Postlar filtri


ጥር ፳፬ /24/


በዚች ዕለት ከእስክንድርያ አገር ከታላላቆቿ ወገን የሆነች የከበረች ተጋዳይ ማርያ አረፈች።

የዚችም ቅድስት ወላጆቿ ክርስቲያኖች ናቸው በአደገችም ጊዜ ሊአጋቧት አሰቡ እርሷ ግን ይህን ጋብቻ አልወደደችም እናትና አባቷም በሞቱ ጊዜ የተዉላትን ገንዘብ ሁሉንም ለድኆች ሰጥታ ከእስክንድርያ አገር ውጭ ከአሉ ገዳማት ወደ አንዱ ገዳም ገባች የምንኵስና ልብስንም ለብሳ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለች ለ12 ዓመትም ከቶ አትተኛም ነበር። ሁልጊዜ እስከማታ ትጾም ነበር።

በዓቷን ዘጋች ምግቧን የምትቀበልበት ትንሽ መስኮት ቀደደች ሥጋውንና ደሙን በዚያው ትቀበላለች በዚያችም በዓት ውስጥ ሃያ ሁለት ዓመት ዘግታ ኖረች። በዚያም በገድል ተጸመደች።

ጥር ዐሥራ አንድ ቀን የከበረ የጥምቀት በዓልም በሆነ ጊዜ ከተባረከው ውኃ ያመጡላት ዘንድ ለምና አመጡላት ፊቷንና እጆቿን ታጥባ ሥጋውንና ደሙን ተቀበለች ከተባረከውም ውኃ ጠጣች ከዚህም በኋላ ታመመች እስከ ጥር ሃያ አንድ ቀንም በመኝታዋ ላይ ተኛች ዳግመኛ በዚች ቀን በሃያ አንድ ሥጋውንና ደሙን ተቀበለች።

ከዚህም በኋላ እመ ምኔቷን አስጠራቻት እግሮቿንም እንድታቀርብላት ብዙ ልመናን ለመነቻትና ስታቀርብላት ሳመቻቸው ፊቷንም አሸችባቸው ወደ ክብር ባለቤት ጌታዬ ክርስቶስ ላቀረቡኝ እግሮችሽ እገዛለሁ አለች ዳግመኛም ደናግሉን ሁሉ አስጠርታ ተሳለመቻቸውና ከሦስት ቀን በኋላ እንዲጐበኟት ለመነቻቸው ይኸውም ጥር ሃያ አራት ቀን ነው በመጡም ጊዜ ሙታ አገኟት ገንዘውም ከደናግል አስክሬን ጋር አኖሩዋት።

@sebhwo_leamlakne


ጥር ፳፪ በዚህች ዕለት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ በመሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ ተሾመ፡፡

🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁


እምርተ ዕለት በዓለ ሢመትከ ዛቲ። ድኅረ ዕረፍተ እም ኪዳነ እስመ ተወከፍከ ባቲ። ዑራኤል ሥዩም ካህነ መስቀል አሐቲ። ማኅበረነ ዕቀብ ኵለሄ እምቅኔተ ሰይጣን መስሐቲ ወጽዋዓ እዴከ ፈኑ ጽሙዓነ ታስቲ


ቅዱስ ዑራኤል ኾይ ይኽች የበዓል ሢመትኽ ዕለት እጅግ የከበረች የተመረጠች ዕለት ናት። ከድንግል ዕረፍት በኋላ ቃልኪዳን የተቀበልክባት ቀን ናትና። ቅዱስ ዑራኤል ኾይ በምዕመን መስቀል ላይ የተሾምክ ታማኝ አገልጋይ ካህን ነኽና። ከአሳሳች ነፃ አውጥተኽ ማኅበራዊ አንድነታችንን ለኹልጊዜ ጠብቅ። የሃይማኖት ጥመኖችንም ታጠጣ ዘንድ የእጅኽን ጽዋ ላክልን።"

@sebhwo_leamlakne

መልክአ ቅዱስ ዑራኤል

የብርሃን መልአክ ከሣታ ምሥጢር የኾንከው  ቅዱስ ዑራኤል ኾይ ጥበቃህና የቃል ኪዳንህ ረድኤት ዘወትር አይለየን። አሜን🙏


@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁

እንኳን አምላክን ለወለደች ለእናታችን ለእመቤታች ለቅድስት ድንግል ማርያም ለዕረፍቷ በዓል (ለአስተርእዮ ማርያም)፣ ለኑሲስ ኤጲስቆጶስ ለቅዱስ ባስልዮስ ወንድም ለከበረ ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ዕረፍት በዓልና ለሮሜ አገር ንጉሥ ለዘይኑን ልጅ ለከበረች ለቅድስት ኢላርያ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ እመቤታችንንም ከመጥቁ ዮሐንስ ጋር በደብረ ማሕው ከተገለጠችበት፣ ከነቢዩ ከቅዱስ ኤርምያስ፣ ከዮሐንስና ከአባ እስክንድር፣ በዋሻ ከቅዱስ ኒቆላዎስና ከኤጲስቆጶስ ከአባ ፊቅጦር ከሁሉም ከመታሰቢያቸው፣ በናፍቁ ንጉሥ በመርቅያን ዘመን በሰማዕትነት ከዐረፉ ከቅዱሳን ጳውሎስና ከቀሲስ ሲላስ ዕረፍት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne


🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿


✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

ጥር ፳፩ በዚህች ዕለት ለከበረች አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል ነው።

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

"ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ"
ትርጉም:-
"ሞት ለሟች ይገባዋል የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል"  ቅዱስ ያሬድ


የእመቤታችን የንግሥ በዓል ነገ በምሥጋና ደብራችን በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ይከበራልና ተገኝተን በጋራ እናንግሥ።

ኑና አብረን እመቤታችንን ከፍ ከፍ እናድርጋት የወላዲተ አምላክ አማላጅነት የቅዱሳን ተራዳኢነት ከእኛ አይለየን።
አሜን🙏


እግዚአብሔር አምላክ በእናቱ በእመቤታችን አማላጅነት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ይሠውረን፡፡ አሜን!🙏

@sebhwo_leamlakne

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ ካመነኰሷቸው ከሳባቱ ከዋክብት አንዱ ለሆኑት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አፍቅረነ_እግዚእ_ዘጉጉቤን ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

@sebhwo_leamlakne


🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿


NIB DECOR 💥 dan repost
💐ንብ ዲኮር 💐
ለሰርግ
ለብራይዳል
ለመልስ
ለቤቢ ሻወር
ለልደት
ለምርቃት እንዲሁም ለተለያዩ ፕሮግራም ዲኮር እንሰራለን
ያናግሩን @pilupadier
በስልክ መስመር 0927334801
0717273301
ለመቀላቀል👇👇

https://t.me/nib_decor


ጥር ፲፮ /16/


በዚችም ቀን የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ ጰላድዮስ አረፈ።

ይህም ቅዱስ ከዋሻው ሳይወጣ የሴቶችን ፊት ሳያይ ሃምሳ ዓመት ኖረ ድንቆች ተአምራቶችን የማድረግና የትንቢት መናገር ሀብት ተሰጠው ዜናውም በቦታው ሁሉ ተሰማ።

በምስር አገር አንድ ነጋዴ በመርከብ ተጭኖ ሲሔድ ማዕበልም ተነሥቶበት ለመሥጠም ደረሰ ከሞት ከዳነም መቶ የወርቅ ዲናር እንደሚሰጥ ስለት ተሳለ ቅዱሱም አዳነው።

ከዚህም በኋላ ነጋዴው የተሳለውን ወርቅ ይዞ ወደ ቅዱሱ በዓት ሔደ። አንድ ሞሪት የሚባል ሰው አግኝቶ ሁሉንም ነገር ነገረው ሞሪትም ከቅዱሱ ዘንድ አደረሰው።  አባ ጰላድዮስም አይቶ ባረከው እንዲህም አለው በዚህ ወርቅ ፍላጎት የለኝም ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ጠቃሚ እንዲሆንህ ሒደህ ለድኆችና ለችግረኞች በትነው አለው ነጋዴው ግን ይቀበለው ዘንድ ከእግሩ ሥር ወድቆ ማለደው ጥቂትም ወሰደለትና እንዲህ አለው ለበረከት ይህን ተቀብየሃለሁ የቀረውን እንዳዘዝኩህ አድርገው አለው።

ነጋዴውም ወርቁን ይዞ ተመለሰ ሞሪትም ሰይጣን አስቶት ነጋዴውን ገሎ ወርቁን ወሰደ በድኑንም ከቅዱሱ በዓት ጣለው።   በማግሥቱም ወደ አገረ ገዥ ሒዶ ስለ ሟቹ ነገረው።

መኰንኑም አባ ጰላድዮስን አሰረውና ስለሟቹ ይመረምረው ጀመር። አባ ጰላድዮስም እርሱ እንዳልገደለው ተናግሮ በሟቹ ላይ ቢጸልይበት ነጋዴው ተነስቶ ሞሪት እንደገደለው ተናገረ። መኮንኑም ተጸጽቶ ሞሪትን ሊገድለው ወደደ አባ ጰላድዮስም አስተወው። ከብዙ ተጋድሎም በኋላ እግዚአብሔርን ደስ አሰኝቶ አገልግሎ በመልካም ሽምግልና አረፈ።

@sebhwo_leamlakne


🗓 #ነገ ማለትም
#ዕለት:- ሐሙስ
      #ቀን:- ጥር ፲፭ ፳፻፲፯(15,2017) ዓ.ም
በቅድስት ቤተክርስቲያናችን
ቅዱስ ቂርቆስ (ዓመታዊ)አቡነ ቆራይ ፣ ቅድስት ለባሲተ ክርስቶስ ፣ አቡነ ያሳይ ፣ አቡነ ተስፋ ሐዋርያ ፣ አባ ሚናት 

አክብረን እና አስበን እንውላለን::

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ አንድ የወይራ ዛፍ ተደግፈው 40 ዓመታት ለጸለዩ #ለአቡነ_አካለ_ክርስቶስ_ዘቤጌምድር ለበዓላቸው መታሰቢያ በዓል፣ #ከዘጠኙ_ቅዱሳን አንዱ ለሆኑት #ለዘሚካኤል በሚሰሩት ስራቸው አረጋዊ ለተባሉት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_አረጋዊ_ለልደታቸውና ወደ ደብረ ዳሞ ለወጡበት ቀን ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ ለቊስጥንጥንያ ንጉሥ ለቴዎዶስዮስ ልጅ ለሙሽራወ #ለቅዱስ_ገብረ_ክርስቶስ_ለበዓሉ መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

@sebhwo_leamlakne

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿


#ተመስገን

ተመስገን /3/ ለምስጋና ስላሰባሰብከን
እግዚአብሔር ተመስገን /2
አዝ

ሁሉን ስሰጠን ያለ ዋጋ ነው
ግን ምንዘምረው ተደርጎልን
ነው
በነፃ አይደለም የምናዜምልህ
ተቀብለን ነው ወስደን ነው ከእጅህ
ተመስገን ነው የአንተ እጅ ሲሰጥ
ተመስገን ነው ሰቶ እንዳልነበር ነው
ተመስገን ነው የዃላን አይሰፍርም
ተመስገን ነው ወስዶ ነበር አይልም
አዝ

ለሁሉም ፀሐይ ቀን የምታወጣ
ድሃን አትንቅም ገንዘብ ስላጣ
ባይኖረው እንኳን በአንተ ይኖራል
ቆርሰህ ስሰጠው ተመስገን ይላል
ተመስገን ነው ክብርህ አይጓደል
ተመስገን ነው በሰማይ በምድር
ተመስገን ነው የድሃ አደጉ አባት
ተመስገን ነው ደጉ እግዚአብሔር
አዝ

ውጊያን ለራስህ ለእኛ ድል ሰተህ
ከክብር ሰገነት ታኖረናለህ
ጠላት እያየ ዘይት የምትቀባ
ፅኑ ግንብ ነህ መጠጊያ አንባ
ተመስገን ነው በመልካምነትህ
ተመስገን ነው ያላሰብከው ማነው
ተመስገን ነው ከአንተ ያገኘነውን
ተመስገን ነው ቆጥረን አንጨርሰው
አዝ

በስደት ሀገር ወተን እርቀን
አንተን ለመማር ሰበሰብከን
የእኛ የምንለው ባይኖረን እኛ
አንተ አለኸን ብርቱ መፅናኛ
ተመስገን ነው በማለዳ አውጥተህ
ተመስገን ነው ሰርክ የምትመልስ
ተመስገን ነው መልካም እረኛነህ
ተመስገን ነው ኢየሱስ ክርስቶስ
አዝ

በጌታ ድጋፍ የቆመ ሰው
ምድር ገፍትራ ጠልፋ አትጥለው
የሺውን ታሪክ በቀን ይሰራል
ሁሉን በሚችል ሁሉን ይችላል
ተመስገን ነው ሌላ ምን ይባላል
ተመስገን ነው ለአንተ ምን ይሰጣል
ተመስገን ነው ሁሉን አሳለፍከው
ተመስገን ነው አዲስ አደረከው

ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇

@ney_ney_emye_maryam
     #ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏

    
🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


ጥር ፲፫ /13/

በዚችም ቀን አባ ነካሮ አረፈ።
ይህም ቅዱስ ሰው ሳያውቀው በሥውር የሚጋደል ሆነ እርሱም ከምንጣፉ በታች እሾህ ይጐዘጕዛል ጤና አግኝቶ እንዳይተኛ ነው በቀንና በሌሊትም ለጸሎት ይተጋ ነበር።

ከትሑትነቱም የተነሣ የበር ጠባቂ አደረጉት። በዚያም ገዳም በመንፈስ ቅዱስ የተሠወሩ ነገሮችን የሚያይ ባሕታዊ መነኰስ አለ በአንዲትም ሌሊት በሕልሙ በከፍታ ቦታ ላይ ቁሞ አየ ከበታቹም ፍሬው በየዓይነቱ የሆነ አትክልት አለ ወንዞችም ከበውታል አባ ነካሮም በመካከላቸው ሁኖ በወዲያና በወዲህ ያጠጣቸው ነበር።

ያ መነኰስም ወንድሜ ነካሮ ሆይ ይህ አትክልት የማን ነው አለው አባ ነካሮም እኔ የተከልኳት ናት ብሎ መለሰለት መነኵሴውም ከፍሬዋ ትሰጠኝ ዘንድ እሻለሁ አለው አባ ነካሮም ሦስት የሮማን ፍሬ ቆርጦ ሰጠው በልብሱም ቋጠረው።

በነቃም ጊዜ እነዚያን የሮማን ፍሬዎች አገኛቸው ወዲያውኑ ወደ አባ ነካሮ ሔደ ከበር ቁሞ አገኘውና ወንድሜ ነካሮ ሆይ በዚች ሌሊት አይተኸኛልን አለው እርሱም አዎን አይቼሃለሁ ሦስት የሮማን ፍሬዎችን ሰጥቼህ የለምን አለው። በዚያንም ጊዜ ያ መነኵሴ ወደ ገዳሙ ሔዶ የሆነውን ሁሉ ለአበ ምኔቱና ለመነኰሳቱ ነገራቸው እነዚያንም የሮማን ፍሬዎች አሳያቸው መነኰሳቱም ከአባ ነካሮ ቅድስና የተነሣ አደነቁ ያን ጊዜም የበጋ ወራት ነበረና የሮማንም ጊዜው አልነበረምና።

በዝቅተኛ ማዕረግ ላይ ስለአደረጉት መነኰሳቱ አዘኑ በከፍተኛም ማዕረግ ሊያደርጉት ሽተው ወደርሱ በሔዱ ጊዜ አጡት ታላቅ ኀዘንንም አዘኑ ከዚህም በኋላ በዚች ዕለት እንዳረፈ መጻተኞች ነገሩአቸው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር


@sebhwo_leamlakne


✨✨✨🍶🍶🍶✨✨✨🍶🍶🍶✨✨✨

✨✨🍶ወይን እኮ የላቸውም✨✨🍶

የቃና ዘገሊላ ታሪክ ውስጥ አስደናቂ ከኾኑ ክስተቶች ውስጥ አንዱ የወይን ማለቅ ጉዳይ ነው። በእርግጥ ቃና ዘገሊላ ውስጥ የተፈጸመው የሰርግ ጉዳይ ጥልቅ መልእክቶችን የተሸከመ መኾኑ በብዙ የሚብራራ ነው። ታሪኩን በጥልቀት ለመረዳት ግን ወደ ታሪኩ ጥልቀት ውስጥ የምንገባበትን በር ማግኘት አለብን። የዮሐንስን ወንጌል ምሥጢራዊነት ወደ መረዳት ከፍታ እስካልወጣን ድረስ በወንጌሉ ውስጥ የተፈጸሙትን አስደናቂ ክስተቶች በአግባቡ መረዳት አንችልም። ማክሲመስ ተናዛዚው መጽሐፍ ቅዱስን በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያን ይመስልና የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለችውን ቅድስተ ቅዱሳን ትመስላለች ይላል። ይህ የሚያመለክተው ወንጌሉ የተሸከመውን ጥልቅ ምሥጢር ነው። እንዲያውም ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ ሦስቱን ወንጌላት በሥጋ የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በመንፈስ ይመስላል። የሌሎቹ ወንጌላት እስትንፋሳቸው የዮሐንስ ወንጌል ነውና!!

ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ የዮሐንስን ወንጌል ለመረዳት ሊቁ ኦሪገን እንዳለው ወደ ጌታ ደረት ጋር ጠጋ ብሎ እንደ ዮሐንስ ከጌታ እመቤታችንን መቀበልን ይጠይቃል። ይህ ኹሉ የሚያመለክተው በወንጌሉ ላይ የተጻፉ ክስተቶችን በችኩልነትና በለብ ለብ ስሜት አልፈን እንዳንሄድና በጥልቀት እንድንመረምር ነው። ሠርግ የተፈጸመባት የገሊላዋ ቃና ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያምን በመያዟ ከሚመጣባት ጉድለት ስትድን እንመለከታለን። ከክርስቶስ ጋር ለምናደርገው ግንኙነት የእመቤታችን ልመና እጅግ አስፈላጊ ነው። እርሷ ቀድማን ጉድለታችንን ባታሰማልን ኖሮ መሽራው ክርስቶስ እንዴት ይቀበለን ነበር!!


ጥምቀትን የጀመረዉ ማነዉ ?
So‘rovnoma
  •   አዳም
  •   አብርሃም
  •   ሙሴ
  •   መልስ የለም
1 ta ovoz


#ብፅዕት_ነሽ

ከእግዚአብሔር ተልኮ የነገረሽን ቃል
አምነሽ የተቀበልሽ ብፅዕት ነሽ ድንግል (2)

በገሊላ ሳለሽ በናዝሬት ከተማ
ከመላዕክት ዓለም ከሰማይ ከራማ
ብርሃናዊው መልአክ ተሸክሞ ዜና
ደስታን አበሰረሽ በታላቅ ትህትና

እኔም ላመስግንሽ ማርያም ድንግል
እንደ ብስራታዊው እንደ ገብርኤል

ሰላም ለኪ ማርያም ድንግል ሆይ አትፍሪ
መዓዛሽን ወዷል እግዚአብሔር ፈጣሪ
ሞገስ አግኝተሻል በቅድመ  ሥላሴ
ክብርን የተመላሽ ምልዒተ ውዳሴ

እኔም ላመስግንሽ ማርያም ድንግል
እንደ ብስራታዊው እንደ ገብርኤል

ትወልጂያለሽ ጌታን በመንፈስ ቅዱስ
ትጠሪያለሽ ስሙን ብለሽ ኢየሱስ
በያዕቆብ ወገን ይነግሣል ዘላለም
ለመንግስቱ ሽረት ፍጻሜ የለውም

እኔም ላመስግንሽ ማርያም ድንግል
እንደ ብስራታዊው እንደ ገብርኤል

ዘመድሽ ኤልሳቤጥ ሳትወልድ የኖረች
በእርጅና ዘመኗ ወንድ ልጅ ጸነሰች
እያለ ሲነግርሽ የሰማዩ ምስጢር
ይሁንልኝ ብለሽ ተቀበልሽ በክብር

እኔም ላመስግንሽ ማርያም ድንግል
እንደ ብስራታዊው እንደ ገብርኤል

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


በአብርሃም ቤት የተገኙ ቅድስት ሥላሴ በቤታችን በሕይወታችን ይግቡ 🙏❤️🙏




🕯ጥር ❼ 💓
።።።።።።።።።።


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🗓 #ነገ ማለትም
#ዕለት:- ረቡዕ
#ቀን:- ጥር ፯ ፳፻፲፯ ዓ.ም

በቅድስት ቤተክርስቲያናችን
✅🔸🔹
አጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ (ዓመታዊ)
ስዕለተ ማርያም ፣ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫ ፣ ቅድስት እኅተ ጴጥሮስ


አክብረን እና አስበን እንውላለን።

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴

እንኳን #በቤተ _ልሔምና_አውራጃው ላሉ ንጉሥ ኄሮድስ በግፍ ለገደላቸው #ለዐሥራ_አራት_እልፍ_አራት_ሺህ_ለንጹሐን_ሕፃናት ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓልና  ከዘጠኙ ቅዱሳን ቀድመው ወደ አገራች ኢትዮጵያ ለመጡ #ደብረ_ሊባኖስ_ገዳም_በስማቸው ለተሰየመላቸው ከዐለት ጠበል እያፈለቁ ድውያንን ለሚፈውሱት ለተአምረኛው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሊባኖስ (መጣዕ) ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ የሴቶችን ጠጉር ሹሩባ ሲሠሩ ከኖሩ# ከአባ አሞን፣ ከታላቁ ነቢይ #ከቅዱስ_ኢሳይያስና_ከቅዱስ_ስምዖን ግብፃዊ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️


🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴

እንኳን #ለኢትዮጽያዊ_ጻድቅ በዓለም ላይ በንግሥና መኖርን ንቀው ለመነኑትና ብዙ ተአምራትን በማድረግ ለሚታወቁት #ለንጉሥ_ዐፄ_ይኩኖ_አምላክ ልጅ ለሆኑት #ለአቡነ_ገብረ_ክርስቶስ_ዘዳግና ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለሊቀ ሰማዕታት #ለቅዱስ_ጊዮርጊስ_ለልደት በዓል በሰላም አደረሰን።


@sebhwo_leamlakne💫


🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️


ጥር ፪ /2/


በዚችም ቀን የከበረ አባት አላኒቆስ ኤጲስቆጶስ በሰማዕትነት ሞተ።

እርሱ ጣዖታቱን እንዲአቃልሉ ለሰዎች እንደሚያስተምራቸው ከሀዲው ንጉሥ በሰማ ጊዜ ይዘው ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ መልእክተኞችን ላከ።

የንጉሥ መልክተኞች መላካቸውን የተመሰገነ አላኒቆስ ሰምቶ በሀገረ ስበከቱ ያሉትን ሕዝቦች ሰበሰባቸውና የቁርባን ቅዳሴን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው ። ከዚህም በኋላ በቀናች ሃይማኖት ጽኑ ከእንግዲህ ፊቴን አታዩኝም አላቸው ። እነርሱም አለቀሱ ሊአስተዉትም አልተቻላቸውም ወጥቶም ራሱን ለንጉሥ መልክተኞች አሳልፎ ሰጠ እነርሱም ወስደው ለእንዴናው አገር መኰንን ሰጡት።

እርሱም ወደ ሀገረ እንድኩ ወስዶ በዚያ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱም በሰለቸው ጊዜ ትከሻውን በሰይፍ ይሠነጥቁ ዘንድ ራሱንም ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ መሞቱን አውቆ አማንያን ከሆኑ መርከበኞች አንዱን እንዲህ ብሎ አዘዘው ወደ ወደቡ ስትደርሱ ሥጋዬን በኮረብታ ላይ አድርግ እርሱም እንዳዘዘው አደረገ።

ከዚህም በኋላ ምእመናን ሰዎች መጥተው ሥጋውን ወስደው ገነዙት የስደቱም ወራት እስቲያልፍ በእነርሱ ዘንድ አኖሩት ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

@sebhwo_leamlakne


🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴

እንኳን #ለሊቀ_ዲያቆናት_ለቀዳሜ_ሰማዕት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ_ለልደቱና_ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ከሶርያ_አገር_ለሆነ በከሀዲው መክስምኖስ ዘመነ መንግስት ሰማዕትነት ለተበቀበለ #ለቅዱስ_ለውንድዮስ ለዕረፍት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ ስልሳ ዘጠነኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_መቃርስ ዕረፍት፣ #ከከበሩ_ከአክሚም_ሰማዕታት የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ከፈጸሙ ስማቸው #ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስና_ሰከላብዮስ ዕረፍት፣ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰማዕትነት ከተቀበሉ ቊጥራቸው #ከካህናት_ስምትት_መቶ፣ #ከዲያቆናት_መቶ_ሠላሳ_ከመምህራን_ኃምሳ፣ #ከሦስት_ከቤተ_ክርስቲያን_ሹማምንት_ከሰማንያ_መሳፍንት_ከሠላሳ_ሁለት_ንፍቅ_ዲያቆናትና_ከመቶ_ኃምሳ_ሕዝባውያን ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne

🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️🔱⚜️

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.