሚልኪያስ ጋር


ልባም ሴት ማን ናት ?

1. ልባም ሴት ራሷን ለክርስቶስ አሳልፋ ትሰጣለች ። አምላኳን ኢየሱስን ታመልካለች ለባሏ ትገዛለች
2.ልባም ሴት ፋሽን ተከታይ አይደለችም ። ልታይ ልታይ አትልም ሰውነቷን ታስከብራለች
3.ልባም ሴት በትዳሯ ላይ በገንዘብ እና በንብረት አስተዳደር ጠንቃቃ ናት ስለዚህ ባሏ ያምናታል
4.ልባም ሴት ለሀሜት ፥ አሉባልታ እና ለወሬ ጊዜ የላትም ልቧ በቃል የተሞላ ነው ።
5.ልባም ሴት ለባሏ ዘውድ ናት
6. ልባም ሴት ንግግሯ በጨው እንደተቀመመ ነው ።
7.ልባም ሴት ዓላማ አላት ።
8.ልባም ሴት ጊዜዋን በአግባቡ ትጠቀማለች ።
9.ልባም ሴት ይቅርታ አድራጊ ነች ቂም ጥላቻ አትይዝም ።
10. ልባም ሴት ለድሀ እና ለምስኪኖች ትራራለች ።

“ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል።”
  — ምሳሌ 31፥10


     




ራስን በትክክለኛ ሰዎች መክበብ

“ወንጌልን እንድሰብክ አደራ እንደተሰጠኝ ተገነዘቡ … እንደ አዕማድ የሚቈጠሩት ያዕቆብ፣ ጴጥሮስና ዮሐንስም፤ የተሰጠኝን ጸጋ ባስተዋሉ ጊዜ፣ለእኔና ለበርናባስ የትብብር ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤ ከዚያም እኛ ወደ አሕዛብ፣ እነርሱ ደግሞ ወደ አይሁድ እንድሄድ ተስማሙ። አጥብቀው ዐደራ ያሉን ድኾችን ማሰባችንን እንዳናቋርጥ ብቻ ነው፤ እኔም ይህንኑ ለማድረግ ጒጒቴ ነበር” (ገላ. 2፡7-10)፡፡

በአጠገባችን የሚገኙት የቅርብ ወዳጆቻችን ሁለት ነገሮችን ይጠቁሙናል፡፡ በመጀመሪያ፣ እነዚያን ሰዎች የቅርብ ወዳጅ ያደረግንበት ምክንያት ቀድሞውኑ ያለንበትን አመለካከት ደረጃ ሲጠቁመን፣ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ እነዚህ ያቀረብናቸው ሰዎች የራሳቸው አመለካከት ይዘው ወደእኛ ስለሚመጡ ለዚያ ተጽእኖ ራሳችንን የማቅረባችንን ሁኔታም ይጠቁማል፡፡ ይህ በቃሉም ሆነ በልምምዳችን የምናውቀው እውነት ነው፡፡

በሌላ አገላለጽ፣ የወዳጅ ምርጫችን ያለንን ቅድመ-አመለካከትና ለወደፊትም ያለንን ተጋላጭነት ጠቋሚ ነው፡፡ከላይ በጳውሎስ ሕይወት እንዳነበብነው፣ በአካባቢህ የሚገኙ ሰዎች የተሰጠህን ጸጋና በውስጥህ ያዘልከውን ራእይ ሲያዩና ሲሰሙ የሚያበረታቱህ አይነት ሰዎች የመሆናቸው ጉዳይ እጅግ ወሳኝ ነው፡፡

ይህንን የማድረጉ ምርጫ ደግሞ በእጅህ ላይ ነው ይለው፡፡ ለምትከታተለው ራእይና ዓላማ የሚመጥንን ወዳጅነት የመምረጥ እድሉም፣ መብቱም ሆነ አቅሙ አለህ፡፡

ስለዚህ ወዳጅ ስትመርጥ የሚከተሉትን መስፈርቶች ተመልከት፡፡

1. ዓላማህን በሚገባ የተገነዘቡትን ምረጥ

“ወንጌልን እንድሰብክ አደራ እንደ ተሰጠኝ ተገነዘቡ”

በውስጥህ ያለውን ዓላማ አንተ በምታየውና በተገነዘብከው መጠን ሙሉ ለሙሉ የሚያውቁልህ ሰዎች ማግኘት ከባድ ነው፡፡ ሆኖም ግን ያንን ለማድረግ ራሳቸውን ያቀረቡልህን ሰዎች በመለየትና የሕይወትህን ዓላማ ማካፈል መልካም ልምምድ ነው፡፡ ምናልባት ከዚህ በፊት ዓላማህን ከሰሙ በኋላ ለመደገፍ ያላቸው ፈቃደኝነት አናሳ የሆነ ሰዎች አጋጥመውህ ይሆናል፡፡ ሆኖም፣ የዓላማ ሰው ያለበትን ውጣ ውረድ በሚገባ የሚገነዘቡ ሰዎች እንዳሉም ማስታወስ ልቦናህን ይደግፈዋል፡፡

2. ከአንተ ደረጃ አለፍ ያሉትን ምረጥ

“እንደ አዕማድ የሚቈጠሩት ያዕቆብ፣ ጴጥሮስና ዮሐንስም”

ለእነ ጳውሎስ ቀኝ እጃቸውን የሰጡ ሶስቱ በሕይወታቸው የተመሰከረላቸው፣ እነሱ ካሉበት አንድ ደረጃ ከፍ ያለ ልምምድ ያላቸው ነበሩ፡፡ የበሰሉ ሰዎች ሌሎች መደገፍና ማበረታታትን ያውቃሉ፡፡ ከእኛ ደረጃ ከፍ ያሉ ሰዎች እነሱ ወደደረሱበት ደረጃ ይስቡናል፡፡ ሰዎች አሁን ካለንበት ደረጃ ደግፈውን ወደሚቀጥለው ደረጃ የማይወስዱን ስላልፈለጉ ብቻ ሳይሆን ስልቻሉም ጭምር ሊሆን ይችላል፡፡

3. ከአንተ ጋር የሚስማሙ፣ ነገር ግን በሃላፊነት የሚጠይቁህን ምረጥ

“እነርሱ ደግሞ ወደ አይሁድ እንድሄድ ተስማሙ … አጥብቀው ዐደራ ያሉን ድኾችን ማሰባችንን እንዳናቋርጥ ብቻ ነው፤እኔም ይህንኑ ለማድረግ ጒጒቴ ነበር”

በሁሉ ነገር የሚስማሙ ሰዎች ያጠፉሃል፣ በሁሉም ነገር የሚቃሙህ ሰዎች ደግሞ ከጉዞህ ይገቱሃል፡፡ ወዳጆችህን ስትመርጥ ዓላማህን በመደገፍ የሚስማሙ፣ ነገር ግን ሚዛናዊነትን ከአንተ የሚጠብቁ መሆናቸውን አረጋግጥ፡፡ የእነጳውሎስ መካሪዎች ምንም እንኳን ቢደግፏቸውም ከተሳሳተ መንገድ እንዲጠበቁ ማስጠንቀቂያና ምክርንም ለግሰዋቸው ነበር፡፡

የሚቀጥለው ትምህርት፡ “የየዕለት ልማዶችን ማዳበር”




📖“በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደ ሆንሁ እንዲሁ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፥ አልተውህም።”
                ኢያሱ 1፥5
            
              #መንፈሳዊ_ድል
              #በፓስተር_ካርል

             
#በእሁድ_የቃልና_የአምልኮ_ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል ያካፈለን #መጋቢ__ካርል ሲሆን "#መንፈሳዊ_ድል!" በሚል ርዕስ ከእግዚአብሔር ቃል (ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል) መጽሐፈ ኢያሱ 1 ቁጥር 5 ጀምሮ ያለውን ክፍል መነሻ በማድረግ ድንቅ ቃል አካፍለውናል። በዚህ ዕለትም ሠላሳ (30) አዳዲስ ነፍሳት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ተጨምረዋል። ክብር ለጌታ ይሁን።

# እግዚአብሔር የተስፋይቱን ምድር ለሙሴ ሰጠው። ነገር ግን እሥራኤል ሁሉ ያን የተሰጠውን የተስፋ ቃል ለመቀበል አልቻለም። አብዛኛው በገዛ መንገዱ ለመሄድ ያዘነብል ነበር። ስለዚህ ሌላ ትውልድ ተነሣ። ይህም ኢያሱና በእርሱ ይመራ የነበረው ሕዝብ ነው።

፨ ለኢያሱ የተገባው የተስፋ ቃል ራሱ ነበር ለሙሴም ተገብቶ የነበረው። እንዲሁም በዚህ ዘመን ላለን ለእኛ በክርስቶስ ኢየሱስ የተሰጠን የተስፋው ቃል ራሱ ሲሆን ይህም በመንፈስ ቅዱስ በኩል የተሰጠን ኪዳን ነው። ይህም የተሰጠን የቤት ሥራችንን እየሰራን እንድንጠብቅ ሲሆን እርሱም ወንጌልን ለዓለም ሁሉ እየሰበክን መኖርን ነው።

፨ ይህም የቤት ሥራ ራዕይ 5:2_9 ላይ በደንብ ተገልጿል።

፨ እግዚአብሔር ኢያሱን "በርታ፥ ጽና፥ አይዞህ!" ብሎታል። ምክንያቱም በኢያሱ ትልቅና አዲስ ነገር መሥራት ፈልጓልና። ስለዚህም ወደፊት ብቻ እንዲሄድ ይነግረዋል።

፨በዚህ ዘመን እንሄድና ወንጌልን እንሰብክ ዘንድ የመንፈስ እንጀራ ያስፈልገናል።

፨ እግዚአብሔር በዚህ ዘመንም ለዓለምና ወደ ዓለም ሁሉ እንዲሄዱ ለተልዕኮ የሚያስነሳው እንደ ኢያሱ ዓይነት የራሱ ሠራዊት አለው። ስለዚህ ወደ ግራም ወደቀኝም ማለት ትልቅ ወጥመድ ነው።

፨የእግዚአብሔር መንፈስ እንደውሃ ነው። ከቤተመቅደሱ ይወጣና ወደ ሁሉ ሥፍራ የመሄድ ኃይል አለው። ደግሞም በሕዝቅኤል መጽሐፍ እንደተጻፈው መጀመሪያ ከቁርጭምጭምት ይጀመርና በመቀጠል ወደ ጉልበት እያለ ወደ ወገብ በመድረስ መላው አካል መጥለቅና መዋኘት እስኪችል ድረስ ቀስ በቀስ ሁለንተናን ይሞላል።

፨ ወደዚህ ውሃ ጠልቀን እስክንዋኝ ድረስ እግዚአብሔር አምላክ ይናገረናል። ከዚህ የተነሣ ወደየትም ባለማየትና ቀጥታ ወደፊት ብቻ በማየት የእውነትን ወንጌል ይዞ ወደ ዓለም ሁሉ መሄድ ይሆናል። ከዚያም ወደ መንፈሳዊ ድል መሻገር ይሆናል።

👉 "ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለሁላችን ይሁን።"

        ...❤🙏❤አሜን❤🙏❤...


       @revealjesus


📖“በሕይወትህ ዕድሜ ሁሉ ማንም አይቋቋምህም፤ ከሙሴ ጋር እንደ ሆንሁ እንዲሁ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ አልጥልህም፥ አልተውህም።”
                ኢያሱ 1፥5
            
              #መንፈሳዊ_ድል
              #በፓስተር_ካርል

             
#በእሁድ_የቃልና_የአምልኮ_ጊዜ የእግዚአብሔርን ቃል ያካፈለን #መጋቢ__ካርል ሲሆን "#መንፈሳዊ_ድል!" በሚል ርዕስ ከእግዚአብሔር ቃል (ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል) መጽሐፈ ኢያሱ 1 ቁጥር 5 ጀምሮ ያለውን ክፍል መነሻ በማድረግ ድንቅ ቃል አካፍለውናል። በዚህ ዕለትም ሠላሳ (30) አዳዲስ ነፍሳት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ተጨምረዋል። ክብር ለጌታ ይሁን።

# እግዚአብሔር የተስፋይቱን ምድር ለሙሴ ሰጠው። ነገር ግን እሥራኤል ሁሉ ያን የተሰጠውን የተስፋ ቃል ለመቀበል አልቻለም። አብዛኛው በገዛ መንገዱ ለመሄድ ያዘነብል ነበር። ስለዚህ ሌላ ትውልድ ተነሣ። ይህም ኢያሱና በእርሱ ይመራ የነበረው ሕዝብ ነው።

፨ ለኢያሱ የተገባው የተስፋ ቃል ራሱ ነበር ለሙሴም ተገብቶ የነበረው። እንዲሁም በዚህ ዘመን ላለን ለእኛ በክርስቶስ ኢየሱስ የተሰጠን የተስፋው ቃል ራሱ ሲሆን ይህም በመንፈስ ቅዱስ በኩል የተሰጠን ኪዳን ነው። ይህም የተሰጠን የቤት ሥራችንን እየሰራን እንድንጠብቅ ሲሆን እርሱም ወንጌልን ለዓለም ሁሉ እየሰበክን መኖርን ነው።

፨ ይህም የቤት ሥራ ራዕይ 5:2_9 ላይ በደንብ ተገልጿል።

፨ እግዚአብሔር ኢያሱን "በርታ፥ ጽና፥ አይዞህ!" ብሎታል። ምክንያቱም በኢያሱ ትልቅና አዲስ ነገር መሥራት ፈልጓልና። ስለዚህም ወደፊት ብቻ እንዲሄድ ይነግረዋል።

፨በዚህ ዘመን እንሄድና ወንጌልን እንሰብክ ዘንድ የመንፈስ እንጀራ ያስፈልገናል።

፨ እግዚአብሔር በዚህ ዘመንም ለዓለምና ወደ ዓለም ሁሉ እንዲሄዱ ለተልዕኮ የሚያስነሳው እንደ ኢያሱ ዓይነት የራሱ ሠራዊት አለው። ስለዚህ ወደ ግራም ወደቀኝም ማለት ትልቅ ወጥመድ ነው።

፨የእግዚአብሔር መንፈስ እንደውሃ ነው። ከቤተመቅደሱ ይወጣና ወደ ሁሉ ሥፍራ የመሄድ ኃይል አለው። ደግሞም በሕዝቅኤል መጽሐፍ እንደተጻፈው መጀመሪያ ከቁርጭምጭምት ይጀመርና በመቀጠል ወደ ጉልበት እያለ ወደ ወገብ በመድረስ መላው አካል መጥለቅና መዋኘት እስኪችል ድረስ ቀስ በቀስ ሁለንተናን ይሞላል።

፨ ወደዚህ ውሃ ጠልቀን እስክንዋኝ ድረስ እግዚአብሔር አምላክ ይናገረናል። ከዚህ የተነሣ ወደየትም ባለማየትና ቀጥታ ወደፊት ብቻ በማየት የእውነትን ወንጌል ይዞ ወደ ዓለም ሁሉ መሄድ ይሆናል። ከዚያም ወደ መንፈሳዊ ድል መሻገር ይሆናል።

👉 "ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለሁላችን ይሁን።"

        ...❤🙏❤አሜን❤🙏❤...


@revealjesus


የሕይወቴን መጽሃፍ የጻፈው  እግዚአብሔር፤
ደራሲው እርሱ ነው ተራኪዋ እኔ ነኝ ፤
የመጨረሻውን ምዕራፉን ሳነበው፤
ደህና ነሽ በሎኛል ደህና ነኝ እላለው።

ደህና ደህና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን፤
ደህና ደህና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን ።


ደህና ነኝ - ቃልኪዳን ጥላሁን(ሊሊ)






" #አይኔን_ጉዳዬ_ላይ_ማድረግ! "
#ጉዳዩ ኢየሱስ ብቻ የሆነ ሰው፤ ከእርሱ ሌላ ነገር ማየት፣ ማሰብ፣ መስማት፣ ማውራት ያቃተው እንዴት የታደለ ነው?! በዚህ ቢሉት በዚያ ልቡንና አሳቡን ከተከለበት ከአምላኩ ውልፍት የማይል፣ ብዙ ነገሮች አባብለው ከትኩረቱ ሊወስዱት ቢጥሩ እንኳን ዞሮ አይኑን ወደ ተከለበት መነሻው የሚመለስ፣ ከእግዚአብሔር ውጪ ርዕስ ያጣ ሰው እንዴት የታደለ ነው?! ይሄንን እያሰላሰልኩ አንድ ነገር ትዝ አለኝ፦ ልጆች እያለን ወላጆቻችን ሱቅ አልያም ሌላ ቦታ ሲልኩን ለመሄድ ከመውጣታችን በፊት የሚሰጠን አንድ ማስጠንቀቂያ ነበር፤ "የላኩሽ ቦታ እስክትደርሺ ድረስ በየመንገዱ እንዳትቆሚ፣ ማንም ቢያናግርሽ መልስ እንዳትሰጪ፣ ቆመሽ ወሬ እንዳታዪ፣ እንዳትጫወቺ.....ወደ ተላክሽበት ቦታ ቀጥ ብለሽ ሄደሽ በፍጥነት ተመለሺ" እነዚህ እና እነዚህን የመሳሰሉት ዛቻ የተቀላቀለባቸው ጥብቅ ማስጠንቀቂያዎች ዓላማቸው ከተላክንበት ስፍራ፣ ተልከን ከወጣንበት ጉዳይ ላይ አይናችንን ሳንነቅል፣ በሌላ በምንም ነገር ትኩረታችን ሳይወሰድ፣ ከቤት የወጣንበትን ዓላማ ዘንግተን በመንገድ ላይ እንዳንባዝንና እንዳንባክን ነው። በዚህ ምሳሌ ውስጥ እኛን እና በዚህ ዘመን ያለንበትን ሁኔታ አስገብቼ ስገመግም አንዳንዴ እንዲሁም አብዛኛውን ጊዜ፣ አብዛኞቻችን አተኩረን ልናይ የተገባንን ነገር፣ ተልከን የወጣንበትን ዓላማ ዝንግት አድርገን፦ በየፌርማታው እየቆምን ሕይወት የሌለበትን፣ የማያሰነብተንን፣ የማያሳድገንን፣ የማይጠቅመንን ወሬ ማየት፤ በጠፊ በአላፊው ነገር መደነቅና መወሰድ፤ ጠልፎ በሚጥለን፣ አንቆ እንዳናፈራ በሚያደርገን፣ በመንገድ በሚያስቀረን የማይመች አካሄድ መጠመድ፤ ከግብ ሳይደርሱ እንደወጡ ለመቅረት መጣደፍ ስራችን ሆኗል።
ብልሆቹ ግን ተልከው የመጡበትን ዓላማ ሳይዘነጉ አይናቸውን ጉዳያቸው ላይ እንደተከሉ፣ ትኩረታቸው በባዕዳን ሳይቀማና ሳይደበዝዝ ከግብ ይደርሳሉ።
ጌታ እግዚአብሔር የልቦና አይኖቻችንን ያብራልን፤ ማተኮር የተገባን ነገር ላይ አይኖቻችንን ተክለን ዘመናችን እንዲጠቀለል ይርዳን!!




"መለኮታዊ ጉብኝት በኢትዮጵያ" የጸሎትና ምስጋና መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው
*****

መለኮታዊ ጉብኝት በኢትዮጵያ" የጸሎትና ምስጋና መርሃ ግብር በርካታ የወንጌል አማኞች በተገኙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተካሄደ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አቢያተ ክርስቲያናት እና በቢሊ ግራሃም ኢቫንጀሊስቲክ ማህበር ቅንጅት በተዘጋጀው በዚህ መርሃ ግብር ላይ ፤ የቄስ ቢሊ ግራሃም ልጅ ፍራንክሊን ቢሊ ግራሃም ለስብከት የተገኙ ሲሆን የጸሎትና እና የዝማሬ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑም ተገልጿል፡፡

አሁን በ Etv Facebook ገጽ ላይ live እየተካሄደ ስለሆነ በመቀላቀል ተካፈሉ 🙏


@revealjesus


በዚህ ሳምንት ለ13 ጊዜ ደጋግሜ የሰማሁት መዝሙር

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.