ታጋይ አምሓራ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Inglizcha


ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም !
መረጃ፣ ጥቆማ፣ ሀሳብና አስተያየት ለማድረስ @TheGreatHQ ን ይጠቀሙ።

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Inglizcha
Statistika
Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
የቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል፣ የአሁኑ ፋኖ!

እውነት ነው፤ ልዩ ነበር የነበረን ልዩ ኃይል። ያ ስንት መስዋዕትነት የከፈለ ሰራዊት፣ ልፋቱና ድካሙ ተትቶ ምንም ዋጋ እንደሌለው ስብስብ እንዲፈርስ ነበር የተሴረበት። ቀድሞውኑ ህዝቡን ለመጠበቅ በብ/ጄነራል አሳምነው የተደራጀው የአማራ ልዩ ኃይል ግን ፋኖን ተቀላቅሎ አሁን ላይ በፋኖነት ህይወት እና በትግል ላይ ይገኛል።

በቀድሞው የአማራ ልዩ ኃይል ውስጥ የነበራችሁ፣ አሁን በፋኖ ውስጥ ያላችሁ ፋኖዎቻችን፣ አክብሮታችን ይድረሳችሁ!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!




የአማራ ፋኖ በጎጃም 4ተኛ(ጃዊ) ክፍለ ጦር ተወርዋሪ ኮማንዶዎችን አስመርቋል።

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!

03/06/2017 ዓ.ም


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ በደራ አዲስ ምልምል ኮማንዶዎችን አስመርቋል። ደራ፣ መተከል፣ ወልቃይት፣ ራያ፣ ፋኖ በልዩነት ሊሰራባቸው ይገባል።

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!

03/06/2017 ዓ.ም




የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር በዘራፊ ቡድኑ ላይ እርምጃ ወሰደ!

አገዛዙ የቡድን እና የነፍስ ወከፍ መሣሪያ አስታጥቆ በፋኖ ስም ያደራጀው ዘራፊ ኃይል በጀግኖቹ በቋራ ኦሜድላ ክፍለ ጦር እርምጃ ተወስዶበታል። በእርምጃው 12 የቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ 6 ያህሉ ተማርከዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ መጀመሪያውኑ ላደራጃቸው ለብልጽግና እጅ ሰጥተዋል።

በሁሉም ቀጠና ሕዝባችንን ያስመረሩ ዘራፊ መንጋዎች ላይ መሰል የሕግ ማስከበር እርምጃዎች ተጠናክረው ይቀጥሉ!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!

02/06/2017 ዓ.ም


በዛሬው የትግል ውሏችን፦

በቤተ አምሓራ (ወሎ)፡ ለገሂዳ ወረዳ ላይ የጠላት ኃይል ካምፕ አድርጎ በተቀመጠበት የለገሂዳ ወረዳ ምክር ቤት እንዲሁም አዲሱ ጤና ጣቢያ ወይም ማጀቴ በመባል በሚጠራው ቦታ ላይ በተወሰደ እርምጃ የአገዛዙ ኃይሎች ዶግ አመድ ሆነዋል።

በተጨማሪም ቀርጨም ላይ በተጣለ ደፈጣ በርከት ያሉ ባንዳ አድማ ብተናዎች ላይመለሱ እስከወዲያኛው ተሸኝተዋል።

በጎጃም፡ በቸርተከል ንዕስ ከተማ ላይ በተፈፀመ የተቀናጀ ኦፕሬሽን ቁጥራቸው ከፍ ያሉ የአገዛዙ ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት አባላት ተደምስሰዋል። በኦፕሬሽኑ መሳሪያዎች እና ተተኳሽ ገቢ ተደርገዋል።

በአጠቃላይ፡ የህልውና ተጋድሎው በሁሉም የአማራ ግዛቶች ተጠናክሮ ቀጥሏል። ጠላት በየቀጠናው ሲቀጠቀ ውሏል።

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!

01/06/2017 ዓ.ም


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በአማራ ፋኖ በጎጃም ስም በአገዛዙ ተዘጋጅቶ ስለተለቀቀው የሀሰት ሰነድ ከአማራ ፋኖ በጎጃም የተሰጠ ማብራሪያ

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


ፋኖነት የጀግንነት መንፈስን የሚያነሳሳ፣ የነፃነት ጥሪን የሚያስተጋባ ልዩ እሴት ነው! ፋኖ ለእኛ ለአማራዎች የኩራታችን ምንጭ ነው። አሁን ላይ ፋኖ ከ80 በላይ ግዙፍ ክፍለ ጦሮች ያሉት፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በጽናትና በጀግንነት የታነጸ ኃይል ነው። ይህ ቁጥር በራሱ የሚናገር ነው፤ ይሄ ሁሉ ክፍለ ጦር የተደራጀው በአመት ከምናምን ብቻ መሆኑ ደግሞ እጅግ አስደናቂ ያደርገዋል።

ይህ ሁሉ ኃይል በአንድ ዓመት ከምናምን ውስጥ መገንባቱ አስደናቂ ብቻ ሳይሆን ታሪካዊም ነው። ያለምንም ማጋነን እንዲህ አይነት ፈጣን እድገት፣ እንዲህ አይነት የህዝብ ድጋፍ በአማራ ፋኖ እንጂ በማንም "ታጋይ ነን" ባዮች ዘንድ አልታየም። ይህም ፋኖ ከህዝብ ለህዝብ እንደሆነ በግልጽ ያሳያል።

ይሁን እንጂ አንድ ነገር ልንዘነጋ አይገባም፤ ይህ ሁሉ ኃይል ገና በአንድ ላይ አልተባበረም። በአንድ ድርጅት በአንድ መዋቅር አልተሰባሰበም። አዎ፣ ፋኖ ሀገር መምራት የሚችሉ ብዙ መሪዎች፣ የውትድርና ጥበብ ባለቤት የሆኑ ብዙ ጀግኖች አሉት፣ ብዙ ክፍለ ጦሮች አሉት፤ ነገር ግን በአንድ ዓላማ አንድ ላይ መቆም አልተቻለም። አንድነታችን ሲጎድል ጥንካሬያችንም ይዳከማልና ከመቼውም ጊዜ በላይ አንድ መሆን ያስፈልገናል። እንደ አንድ አይደለም አንድ እንጂ!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


በሰሜናዊ ኬንያ፣ በመርሳቢት እና ኢሲዎላ አውራጃዎች ላይ የነበረ ሳዳም ቡኬ የተባለ የኦነግ ሸኔ አመራር፣ ኬንያ በአካባቢው በጀመረችው ዘመቻ በቁጥጥር ስር መዋሉን የኬንያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ለጠቅላላ እውቀት እንጂ እኛ ምንም አያገባንም!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


እስካሁን በፋኖ ከተደመሰሱ ኮለኔሎች መካከል፦

1ኛ. ኮለኔል ሸዋነህ ገበየሁ (የ59ኛው ክፍለጦር ዋና አዛዥ) - ሸበል በረንታ ቀጠና
2ኛ. ኮለኔል ሞሐመድ አሕመድ (59ኛ ክፍለጦር ምክትል አዛዥ) - ቋሪት
3ኛ. ኮለኔል ከተማ - እብናት

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
አዲሱ የአማራ ትውልድ!

አማራነቱን በኩራት የተቀበለ፣ ፋኖነትን በልቡ ያሰረፀ፣ በደም ስሩ ማንነቱን የሰበዘ የአማራ አዲስ ትውልድ መጥቷል! ድሉ የእኛ ነው!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
አርበኛ ሐብቴ ወልዴ በአንድ ወቅት ከተናገረው የተወሰደ፦ "አማራ ከሆነ አማራ ብቻ ሆኖ ይቁም!"

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


ኦነግና ወያኔ ታገልኩ ቢሉ የኦሮሚያ ሪፐብሊክን ለመመስረትና ታላቋን ትግራይ ለመገንባት ነው፤ ፋኖ ሲታገል ግን የህዝቡን ህልውና ለማረጋገጥ፣ ነጻነቱን ለማስከበር እንዲሁም የኢትዮጵያን አንድነት ለመጠበቅ ነው። ፋኖ ከሌሎች ለየት የሚያደርገው ለግል ዓላማ ሳይሆን ለህዝቡ አልፎም ለሀገር የሚታገል መሆኑ ነው።

አንዳንዴ ፋኖን ከእነዚህ የጥፋት ኃይሎች ጋር ሲያነጻጽሩ ስንመለከት በእጅጉ አለማወቃቸውን እናውቃለን። ፋኖማ ፋኖ ነው!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


ሰበር የድል ዜናዎች!

በየእለቱ የድል አድራጊነት ዜናዎች በጆሯችን ሲስተጋቡ ልባችን በደስታ ቢሞላም፣ እነዚህ ዜናዎች ከፕሮፓጋንዳዊ ይዘት ባለፈ፣ መሬት ላይ ተጨባጭ ለውጥ እያመጡ ይሆን? ዘላቂ ድልን ለማረጋገጥ እየሰራን ነው ወይስ ጊዜያዊ ስሜትን ለማርካት ብቻ? የአገዛዙ ኃይሎች በየገጠር ቀበሌው እየተሰማሩና በፋኖ ይዞታዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት እየሰነዘሩ ሲመከቱ፣ ያ እንዴት የድል ዜና ሊሆን ይችላል? ዜናውን በደስታ ከመቀበል ባለፈ፣ ለድሉ ዘላቂነትና ለህዝባችን ደህንነት መሠረት እየጣልን መሆኑን ማረጋገጥ አለብን። አንድነታችንን አጠንክረን፣ ጠላትን በተጨባጭ እያደከምን፣ ለወገናችን አስተማማኝ ምድር እየፈጠርን መሆኑን በፅናት እንፈትሽ!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


በትግራይ ደርቢው ደርቷል። እኛ በቤተሰብ መኻል አንገባም አዛው ተቦጣቦጡ። ጌቾ ግን 😁


12ኛውን ሰዓት እየጠበቅን ነው!

"አንድ አማራዊ ተቋም ልንመሰርት 11ኛው ሰዓት ላይ ደርሰናል። መተዳደሪያ ደንቦችን፤ አዋጆችን፤ አርማና ስም መርጠን ጨርሰናል። በቅርቡ በአጭር ቀናት አንድነቱን እናበስራለን!" ይህ የአርበኛ አስረስ ማረ ንግግር የፋኖ አንድነት ምን ያህል እንደተቃረበ የሚያሳይ ብስራት ነው። 11ኛው ሰዓት ለንጋት 12 ሰዓት መድረስ አግባቡን ጠብቆ እንዲሄድ እያመለከትን፣ 12ኛውን ሰዓት በተስፋ እየጠበቅን ነው!

ይህ 12ኛው ሰዓት ግን ከቃላትና ከምኞት የዘለለ ነገር የሚፈልግበት ሰዓት ነው። ለረጅም ጊዜ ስንጠብቀው የነበረው የአንድነት ብስራት እውን የሚሆነው በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ሲረጋገጥ ነው። ቃላት ኃይል አላቸው፣ ነገር ግን ተግባር ከቃላት እጅግ የላቀ ኃይል አለው።

አሁን ላይ፣ የፋኖ በአንድ ቤት ሥር መሰባሰብ ከምን ጊዜውም በላይ እጅግ ወሳኝና ግዴታም ጭምር ነው። ጊዜውም የዘገየ ቢሆንም፣ የአንድነቱ ብስራት እውን የሚሆነው ሁሉም ፋኖዎች ለአንድ ዓላማ ሲቆሙና ሲሰለፉ ብቻ ነውና ሁሉንም ያማከለ ድርጅት እንጠብቃለን። አሁን የምንጠብቀው አንድነት በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር የሚታይ አንድነት ነው።

ለዚህ ጉዳይ መሳካት ደከመኝ፣ ሰለቸኝ፣ ታከተኝ፣ አቃተኝ፣ ሳትሉ በብዙ ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታዎች ውስጥ ሁናችሁ እየሰራችሁ ላላችሁ ክብራችን ከፍ ያለ ነው።

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


እናንተ 'ከቃል እስከ ባህል' እያላችሁ በህዝቡ ላይ ስትቀልዱ፣ እኛ ደግሞ 'ከመቃብር እስከ ሲኦል' ግሪሳችሁን በተግባር እየላክን ነው!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!


የጦሩ አለቃ! ጄነራል!


ሰበር ዜና: ነበልባሎች በኤጀሬ!

የታላቁ አርበኛ ደራሲ አሰግድ መኮነን ልጆች በኦሮሚያ ምድር ገድል ሲፈጽሙ ውለዋል። ጦርነቱ ከክልሉ መውጣት መጀመሩ ይበል የሚያሰኝና ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ነው።

የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ አባላት በኦሮሚያ ክልል ኤጀሬ ከተማ ላይ የተሳካ ኦፕሬሽን ፈጽመዋል። አናብስቶቹ ከሞጆ ወደ ኤጀሬ የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት፣ በከተማዋ የነበረውን የአገዛዙን ካምፕ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር ድል አድርገዋል። በኦፕሬሽኑ በርካታ የጠላት ኃይሎች ላይመለሱ ተሸኝተዋል። በርካቶቹም ክራንች አንጋች ሊሆኑ ተገደዋል።

ይህን ተከትሎ ከሞጆ ወደ ኤጀሬ የሚደረግ ማንኛውም የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ መቋረጡ ተረጋግጧል።

ድል ለአማራ ፋኖ!
ድል ለአማራ ህዝብ!
ክብርና ሞገስ ለትግሉ ሰማእታት!

ታጋይ አምሓራ
ነፃነት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም!

22/05/2017 ዓ.ም

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.