ሰሌዳ | Seleda


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ @Contact_officework ያናግሩን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


⚡️በአዲስ አበባ ከተማ 18 ሄክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ ሊቀርብ ነው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያቀርብ ነው። በመዲናይቱ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች የሚገኙት እነዚህ ቦታዎች፤ ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸው ተገልጿል።

በከተማይቱ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት እና ባንክ ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች “በተለያየ አግባብ ወደ መሬት ባንክ የገቡ ይዞታዎች” ናቸው። በአሁኑ ዙር ጨረታ በቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመሬት ይዞታዎች እንዳልተካተቱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች ዝርዝር፤ በነገው ዕለት ታትሞ በሚወጣው “አዲስ ልሳን” ጋዜጣ ማግኘት እንደሚቻል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ይህንን ተከትሎ የጨረታ ሰነድ ሽያጩ “ከእጅ ንኪኪ በጸዳ መልኩ” ከመጪው ሰኞ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 12 ድረስ ባሉት ቀናቶች የሚከናወን መሆኑንም ጠቁሟል።

@seledadotio
@seledadotio


✨አየር መንገዱ ዛሬ ማታ የሚጀመሩ ሁለት በረራዎችን ጨምሮ በሴቶች ብቻ የሚደረጉ 6 በረራዎች ሊያካሂድ ነው።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ በሴቶች ብቻ የሚደረግ በረራ ሊያካሂድ መሆኑን አስታውቋል።


በረራው ወደ 6 አገራት የሚደረግ ሲሆን፤ ሁለቱ ዛሬ ማታ የቀሩት አራት በረራዎች ደግሞ ነገ የሚደረጉ ናቸው።


በረራዎቹ  ከካፒፔን እስከ አየር ተቆጣጣሪ እና ቴክኒሻን ድረስ በሴቶች ብቻ የሚደረጉ መሆናቸው ተገልጿል።


ባህርዳር፣ አቴንስ፣ ዴልሂ ፣ዱባይ፣ ሳኦፖሎ እና ዊንድሆክ ከተሞች መዳረሻ ናቸው ተብሏል።


በዓለም ለ114ኛ ጊዜ በአገራችን ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረው የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በረራዎቹ መዘጋጀታቸው ነው የተገለፀው።


ዕለቱ "መብት፣ እኩልነት እና አቅም መጎልበት ለሴቶች በሙሉ" በሚል መሪ ቃል የሚከበር ይሆናል ተብሏል።


አየር መንገዱ አሁን ላይ 8 ዋና አብራሪ ሴት ካፒቴኖች እና 70 ምክትል ሴት አብራሪዎች እንዳሉት ተገልጿል።

@seledadotio
@seledadotio


👀የሚስቱ እግር እባብ መስሎት ከባድ ጉዳት ያደረሰው ባል

ይህ ነገር የተፈጠረው በአውስትራሊያ ከተማ ሜልበርን ሲሆን ባል ከስራ ደክሞት ወደ ቤቱ ይሄዳል

ወዲያው ቤቱ ገብቶ ወደ መኝታ ክፍል ሲገባ ሚስት ባሏን ለማማል ብላ እንደ እባብ ያለ እስቶኪንግ አድርጋ ተኝታ ነበር

ወዲያው ባል ወይኔ ጉድ ሁለት እባብ አልጋ ላይ አለ ብሎ በBaseball መምቻ እንጨቱ ቀስ ብሎ ገብቶ አንድ እግሯን ሲመታው ሚስት
"ውይ ኡኡኡ.... እኔ ነኝ" ብላ በመንቃት ሁለተኛው ሳይደግም አንደኛው ተሰብሮ ሆስፒታል ገብታለች

@seledadotio
@seledadotio


⚡️ዲዲ አዳዲስ ክሶች ቀረቡበት

አሁን የተመሰረተበት ክስ ደግሞ ሰራተኞቹን ለረጅም ሰዓታት እንዲሰሩ በማስገደድ እና የ20 አመት ህገወጥ ዝውውር ንግዱን ያልደገፉትን በማስፈራራት ነው ተብሏል።

@seledadotio
@seledadotio


በአፋጣኝ የተኩስ ማቆም ፣ የአየር እና የባህር ላይ ጥቃቶችን ማቆም በሩሲያ እና በዩክሬን ግጭት ውስጥ በራስ የመተማመን እርምጃ ያዳብራል ለውጤታማ ድርድርም ይረዳል ሲሉ ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ሃሳብ አቅርበዋል።

@seledadotio
@seledadotio


ማስታወቂያ‼️

የመኪና ግዢ ሂደትዎን እንዴት ቀላል ማድረግ እንደሚችሉ እያሰቡ ነው?

ትክክለኛውን መኪና በትክክለኛው ዋጋ ከትክክለኛው አከፋፋይ እንዲያገኙ እንረዳዎታለን።🔥

መኪና ለመግዛት ካሰቡ ብዙ አማራጭ እኛ ጋር ያገኛሉ እንዲሁም ለዘመናዊ መኪና ፈላጊዎች ስለሚገዙት መኪና እናማክራለን!!!

ከስር ባለው ሊንክ የቴሌግራም ቻናላችንን Join በማለት ስለመኪና ወቅታዊ ዋጋ እና መረጃ ያግኙ 👇👇👇👇👇👇
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer
https://t.me/AbrahamDealer

@Ab_Cars
ስለመረጡን እናመሰግናለን


❗️ትራምፕ ለኢራን መሪ ካሜኒ የኒውክሌር ስምምነትን ለመደራደር ደብዳቤ እንደላኩ ተናግረዋል

Trump says he sent a letter to Iran’s leader Khamenei to negotiate a nuclear deal

@seledadotio
@seledadotio


👀በኢትዮጲያ የአዞ ስጋ ሽያጭ ሊጀመር ነው፡፡

የአዞ ስጋን የሚያዘጋጅ እና የሚሸጥ ምግብ ቤት በአርባምንጭ ሊከፈት መሆኑን ጣቢያችን ሰምቷል፡፡

የአርባምንጭ አዞ እርባታ ስራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ዳኜ ለኢትዮ ኤፍ ኤም በሰጡት ማብራሪያ፤ በአርባምንጭ ከተማ የአዞ ስጋ ምግብ ቤት ለመክፈት እንቅስቃሴ መጀመሩን ገልጸዋል።

የውጪ ሃገር ቱሪስቶች የአዞ ስጋ ለመመገብ የሚጠይቁ መሆኑን የገለፁት አቶ ዳዊት፤ ጥናት ተደርጎ ከአንድ ዓመት በኋላ ሬስቶራንቱን ለመክፈት እንደታሰበም ተናግረዋል።

የውጭዎቹ ቱሪስቶች ጋር ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለ ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ ዳዊት አንስተው ፤ አሁን ላይ በሃሳብ ደረጃ ነው ያለው ጉዳዩ ወደተግባር አልተገባም ብለዋል፡፡

በአካባቢው አዞዎቹን የሚንከባከቡ ሰዎች የአዞ ስጋ እንደሚመገቡ የሚናገሩት አቶ ዳዊት ይህም በስፋት እንደተለመደ እና አዲስ ነገር እንዳለሆነ አስተውሰዋል፡፡

የአዞ ስጋ በጣም ጣፋጭ እና መድሃኒትም መሆኑንን በጥናት አረጋግጠናል እናም በቅርቡም የአዞ ስጋ ሽያጭ በይፋ እንደሚጀመርም ገልጸዋል፡፡


2ሺ5መቶ ኦዞዎች እንዳሏቸው እና አሁንም ሰፋ ባለ መልኩ እየተፈለፈሉ መሆኑን አቶ ዳዊት ተናረዋል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


⚡️ከ750 በላይ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሠራተኞች በተቋሙ ከስራ 'እንደሚሰናበቱ መገለጹና 5 ሠራተኞች መታሰራቸው' ቅሬታ አስነሳ

በማህበራት ተደራጅተው ከአስራ አምስት ዓመት በላይ ለሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ያገለገሉ ከ750 በላይ ሠራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ “በመጠየቃቸው ብቻ ዩኒቨርስቲው ከስራ ገበታቸው እንደሚያሰናብታቸው” መግለጹንና ከጥያቄው ጋር ተያይዞ ከ5 በላይ ሠራተኞች መታሰራቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ለደህንነታቸው በመስጋት ስሜ ባይጠቀስ ያሉ ሠራተኛ፤ "እኔ ጽዳት ነው የምሰራው። 17 ዓመታት አገልግያለሁ። በወር 1100 ብር ነው ሚከፈለኝ። ጭማሪ ስንጠይቅ የምንከፍለው ጭማሪ የለም እናሰናብታቹኋላን አሉን። ከፈለጋችሁ መክሰስ ትችላላችሁ የሚል ምላሽ ተሰጠን" ብለዋል።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጲያ በሚል መሪ ቃል በመስቀል አደባባይ የወንጌል መርሃግብር ሊካሄድ ነዉ፡፡

የዝማሬ፣ የአምልኮ እና የወንጌል መርሀግብር የካቲት 29 እና 30 በመስቀል አደባባይ ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ እንደሚደረግ የቢሊ ግራሃም የወንጌል ማህበር አስታወቀ፡፡

የቢሊ ግራሃም የወንጌል ማኅበር በመስቀል አደባባይ ለሚያደርገው የሁለት ቀናት መርሐ ግብር መጋቢ ፍራንክሊን ግራሃም ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸዉ ተገልጿል፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ከ3 ሚሊየን ለሚበልጡ ሰዎች የምግብ እርዳታ ማቅረቡን እና ከ5 መቶሺህ ለሚበልጡ ሰዎች የህክምና እርዳታ መስጠቱ ተነስቷል፡፡

በተጨማሪም ከ2መቶ60ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች ንጹህ ውሃ፣ የንጽህና መጠበቂያ ግብዓቶች እና አገልግሎቶች እንዳበረከተም ነዉ የተገለጸዉ፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ በትግራይ፣ አፋር እና አማራ ክልሎች ውስጥ ለሚገኙ 3መቶሺህ ስደተኞች እና ተፈናቃዮች ምግብ እያቀረበ እንደሚገኝም ተገልጿል፡፡

በትግራይ እና አማራ ክልሎች ውስጥ ከ52 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ተንቀሳቃሽ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም በመግለጫዉ ወቅት ተነስቷል፡፡

ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ በቆሼ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቦታ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች የሚደረግ ድጋፍ መኖሩም በመግለጫው ወቅት ተገልጿል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


ፒያሳ❗️ፒያሳ❗️ፒያሳ❗️ፒያሳ
   ጊወርጊስ አደባባይ ፊትለፊት

#ቴምር ሪልስቴት(የንግድ ሱቅ)
4,235ካሬ ላይ ያረፈ ግዙፍ የገበያ ማዕከል በ18ወር የሚረከቡት ከ20ካሬ ጀምሮ የንግድ ሱቆች በሽያጭ ላይ ነን

የ20ካሬ ሱቅ ጠቅላላ ዋጋ👇👇👇
🏪4th & 5th floor=3,900,000ብር
  ቅድመ ክፍያ=900,000ብር
🏪3rd Floor=4,200,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=1,200,000ብር
🏪2nd Floor=4,800,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=1,500,000ብር
🏪1st Floor=5,500,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=2,000,000ብር
🏪Ground Floor=7,000,000ብር
   ቅድመ ክፍያ=2,800,000ብር

#ቴምር ሪልስቴት(አፓርታማ)
🎅ፒያሳ ኢኖቬሽን ሚኒስቴር ፊትለፊት(ሊሴ ት/ቤት ጀርባ) አፓርታማ ሽያጭ

🧲66ካሬ-142ካሬ(1መኝታ-3መኝታ) 10% ቅድመ ክፍያ ብቻ ቀሪ ክፍያ በ18ግዜ ዙር በ3አመት ተከፍሎ ይጠናቀቃል

👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል!!
❗️በኢትዮጵያ ብር ብቻ የሚዋዋሉት!!!
    
    ፈጥነው ይደውሉ
   📞+251926172402 / +251951513585

#temerrealestate #apartment #AddisAbabaApartments #realestateinethiopia


☄️አሜሪካ ዘለንስኪን ለመተካት ከተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች ጋር በድብቅ ውይይት መጀመሯ ተሰማ

የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ደጋፊዎች የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮለደሚር ዘለንስኪን ከሚቃወሙ የፖለቲካ መሪዎች ጋር ሚስጥራዊ ውይይት መጀመራቸው ተነግሯል፡፡

ዋሽንግተን በዩክሬን ምርጫ እንዲደረግ ግፊት እያደረገች መሆኗን ተከትሎ ነው ፕሬዝዳንት ዘለንስኪን ሊተኩ ከሚችሉ የፖለቲካ ሰዎች ጋር ነው እየመከረች የምትገኘው።

ቮለድሚር ዘለንስኪ በአሁኑ ወቅት በሀገራቸው ዜጎች ያላቸው የተቀባይነት ደረጃ 44 በመቶ ነው።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️በወርቅ ማምረት ሥራ ላይ የተሠማሩ የ32 አምራቾች ፈቃድ መሰረዙ ተገለፀ


በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል፣ የማዕድን ዘርፉ አፈጻጸም አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የክልሉ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ አስታውቋል።

በክልሉ ከሚገኙ 58 ልዩ አነስተኛና 12 ባሕላዊ የወርቅ አምራቾች መካከል አፈጻጸማቸው ደካማ የሆኑት 32ቱ ፈቃዳቸው መሰረዙ ተገለጿል ።

የክልሉ የማዕድንና ኢነርጂ ልማት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገብረማርያም ሰጠኝ በስድስት ወራት ውስጥ ምንም ዓይነት ወርቅ ማምረት ያልቻሉ 12 ልዩ አነስተኛና ሁለት ባሕላዊ አምራቾች አሉ። አሳማኝ ምክንያት ካላቀረቡ በቀጣይ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስጠንቅቀዋል።

በድንጋይ ከሰል ማምረት ፍቃድ ከወሰዱ ከ20 በላይ ባለፍቃዶች መካከል፣ እስካሁን ወደ ማምረት የገቡት ስምንት ብቻ መሆናቸው ተጠቁሟል።

በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 150 ኪሎ ግራም ወርቅ ለማምረት ታቅዶ 75.525 ኪሎ ግራም፣ እንዲሁም 100 ሺህ ቶን ድንጋይ ከሰል ለማምረት ታቅዶ 50 ሺህ ቶን ብቻ ማምረት መቻሉ ተነገረ ሲሆን የምርት እጥረቱ ምክንያት ሕገወጥነት እና ወደ ሥራ ያልገቡ አምራቾች መኖራቸው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ሲል ካፒታል ዘግቧል ።

@seledadotio
@seledadotio


☄️የባንክ ተሽከርካሪ በመገልበጡ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ተበተነ

የሶርያ ማእከላዊ ባንክ ተሽከርካሪ በመገልበጡ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ መበተኑ ሳያንስ የበተነውን እንደ እቃ ለመሰብሰብ ባካባቢው የነበሩ ሰዎች እንዲተባበሩት ማድረጉ እያስገረመ ነው።

ከአመታት ጦርነት በኋላ የመንግስት ሽግግር ላይ የምትገኘው ሶርያ ማእከላዊ ባንክ የሆነ ተሽከርካሪ አንድ ጎማው ፈንድቶ የመገልበጥ አደጋ ሲገጥመው በውስጡ ይዞት የነበረው በሚሊየኖች የሚቆጠር የሶርያ ፓውንድ መበተኑ ተዘግቧል።

አሽከርካሪው እንዳልተጎዳ የተገለፀ ሲሆን። እዚም እዚያ የተበተነውን ገንዘብ ለመሰብሰብ ባካባቢው የነበሩ ሰዎች መሳተፋቸው አጀብ አሰኝቷል።

በምስሉም ላይ የታሰረ ገንዘብ ጨምሮ የተበተነውን የሶርያ ፓውንድ ሰዎች ሲለቅሙ ይታያል።

ከሶርያ የወጡ ዘገባዎች እንደገለፁት ገንዘቡ ለሰራተኞች ደሞዝ ለመክፈል ሲጓጓዝ የነበረ መሆኑ ተዘግቧል::

@seledadotio
@seledadotio


❗አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል 28 ቢሊዮን ብር ፈጀ

የአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ከ28 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ተነግሯል።

የማዕከሉ ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ሲሳይ ገመቹ እንደገለጹት፣ ከዚህ ውስጥ ከ22 ቢሊዮን ብር በላይ የሚሆነው በባለአክሲዮኖች የተከፈለ ካፒታል ነው።

ማዕከሉ በምስራቅ አፍሪካ ከመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚመደብ ሲሆን፣ ሁለት ትላልቅ አዳራሾች እና ስምንት ትናንሽ አዳራሾች አሉት። በተጨማሪም በዙሪያው የሚገኙ ስድስት ህንፃዎች ወደ 1000 አልጋዎችን ወደሚይዙ ሆቴሎች እየተቀየሩ መሆኑ ተገልጿል።

ወደ 2000 ገደማ መኪኖችን ማስተናገድ የሚችል የመኪና ማቆሚያ ቦታ ያለው ይህ ማዕከል 50 የንግድ ድርጅቶችን ማስተናገድ የሚችሉ የንግድ ቦታዎችም አሉት ተብሏል።

በቀጣዮቹ ሶስትና አራት ወራት 10 ተቋማት ዝግጅቶቻቸውን ለማካሄድ ቦታ ማስያዛቸውን ዋና ስራ አስኪያጁ መናገራቸውን የዘገበው ኢፕድ ነዉ::

@seledadotio
@seledadotii


⚡️የደቡብ ኮሪያ አየር ኃይል በስህተት የሀገሪቱን ዜጎች በቦምብ ደበደበ


ከኬ.ኤፍ 16 ተዋጊ ጄት በልምምድ ወቅት 8 ቦምቦች ንጹሃን ላይ መጣሉ ተነግሯል።

የቦምብ ጥቃቱ ከሰሜን ኮሪያ በ25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ቡቸን ከተማ ላይ ነው የተፈጸመው።

በጥቃቱ 15 ስዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ተዘግቧል።


⚡️ዘለንስኪ ለብራሰልሱ የመሪዎች ጉባኤ በዝግጅት ላይ እያሉ የሩሲያው ሚሳኤል በትውልድ ከተማቸው ላይ ጥቃት መፈፀሙ ተነገረ ፡፡

ዩክሬን ውስጥ በዘለንስኪ የትውልድ ከተማ የሩሲያው ሚሳኤል በሆቴል ላይ በፈፀመው ጥቃት 4 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል፡፡

ጥቃቱ ዘለንስኪ በብራሰልስ ለአውሮፓ የመሪዎች ጉባኤ በመዘጋጀት ላይ እያሉ በክሪቪ ሪክ ከተማ የተፈፀመ ነው ተብሏል፡፡

ጉባኤው አውሮፓዊያን ለዩክሬን የሚሰጡትን ድጋፍ ለማሳደግ አለማው ያደረገ ስለመሆኑ ቢቢሲ በዘገባው ተቅሷል፡፡

ሰኞ እለት አሜሪካ ለዩክሬን የምትልከውን ወታደራዊ እርዳታ ማገዱዋን ተከትሎ በፖላንድ ውስጥ የሚገኙ መሳሪያዎች እንኳን ድንበር መሻገር አለመቻላቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


🇬🇧🇷🇺የሩሲያ ፍርድ ቤት የብሪታኒያ ቅጥረኛ ወታደር ጄምስ ስኮት ሪስ አንደርሰን ላይ የ19 አመት እስራት ፈረደበት።

ከዩክሬን ጦር ኃይሎች ጎን ተሰልፎ በኩርስክ ክልል ሲዋጋ ነበር በሩሲያ ጦር የተማረከው።


☄️የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ ትዕዛዝ ተላለፈ


ከ3 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ የታክስ ዕዳ ያለባቸው 62 ግብር ከፋዮች ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ማስተላለፉን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ገለፀ፡፡

የግብር ዕዳ ያለባቸውና በተደጋጋሚ ጥሪ ቢደረግላቸውም ዕዳቸውን ለመክፈል ፈቃደኛ ያልሆኑ 62 ግለሰቦችን ላይ ነው ትዕዛዙ የተላለፈው::

በዚህም ቢሮው በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀፅ 44 ንዑስ አንቀፅ ከ1-3 ለተቋሙ በተሰጠ ስልጣን መሰረት ከሀገር እንዳይወጡ ለፌዴራል የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዝርዝራቸውን ማስተላለፉን አሳውቋል፡፡

ቢሮው በ2017 በጀት ዓመት የግብር ዕዳቸውን በአግባቡ ሳይወጡ የሚሰወሩ ግብር ከፋዮችን በመከታተል ግዴታቸውን እንዲወጡ ለማስቻል የዕዳ ክትትልና አስተዳደር የስራ ክፍልን በአዲስ መልክ በማደራጀት ወደ ተግባር መግባቱን አስታውቋል::

በዚህም ባለፉት ስድስት ወራት ከ6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ዕዳ መሰብሰቡን ገልጿል፡፡

ግብር ከፋዮች የሚጠበቅባቸውን ግብር በወቅቱና በታማኝነት በመክፈል ለከተማዋ ሁለንተናዊ እድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ቢሮው ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


📈90 ሺ ብር በ100 ሺ ብር እየተሸጠ ነው!

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኮንትሮባንድ ንግድ በመስፋፋቱና የጥሬ ገንዘብ እጥረት በማጋጠሙ እጃቸው ላይ ገንዘብ ያላቸው አትርፈው መሸጥ ጀምረዋል ተባለ፡፡

እንደማሳያም 90,000 ብር በ100,000 ብር ይሸጣል፡፡ ከባንኮች አንድ ሰው በቀን ከ500 ብር በላይ ማውጣት አይችሉም መባሉን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል፡፡

የህዝብ እንደራሴዎች ም/ቤት አባል እና የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ መብራቱ አለሙ የጥሬ ገንዘብ እጥረት በባንኮች መፈጠሩን እና የኮንትሮባንድ ንግድ መስፋፋትን የተመለከቱት በምርጫ አካባቢያቸው በመተከል ዞን በመገኘት ባደረጉት ህዝባዊ ውይይት መሆኑን ነገረውኛል ብሏል ሸገር፡፡

የኑሮ ውድነቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ተባብሷል የሚሉት የህዝብ እንደራሴው ይህንንም በህዝባዊ ውይይታችን ተመልክተናል ብለዋል፡፡

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.