Postlar filtri


በእግዚአብሔር የሚያምኑ ሰዎች መደሰት የማይገባቸው በምንድን ነው?
So‘rovnoma
  •   በጭፈራና በዘፈን
  •   በእግዚአብሔር
  •   ወደ እግዚአብሔር ቤት በመሄድ
  •   ለ እና ሐ
177 ta ovoz


ጌታችን መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አብይ ፆምን የፆመው የት ሆኖ ነው ?
So‘rovnoma
  •   ገዳመ ቆሮንቶስ
  •   ደብረ ዘይት ተራራ
  •   ደብረታቦር
  •   ቀራኒዮ
240 ta ovoz


የካቲት ፳፭ /25/


በዚች ቀን የከበሩ አውሳንዮስና ፊልሞና ስሟ ሉቅያ የሚባል አንዲት ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ።

እሊህ ቅዱሳንም በአፍራቅያ ሀገር ሳለ በከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ትምህርት ያመኑ ናቸው ከሀድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለሚጠሩት ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን በአደረጉ ጊዜ አይተው በስሕተታቸው ሊዘብቱ እሊህ ቅዱሳን ተሰብስበው ወደ ጣዖቱ ቤት ገቡ ሰዎችም ለጣዖቱ ሲሠዉና ከፍ ከፍ ሲያደርጉት በአዩአቸው ጊዜ በክብር ባለቤተ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እሳትነት ልባቸው ነደደ ከጣዖቱም ቤት ወጥተው ወደ ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሔደው የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብሩንና ልዕልናውን አብዝተው አመሰገኑ።

ከዚያ ካሉት አንድ ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደ ዘበቱ የተናገሩትን ልብ ብሎ በመኰንኑ ዘንድ ወነጀላቸው መኰንኑም በፈረስ ተቀምጦ ሔደ ከወታደሮቹም ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ከበባት ከምእመናንም ሰዎች የሸሹ አሉ።

እሊህንም ሦስቱን ቅዱሳን ያዛቸው የብረት ዘንጎችን በእሳት አግለው በቅዱሳኑ ጐኖች ውስጥ አደረጉት ከዚህም በኋላ የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጒድጓድ ወረወሩትና ነፍሱን እስከ ሰጠ ድረስ በደንጊይ ወገሩት።

የከበረ ፊልሞናንና የከበረች ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ በጸና ሥቃይ ያሠቃዩአቸው ጀመር ነፍሳቸውንም ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን ወሰደ።

በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነሆ የምስክርነታቸውና የሃይማኖታቸው መታሰቢያ ተጽፎአል ። በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@ney_ney_emye_maryam
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


እንኳን ለከበሩ #በቅዱስ_ጳውሎስ ትምህርት ላመኑ #ለቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞ፣ ለድንግል #ቅድስት_ሉቅያ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለከበረ #ሐዲስ_አባ_እንጦኒ ይህም ረውሕ ለሚባለው ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ ለሆነ ዐሥራ ስምንቱ ዓመት ቆሞ ሳይቀመጥ ለጸለየ #ለአባ_አቡፋ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሮሜ አገር #ከዲያቆን_ቶና ከአገረ ቊስ #ሚናስ_ከጋዛ_ይልማድዮስ በሰማዕትነት ከዐረፉ፣ #ከደማይልናልና_ከርጊኖስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ  ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።

@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


ጌታዬና አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
✍️✍️✍️✍️✍️
በዚያ በምኩራብ ስታሰተምር ሳለ ፲፰ አመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባትንንና ቀና ብላ ትቆም ዘንድ የማትችለውን ሴት ከድካምሽ ተፈትተሻል ባልካት ጊዜ ቀጥ ብላ እንደቆመች፤ እኔም የኃጢአቴ ብዛት እንደ ሸክም ከብዶኝ ጎብጫለሁና አቤቱ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ሸክሜን አንሳልኝ፤ ቀና ብዬ እንድሄድ እርዳኝ።

አሜን 🙏🙏
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


#አማኑኤል_ይቅር_ባይነዉ

አማኑኤል ይቅር ባይነዉ ፍቅር
ምህረት ከቦት በሰማያት ሚኖር
እያመመው አባቱን እየጠራ
አይቻለው ለሚገድሉት ሲራራ

#አዝ

አይምረኝም አትበሉ ጨካኝ ንጉስ አይደለም
ደሙ ብቻ ያነፃናል ከሀጢአታችን ዘለዓለም
እንደሞላ ጅረት ፈሶ ምድራችንን አጥለቅልቋል
የእሱ ምህረት ሀይል ሆኖት ስንቱ ከሞት አፈትልኳል

#አዝ

የጨለመው እየነጋ የተሻለ ቀን ይመጣል
በፍቅሩ ጦር ሳይወጋ ማን ከሞት እሮጦ ያመልጣል
ያን ክፉ ቀንበድል አልፈን እንደ ዋርካ የሰፋነው
ነውርን ሁሉ በሚከድን በሞተልን በኢየሱስ ነው

#አዝ

የእሱን ፍቅር የሚያሸንፍ አንዳች ሀጢአት የለምና
ወደጌታ ለመመለስ አንዳች እንኳን እዳትፈራ
ሀገራችን በሰማያት ነው የሚወድቅ የለም የሚረሳ
ሰማያትን እንወርሳለን ከቤቱ ደም የተነሳ

#አዝ

ወዳጅ አለን አንድ ብቻ በሰማያት የምድርም
ስሙ ኢየሱስ የተባለ ሰውን ሁሉ የሚያፈቅር
ከመቃብር በላይ ሆኖ ፍቅሩ አለምን አስገረመ
እሄን ሁሉ ጎስቋላ ሰው በትክሻው ተሸከመ

ዘማሪ ዕዝራ ኃ/ሚካኤል


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


ይህንን checklist ይጠቀሙ።


የሳምንት 2 ቅድስት ቻሌንጅ

ዳሩ ግን፦እኔ ቅዱስ ነኝና ቅዱሳን ኹኑ ተብሎ ስለ፡ ተጻፈ የጠራችኹ ቅዱስ እንደ ኾነ፡ እናንተ ደግሞ በኑሯችኹ ዅሉ ቅዱሳን ኹኑ።
-1ኛ ጴጥ 1:15-16


የካቲት ፳፬ /24/


በዚች ቀን የከበረ አባት ኤጲስቆጶስ አጋቢጦስ አረፈ።

ይህም አባት በከሀድያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ነበር። ወላጆቹም ደጎች ምእመናን ነበሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረውት ዲቁና ተሾመ።

ከዚህም በኋላ እናትና አባቱን ትቶ ወደ አንድ ገዳም ሔዶ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደለ የሸመገሉ መነኰሳትን አገለገለ። የተጋድሎውና የኃይሉ ጽናት ወሬው በተሰማ ጊዜ ስሙ ሉክያኖስ የሚባል መኰንን ወደርሱ ልኮ አስመጥቶ ያለ ውዴታው በግድ የጭፍራ አለቃ አድርጎ ሾመው።

ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እጅግ የሚወደው መልከ መልካም የሆነ ወጣት ብላቴና ነበር ክፉ ጋኔንም ያሰቃየው ነበር። ከዚህ ከአስጨናቂ ደዌ ያድነኝ ዘንድ የወታደሩ አለቃ አጋቢጦስን ፈጥናችሁ አምጡልኝ አለ።

ቅዱሱም በእግዚአብሔር ኃይል አዳነው በመጨረሻም ንጉሡን ከወታደርነት ውስጥ አሰናብተኝ አለውና አሰናበተው አስቀድሞ ወደ ነበረባትም ቦታው ተመለሰ ብዙ ዘመናትም እጅግ እየተጋደለ ኖረ። በዚያችም አገር በኤጲስቆጶስነት ተሹሞ በዙ ተአምራትን እያደረገ የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለም አሜን።

@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን ለከበረ አባት ለንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ወታደር አለቃ ለነበረው ብዙ ተአምራትን ላደረገ፤ ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ለገደለው ለኤጲስቆጶስ ቅዱስ አጋቢጦስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ በጋዛ ሰማዕት ከሆኑ ከጢሞቴዎስ፣ ከቆጵሮስ ከአገረ ከሚናስ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁


አንተ ሰይፍና ጦር ጭሬም ይዘህ ትመጣብኛለህ እኔ ግን ዛሬ በተገዳደርኸው አምላክ ስም በሰራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ስም እመጣብሃለሁ።
1ኛ ሳሙ 17፡45

ዐድዋ - ቅዱስ ጊዮርጊስ ገበዘ ኢትዮጵያ


የካቲት ❷❸

እንኳን ለኢትዮጵያ ገበዝ (ጠባቂ) ለአድዋው አርበኛ፣ ለፍጡነ ረድኤት፣ ለገባሬ ተአምር ሊቀ ሰማዕታት ለቅዱስ ጊዮርጊስ በ1888ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ንጉሠ ነገሥትን ምኒልክና ሰራዊቱ ለረዳበት፤ ኢትዮጵያ በሮማውያንን (ጣልያንን) ድል ለተቀዳጀችበት ለ129 (ለአንድ መቶ ሃያ ዘጠነኛው ) ለአድዋ በዓል በሰላም አደረሰን።

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


[ቅዱስ ጊዮርጊስ (ዓመታዊ)
ልበ አምላክ ዳዊት፣ ጠቢቡሰለሞን፣ሰማዕቱ ቅዱስ ቤድራቶስ]

አክብረን እና አስበን እንውላለን።

(#ዕለት:- እሁድ
      #ቀን:- የካቲት ፳፫ ፰፳፻፲፯ ዓ.ም)


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨

ጊዮርጊስ ሆይ፤ ለክብርት ክንድህና ተባባሪዋ ለሆነችው መዳፍህም ሰላም እላለሁ። እንዲሁም ለጣቶችህና እንደ ዕንቍ ፊርጥ ለሚያበሩ የእጆችህም አጽፋር ሰላም እላለሁ።

ተአምር ሠሪው ሰማዕት ሆይ፤ የሰማዕታትና የጭፍሮቻቸው ሁሉ አለቃ ነህና አቤቱ በጥበብህ ከባሕረ ኅዘን አሻግረን በባሕር ላይ መሄድ ያልለመደ የባሕርን ጠባይ ሊያውቅ አይችልምና።

#መልከአ ጊዮርጊስ

@sebhwo_leamlakne

🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨🍁🍁🍀🍀✨


የንሰሐ መዝሙሮች


#ለድሆች_ወንጌ

#መሠረቷ_ጉል

#መች_ይረ

#መፃ

#ማረኝ_መመኪ

#ሰላሜ_ነህ_ፀጥ

#ርግብና_ዋ

#በርጠሚዮስ_

#በብርሀን_ፀ

#በቤተ_መቅደ

#በሚፈርደው_ፈረዱ

#በፈቃዱ_ለሕማም_ተ

#በፍቅር_ላዚ

#ታላቅ_መሆን_የፈ

#ና_ና_የምስጋና_
ጌታ
#እውነት_ስለ

#እንተ_በህ
ሊና
#እንደ_ቸርነትህ
#እኔ_አንተ_

#እኔ_እሆ
ንን
#እኔስ_በምግባሬ
#እጠበኝ_ቆሽሻ

#እኔን_ደካማ
ውን
#ኪዳነምህረት_እናቴ
#ዓለምን_ለማ

#የሉም_ከሳ

#ያንተ_ይሁን_ምር

#ይቅር_ስላልከኝ_

#ደም_ግባት_አ

#ዘወ

#ፈቃዴ_ነው_የሰውን_ነገር_ላልና

#ፈ
ራሁ




መዝሙራቱ ለፍለጋ እንዲመቹ በፊደል ተርታ የተቀመጡ ሲሆን ከዚህ ዝርዝር ውስጥ የፈለጋችሁትን መዝሙር ስትነኩት ከስር ቀስት ያመጣላችኋል ቀስቱን በምትነኩበት ሰአት ቦታው ላይ ይወስዳችኋል

እንዲሁም ከዚህ ከማውጫው ግርጌ leave a comment  የምትል ቦታ አለች እሱን ቦታ በመንካት አስተያየት መስጠት እና ጥያቄ መጠየቅ ትችላላችሁ።
የአባቶ ች አስተማሪ ትምህርቶች


እሰይ ነጋ - ቅዱስ ኃያል፣ የድንግል ልጅ ልዑል እግዚአብሔር ክበር ተመስገንልን።
በፍቅር ዋሉ ክርስቲያኖች!

በመለኮት ሞት ሳይኖርበት በሥጋ ሞትን ገንዘብ አደረገ ፤ በመለኮት መወሰን ሳይኖርበት በሥጋ ተወሰነ፥ የማይመረመር ሰማያዊ እርሱ ሥጋን ተዋሕዶ በምድር ተገለጠ ፤ የማይታየው ታየ ፥

በኃጢአት ወድቆ የነበረ የቀደመ ሰው አዳምን ዳግመኛ ያከብረው ዘንድ እግዚአብሔር ፍጹም ሥጋን ነፍስንም ተዋሕዶአልና።

#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘእንዚናዙ  


#ጾም_ጸሎት_ስግደት #ወላዲተ_አምላክ_ማርያም
መልካም ቀን! ውድ የተዋሕዶ ልጆች🙏


እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን( መዝ 150 - 6 )

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መዝሙሮችን ለማግኘት
ይሄን link በመንካት ይቀላቀሉን 👇👇👇


@Sebhwo_leamlakne
#ሼር
🙏🙏🙏🙏🙏


🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ🕊


✨🌱🍂✨️🌱🍂✨️🌱🍂✨️🌱🍂✨️🌱🍂✨️

‘’አዳም ከልጆቹ ጋር ያመሰግንሻል። በሱ የተፈረደ መርገመ ሥጋ ባንቺ ጠፍቷልና፡፡…

ዕብራዊው ያዕቆብም ከልጁ ከይሁዳ ጋር ያመሰግንሻል። የርሱ በረከት በልጅሽ ተፈጽሟልና። እግዚአብሔር ይሁዳን ባረከው እንዲህ ሲል፡፡ ይሁዳ ሆይ ወንድሞችህ አንተን ያመሰግናሉ። እጅህ በጠላቶችህ ደንደስ ላይ ነው፡፡ የአባትህ ልጆች ይሰግዱልሃል፡፡…

ሙሴ ከእስራኤል ልጆች ሁሉ ጋር ያመሰግንሻል። እግዚአብሔር በሙሴ ኦሪት ስላንቺ እንዲህ ይላልና፡፡ ሰማይ አድምጥ እነግርህማለሁ ምድርም ያፌን ነገር ትስማ። ትምህርቴም እንደ ዝናብ ትፍሰስ ነገሬም እንደ ጠል እንደካፊያም በእርሻ ላይ ይውረድ። እንደ ጠፈጠፍም እንደ ነጠብጣብም ሣር ይሁን። እንግዲህ አንቺን እርሻ ብሎ ጠራሽ ልጅሽን ደግሞ ጠል አለው፡፡

ዳዊት ከመዘምራን ጋር ያመሰግንሻል። እንዲህ ሲል መሠረቶቿ በተቀደሱ ተራራዎች ናቸው። እግዚአብሔር ከያዕቆብ መኖርያዎች ይልቅ የጽንን ደጆች ይመርጣቸዋል። የእግዚአብሔር አገር ሆይ በአንቺ የተከበረ ነገር ይባላል፡፡

ማኅበረ መላእክት ሁሉ ያመሰግኑሻል። በንጽሕና ሥርዓት እርሳቸውን መስለሻልና፡፡

ማኅበረ ነቢያት ሁላቸው ያመሰግኑሻል። ትንቢታቸው ባንቺ ተፈጽሟልና፡፡

የሐዋርያት ማኅበር ያመሰግኑሻል። የተወደደ ልጅሽ ወንድም ሆኗቸዋልና። ለመንግሥቱም ወራሾች አድርጓቸዋልና፡፡

የበጎ ጎልማሶች ሰማዕታት ያመሰግኑሻል። የልጅሽን መከራ አንድነት በሥጋቸው ተቀብለዋልና፡፡

ደናግል መነኮሳት ያመሰግኑሻል። አኗኗራቸውን ለንጽሕናሽ አምሳል ብፅዓት አድርገዋልና፡፡

ሊቃነ ጳጳሳት ኤጲስቆጶሳት ያመሰግኑሻል። የልጅሽ አንደበት ሥልጣን በአንደበታቸው ተዋህዷልና።

ቀሳውስት ያመሰግቡሻል። ለክህነታቸው መዓርግ ልጅሽ አለቃ ሁኗልና፡፡

ስለ በጎ መልእክት የሚፋጠኑ ዲያቆናት ያመሰግኑሻል። በልጅሽ ገዥነት የምሥጢር አገልጋዮች መልእክተኞች ሆነዋልና፡፡

አናጉንስጢስ መዘምራን ያመሰግኑሻል። ለልጅሽ ምስጋና በቤተ መቅደስ ድምፃቸው እንደ ወርቅ ጸናጽል ይሰማልና፡፡

የክርስቲያን ማኅበር ሁሉ ያመሰግኑሻል፡፡ ከልጅሽ ከቀኙ ጎኑ የተገኘውን የጥምቀት ድርብ በፍታ ተጎናጽፈዋልና፡፡''

ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
አርጋኖን ዘሰኑይ ምዕ ፲፪ ፥ ፮ - ፴፭




@sebhwo_leamlakne

✨🌱🍂✨️🌱🍂✨️🌱🍂✨️🌱🍂✨️🌱🍂✨️


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿

እንኳን  አምላክን ለወለደች #ለእመቤታች_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም ለወራዊ በዓልዋ መታሰቢያ፣ ለከበረ ለሐዋርያው #ለቅዱስ_ጳውሎስ ደቀ መዝሙር ለሆነ #ለቅዱስ_አናሲሞስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ ለእስክድርያ ኃምሳ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳሳት #ለአባ_ገብርኤል ለዕረፍት በዓልና ለአገረ ስሐ ኤጲስቆጶስ ለከበረ አባት #ለአባ_ዘካርያስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ከአባ_አካክዮስና ከኢትዮጵያ አገር ጳጳስ #ከአባ_ገብርኤል ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።


@sebhwo_leamlakne


🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿


እግዚአብሔር ቀስተ-ደመናን የቃልኪዳን ምልክት አድርጎ የሰጠው ለማን ነው?
So‘rovnoma
  •   ኖህ
  •   ሙሴ
  •   ያዕቆብ
  •   አብርሃም
452 ta ovoz


በራዕይና በህልም አስተዋይ የነበረው ማን ነው?
So‘rovnoma
  •   ሰሎሞን
  •   ዳዊት
  •   ዳንኤል
  •   ሳምሶን
420 ta ovoz

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.