ስፑትኒክ ኢትዮጵያ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ያልተነገረውን እንነግርዎታለን
ስለ አፍሪካ በእንግሊዘኛ ቋንቋ፤ @sputnik_africa

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
#sputnikviral | 🇪🇹🐏 'በፈጣሪ ሰም በፆሙ እንኳ ምን አል ብተዉኝ' 🤣

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇪🇹 ✈️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET-302 አደጋ ተጎጂዎች የመታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

የሐውልት ምርቃቱ አደጋው በተከሰተበት የስድስተኛ ዓመት መታሰቢያ ቀን ተመርቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ET-302 መጋቢት 1 ቀን 2011 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ኬንያ ለመብረር በተነሳ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ተከስክሶ የሁሉም ተሳፋሪዎች ሕይወት ማለፉ ይታወሳል፡፡

ምስሎቹ ከማህበራዊ የትሥሥር ገፆች የተገኙ ናቸው

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇳🇦 ቀጣይዋ የናሚቢያ መሪ ናንዲ-ንዳይትዋህ የገዥው ፓርቲ ስዋፖ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ሹመታቸውን በተቀበሉበት ወቅት ባደረጉት ንግግር የስዋፖ ፓርቲ አባላት በእሳቸው ላይ እምነት ስላሳደሩ ምስጋናቸውን ገልጸዋል።

ኔቱምቦ ናንዲ-ንዳይትዋህ በ2016 ዓ.ም ጥር ወር ህይወታቸው ያለፈው ፕሬዝዳንት ሃጌ ጌንጎብን በመተካት ነው የፓርቲው ፕሬዝዳንት የሆኑት።

"ይህን አደራ በሙሉ ልቤ እቀበላለሁ። እኔን በመምረጥ አባላቶቻችንን እና የናሚቢያን ሕዝብ ለማገልገል ያላችሁን አንድነት አሳይታችኋል። እኔን ፕሬዝዳንት አድርጋችሁ በመምረጣችሁ ፓርቲያችንን እንድመራ ያላችሁን የማያወላዳ ድጋፍ አረጋግጣችኋል። አመሰግናለሁ ጓዶች። ከሚከፋፍለን አንድ የሚያደርገን ይበልጣል" ሲሉ ናንዲ-ንዳይዋትህ ተናግረዋል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇸🇴 የሶማሊያ ጦር ባካሄደው የአየር ጥቃት ከፍተኛ የአልሻባብ አዛዥ ተገደለ

ዩሱፍ ዴግናስ በመካከለኛው ሸበሌ ክልል በኤል-ባድ አቅራቢያ እንደተገደለ ተገልጿል። በአካባቢው በመንግሥት ኃይሎች እና ታጣቂዎች መካከል ለቀናት የቆየ ከፍተኛ ግጭት ሲካሄድ ነበር ተበሏል። የመንግሥት ሚዲያዎች እንደዘገቡት ዴግናስ በመካከለኛው ሸበሌ የአልሻባብ* ዘመቻዎችን ያቀነባብር ነበር። የአዛዡ ግድያ ቡድኑ በክልሉ ውስጥ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደሚያሰናክል ተነግሯል፡፡

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በአካባቢ ሚሊሻዎች ከሚታገዘው ብሄራዊ ጦር እና ከአፍሪካ ሕብረት ኃይሎች ጋር በመሆን በቅርቡ በአልሻባብ ላይ “መጠነ ሰፊ ጦርነት” ለማወጅ ቃል መግባታቸው ይታወሳል።

* በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ ሀገራት የታገደ አሸባሪ ድርጅት

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
🇷🇺🇸🇾 ሩሲያ እና አሜሪካ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በሶሪያ ጉዳይ ዙርያ በዝግ እንዲመክር ጠየቁ

🇺🇳 ሞስኮ በምዕራብ ሶሪያ በሲቪሎች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት የተመለከተው ውይይት በዛሬው እለት ይካሄዳል ብላ እንደምትጠብቅ በተመድ የሩሲያ ምክትል ቋሚ ተወካይ ዲሚትሪ ፖሊያንስኪ ተናግረዋል።

ከማህበራዊ የትሥሥር ገጾች የተገኘው ተንቀሳቃሽ ምስል ሲቪሎች በሶሪያ ላታኪያ ግዛት በሚገኘው የሩሲያ ሃሜሚም አየር ማረፊያ ተጠልለው ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


📡 አሜሪካዊው ቢሊየኔር ኤለን መስክ በዩክሬን ያሉትን የስታርሊንክ ተርሚናሎች በፍፁም እንደማያጠፋ ተናገረ

"በዩክሬን ፖሊሲ የቱንም ያህል ባልስማማ ስታርሊንክ ተርሚናሎቹን ፈጽሞ እንደማያጠፋ ግልፅ ማድረግ እፈልጋለሁ። የተናገርኩት ያለ ስታርሊንክ የዩክሬን መስመሮች እንደሚበጣጠሱ እና ሩሲያውያን ግንኙነቶቻቸውን ማቋረጥ እንደሚችሉ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ነገር በጭራሽ አናደርግም ወይም ለመደራደሪያነት አንጠቀምበትም" ሲል ኤለን መስክ በኤክስ ገፁ ላይ ፅፏል።


ኤለን መስክ የስታርሊንክ ስርዓት የዩክሬን ጦር የጀርባ አጥንት እንደሆነ እና ለማጥፋት ከወሰነ የዩክሬን ጦር ግንባር ይፈራርሳል ማለቱ ይታወሳል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
🇨🇦🇺🇸 "ካናዳ በምንም ዓይነት መልኩ የአሜሪካ አካል አትሆንም" ሲሉ ተመራጩ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ተናገሩ

🚫 ካናዳ "በዘመኗ ከፍተኛ ቀውስ" ውስጥ ትገኛለች ሲሉ የሀገሪቱ ገዥ ሊበራል ፓርቲ መሪ ሆነው የተመረጡት ማርክ ካርኒ ተናግረዋል፡፡

ተመራጩ የካናዳ ጠቅላይ ሚኒስትር የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ "ያልተገባ ቀረጥ" ካናዳ ላይ በመጣል ኢኮኖሚዋን ለማዳከም እየጣሩ ነው ብለዋል።

🔄 ከዚህ ቀደም የካናዳ ባንክ ገዥ በመሆን ያገለገሉት ማርክ ካርኒ፤ ጀስቲን ትሩዶን ተክተው የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በትላንትናው እለት ተሾመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇪🇹 የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰባት ሚሊዮን ኩንታል ሲሚንቶ ለገበያ ማቅረቡን አስታወቀ

ፋብሪካው ወደ ስራ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን 7 ሚሊዮን ኩንታል ሲሚንቶ ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል፡፡የሲሚንቶ ፋብሪካው በአሁን ሰዓት በቀን 100 ሺህ ኩንታል ሲሚንቶ የሚያመርት ሲሆን በዚህም ከሀገሪቱ የሲሚንቶ ፍላጎት 33 በመቶ የሚሆነውን አቅርቦት እንደሚሸፍን የመንግሥት ሚዲያ ዘግቧል፡፡

ለሚ የሲሚንቶ ፋብሪካ ከአንድ ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል ፈጥሯልም ነው የተባለው፡፡

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇪🇹 አባ ገዳ ጉዩ ቦሩ 72ተኛው የቦረና አባ ገዳ ሆነው ተመረጡ

በትላንትናው እለት በተካሄደው የስልጣን ርክብብ ሥነ-ሥረዓት 72ኛ አባ ገዳ ሆነው የተመረጡት ጉዩ ቦሩ ስልጣናቸውን ተረክበዋል። አባ ገዳ ጉዮ ቦሩ በስልጣን ዘመናቸው የሕዝቦች አንድነት እንዲጠናከር እና ሰላም እንዲሰፍን አበክረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

አባ ገዳ ጉዩ ለሚቀጥሉት ስምንት ዓመታት የቦረና አባ ገዳ ስርዓትን እንደሚመሩ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇮🇱🇵🇸 የእስራኤል ኢነርጂ ሚኒስትር የጋዛ ሰርጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦት በአስቸኳይ እንዲቆም አዘዙ

"የጋዛ የኃይል አቅርቦት በአፋጣኝ እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ፈርሜያለሁ። ሁሉንም ታጋቾች ለማስፈታት እና ሃማስ ከጦርነቱ በኋላ በጋዛ አለመኖሩን ለማረጋገጥ በእጃችን ያሉ ሁሉኑም መሳሪዎች እንጠቀማለን" ሲሉ የኢነርጂ ሚኒስትሩ ኢላይ ኮህን ተናግረዋል።


ሰኞ እለት ለሃማሰ ማስጠንቀቂያ ያስተላለፉት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ፤ የፍልስጤም እስላማዊ ቡድን ታጋቾቹን የማይለቅ ከሆነ “በጭራሽ የማያስበው” መዘዝ ይጠብቀዋል ብለዋል። 

እስራኤል የፍልስጤም ታጣቂዎች የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማራዘም የቀረበውን ጥያቄ የማይቀበሉ ከሆነ ወደ ጋዛ በሚገባው ዕርዳታ ላይ እገዳ እንደምትጥል ባለፈው ሳምንት መጨረሻ አስታውቃለች።

የዕርዳታውን መቋረጥ የተቸው ሃማስ፤ እስራኤል “የጋራ ቅጣት የጦር ወንጀል ፈጽማለች” ሲል የወነጀለ ሲሆን፤ ድርጊቱ በጋዛ የሚገኙ እስራኤላውያን ታጋቾችንም ጭምር ይጎዳል ብሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇿🇦📡 ደቡብ አፍሪካ ኤለን መስክ ስታርሊንክ በሀገሪቱ የታገደበትን ምክንያት አስመልክቶ የሰጠውን አስተያየት ውድቅ አደረገች

ደቡብ አፍሪካ የተወለደው ኤለን መስክ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በኤክስ ገፁ ላይ ባጋራው ፅሐፍ “ስታርሊንክ በደቡብ አፍሪካ ውስጥ እንዲሠራ አልተፈቀደለትም። ምክንያቱም እኔ ጥቁር አይደለሁም” ብሏል።

"ይህ እውነት አይደለም፤ እውነት እንዳልሆነ አንተም ታውቃለህ። ከቆዳ ቀለም ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የለውም። የሀገሪቱን ሕጎች እስካከበረ ድረስ ስታርሊንክ ደቡብ አፍሪካ ውስጥ መሥራት ይችላል" ሲሉ የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ከፍተኛ ባለስልጣን ክላይሰን ሞንዬላ ምላሽ ሰጥተዋል።


የመስክ ትችት የውጭ የቴሌኮሙኒኬሽን ኦፕሬተሮች 30 በመቶ ድርሻቸው በታሪክ በተገለሉ ቡድኖች እንዲያዝ በሚያስገድደው የጥቁር ኢኮኖሚ ማብቃት ደንብ ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን አይቀርም ነው የተባለው። ስታርሊንክ ደንቡ እንደገና እንዲሻሻል ጥያቄ አቅርቦ እንደነበርም ተገልጿል።

በጉዳዩ ላይ አስተያየቱን የሰጠው የሀገሪቱ የቴሌኮም ባለስልጣን (አይካሳ) ስታርሊንክ የአገልግሎት ፈቃድ እንዳልጠየቀ አስታውቋል።

በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምስል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇺🇸🇸🇸 ዩናይትድ ስቴትስ በደቡብ ሱዳን እየተባባሰ የመጣውን የፀጥታ ሁኔታ ተከትሎ ከአስቸኳይ ጊዜ ሠራተኞች ውጪ ያሉ የመንግሥት ሠራተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አዘዘች

🗣 “በተለያዩ የፖለቲካ እና የጎሳ ቡድኖች መካከል የሚካሄደው ግጭት ቀጥሏል። ሕዝቡ በቀላሉ የጦር መሳሪያዎችን እያገኘ ነው። በተጨማሪም በመላ ሀገሪቱ የተንሰራፋው የከብት ዝርፊያ ወደ ግጭት ሲያምራ ይታያል" ሲል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ "እንደ የመኪና ዝርፊያ፣ ግድያ፣ የደፈጣ ጥቃት፣ አካላዊ ጥቃት፣ ዝርፊያ እና እገታን የመሳሰሉ ከባድ ወንጀሎች ጁባን ጨምሮ በደቡብ ሱዳን እየተስፋፋ ነው" ሲል የገለጸ ሲሆን፤ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞች በሚያጋጥማቸው ትንኮሳ እና ጥቃት ምክንያት ስራቸው "በጣም አደገኛ" ሆኗል ብሏል።

🇺🇳 ይህ በእንዲህ እንዳለ በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፤ መሪዎች በሀገሪቱ ሌላ አስከፊ ቀውስ እንዳይከሰት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና በግጭቱ አፈታት ዙርያ የፈረሙትን የሰላም ስምምነት እንዲያከብሩ ጠይቋል።

🗣 "ደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነቱን በመተግበር፣ ተቋማትን በማጠናከር እና የዴሞክራሲ መሠረት በመገንባት ወደፊት መጓዝ ይኖርባታል፡፡ አሁን በመታዘብ ላይ ያለነው ከዓመታት በፊት የነበረውንና ሀገሪቷን ለውድመት የዳረገውን ግድየለሽ የስልጣን ሽኩቻ ነው" ሲሉ የኮሚሽኑ ሊቀመንበር ያስሚን ሶካ በመግለጫቸው ተናግረዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇬🇧 ብሪታኒያ አሜሪካን ችላ በማለት ከዩክሬን ጋር መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችል የስለላ ጥምረት ልትፈጥር ነው ተባለ

ይህ ሀሳብ አሜሪካ ከኪዬቭ ጋር የምታደርገውን የመረጃ ልውውጥ ካቆመች እና ብሪታንያ እና ሌሎች አጋሮቿ መረጃዋን ወደ ዩክሬን እንዳያስተላልፉ መከልከሏን ተከትሎ የመጣ ነው።

ፋይፍ አይስ ኢንቴል አሊያንስ በሚባለው የመረጃ ጥምረት ሥር የሚቋቋመውና ፎር አይስ ተብሎ ይጠራል የተባለው ንዑስ ቡድን፤ ያለ ዩናይትድ ስቴትስ እገዳ መረጃ መለዋወጥ እንደሚያስችል የብሪቲሽ ጋዜጣ ዘገባ አስነብቧል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


📡 🇺🇸 አሜሪካዊው ቢሊየነር ኤለን መስክ ስታርሊንክን ብዘጋ የዩክሬን የጦር ግንባር ይፈራርሳል ሲል ተናገረ

በዩክሬን የማዕድን ሃብት ዙርያ ድርድር በተካሄደበት ወቅት፤ የአሜሪካ ተደራዳሪዎች ስታርሊንክ ለዩክሬን የሚያቀርበውን የሳተላይት አገልግሎት የማቋረጥ ሃሳብ ማቅረባቸውን የምዕራቡ ዓለም ሚዲያዎች ዘግበዋል። መስክ በበኩሉ ሪፖርቱን ውድቅ አድርጓል።

"የእኔ የስታርሊንክ ስርዓት የዩክሬን ጦር የጀርባ አጥንት ነው። ስርዓቱን ባጠፋ በአጠቃላይ የጦር ግንባራቸው  ይፈራርሳል" ሲል በኤክስ ገፁ የፃፈው ኤለን መስክ፤ ግጭቱ እንዲቆም ጥሪ አቅርቧል።


በእንግሊዘኛ ያንብቡ

መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇪🇹🌱 ኢትዮጵያ ለስድስት ወራት የሚቆይ ፀረ-ብክለት ዘመቻ መጀመሯን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ

ለስድስት ወራት በሚቆየው የፀረ-ብክለት ዘመቻ የአረንጓዴ አካባቢ ግንዛቤን በህብረተሰቡ ዘንድ ለማስረጽ አቅዶ እየሰራ መሆኑን ባለስልጣኑ አስታውቋል። ለሁለተኛ ገዜ የሚካሄደው ይህ ዘመቻ "ጽዳትና አረንጓዴን የኢትዮጵያ ባህል ማድረግ" በሚል መሪ ቃል በቅርቡ ይጀመራል ሲሉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሌሊሴ ነሜ ተናግረዋል።

የዘመቻው ዓላማ በአካባቢ ብክለት ዓይነቶች እና ቅድመ መከላከል እርምጃዎች ዙርያ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግና የማህበረሰቡን የተባበረ እርምጃ ወሳኝነት ማጉላት እንደሆነ የባለስልጣኑ ዳይሬክተር ጠቁመዋል።

♻️ ሌሊሴ አክለውም የፕላስቲክ ብክለት ሕጎችን በትክክል መተግበር፣ ደረቅ እና አደገኛ ቆሻሻዎችን በአግባቡ ማስወገድ እና ሁሉም ፕሮጀክቶቸ የአካባቢ እና የማህበራዊ ተፅእኖ ግምገማን እንዲያከብሩ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው፤ ይኽንን በሚጥሱት ላይ ሕጋዊ ቅጣት ይጣላል ብለዋል።

📄 የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን በዘመቻው ላይ በጋራ መሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ባሳለፍነው ሳምንት ተፈራርሟል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇬🇭 የጋና ፕሬዝዳንት በሳህል ሀገራት ጥምረት እና ኢኮዋስ መካከል መተማመን ለመፍጠር ቃል ገቡ

ፕሬዝዳንቱ ጆን ማሃማ በማሊ ባማኮ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በሁለቱ ቡድኖች መካከል “መተማመን እንደሌለ” ገልፀው፤ መተማመኑን ለመመለስ ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

የማሃማ የማሊ ጉብኝት በጋና እና ማሊ መካከል ያለውን ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት እንዲሁም የማሊ ዲያስፖራ ጋና ውስጥ የሚጫወተውን ሚና በማጠናከር ላይ ያተኮረ እንደነበር ታውቋል። በተጨማሪም የሁለቱን ሀገራት የጋራ ትብብር ኮሚሽን ማነቃቃትና ሽብርተኝነትን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ጨምሮ ቁልፍ የጸጥታ ችግሮችን ለወቅረፍ ያለመ ውይይት ተደርጓል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇸🇾 የሶሪያ የሰብዓዊ መብቶች ታዛቢ አዲሱ የሀገሪቱ መንግሥት 340 ሰዎችን ገድሏል ሲል ወነጀለ

መቀመጫውን ብሪታኒያ ያደረገው የሶሪያ የሰብዓዊ መብት ታዛቢ ድርጅት "መከላከያ ሚኒስቴሩ እና አጋር ኃይሎች በዘፈቀደ በፈጸሙት የጦር ወንጀል እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት 340 ሰዎች ተገድለዋል" ያለ ሲሆን፤ ከሟቾቹ መካከልም ሴቶች እና ህጻናት እንደሚገኙበት ጨምሮ ገልጿል።

💥 በላታኪያ እና ታርቱስ ግዛቶች የተቀሰቀሰው አለመረጋጋት ሐሙስ እለት የጀመረ ሲሆን፤ የአይን እማኞች የውጭ ሀገር ተዋጊዎች በአካባቢው ገብተዋል ሲሉ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

"ከየት እንደመጡ ባለውቅም፤ አረብኛ ግን አያወሩም። ያገኙት ላይ በመተኮስ፤ መሸሽ ያልቻሉትን ይዘዋል። ከቤታችን መውጣት ፈርተናል፤ ምግብ እና ውሃ እያለቀብን ነው” ሲል አንድ የአይን እማኝ ተናግሯል።

ሌሎች እማኞች በላታኪያ ጎዳናዎች ያልተቋረጠ የጥይት ተኩስ እና እስር እንደነበር ተናግረዋል።

"የታጠቁ ሚሊሻዎች ሱቆችን በመውረር ያገኙትን ይዘርፋሉ። ሃሜሚም በሚገኘው የላታኪያ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ብዙ ሰዎች እንደተሰበሰቡ በኢንተርኔት አይተናል፤ አሁን ግን መሄድ አደገኛ ነው፤ ምክንያቱም ልትታሰር ወይም ልትገደል ትችላለህ" ሲል ሌላኛው እማኝ ገልጿል።

የማህበራዊ ትሥሥር ገጽ ምስሎች ግጭቱን የሚሸሹ ሲቪሎች ላታኪያ ወደሚገኘው የሩሲያ ሃሜሚም አየር ማረፊያ ለመሸሸግ ሲሄዱ ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia


🇷🇸 የሰርቢያ ፓርላማ የብሪክስ ትብብር ቡድንን አቋቋመ

ቡድኑ በሰርቢያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ቩሊን እና በሶሻሊስቶች ንቅናቄ (ዲኤስ) ፓርቲ አነሳሽነት እንደተቋቋመ እና በምዝባ ሂደት ላይ እንደሆነ የዲያስፖራ እና ሰርቦች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ድራጋን ስታኖጄቪች ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

"የዲኤስ ምክትል ፕሬዝዳንት ቦጃን ቶርቢካ የቡድኑ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል። እኔ ምክትል ሆኛለሁ። ፓርቲያችን (የህዝብ ድምጽ) ይህንን ሙሉ በሙሉ ይደግፋል። ሂደቱ ከትናንት በስቲያ ለፓርላማ ቀርቧል” ሲሉ ስታኖጄቪች ተናግረዋል።

ሆኖም ገዥው የሰርቢያ ተራማጅ ፓርቲ ተነሳሽነቱን የተቃወመው ሲሆን 18 የሕግ አውጭዎች ግን ደግፈውታል ያሉት ባለስልጣኑ፤ ቡድኑን የተመለከቱ መረጃዎች በቅርቡ በፓርላማው ድረ-ገጽ ላይ እንደሚለጠፉ ገልጸዋል።

📄 የብሪክስ ትብብር ቡድን ቻርተር እንደተዘጋጀ እና ፍላጎት ያላቸው ሀሉም ተወካዮች ማግኘት እንደሚችሉ ተናግረዋል።

"ይህ ለወደፊት ጥሩ ውጤት የሚያመጣ አዎንታዊ ሁነት ነው ብዬ አምናለሁ" ሲሉ ስታኖጄቪች አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

📲 መተግበሪያውን አሁኑኑ ያውርዱ፦

👉  APK ፋይል ሊንክ 

ስፑትኒክ ኢትዮጵያን ይወዳጁ 👉 @sputnik_ethiopia

18 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.