Postlar filtri


የኤርትራ መንግሥት ከ60 አመት በታች ያሉ ዜጎቹ ወደካምፕ እንዲገቡ አዘዘ

የኤርትራ መንግሥት ያገቡና የልጆች እናት የሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እድሜአቸው ከ60 አመት በታች የሆኑ ዜጎቹ እንዲዘመገቡና ወደ ካምፕ እንዲገቡ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ወታደራዊ ግዳጁ ከዚህ በፊት በውትድርና ላይ የነበሩ ዜጎችን የሚጨምር ሲሆን፤ ስልጠናውን የወሰዱ አካላትም በተጠባባቂነት እንዲቆዩ ይደረጋል ተብሏል።

በተጨማሪም ያገቡ እና ልጆች ያሏቸው ሴት ወታደሮች ወደ ቀድሞ ወታደራዊ ክፍላቸው እንዲመለሱ ታዝዘዋል።

በወታደራዊ ግዳጁ መመሪያ መሰረት ዕድሜያቸው ከ50 አመት በታች የሆኑ ግለሰቦች ከሀገር እንዳይወጡ የተከለከሉ ሲሆን፤ ይህም የግዳጅ ምልመላው ጥብቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው ተብሏል።

የወታደራዊ ግዳጁን መመሪያ ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደቦች ተጥለዋል።

የክልል አስተዳደሮች ለወታደራዊ ግዳጅ የሚመለምሏቸውን ዜጎች የማሰባሰብ፣ የመመዝገብ እና የማሳወቅ ስራ መጀመራቸውንም ዘገባዎች አመላክተዋል።

ለወታደራዊ ግዳጅ ምልመላው ድንገተኛ እና ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ቅስቀሳ እየተደረገ ሲሆን፤ ይህም በኤርትራ ህዝብ ዘንድ ድንጋጤ ፈጥሯል።

የኤርትራ መንግሥት ለሌላ ዙር የትጥቅ ግጭት እየተዘጋጀ ነው የሚል ስጋትም እየጨመረ መምጣቱ ተጠቅሷል።

ቀደም ሲል ከወታደራዊ አገልግሎት በተለያየ ምክንያት የወጡትን ጨምሮ የሲቪል ዜጎችን በግዳጅ መልሶ ማሰባሰብ የመንግስትን የማያቋርጥ ወታደራዊ ፖሊሲ እና መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን ችላ ባይነት እንደሚያሳይ በውጭ የሚገኙ የኤርትራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

@sheger_press
@sheger_press


ነባሩ ፓስፖርት ምን ይሆናል?

የኢሜግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ኢ-ፓስፖርት ዛሬ ይፋ አድርጏል::አዲሱ ኢ-ፓስፖርት የአንድን ግለሰብ ባዮሜትሪክ መረጃ ጨምሮ የጣት አሻራዎችን፣ የፊት ለይቶ ማወቂያ እና የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ ያካተተ እንደሆነ ተገልጿል።ይህን ተከትሎ ታዲያ አሁን አገልግሎት ላይ ያለው ነባሩ ፓስፖርት ምን ሊሆን ነው? የሚል ጥያቄ ያስነሳል::

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ይፋ እንዳደረገው ነባሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስከሚያበቃ ድረስ ስራ ላይ ይውላል::ቀደም ሲል ፓስፖርት የነበራቸው የፓስፖርቱ የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ መጠቀም እንደሚችሉ ታውቋል::

አዲሱን ፓስፖርት መቀየር የሚፈልጉ ከሆነ ግን አሻራ ከሰጡ በኋላ በአስር ቀናት ውስጥ ፓስፖርቱ በእጃቸው እንደሚገባ ነው የተገለፀው፡፡በሂደት ግን ነባሩ ፓስፖርት በአዲሱ የኢ-ፓስፖርት እንደሚተካ አገልግሎቱ ይፋ አድርጏል::ከዚህ ቀደም ለ125 አመታት ኢትዮጵያ ትጠቀምበት የነበረውን የማንዋል ፓስፖርት ወደቴክኖሎጂ ለመቀየር በማሰብ ነው አዲሱ ፓስፖርት ይፋ የተደረገው::

Via EBC

@sheger_press
@sheger_press


ቀበሌዎች እና ገበሬ ማህበራት ኬላዎችን በማሰር ክፍያ እየጠየቁ ነዉ ተባለ፡፡

አሽከርካሪዎች በአጭር ኪሎሜትር ልዩነት በተደጋጋሚ ኬላዎች ላይ ክፍያ እየተጠየቁ መሆኑንም አስታዉቀዋል፡፡

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የጣና ከባድ መኪና አሽከሪካሪዎች ማህበር ዋና ጸሃፊ አቶ ሰጡ ብርሃን፤በአማራ ክልል በ2014 ላይ ኬላዎች ተነስተዉ ነበር ያሉ ሲሆን፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ወደ ነበረዉ አሰራር በመመለሱ ቀበሌዎች እና ገበሬ ማህበራት ሳይቀሩ ኬላዎች በማድረግ ክፍያ በመጠየቅ ላይ ናቸዉ ብለዋል፡፡

በአጭር ኪሎሜትር ልዩነት በተደጋጋሚ ኬላዎች ላይ ክፍያ እንጠየቃለን ይህ ለትራንስፖርት አገልግሎቱ ከባድ ተጽዕኖን እየፈጠረ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ይሄ ጉዳይ አሽከርካሪዎች ላይ ከሚያሳድረዉ ጫና ባልተናነሰ በሸማች ማህበረሰቡ ላይ የራሱን ተጽዕኖ እያሳደረ መሆኑንም ነዉ አቶ ሰጡ የተናገሩት፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ፤ በኢትዮጵያ ኬላ ይነሳ ተብሎ በመንግሥት ደረጃ ቢወሰንም በተለያዩ ምክንያቶች ግን 2መቶ83 ሕገወጥ ኬላዎች በመላዉ አገሪቱ ይገኛሉ ማለታቸዉ ይታወሳል ።

እነዚህ ኬላዎች የምርት ነፃ ዝውውርን በመገደብ በኢኮኖሚ እንቅስቃሴዉ ላይም  አሉታዊ ጫና ያላቸው መሆናቸዉ በተደጋጋሚ ተነስቷል፡፡

Via ኢትዬ ኤፍ ኤም

@sheger_press
@sheger_press


Update

የኤርትራ ኤምባሲን በተመለከተ

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ በተመለከተ የኤምባሲው ጉዳይ ፈፃሚ አቶ ቢኒያም በርሄ "የተባለው ሀሰት ነው "ብለዋል።

አቶ በርሄ "ስለ ኤምባሲ የተነገረው ሀሰት ነው"ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ያሉት ነገር የለም።

በአዲስ አበባ የኤርትራ ኤምባሲ ሠራተኞች በስራ ላይ አለመኖራቸው እና ኤምባሲው የመዘጋት እጣ ፈንታ እንደገጠመው ግን የውስጥ መረጃ ምንጮች ጠቁመዋል።

@sheger_press
@sheger_press


አዳዲስ መረጃዎችን ይፈልጋሉ?

በፕሮፌሺናል ጋዜጠኞች ተከፍቶ መረጃዎችን ተከታትሎ በሚዛናዊነት የሚያቀርብ ቻናል ልጠቁማችሁ ፡፡

ተማመኑበት ታተርፉበታላችሁ ተቀላቀሉት
👇👇👇
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0
https://t.me/+gPveFwjiiXdiMDE0


ወሊሶ በደረሠ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ በደረሠ  የተሽከርካሪ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት አልፏል።

የሠሌዳ ቁጥሩ ኮድ ፣3-83143 ኢቲ የጭነት ተሽከርካሪ ሴኖትራክ ተሽከርካሪ ከጐሮ ወደወሊሶ ሲጓዝ ከወሊሶ ወደ ወልቂጤ አስራ ሰባት ሰው አሣፍሮ  ሲጓዝ ከነበረ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ  የሚኒባሱ ሹፌሩን ጨምሮ ወዲያው አራት ሠዎች ህይወት አልፏል።

በሆስፒታል ደግሞ ሑለት ሰው በአጠቃላይ ስድስት ሠው ሲሞት አስራ አንድ ሰው ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል። አደጋው ዛሬ ንጋት ላይ የደረሠ ሲሆ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወሊሶ ቅዱስ ሉቃስ ሆስፒታል በህክምና ድጋፍ ላይ እንደሚገኙ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኢንስፔክተር ትግሉ ለገሠ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

@sheger_press
@sheger_press


❖ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻውም እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ከቤተ-ክርስቲያን የሚዲያ አካላት ጋር በመነጋገርም ዶክሜንተሪዎችን እንዲሰሩና ምዕመኑ ገዳማዊያኑ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለማስቻል ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል፡፡

‹ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል፣በጎነቱንም መልሶ ይክፍለዋል› እንዲል ጠቢቡ ሰለሞን፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድህነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን፣ ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957
ወይም 0938644444


🙏🙏🙏❤️❤️❤️

ተመስገን.........

በሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ ከ 12,000,000 ብር በላይ የተሰባሰበ ቢሆንም አሁንም ገዳሙ ድጋፍ ይፈልጋል"

በማዕከላዊ ጎንደር ሐገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው ይህ ገዳም፣ ከዘጠና በላይ መነኮሳትና በመቶ የሚቆጠሩ ፀበልተኞች የሚገኙበት እጅግ ድንቅ ተዓምር ያለበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም ቢሆንም መነኮሳቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር ተጋርጦባቸው ይገኛሉ።

በአንድ በኩል አካባቢው በርሃማ በመሆኑ በበጋ ወቅት ለከፍተኛ ድርቅ ይጋለጣል፣በዚህም ምክንያት ምንም ዓይነት አዝዕርት አይበቅልበትም፣ይህን ተከትሎ ቀደም ሲል ድጋፍ ያደርጉ የነበሩት የአካባቢው ነዋሪዎች ሳይቀር ለገዳሙ ምንም አይነት ድጋፍ ለማድረግ ተቸግረዋል።

ገዳማዊያኑ የሚቀምሱት እህል፣የሚለብሱት ልብስ በመጠኑ የተሟላላቸው ቢሆንም ከጾም፣ ጸሎት መልስ ስጋቸውን የሚያሳርፉበት በዓት (ቤት) የላቸውም። በአንድ ደሳሳ ጎጆ በዓት ውስጥ ለሶስት ለአራት የሚያድሩበት በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ዉስጥ ይገኛሉ።

በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማዊያን ዛሬም ከጸሃይ፣ ከብርድ፣ ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ፣ ገዳማዊያኑን ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ፣ በጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን፣ ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት፣በሐገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት በመሰራት ላይ ይገኛል።

እነዚህን የታቀዱ ለገዳሙ አስፈላጊ እና መሰረታዊ የሆኑትን የልማት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ ለማሰባሰብ የሚረዱ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶችን ለመጠቀም ጥረት ተደርጓል።

ከነዚህም ውስጥ፦ ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የሚገልጹ እና የሚያሳዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እንዲሁም ትሁፊት በጠበቀ መልኩ፡

❖ በቴሌቪዥንና ራዲዮን ማስታወቂያዎችን በማስተላለፍ ሕብረተሰቡ መረጃዉ ኖሮት የተቻለውን ድጋፍ እንዲያደርግ

❖ በማሕበራዊ ሚዲያ ማለትም፡ በፌስቡክ፣ በዩቲዩብ፣ በቲክቶክ፣ በቴሌግራም፣ በኢንስታግራምና ሌሎችንም በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ሥራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል።

በዚህም እስካሁን 11,000,000.00 (አስራ አንድ ሚሊዮን) ብር የሚያህል የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም 1,200,000.00(አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር የሚሆን የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።

ፕሮጀክቱ ከተጀመረ 11(አስራ አንድ) ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በነዚህ ጊዚያት በመጀመሪያው ምዕራፍ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል።

ከተሰሩ ስራዎች መካከል ፡-

❖ የእናቶች በዓት ወይም ቤት በጥሩ ሁኔታ ተሰርቷል።

❖ 170 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ ለእናቶችም ለአባቶችም ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረው ቦታ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ለገዳማዊያን እንቅስቃሴ ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።

❖ በአካባቢው ምንም አይነት የመብራት አገልግሎት ያልነበረ ሲሆን አሁን የሶላር መብራት ተሟልቶ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ ተችሏል።

❖ ቤተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቤት ተሰርቷል፤ የሚያስፈልጉ ሙሉ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል።

❖ ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።

❖ ለገዳማዊያኑ የእደ-ጥበባት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ተከናውኗል እንዲሁም የሸማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድረግ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፣ ለስራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች እና የጥሬ እቃ ግብዓቶችም ተሟልተዋል።

❖ የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽን ግዢ ተከናውኗል።

❖ አካባቢው በተደጋጋሚ በድርቅ የሚጠቃ በመሆኑ ለገዳማዊያኑ የተሻለ ለማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

❖ ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሎ ሜትር ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ሥራ ተሰርቷል።

❖ የእናቶች የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል።

❖ ለግንባታ አገልግሎት የሚውል የሲምንቶ ማቡኪያ ማሽን፣የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽነሪ ግዥ ተፈጽሟል።

❖ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የገዳሙ ይዞታ ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ያልነበረው በመሆኑ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታው እንዲረጋገጥለት ተደርጓል።

❖ ገዳማዊያኑ እየሰሩ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ ለማድረግ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያተ ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ ወደ ስራ ተገብቷል።

❖ ለግንባታ የሚውል በሃሙሲት ከተማ 30 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከመንግስት በሊዝ በመውሰድ በዚህም የአብነት ት/ቤት ፣ አለማዊ ት/ቤት እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ በተጨማሪም ሌሎችም ለገዳማዊያኑ አስፈላጊ የሆኑ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ይሆናል።

የልማት ስራዎች ከተጀመሩ አጭር ጊዜ በመሆኑ እስካሁን የተሰሩ ስራዎች አበረታች ቢሆኑም ከዚህ በተሻለ ፍጥነት መስራት እንዳይቻል የተለያዩ ተግዳሮቶች አጋጥመዋል፡፡

❖ በገዳሙ ውስጥ ስራ የሚሰራባቸው ቀናት ውስን መሆን፤ ማለትም ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ ገዳማዊያኑም የሚያከብሯቸው በዓላት ሲጨማመሩ በወር ውስጥ የሚሰራባቸው ቀናት ከ 4 (አራት) – 14 (አስራ አራት) የሚሆኑ ቀናት ብቻ ናቸው።

❖ በግንባታ እቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል የዋጋ ልዩነትም አንዱ ችግር ነው።

❖ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ችግሮች ተጠቃሽ ሲሆኑ

❖ ከሚዲያው አካባቢ በተለይም ቲክቶክ አንዳንድ ቲክቶከሮች ፣ የገዳሙ አባቶችን ሆነ የቤተክርስቲያን መዋቅር ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁና ያለ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በይመስለኛል ብቻ፣ የገዳሙንም የተከታዮቻቸውንም ክብር በማይመጥን መልኩ ተገቢና ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት የሚሉት ከብዙዎቹ ተግዳሮቶች ጥቂቶቹ እነዚህ ናቸው።

እስካሁን የተከናወኑ ስራዎች በተለይም የእናቶችን ችግር በመቅረፍ ደረጃ ጥሩና አስደሳች ቢሆንም በአባቶች በኩል ገና ብዙ ስራዎች ይቀራሉ፡፡በመሆኑም በቀጣይ በትኩረት ከሚሰሩ ስራዎች መካከል፡-

❖ የአባቶች በዓት ግንባታ ሥራ

❖ የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ

❖ የአባቶች የመጸዳጃ ቤት ግንባታ ሥራ
❖ የእንጨት እና የብረታብረት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ሥራ፣
❖ የእህል መጋዘን ግንባታ ሥራ

❖የቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ ሥራ

❖ የአብነት ት/ቤት ፣ ዓለማዊ ት/ቤት እና የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ ግንባታ ሥራ

❖ የጸበልተኞች ማረፊያ ቤት ግንባታ ሥራ እንዲሁም

❖ የውሃ እና መብራት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ በቀጣይ ከሚሰሩት ስራዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው፡፡

በቀጣይ ለሚሰሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ የሚሆን ድጋፍን ለማሰባሰብ በቀጣይም የተለያዩ መርሀ-ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል።

ለአብነትም፡-

❖ ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ምዕመኑ ከገዳሙ በረከት እንዲያገኙ እንዲሁም ገዳሙን እንዲጎበኙ የጉዞ መርሃግብር ተዘጋጅቷል።

❖ የድጋፍ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ-ግብር በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የሚከናወን ይሆናል።

❖ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያ በተገኙበት ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ይኖራል፤


በኢትዮጵያ ፈንታሌ የተከሰተው የመሬት መናወጥ የምስራች ዜና ይዞ መጥቷል

የኢሮፒያን ሳተላያት መረጃ ይዞ በወጣው መሰረት ከሰሞኑን በፈንታሌ ሲከሰት የነበረው የመሬት ርዕደት እንደተፈራው አደጋ ሳይሆን እጅግ ባልተለመደ መልኩ ሚቴን የተሰኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ከምድር ሆድ እቃ ውስጥ ይዞ ወጥቷል ብሏል።

በሚቴን የተፈጥሮ ጋዝ ዙሪያ የሚሰራው የካናዳው ድርጅት GHGsat እንደገለፀው በፈንታሌ ተራራ በአሁን ሰዓት በ ቀን 1,400 ቶን የሚቴን ጋዝ እየወጣ ይገኛል ። ይህንንም በንፅፅር ሲያስረዳ 1,400 ቶን ጋዝ በቀን ማለት 20ሚሊየን ኪሎ ግራም የከሰል ድንጋይ ቢቃጠል የሚገኘው ሃይል እንደ ማለት ነው ብሏል ግዝፈቱን ለማስረዳት ።

በሌላ በኩል በአሁን ሰዓት በቀን እየወጣ ያለው 1400 ቶን የሚቴን ጋዝ 8000 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨት የሚችል ሲሆን ይህም... ከህዳሴው ግድብ ሀይል ማመንጫ በ3ሺ ሜጋ ዋት ይልቃል ።

ይህ ብቻ ሳይሆን እንደማየነኛውም የተፈጥሮ ጋዝ ይህ አሁን ፈንታሌ በራሱ ግዜ በገዛ ፍቃዱ እነሆ በረከት ብሎ ብቅ ያለው ሚቴን በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋለ በአሁን ሰዓት እጅግ ተፈላጊ ወደ ሆነው LNG (Liquefied Natural gas ) ተቀይሮ ወደ 2 ሚሊየን ሊትር በቀን ማምረት ይቻላል ።
በዚህም አያበቃም ... ለግብርና ምርጥ ወሳኝ የሆነው የተፈጥሮ ማዳበሪያ ቢለወጥ ኢትዮጵያ በአለማችን ከፍተኛው ፖታሽ ሃብት ባለቤት እንደመሆኗ የኢትዮጵያን የማዳበሪያ ፍላጎት አሟልቶ በኤክስፖርት የሀብት ምንጭ የሚሆን ሀብት ነው ተብሏል።
በቀላሉ ለማስረዳት ኢትዮጵያ ሳይታሰብ የተፈጥሮ ጋዝ ምድሯን ፈንቅሎ ወጥቷልና አስፈላጊው ጥናትና በጀት ተይዞ ወደ ስራ ሊገባ ይገባል ።

@sheger_press
@sheger_press

4.5k 0 18 14 66

ነባሩን ፓስፖርት ለያዛችሁ አጫጭር መረጃዎች‼️

👉 ነባሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል፣

👉 የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል፣

👉 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈት አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል፣

👉 ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል፣

👉 ከፓስፖርት በተጨማሪ ከ10 በላይ የጉዞ ሰነዶችን እንዲዘምኑ ማድረግ ተችሏል፣

👉 አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆን ተነግሯል።

@sheger_press
@sheger_press


በአዲስ አበባ ከተማ አምስት ሊትር ዘይት ከ1400 እስከ 1600 ብር እየተሸጠ ይገኛል

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ መጠን እየጨመረ እንደሚገኝ ብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባደረገው የገበያ ቅኝት ለማወቅ ችሏል።

በተደገው የገበያ ቅኝት ከዚህ ቀደም 1200 እስከ 1300 ብር ይሸጥ የነበረው አምስት ሊትር የምግብ ዘይት አሁን ላይ ከ200 መቶ እስከ 300 ብር ጭማሪ አሳይቷል።

እንዲሁም መሰረታዊ የምግብ ፍጆታ የሚባሉት ምስር ከ200 ወደ 270 ፣ እንቁላል ከ11 ብር ወደ 18 ብር ጭማሪ የታየበት ሲሆን ሌሎች ምርቶች ላይ በአንድ ሳምንት ውስጥ የተጋነነ የዋጋ ጭማሬ መኖሩን በቅኝታችን አረጋግጠናል።(ዳጉ)

@sheger_press
@sheger_press

6.7k 0 10 21 50

12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ

#Ethiopia | የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት ይዘጋጃል፡፡

የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው። ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው፡፡

በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ አሉ፡፡

በመሆኑም የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል።

ስለሆነም የፈተና ዝግጅቱ፡-
1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣
2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣
4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ ይሆናል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ ይሆናል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ስለሆነም ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት!
የካቲት 2017 ዓ.ም

@sheger_press
@sheger_press


ለሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም 11 ሚሊዮን ብር መሰብሰቡ ተገለፀ
I በማዕከላዊ ጎንደር ሐገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው ሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንደነት ገዳም፣ ከዘጠና በላይ መነኮሳትና በመቶ የሚቆጠሩ ፀበልተኞች የሚገኙበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም ቢሆንም መነኮሳቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር ተጋርጦባቸው እንደሚገኝ ተነግሯል።
ገዳማዊያኑ የሚቀምሱት እህል፣ የሚለብሱት ልብስ በመጠኑ የተሟላላቸው ቢሆንም ከጾም፣ ጸሎት መልስ ስጋቸውን የሚያሳርፉበት ቤት የላቸውም፣ በአንድ ደሳሳ ጎጆ ቤት ውስጥ ለሶስት ለአራት የሚያድሩበት በጣም አሳዛኝ ሁኔታ ዉስጥ እንደሚገኙ ነው የተገለፀው።
ገዳማዊያኑን ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ፣ በጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገው፣ በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን፣ ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት፣ በሐገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት በመሰራት ላይ ይገኛል ተብሏል።
ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታ የሚገልጹ እና የሚያሳዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እንዲሁም ትሁፊት በጠበቀ መልኩ በቴሌቪዥን፣ በሬዲዮ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎችን በማስተላለፍ ሕብረተሰቡ መረጃዉ ኖሮት የተቻለውን ድጋፍ እንዲያደርግ ተደርጎ በዚህም እስካሁን 11,000,000 (አስራ አንድ ሚሊዮን) ብር የሚያህል የገንዘብ ድጋፍ እንዲሁም 1,200,000 (አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር የሚሆን የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ እንደተቻለ ተገልጿል።
ፕሮጀክቱ ከተጀመረ 11 (አስራ አንድ) ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው ምዕራፍ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል።
ከተሰሩ ስራዎች መካከል ፡-
❖ የእናቶች በዓት ወይም ቤት በጥሩ ሁኔታ ተሰርቷል።
❖ 170 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ ለእናቶችም ለአባቶችም ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረው ቦታ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት ለገዳማዊያን እንቅስቃሴ ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።
❖ በአካባቢው ምንም አይነት የመብራት አገልግሎት ያልነበረ ሲሆን አሁን የሶላር መብራት ተሟልቶ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ ተችሏል።
❖ ቤተ-እግዚአብሔር ወይም ማዕድ ቤት ተሰርቷል፤ የሚያስፈልጉ ሙሉ ቁሳቁሶችም ተሟልቷል።
❖ ገዳማዊያኑ በተደጋጋሚ የሚያጋጥማቸውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በዘላቂነት ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
❖ ለገዳማዊያኑ የእደ-ጥበባት ውጤቶችን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ተከናውኗል እንዲሁም የሸማ ስራ ሙያ እንዲሰለጥኑ በማድረግ ወደ ስራ እንዲገቡ ተደርጓል፣ ለስራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች እና የጥሬ እቃ ግብዓቶችም ተሟልተዋል።
❖ የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽን ግዢ ተከናውኗል።
❖ አካባቢው በተደጋጋሚ በድርቅ የሚጠቃ በመሆኑ ለገዳማዊያኑ የተሻለ ለማድረግ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
❖ ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሎ ሜትር ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ሥራ ተሰርቷል።
❖ የእናቶች የመጸዳጃ ቤቶች ግንባታ ተከናውኗል

❖ ለግንባታ አገልግሎት የሚውል ሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን፣ የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽነሪ ግዥ ተፈጽሟል
❖ የገዳሙ ይዞታ ህጋዊ የይዞታ ማረጋገጫ ያልነበረው በመሆኑ የገዳሙ ህጋዊ ይዞታ እንዲረጋገጥ ተደርጓል።
❖ ገዳማዊያኑ ቀጣይነት ያለው ገቢ እንዲያመነጩ በማሰብ በሃሙሲት ከተማ የሸቀጣ ሸቀጥ እና የንዋያት ቅዱሳት መሸጫ ሱቅ ተከፍቶ ወደ ስራ ተገብቷል።
❖ ለግንባታ የሚውል በሃሙሲት ከተማ 30ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ከመንግስት በሊዝ በመውሰድ የአብነት ት/ቤት፣ አለማዊ ት/ቤት እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ጣቢያ በተጨማሪም ሌሎችም ገዳማዊያን አስፈላጊ የሆኑ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ይሆናል።
ከሚዲያው አካባቢ በተለይም ቲክቶክ አንዳንድ ቲክቶክሮች የገዳሙ አባቶችን ሆነ የቤተክርስቲያን መዋቅር ምንም አይነት መረጃ ሳይጠይቁና ያለ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በይመስለኛል ብቻ፣ የገዳሙንም የተከታዮቻቸውንም ክብር በማይመጥን መልኩ ተገቢና ትክክለኛ ያልሆኑ መረጃዎችን ማሰራጨት ተገቢ አይደለም ተብሏል።
በቀጣይ ለሚሰሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ የሚሆን ድጋፍን ለማሰባሰብ በቀጣይም የተለያዩ መርህ-ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል።
ለአብነትም፡-
❖ ከመጋቢት 25 እስከ ሚያዝያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ምዕመኑ ከገዳሙ በረከት እንዲያገኙ እንዲሁም ገዳሙን እንዲጎበኙ የጉዞ መርሃግብር ተዘጋጅቷል።
❖ የድጋፍ ማሰባሰቢያ የቀጥታ ስርጭት መርሃ ግብር በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት የሚከናወን ይሆናል።
❖ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሊኒየም አዳራሽ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ሊቃውንት ቤተክርስቲያን በተገኙበት ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ይኖረናል፤
❖ የሚዲያ ንቅናቄ ዘመቻውም እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ከቤተ ክርስቲያን የሚዲያ አካላት ጋር በመነጋገርም ዶክሜንተሪዎችን እንዲሰሩና ምዕመኑ ገዳማዊያኑ ያሉባቸውን ችግሮች በመረዳት ድጋፍ እንዲያደርጉ ለማስቻል ስራዎች የሚሰሩ ይሆናል፡፡


@sheger_press
@sheger_press


አዲሱ ፖስፖርት ዛሬ ይፋ ተደረገ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ዘርጋሁት ባለው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሚስጥራዊ ህትመትና ቴክኖሎጂ ልምድ አለው ከተባለው የጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ አማካይነት ዘመኑ በደረሰበት የሚስጥራዊ ህትመት የታተመ አዲስ ፖስፖርት ዛሬ የካቲ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በሳይንስ ሙዚየም ይፋ እያደረገ ነው፡፡

@sheger_press
@sheger_press


በትግራይ በጸጥታ ኃይሎች እና ነዋሪዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት 17 ሰዎች መጎዳታቸው ተገለጸ

በትግራይ ክልል ሰሓርቲ በተባለች ወረዳ የአንድ ቀበሌ አስተዳዳሪ ማኅተም በኃይል ነጥቀዋል የተባሉ የፀጥታ አባላት ወሰዱት በተባለ ርምጃ 17 ሰዎች መጎዳታቸውን የወረዳው አስተዳዳሪ ተናገሩ።

የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ፣ የሰራዊቱ አባላት ጣልቃ መግባታቸውን ገለፆ፣ “እንዲኽ ያለ ጣልቃ ገብነት ክልሉን ወደ ከባድ ቀውስ ያስገባዋል” ብሏል።(VOA)

@sheger_press
@sheger_press

15 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.