ሰሌዳ | Seleda


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን ሰሌዳ ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ!
ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ @Contact_officework ያናግሩን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


❗️ጠ/ሚንስትሩ ያጋሩት ፎቶ ከአንተርኔት ላይ የተወሰዱ ናቸው

በጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ሚድያ ገፆች ላይ የሚታዩት የአፕል ምስሎች ከሌላ ሀገር የተወሰዱ ናቸው

ትናንት ምሽት በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የፌስቡክ እና ኤክስ (ትዊተር) አካውንቶች ላይ "የአፕል ግብርና ምርታማነታችን እድገት እያሳየ ነው" ከሚል ፅሁፍ ጋር የተለቀቁ ስድስት የአፕል ምስሎችን ተመልክተናል።

ይሁንና በምስሎቹ ዙርያ ኢትዮጵያ ቼክ ባደረገው አሰሳ ሁሉም ፎቶዎች ከሌላ ሀገር የተወሰዱ እና ኢንተርኔት ላይም በፍለጋ የሚገኙ መሆናቸውን መመልከት ችሏል።

ለማሳያነት በምስሉ ላይ 1 እና 2 ተብለው የሚታዩት ምስሎች ከእነዚህ ድረ-ገፆች ላይ የተወሰዱ ናቸው:

ምስል 1: በአሜሪካን ሀገር የሚመረተውን 'ኮርትላንድ የአፕል ዛፍ' ያሳያል: https://onlineorchards.com/products/cortland-apple-tree-one-of-the-slowest-to-brown-after-slicing

ምስል 2: በላቲን አጠራሩ 'ማሉስ ሳፕ' የተባለ በአሜሪካ የሚገኝ የአፕል ምርትን ያሳያል: https://restoringeden.co/product/4-in-1-combination-apple-2/

ሌሎቹ ምስሎችም በተመሳሳይ ከእነዚህ ድረ-ገፆች የተወሰዱ ናቸው:

https://www.facebook.com/share/1BdVptkgPC/

https://www.pomonafruits.co.uk/fruit-nut-trees/apple-trees/dessert-apple-trees/apple-tree-spartan

https://www.alamy.com/sulen-apfel-malus-domestica-jucunda-image389956155.html

አፕል ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ማእከላዊ ኢትዮጵያ፣ በምስራቅ ጎጃም እና በጋሞ ዞን ባሉ አካባቢዎች እንደሚመረት የመረጃ ማጣርያ ዴስካችን ያሰባሰባቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ይሁንና በጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የተጋሩት ምስሎች ኢትዮጵያ ውስጥ ያለ የአፕል ምርትን እንደማያሳዩ እነዚህ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

በርካታ ተከታታይ ያሏቸው ባለስልጣናት፣ ተቋማት፣ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የሚያጋሯቸው ፅሁፎች፣ ምስሎች፣ ቪድዮዎች እና ሌሎች መረጃዎች እውነትነታቸውን ቀድመው በማረጋገጥ የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የሚደረግ ጥረትን ሊደግፉ ይገባል።

@seledadotio
@seledadotio


☄️Breaking : 83 በመቶ የUSAID ፕሮግራሞች ተሰረዙ

ከስድስት ሳምንት ግምገማ በኋላ አሜሪካ 83 በመቶ የሚሆነውን የUSAID ፕሮግራሞችን መሰረዟን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሮቢዮ በ X ገጻቸው አስታውቀዋል።

በቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረግባቸው የነበሩ 5200 ኮንትራቶች ተቋርጠዋል ያሉት ሚኒስትሩ እነዚህ ለብሔራዊ ጥቅማችን ምንም የማያገለግሉ አንዳንዶቹ የሚጎዱ ጭምር ናቸው ሲሉ ነው የገለጹት።

ቀሪ 18 በመቶ የሚሆኑት ፕሮግራሞች (1000 የሚጠጉ) በስቴት ዲፖርትመንቱ በአግባቡ እየተመራ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።
@seledadotio
@seledadotio


⚡️ሰሜን ኮሪያ በርካታ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራዎች ማድረጓ ተገለጸ፡፡

ደቡብ ኮሪያ እና አሜሪካ በጋራ ወታደራዊ ልምምዶችን በጀመሩበት በአሁኑ ወቅት ሰሜን ኮሪያ በርካታ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራዎችን ማድረጓ ተሰምቷል፡፡

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደስልጣን ከመጡ በኋላ ሰሜን ኮሪያ ያደረገችዉ የመጀመሪያዉ የባለስቲክ ሚሳዔል ሙከራ መሆኑም ተገልጿል፡፡

የደቡብ ኮሪያ ጦር እንዳስታወቀው ሰሜን ኮሪያ በዚህ አመት ብቻ ለአምስተኛ ጊዜ የባለስቲክ ሚሳኤል ሙከራ አድርጋለች፡፡

የሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል ሙከራ በጋራ ወታደራዊ ልምምድ ማድረግ ለጀመሩት ደቡብ ኮሪያና አሜሪካ መልዕክት ለማስተላለፍ ያለመ ነዉ ተብሏል፡፡

የሁለቱ አገራት የጋራ ወታደራዊ ልምምድ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር መጋቢት 20 ድረስ እንደሚቀጥል ተገልጿል ሲል የዘገበው አልጀዚራ ነው፡፡


@seledadotio
@seledadotio


❗️በታላቁ ህዳሴ ግድብ ከተመረተ ዓሳ 1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገለጸ

በታላቁ የ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከተመረተ ዓሳ 1.4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን የቤኔሻንጉል ጉምዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

የቢሮው የእንስሳት ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ በርሃኑ ኢትቻ (ዶ/ር) በክልሉ በ2017 በጀት ዓመት ስምንት ወራት ሶስት ሺህ 700 ቶን ዓሳ ተመርቷል፡፡ ከተመረተው ዓሳ 95 በመቶ የሚሆነው ከዓባይ ግድብ የተገኘ ነው ብለዋል።

ከህዳሴ ግድቡም በቀን በአማካኝ 14 ሺህ 646 ኪሎ ግራም የዓሳ ምርት እየተገኘ መሆኑን ለኢፕድ ገልጸዋል።

በክልሉ አንድ ኪሎ ግራም ዓሳ 400 ብር እየተሸጠ ይገኛሉት የምክትል ቢሮ ኃላፊው፣ የዓሳ ምርት ከክልሉ አልፎ ወደ አዲስ አበባና ሌሎች የክልል ከተሞች እየተላከ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዓባይ ግድብ ዓሳ የሚያወጡ 64 ማህበራት መደራጀታቸውን ገልጸው፤ ወደስራ የገቡት 22 ማህበራት ብቻ መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

ከዓባይ ግድብ የሚገኘውን የዓሳ ምርት ለማሳደግ የዘመናዊ ግብዓት አቅርቦትን ማሟላትና የተደረጁት ማህበራትን ወደስራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ በፊት በዓመት ከ1000 ሺህ 200 ቶን ያልበለጠ ዓሳ ሲመረት እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


☄️ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አወዛጋቢው የዶላር ገበያ

በቅርቡ ብሄራዊ ባንክ በመጣው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ60 ሚሊዮን ዶላር ውስጥ 40 በመቶውን በጨረታ ቢያገኝም ዝቅተኛውን የግዢ ዋጋ ማስመዝገቡን ቀጥሏል።

ጥንቃቄ የተሞላበት ስትራቴጂው ባንኩ የውጭ ምንዛሪ ገበያን በማረጋጋት ረገድ ያለውን ሚና እና የገንዘብ ልውውጥን ለመቆጣጠር ካለው ዓላማ ጋር ተዳምሮ ያሳያል ሲል አዲስ ፎርቹን ዘግቧል።

ብሄራዊ ባንክ ባመጣው ጨረታ ላይ አንዱን ዶላር በአማካይ ዋጋ በ135 ብር እንደሽጠ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ግን ባንኮች አንድን ዶላር በአማካይ ከ130 በታች እያገበያዩ መሆኑ ከሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር ::

The state-owned Commercial Bank of Ethiopia (CBE) secured 40pc of the 60 million dollars at auction but continued to post the lowest buying rates.

Its cautious strategy displayed the Bank's role in stabilising the foreign exchange market, coupled with its intent to manage liquidity.


@seledadotio
@seledadotio


⚡️"እኔ ስታርሊንክን ባጠፋው የዩክሬን የጦር ግንባር ይፈርሳል" ሲል ኤሎን መስክ ተናገረ፡፡

አሜሪካዊው ቢሊየነር አሎን መስክ ዛሬ ባሰፈረው መልእክት የሳተላይት ኢንተርኔት አገልግሎት መስጫ የሆነውን ስታር ሊንክ ለዩክሬይን ጦርነት ወሳኝ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የዩክሬይን ማናቸውም ወታደራዊ ግንኙነቶች የሚከናወኑት በእሱ ባለቤትነት በሚተዳደረው በዚሁ ስታር ሊንክ አማካኝነት እንደሆነም ገልጿል፡፡ መስክ በኤክስ ገፁ ላይ ‹‹እኔ ፑቲንን ከዩክሬይን ጋር በሚደረገው ጦርነት ፈትኜዋለሁ፡፡ እናም የእኔ ስታር ሊንክ ሲስተም ለዩክሬይን የጀርባ አጥንት ነው›› ካለ በኋላ ስታር ሊንኩን ቢያጠፋው የዩክሬይን የጦር ግንባር ሙሉ በሙሉ እንደሚፈራርስ አስረድቷል፡፡

ለአመታት በተደረገው በዚህ ጦርነት ዩክሬን ላታሸንፍ ነገር ይህንን በማድረጉና ሰዎች በመሞታቸው እንደሚፀፅተውም አስረድቷል፡፡ ጨምሮም ‹‹አሁን ሁሉም የሚመለከተው ሁሉ ይህ ሰው እየበላ ያለው ጦርነት እንዲቆም ማድረግ አለበት፡፡ አሁን ሰላም ያስፈልጋል›› ብሏል፡፡

ኤሎን መስክ ይህንን መልእክት ያሰፈው የዩክሬይኑን ፕሬዝደንት ዘለንስኪን ከሩሲያ ጋር የማያልቅ ጦርነት ማድረግ እንደሚፈልጉ ገልፆ ‹‹ጨካኝ›› ካላቸው ከቀናት በኋላ ነው፡፡ ሩሲያና ዩክሬይን ጦርነቱን ከጀመሩ ሶስት አመታት የሞላቸው ሲሆን በሁለቱም በኩል ከፍተኛ ሰብአዊ ጉዳት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡

@seledadotio
@seledadotio


👀የ10 ሰአት በረራው በሽንት ቤት ምክንያት ተቋረጠ

በርካታ የአውሮፕላኑ መጸዳጃ ቤቶች ከጥቅም ውጪ በመሆናቸው ወደ ደልሂ ይጓዝ የነበረው የኤር ኢንዲያ በረራ ወደ አሜሪካ ቺካጎ ለመዞር መገደዱ ተነግሯል።

ቪው ፍሮም ዘ ዊንግ የተሰኘው ታዋቂው የአቪዬሽን ድረ-ገጽ ባወጣው ዘገባ የኤር ኢንድያ በረራ ቁጥር 216 ከቺካጎ ቢነሳም ከ12ቱ መጸዳጃ ቤቶች 11ዱ በመዘጋታቸው ወደ ኋላ ለመመለስ ተገዷል ተብሏል።


ከዚሁ አየር መንገድ ጋር በተያያዘ

ከሙምባይ ወደ ኒውዮርክ ሲበር የነበረው የኤር ኢንዲያ በረራ በበረራ አጋማሽ ላይ የቦምብ ስጋት በመገኘቱ ወደ ኋላ ለመመለስ ተገዷል ተብሏል

322 ሰዎችን አሳፍሮ የነበረው ቦይንግ 777-300 ER የደህንነት ፕሮቶኮሎችን ተከትሎ ወደ ሙምባይ በሰላም ተመልሷል

ዛሬ ለኤር ኢንዲያ መልካም ሰኞ አልሆነለትም 😁

@seledadotio
@seledadotio


❗️ ታላቅ እድል እንዳያመልጥዎ
#ADS
እንደ እሷ ያስተዋውቁ
በቅናሽ ዋጋ ሚሊየኖች ጋር ይድረሱ
ኪሶትን በማይጎዳ ዋጋ ፌስቡክ እና ኢንስተግራም ቡስት ይሞክሩት
ለበለጠ መረጃ በቴሌግራም - @catalystpromo
ይጻፉልን


⚡️እስራኤል በመላው ጋዛ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት አቋረጦች

የሀገሪቱ የኢነርጂ ሚኒስትር ኢሊ ኮኸን "ታጋቾችን ለማስለቀቅ እና ሃማስ ከጦርነቱ በኋላ በጋዛ ህልውና እንዳይኖረው ለማረጋገጥ ሁሉንም አማራጮች እንጠቀማለን" ሲሉ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ የሰጡት ትዕዛዝ በተለይ የተጣራ የመጠጥ ውሃ ለማቅረብ የሚውሉ ማሽኖችን ከስራ ውጭ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

የጠቅላይይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ አስተዳደር በቀጣይም ወደ ጋዛ ውሃ እንዳይገባ ሊከለክል እንደሚችል ነው የተነገረው።

እስራኤል ባለፈው ሳምንት እሁድ ማንኛውም የሰብአዊ ድጋፍ ወደ ጋዛ እንዳይገባ ማገዷ ይታወሳል።

@seledadotio
@seledadotio


❗️ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

በማይናማር በእገታ እና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ በህንድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያዊያን መካከል 32ቱን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል፡፡

43 ኢትዮጵያዊያን ዛሬ ምሽት ይገባሉ ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን÷ በታይላንድ ማቆያ የሚገኙ 58 ኢትዮጵያዊያንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ኤምባሲው ጥረት እያደረገ ይገኛልም ተብሏል።

በተያያዘ መንግሥት ጃፓን በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያዊያንን ወደ ታይላንድ በማሻገር ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡

ሕብረተሰቡ በሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ሀሰተኛ ቅስቀሳ ተታሎ የሥራ ስምሪት ውል ወዳልተፈጸመባቸው ሀገራት ከሚደረጉ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ጥሪ መቅረቡን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

@seledadotio
@seledadotio


👀በሚስቱ ቢጠየቅም ፍቃደኛ ያልሆነው ወጣት ከፍተኛ የደም መፈሰስ አጋጥሞት ሆስፒታል ገባ

ሐኪሞች የተበጣጠሰ የደም ቧንቧ እንዳለ ካረጋገጡ በኋላ ጉዳቱን ለማስተካከል ድንገተኛ ቀዶ ህክምና አድርገውለታል። የሰውዬው ሚስት አፍንጫውን መጎርጎር ልማዱ እንደሆነ በማንሳት ከቀዶ ህክምና እያገገመ በነበረበት ወቅት ባጋራችው ቪዲዮ “ማር፣ ለምን አፍንጫህን ተነስተህ አትጎረጉርም? ተነሥተህ መልሰ ስጠኝ እንጂ” ስትል የቀረፀችው ምስል በርካቶች ተቀባብለውታል።

የጤና ባለሙያዎች እንደሚያስጠነቅቁት አፍንጫን መጎርጎር ከፍተኛ የሆነ የኢንፌክሽን ይፈጥራል፣ በከፋ ሁኔታ ደግሞ በአፍንጫው ክፍል ውስጥ ያሉ የደም ስሮች ወይም ቲሹዎች ይጎዳል፣ አልፎ ተርፎም ደም ወሳጅ ቧንቧን እንዲጎዳ ያደርጋል።


❗️የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ያላመኑበትን ግብርና ታክስ በተጨማሪ በሌሎች ችግሮች እየተፈተኑ እንደሚገኙ ተገለፀ

የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ፎረም በከተማው ውስጥ የሚገኙ ባለሀብቶች ከባድ ችግሮች እያጋጠሟቸው መሆኑን ገልጿል። ፎረሙ የባለሀብቶችን ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

የባለአብቶች ፕሬዝዳንት አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ለካፒታል እንደገለጹት፣ ባለሀብቶቹ ያላግባብ ድርጅቶቻቸው መታሸግ፣ መፍረስ፣ መነጠቅ (መቀማት)፣ ሥራ እንዲያቆሙ መደረግ፣ ያላመኑበትን ከፍተኛ ግብርና ታክስ ለማስከፈል ማስገደድ፣ የባንክ አካውንታቸው መታገድ፣ ከሀገር እንዳይወጡ ወይም እንዳይገቡ እየተደረጉ ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በስልክ ዛቻና ማስፈራሪያ ማድረስ፣ የማያምኑበትን አሰልቺና ተደጋጋሚ መዋጮዎች መጠየቅ፣ እንዲሁም ተረጋግተው ሥራቸውን እንዳይከውኑ ማዋከብ፣ የብድር አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ያለማግኘት እና የመሳሰሉት ችግሮች እየደረሱባቸው መሆኑን ሰምተናል ብለዋል።

ይህን ተከትሎ ፎረሙ ከመጋቢት 01 እስከ 27 ቀን 2024 ዓ.ም ድረስ የከተማውን ባለሀብቶች ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል መዘጋጀቱንና ባለሀብቶችም መረጃቸውን በሰነድ በማቅረብ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።

የባለሀብቶቹ ቅሬታ ከተሰበሰበ በኋላ ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ችግሮቹ እንዲፈቱ ፎረሙ እንደሚሰራ አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ተናግረዋል።

@seledadotio
@seledadotio


☄️በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል የተባለዉ አዲስ መመሪያ ወጣ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ አዲስ መመሪያ አውጥቷል።

"የባዮኤክቫለንስ ጥናት ማዕከል እና የባዮአናሊቲካል ላብራቶሪ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1043/2017" ተብሎ የሚጠራው ይህ መመሪያ፣ በገበያ ላይ የሚውሉ የመድኃኒት ምርቶች ተመሳሳይ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃዎችን ማሟላታቸውን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በተለይም በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ተመሳሳይ የሆነ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃ እንዲኖራቸው ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ መመሪያ "ባዮኢኩዊቫለንስ" የተሰኘ ልዩ ጥናት በማድረግ በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ያላቸውን ተመሳሳይነት ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል።

በተጨማሪም፣ መመሪያው የመድኃኒት
ማምረቻ ተቋማትና ላቦራቶሪዎች ፈቃድና ቁጥጥር ላይ እንደሚያተኩር ካፒታል ለመረዳት ችሏል።

መመሪያው በኢትዮጵያ የመድኃኒት ቁጥጥር ላይ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፣ ለመድኃኒት ኢንዱስትሪው ዕድገት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ይጠበቃል። በተጨማሪም፣ ለሕዝብ ተደራሽና ጥራት ያላቸውን መድኃኒቶች ለማቅረብ ያለመ ነው ተብሏል።

@seledadotio
@seledadptio


☄️ሰሌክታ ግሩፕ በፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ከኢትዮጵያ ወጣ

በስዊዘርላንድ ዋና መስሪያ ቤቱን ያደረገው ሰሌክታ ግሩፕ በሰሜን ኢትዮጵያ ኩንዚላ የሚገኘውን የምርት ማዕከሉን በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በወታደራዊ ሁኔታዎች ምክንያት ወደ ኬንያ እና ኡጋንዳ ማዛወሩን አስታዉቋል።

ኩባንያው የዚህ ውሳኔ ምክንያት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰራተኞች ደህንነት ስጋት መፍጠሩ እና የሎጂስቲክስ ችግሮች መከሰታቸው እንደሆነ ገልጿል።

የኩባንያዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንስጋር ክሌም ይህን ውሳኔ "አሳማሚ እርምጃ" ብለው የገለፁት ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ያደረጉትን ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እና ጥረት ከንቱ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ውሳኔ በኩንዚላ አካባቢ ከ1,000 በላይ የስራ እድሎችን የሚያሳጣ ሲሆን፣ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ወደ 10,000 የሚሆኑ ሰዎችን ይጎዳል። ኩባንያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ህይወት መስመር እንደነበር እና መውጣቱ ትልቅ ጉዳት እንደሚያስከትል ገልጿል።

ካፒታል ያገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ሰሌክታ ግሩፕ በኬንያ እና ኡጋንዳ ያሉትን የምርት ማዕከላት በማጠናከር ለደንበኞች የምርት አቅርቦት እንዳይቋረጥ ማረጋገጡን ገልጿል። ወደፊት ሁኔታዎች ሲሻሻሉ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ተስፋ እንዳለውም አስታውቋል።

ሰሌክታ ግሩፕ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም የሆነ የአበባ እና የጌጣጌጥ እፅዋት አምራች ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️"የሪፖርተር መረጃ የተሳሳተ ነው

ተቋሙ ምንም አይነት  አዲስ ታሪፍ ጭማሪ አልተደረገም"

ከሚያዝያ ወር ጀምሮ አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሆነ ተደርጎ በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ የትስስር ገፆች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ የተሳሳተ ነው።

ተቋሙ ከመስከረም  2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ4 ተከታታይ አመታት  በማኅበረሰቡ ላይ ጫና እንዳይፈጠር በየሩብ አመቱ ተከፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የታሪፍ ማስተካከያ  ከማስፈፀም ውጪ አዲስ ተግባራዊ ያደረገው የታሪፍ ማሻሻያ አለመኖሩን እንገልፃለን ብሏል።

@seledadotio
@seledadotio


☄️የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድጋሚ የዋጋ ጭማሪ ሊደረግበት ነው

በዚህም መሠረት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ በመኖሪያ ቤት ታሪፍ ላይ 0.50 ኪሎ ዋት ሰዓት የሚጠቀሙ ደንበኞች የፍጆታ ታሪፍ 0.60 ሳንቲም እንዲከፍሉ የሚደረግ ሲሆን፣

የአገልግሎት ክፍያ ተመንን በተመለከተ ለድኅረ ክፍያ አሥር ብር ከ95 ሳንቲም ሲከፍሉ፣ ለቅድመ ክፍያ አራት ብር ከ18 ሳንቲም እንደሚከፍሉ ሪፖርተር ያገኘው ሰነድ ያሳያል፡፡

የመኖሪያ ቤት ታሪፍን በተመለከተ ከ51 እስከ 100 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች አንድ ብር ከ49 ሳንቲም፣ ከ101 እስከ 200 ኪሎ ዋት ሁለት ብር ከ67 ሳንቲም፣ ከ201 እስከ 300 ኪሎ ዋት የሚጠቀሙ ደንበኞች ሦስት ብር ከ84 ሳንቲም እንደሚከፍሉና በየኪሎ ዋቱ መጠን ክፍያው የሚለያይ እንደሆነ ሰነዱ ያስረዳል።

@seledadotio
@seledadotio


❗የአለም ዋንጫ ተሳታፊ አገራት ወደ 64 ከፍ ለደረግ ነው


የአለም እግር ኳስ ማህበር ፊፋ በ2030 የአለም ዋንጫ ላይ የሚሳተፉ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ እያጤነ እንደሚገኝ ተሰምቷል፡፡

ባሳለፍነው ረቡዕ በጀመረው የእግር ኳስ ማህበሩ ምክር ቤት ጉባኤ ላይ ኡራጓይ ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት ካገኘ ከማህበሩ አባላት አንድ አራተኛው በአለም ዋንጫ እንዲሳተፉ እድል ይፈጠራል።

በአለም አቀፍ ደረጃ ሰፊ ተከታታዮች እና ተወዳጅነት ያለው የአለም ዋንጫ በየአራት አመቱ በተለያዩ ሀገራት አዘጋጅነት ከ1930 ጀምሮ ለ22 ጊዜ ተካሂዷል፡፡

በ18 የተለያዩ ሀገራት አስተናጋጅነት የተካሄደው ውድድር ከጊዜ ወደጊዜ ከተሳትፎ እና ከአካታችነት ኮታ ጋር በተያያዘ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ይነሱበታል።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️ሁሉም ወንድ ዜጎቿ ወደ ወታደራዊ ስልጠና

ፖላንድ ሁሉም ወንድ ዜጎቿ በወታደራዊ ስልጠና ውስጥ እንዲያልፉ የሚያደርግ ረቂቅ ህግ ለፓርላማው አቀረበች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ተስክ ረቂቅ ህጉን ለፓርላማው ባቀረቡበት ወቅት በሀገሪቱ ከፍተኛ ወታደራዊ ስልጠና እንዲሰጥ ያስችላል የተባለው ዕቅድ ዝርዝር በመጪዎቹ ወራት ይፋ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

እቅዱ ወታደራዊ ስልጠና የሚያገኙት ወንዶች በቀጥታ መከላከያ ሰራዊቱን የሚቀላቀሉ ሳይሆኑ በግጭት ወቅት ብቁ ወታደራዊ ቁመና ተላብሰው መሰለፍ የሚችሉበትን ክህሎት እንዲያገኙ የሚያደርግ ነው።

ፖላንድ በአሁኑ ወቅት 200 ሺህ ወታደሮች ያሏት ሲሆን በአቅራቢዋ ከሚገኙ ሀገራት አንጻር አነስተኛ ነው የተባለውን የሰራዊት ቁጥር ወደ 500 ሺህ ለማሳደግ አቅዳለች።

@seledadotio
@seledadotio


⚡️በአዲስ አበባ ከተማ 18 ሄክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ ሊቀርብ ነው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ፤ በጥቅሉ 18 ሄክታር ስፋት ያላቸው 427 ቦታዎችን ለሊዝ ጨረታ ሊያቀርብ ነው። በመዲናይቱ ዘጠኝ ክፍለ ከተሞች የሚገኙት እነዚህ ቦታዎች፤ ለመኖሪያ እና ለንግድ አገልግሎት የሚውሉ መሆናቸው ተገልጿል።

በከተማይቱ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅት እና ባንክ ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ተስፋዬ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደተናገሩት፤ ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች “በተለያየ አግባብ ወደ መሬት ባንክ የገቡ ይዞታዎች” ናቸው። በአሁኑ ዙር ጨረታ በቦሌ እና ልደታ ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የመሬት ይዞታዎች እንዳልተካተቱ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ለጨረታ የሚቀርቡት ቦታዎች ዝርዝር፤ በነገው ዕለት ታትሞ በሚወጣው “አዲስ ልሳን” ጋዜጣ ማግኘት እንደሚቻል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ይህንን ተከትሎ የጨረታ ሰነድ ሽያጩ “ከእጅ ንኪኪ በጸዳ መልኩ” ከመጪው ሰኞ መጋቢት 1 እስከ መጋቢት 12 ድረስ ባሉት ቀናቶች የሚከናወን መሆኑንም ጠቁሟል።

@seledadotio
@seledadotio


✨አየር መንገዱ ዛሬ ማታ የሚጀመሩ ሁለት በረራዎችን ጨምሮ በሴቶች ብቻ የሚደረጉ 6 በረራዎች ሊያካሂድ ነው።


የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለም አቀፉን የሴቶች ቀን አስመልክቶ በሴቶች ብቻ የሚደረግ በረራ ሊያካሂድ መሆኑን አስታውቋል።


በረራው ወደ 6 አገራት የሚደረግ ሲሆን፤ ሁለቱ ዛሬ ማታ የቀሩት አራት በረራዎች ደግሞ ነገ የሚደረጉ ናቸው።


በረራዎቹ  ከካፒፔን እስከ አየር ተቆጣጣሪ እና ቴክኒሻን ድረስ በሴቶች ብቻ የሚደረጉ መሆናቸው ተገልጿል።


ባህርዳር፣ አቴንስ፣ ዴልሂ ፣ዱባይ፣ ሳኦፖሎ እና ዊንድሆክ ከተሞች መዳረሻ ናቸው ተብሏል።


በዓለም ለ114ኛ ጊዜ በአገራችን ለ49ኛ ጊዜ የሚከበረው የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በረራዎቹ መዘጋጀታቸው ነው የተገለፀው።


ዕለቱ "መብት፣ እኩልነት እና አቅም መጎልበት ለሴቶች በሙሉ" በሚል መሪ ቃል የሚከበር ይሆናል ተብሏል።


አየር መንገዱ አሁን ላይ 8 ዋና አብራሪ ሴት ካፒቴኖች እና 70 ምክትል ሴት አብራሪዎች እንዳሉት ተገልጿል።

@seledadotio
@seledadotio

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.