ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


❤ በየቀኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስንክሳር የሚታሰቡ የቅዱሳን ታሪክ፣ የኢትዮጵያኑ ቅዱሳን በየበዐላቸው ቀን አስደናቂ፣ አስገራሚ ገድላቸው፣ ቃል ኪዳናቸው፣ የቅዱሳን ሰላምታ፣ የየቀኑ የቅዳሴ መልዕክታ፣ የሐዋርያት ሥራ፣ የወንጌል ጥቅስ እና ምስባክ ይቀርብበታል።
❤ የፌስቡክ አድራሻዬ ሊንክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri






❤ በሰሜን_ሸዋ_ሀገረ_ስብከት በግሼ ራቤል ወረዳ ለሚገኘው #የመኘት_ቅዱስ_በዐለ_ወልድ_ቤተ_ክርስቲያን የምርቃት በዐል ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም የወረዳው ቤተ ክህነት የየመምሪያው ሀላፊዎች፣ የአካባቢው ሕብረተሰብ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ። ፈጣሪያችን ቅዱስ በዐለ ወልድ ሆይ! ሳይገባን በዚህ በዐልህ ላይ ያሳተፈከን ክብር ምስጋና ይግባህ። ለአገራችንን ኢትዮጵያን ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትና መተሳሰብን ላክልን።






❤ ውድ የቴሌግራሜ ቻናል ተከታታይ ተወዳጅ ቤተሰቦቼ ቸር ሰነበታችሁ #በሰሜን_ሸዋ_ሀገረ_ስብከት በግሼ ራቤል ወረዳ ለሚገኘው #የመኝት_ቅዱስ_በዐለ_ወልድ_ቤተ_ክርስቲያን ባለፈው የጠየኳችሁ ለምርቃቱ የሚያስፈልጉ የቀሩት መንበሩን፣ ምንጣፋኑ፣ መጋረጃውና ድባብ ጥላው የመሳሰሉት ነገሮች የመጀመሪያ ሶላርና ድምጽ ማጉያው የገዙት ወንድሞች ስላሟሉ የምርቃቱ በዐል ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ስለሆነ። እኔም አንድ ወንድሜ አንድ እህቴ  በሰጡት ገንዘብ የቀሩቱ ነገሮች መዝሙረ ዳዊት፣ መጽሐፍ ግንዘት፣ የግሪክ እጣን፣ ሽቶ፣ የፕላስቲክ ወንበር፣ የቅዳሴ ጠበል መስጫ የሚሆኑት መቊረርቱን፣ ኩባያው ይዤ የምርቃቱ በዐል ለማክበር ስለሄድኩ #ከጥር_27_እስከ_ጥር_29 ያለው ቀድሜ Post ስላደረኩት ወደኋላ እያላቹ የየቀኑን ተመልኩቱ።


❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላ በአውሲም ከተማ መኰንኑ አርያኖስ ደረሰ፡፡ የሀገሩን ታላላቅ ሰዎችንም አቅርቦ ስለከበረ ቅዱስ ቢፋሞን ጠየቃቸው፡፡ የአገር ሽማግሎችም ስለእርሱ አዘኑ-እርሱ ተአምራትን የሚያደርግ አማልክትንም የሚረግም መሆኑን ያውቃሉና፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ቢፋሞን ቤተሰቦቹን ተሰናብቶ ያማሩ ልብሶቹን ለብሶ ፈረስ ጋልቦ የሀገሩ ሽማግሎችና መኮንኑ ካሉበት ቦታ ደረሰ፡፡ መኮንኑ አርያኖስም ባየው ጊዜ ደስ ብሎት በክብር ሰላምታ ሰጠው፡፡

❤ ቅዱስ ቢፋሞንም "የሰላም ትርጓሜው ደስታ ነው፣ እኔ በጌታዬና በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ደስታ አለኝ አንተና ባልንጀሮችህ ግን በሰማያት ደስታ የላችሁም" አለው፡፡ አርያኖስም "እኔ ክፉ ነገርን እንድትነግረኝ አልመጣሁም፣ ለአማልክት እንድትሠዋ በንጉሡ ደብዳቤ ታዝዤ መጣሁ እንጂ" አለው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም "አማልክቶቻችሁ አፍ እያላቸው የማይናገሩ፣ እጅ እያላቸው የማይዳስሱ፣ ጆሮ እያላቸው የማይሰሙ፣ ዐይን እያላቸው የማያዩ፣ አፍ እያላቸው የማይተነፍሱ ናቸውና የሠሩአቸውና የሚያመልኳቻም እንደ እነርሱ ይሁኑ፡፡ እኔ ግን ሰማይንና ምድርን በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ ለፈጠረ ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ አሰግዳለሁ" አለው፡፡ መኰንኑ አርያኖስም ይህንን ነገር ከቅዱስ ቢፋሞን አፍ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎችም አሠቃየው፡፡ ዳግመኛም በፈረሶች ላይ አሥሮ መሬት ለመሬት እየጎተተ ከተማውን ሁሉ አዞረው፡፡ የቅዱስ ቢፋሞን እናቱና አገልጋዩ በመጡ ጊዜ በከበረች የወንጌል ቃል አጽናናቸው፡፡ እነርሱና ሌሎችም የከተማው ሰዎች "እኛም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ የምናምን ነን፣ ሰማዕትም እንሆን ዘንድ እንወዳለን" ብለው ጮኹና የመኰንኑን ለወንበር ገለበጡት፡፡ መኰንኑም ጥልቅ ጉድጓድ አስቆሮ እሳት አስነድዶ ከዚ ውስጥ ጨመራቸውና ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የድል አክልሊን ተቀዳጁ፡፡ ቁጥራቸውም አምስት መቶ ሆነ፡፡ እነዚህም 500 ቅዱሳን ምስክርነታቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ቅዱስ ቢፋሞን ያጽናናቸውና ያበረታቸው ነበር፡፡ የከበረች እናቱም በላይዋ ላይ እንዲጸልይ ለመነችው፣ እርሱም በመስቀል ምልክት በላይዋ አማተበና በሰላም ሂጂ አላት፡፡ እርሷም ወዲያው ማንም ሳይነካት ዘላ ከእሳቱ ገባች፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡

❤ የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንን ግን አርያኖስ ወደ ንጉሡ መክስምያኖስ ሰደደው፡፡ ንጉሡም "የነገሥታቱን ትእዛዝ የምትተላፍ ለአማልክት የማትሠግድ ሥራየኛው ቢፋሞን አንተ ነህን?" አለው፡፡ ቅዱሱም "እኔ ሥራይን አላውቅም፣ ለረከሱ አማልክትህ ግን አልሰግድም፣ አንተም እነርሱም በአንድነት ወደ ገሃነመ እሳት ትወርዳላችሁ" አለው፡፡ ንጉሡም ይዞ በእጅጉ አሠቃው፡፡ ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ወደ መኮንኑ ኄሬኔዎስ ላከው፡፡ እርሱም ካሠቃው በኋላ መልሶ ለአርያኖስ ላከው፡፡ በእነዚህም ጊዜ ቅዱስ ቢፋሞን ምንም አልበላም ነበር፡፡ አርያኖስም በብረት ችንካሮች ቸነከረውና "ለአማልክት ካልሰገድክ አጠፋሃለሁ" አለው፡፡ ቅዱሱም ንጉሡንና አማልክቱን ረገማቸው፡፡ መኰንኑም በዚህ ጊዜ አሥሮ እየጎተተ በከተማው ሁሉ አዞረው፡፡ ከእንዴና ከተማ ውጭ አውጥቶ በእሳት አቃጠለው፤ ነገር ግን ጌታችን ቅዱስ ቢፋሞንን ከእሳቱ ውስጥ ያለምንም ጉዳት በደህና አወጣው፡፡ ቅዱሱም በእሳት ቆሞ ሳለ ከእግሮቹ ብዙ ደም ፈሰሰ፡፡ በዚያም ቦታ አንድ ዐይነ ሥውርና ለምጻም ሰው ነበረ፡፡ እርሱም ከቅዱስ ቢፋሞን ደም ወስዶ ዐይኑን ቢቀባው ወዲያው ማየት ቻለ፣ ከለምጹም ነጻ፡፡ ከዚህም በኋላ "እኔም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኛለሁ" ብሎ ጮኸ፡፡ ወዲያውም መኰንኑ ተናዶ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፡፡

❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ አርያኖስ የቅዱስ ቢፋሞንንም አንገት በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም አገልጋዩን ዲዮጋኖስን ወደ እርሱ አቅርቦ ሥጋውን በስውር እንዲጠብቅ ደሙንም በበፍታ ልብስ እንዲቀበል ይኸውም ከመከራው ዘመን በኋላ ለበረከት እንዲሆን ነገረው፡፡ ገድሉንም ለምእመናን እንዲነገር ከነገረው በኋላ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበና ወደ ጭፍሮቹ ሄዶ "የታዘዛችሁትን ፈጽሙ" በማለት እንዲሰይፉት ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ወደ ላይኛው ግብጽ አጥማ አውራጃ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ የተዘጋጀለትንና አስቀድሞ ያየውን የክብር አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ከአንገቱም ብዙ ደም በፈሰሰ ጊዜ አገልጋዩ ዲዮጋኖስ በፍታውን ዘርግቶ ደሙን ተቀበለ፡፡ በቦታው መዓዛው እጅግ ጣፋጭ የሆነ ሽታ በሸተተ ጊዜ ችፍሮቹ ደንግጣና ፈርተው ከቦታው ሸሹ፡፡ ምእመናንም መጥተው ሥጋውን ወስደው በክብር ገንዘው ቀበሩት፡፡ ከመቃብሩም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡

❤ አገልጋዩም ያችን በፍታ ወደ አገሩ ወስዶ ምን እንደሚያደርግ እያሰበ ሳለ ቅዱስ ቢፋሞን ተገለጠለትና ለወዳጁ ለቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎችም ሁሉ ገድሉን እንዲነግር አዘዘው፡፡ እርሱም በመርከብ ተሳፍሮ ሲሄድ በመርከብ ሳለ ጌታችን በዚያች በቅዱስ ቢፋሞን ደም በታለለች በፍታ ብዙ ተአምር አደረገ፡፡ ዲዮጋኖስም የቅዱሱን ገድል ነገራቸው፡፡ እነርሱም እያደነቁ ወደ አገሩ አውሲም አደረሱት፡፡ ዲዮጋኖስም አውሲም እንደደረሰ ለቅዱስ ቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎች ሁሉ የቅዱስ ቢፋሞንን ገድል ነገራቸው፣ ያችንም በደሙ የታለለች በፍታ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ብዙ ተአምራት እያደረገችላቸው ከእነርሱ ጋር በክብር አኖሯት፡፡

❤ የመከራው ዘመን አልፎ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ከነገሠ በኋላ እግዚአብሔርም የከበረ የቅዱስ ቢፋሞንን ሥጋ ለምእመናን አለኝታና መጽናኛ ለበሽተኞችም የሚፈውስ ኃይል እንዲሆን ሊገልጠው ወደደና ገለጠው እርሱም በላይኛው ግቡጽ በጥማ አውራጃ በቃው ከተማ በጥር ሃያ ሰባት በዚች ቀን በሰማዕትነት የሞተ ነው ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በተጋዳይ በቅዱስ ቢፋሞን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን፡፡ ምንጭ፦ የጥር 27 ስንክሳር።

                            
                           ✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለከ_እንተ_ረከብከ_ሞገሰ። ኅቡአተ ትፍትን ወዘማዕቅት ከርሠ። #ሱርያል_መልአክ እንዘ ትስእል መንፈሰ። ፍጥረታተ ኵሎ አመ በማየ አይኅ ደምሰሰ። እግዚአብሔር አትረፈ ሰማኒተ ነፍሰ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር _27።

                            ✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኵሎ አሚረ። ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ። ንቃህ እግዚኦ ለምንት ትነውም"። መዝ 43፥22። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥5-20፣ ይሁ 1፥11-16 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-22። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 11፥8-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ወይም የቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የመልአኩ የቅዱስ ሱርያል የመታሰቢያ በዓልና የቅዱስ ኄኖክ የዕርገቱ መታሰቢያ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራምና ፌስቡክ ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያሉትን ሊኮች ይጫኑት።  

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA

https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886



8 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.