ትምህርት በቤቴ®


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Inglizcha
Toifa: Ta’lim


A channel created for sharing
🔺study tips,
🔺short notes,
🔺tutorials,
🔺educational news,
🔺life tips and some motivational quotes ...

Buy ads: https://telega.io/c/temhert_bebete
📩 For comment- @Tmhert_bebete_info_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Inglizcha
Statistika
Postlar filtri


🚀  አስደሳች  ዜና ለሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ
ከኢን አፋሪካ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ

መገኛውን በፒያሳ ያደረገው ኢንአፍሪካ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ ከ እህት ኩባንያው ኢንአፍሪካ ቱጌዘር ጋር በመተባበር የተማሪዎች ምዝገባ እና የገለፃ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።🎉

📍ካሌብ ሆቴል
📅የካቲት 9 ከ  ⏰2:00እስከ 10:00

የሪሚዲያል ኮርሳችንን በመመዝገብ ውጭሀገር ሄደው ለመማር ሙሉ እገዛ ከኢንአፋሪካ ቱጌዘር ያግኙ ።
እንዲሁም የኢንግሊዘኛ ቋንቋ ስልጠና🇺🇸 ከአሜሪካ በመጡ መምህራን ያግኙ

📌በሌሎች ኮሌጆች ጋር የሪሚዲያል ኮርስ እየወሰዳችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ትልቅ ቅናሽ ያዘጋጀን ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ወደውጭ ሀገራት ወደሚገኙ ዮኒቨርሲቲዎች እንዴት አፕላይ ማድረግ እንደሚችሉ ስልጠና በነፃ ያገኛሉ።

🎁የተለያዮ አለም አቀፋ አጋሮች እና በሞያውየካበቱ መምህራኖች

ከ ሪሚዲያል በተጨማሪ

✅በ TVET
✅ዲግሪ እና ማስተርስ ፕሮግራም
✅ሲፒዲ ስልጠና

💰ጓደኞቾን በመጋበዝ የ 800 ብር ተሸላሚ ይሁኑ

✍አሁኑኑ ይመዝገቡ

https://forms.gle/R7oZQ9vxNMvaiogp9


#Exit_Exam_ውጤት_ተለቋል

ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት ተለቋል።

https//:result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት ExitExam የሚለውን በመምረጥና የራስዎን User Name በማስገባት ውጤትዎን መመልከት ይችላሉ።

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም መሠጠቱ ይታወቃል።


መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


Inafirca International College dan repost
🚀 Exciting News!
For Remedial Program Students
In Africa International College

Our college located in Piassa with a training center in CMC, has partnered with our sister company, In Africa Together, to organize a student registration & orientation event! 🎉

📍 Kaleb Hotel
📅 Feb 16 | ⏰ 2:00 - 10:00 PM

Join our Remedial Course & get FULL support for Study Abroad & an English course with American 🇺🇸 instructors!

📌For those who are learning remedial program at another college we have a big discount and also a free study abroad support program if they will transfer to our college.

🎁International Partners and professional teachers, join the event !

We also offer:
✅ TVET Programs
✅ Degree & Master’s Programs
✅ CPD Trainings

💰 Refer & Earn! Get 800 ETB per student you refer!

✍️ Register now:
https://forms.gle/R7oZQ9vxNMvaiogp9


የመውጫ ፈተና ውጤት ከሁለት ቀናት በኋላ ይፋ ይደረጋል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከጥር 26-30/2017 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በ87 የፈተና ማዕከላት መሰጠቱ ይታወቃል፡፡

ከፈተናው ጋር በተያያዘ በርካታ ቅሬታዎች ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ደርሰዋል፡፡ በተለይ የComprehensive Nursing ተፈታኝ ተማሪዎች፥ ፈተናው ከBlue Print ውጪ የተዘጋጀ እንደነበር በመግለፅ ትምህርት ሚኒስትር ለቅሬታቸው አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

የመውጫ ፈተና ውጤት ከሁለት ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚደረግ ከትምህርት ሚኒስቴር መስማቱን የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ገልጿል፡፡

ሚኒስቴሩ ከComprehensive Nursing የመውጫ ፈተና ጋር ተያይዞ የቀረበ ቅሬታን እያጣራ እንደሚገኝ ለህብረቱ አስረድቷል፡፡

በዚህም ከሁለት ቀናት በኋላ (ረቡዕ/ሐሙስ) አጠቃላይ የመውጫ ፈተና ውጤት ይፋ እንደሚደረግ ሚኒስቴሩ አሳውቋል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


ላለፉት አምስት ተከታታይ ቀናት በመላ ሀገሪቱ ሲሰጥ የቆየው 4ኛው የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ አመሻሹን ተጠናቋል፡፡

ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በ87 የፈተና ማዕከላት የተሰጠ ሲሆን፤ 176 ሺህ የሚሆኑ ተፈታኞች ለመውጫ ፈተናው ተቀምጠዋል።

ምስል፦ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


#MoE

አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም ጠዋት 5፡30 የሚጀመረው የመውጫ ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 የሚጀመረው ፈተና ወደ 10፡30 የተቀየረ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

የመፈተኛ ማዕከላት በነበሩበት የሚቀጥሉ መሆኑ ተገልጿል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


ለ4ኛ ጊዜ በመሰጠት ላይ የሚገኘው የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ አራተኛ ቀኑ ላይ ደርሷል፡፡

ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ በ87 የፈተና ማዕከላት እየተሰጠ ሲሆን፤ 176,045 ተፈታኞች ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ብቻ ከ18 ሺህ በላይ ተፈታኞች ፈተናውን እየወሰዱ እንደሚገኙ በዩኒቨርሲቲው የትምህርትና ምርምር ተቋም የፈተና ማዕከል ዳይሬክተር ብርሃኑ አበራ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡

ባለፉት ሦስት ቀናት በነበረው የፈተና አሰጣጥ፤ ተንቀሳቃሽ ስልክ ይዘው ወደ ፈተና ጣቢያ ለመገባት ከሞከሩ ጥቂት ተማሪዎች እና አልፎ አልፎ የመብራት መቆራራጥ ከማገጠሙ በስተቀር ሌላ በዩኒቨርሲቲው ያጋጠመ ችግር አለመኖሩን ኃላፊው ለትምህርት ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ዴስክ ተናግረዋል፡፡

የቅደመ-ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ነገ ጥር 30/2017 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


In Africa Together dan repost
🚀 IAT Student Event Alert! 🚀
🎤 Hosted by In Africa Together (IAT)

✅ Licensed in 🇺🇸 Michigan, USA & 🇪🇹 Addis Ababa, Ethiopia 

✨Exclusive Offer for High School Students!✨ 
🎉 Enjoy a 10% discount just bring your High School ID!

📅 Date: Sunday, February 9
📍 Venue: Kaleb Hotel (Next to Harmony Hotel) 
⏰ Time: 2:00 AM – 8:00 AM (Local Time) 
 
🎓 No Pre-Payment Required
📜 No English Proficiency Exam
✅ 100% Admission Guarantee

🇺🇸 USA – 66% Scholarship + 34% Covered by Student Loan
🇨🇳 China – Full Scholarship + Pocket Money Allowance

🎯 Apply for: 
- Bachelor’s Degree 
- Master’s Program 
- PhD Programs 

📦 Our Packages Improve Your Visa Chances!

🔗 Secure Your Spot – Register Now!👇🏾 
https://forms.gle/aWzxNFkQJS8ozaLU7


የጤና ተመራቂዎች የሙያ ብቃት ምዘና (COC) መቼ ይሰጣል?

ከትናንት ጥር 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ የጤና ተማሪዎችን ጨምሮ የቅድመ-ምረቃ ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና እየተሰጠ ይገኛል።

የሙያ ብቃት ምዘና (COC) ለመውሰድ እየጠበቁ የሚገኙ የጤና ተመራቂዎች (ምዘናውን በድጋሜ የሚወስዱትን ጨምሮ) ምዘናው መቼ እንደሚሰጥ ቲክቫህን ጠይቀዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ጤና ሚኒስቴርን የጠየቅን ሲሆን፤ በትምህርት ሚኒስቴር እየተሰጠ የሚገኘው የመውጫ ፈተና መጠናቀቅና ውጤት መገለፅን ተከትሎ COC የሚወስዱ አመልካቾች (ድጋሜ ተፈታኞችን ጨምሮ) ምዝገባ እንደሚደረግ ከሚኒስቴሩ አረጋግጠናል።

የCOC ምዘናውን በየካቲት ወር መጨረሻ ወይም በመጋቢት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ለመስጠት በጊዚያዊነት መታቀዱን ከሚኒስቴሩ ሰምተናል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


ዛሬ መሠጠት የተጀመረውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና #በጥብቅ የፈተና ዲሲፕሊን እንዲሰጥ እያደረጉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎች ገለፁ።

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተፈታኞች ወደፈተና ማዕከላት ይዘው እንዳይገቡ የተከለከሉ ነገሮችን ፍተሻ በማድረግ መያዙን ገልጿል።

በዚህም ዩኒቨርሲቲው ኩረጃ እና ስርቆት የሚያግዙ ክልክል የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይዘው የተገኙ ተማሪዎችን ወደ መፈተኛ ክፍሎች እንዳይገቡ አድርጓል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


#EXITEXAM #note

ትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከጥር 26 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ ይሰጣል።

⚡️በፈተና ወቅት ከተፈታኝ ተማሪዎች ምን ይጠበቃል ?


👉🏾 ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍል ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

👉🏾 ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው ይህም ማለት ከጥዋቱ 2፡00 በፊት ፤ ከሰዓት ደግሞ ከ8፡00 በፊት ተፈታኞች መገኘት አለባቸው።

👉🏾 ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

👉🏾 ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

👉🏾 ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

👉🏾 ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገር እና ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

👉🏾 ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

👉🏾 ተፈታኞች በምንም ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

👉🏾 ሁሉም ተፈታኞሽ ለፈታኝ መምህራንና ለአስተባባሪዎች  መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብ እና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 በድጋሚ ተፈታኞች የፈተና መግቢያ ትኬት (Exit Exam Entry Ticket) መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

NB.  ሁሉም ተፈታኞች ወደ መፈኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

⚡️ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ

👉🏾 የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

👉🏾 ፈታኝ መምራህን የተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

👉🏾 በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

👉🏾 የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

👉🏾 በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

👉🏾 ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

👉🏾 ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ሲኮርጂ ወይንም ሲያስኮርጅ የተገኘ ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

👉🏾 ፈተናው ከጀመረ 15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።

👉🏾 የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ

🌺 መልካም ፈተና 🌺

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ 176 ሺህ ተማሪዎች ተመዝግበዋል።

ፈተናውን በድጋሚ የሚወስዱትን ጨምሮ በጠቅላላው 176 ሺህ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

ፈተናው በኢትዮጵያ በሚገኙ በሁሉም የኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ሲሆን፤ ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ያልሆነው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥም እንደሚሰጥ በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለአሐዱ ራዲዮ ተናግረዋል።

የግል ኮሌጅ ተማሪዎችም በመረጡትና በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ፈተናቸውን ይወስዳሉ ብለዋል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


In Africa Together dan repost
🚀 IAT Student Event Alert! 🚀
🎤 Hosted by In Africa Together (IAT)

✅ Licensed in 🇺🇸 Michigan, USA & 🇪🇹 Addis Ababa, Ethiopia 

Exclusive Offer for High School Students!✨ 
🎉 Enjoy a 10% discount just bring your High School ID!

📅 Date: Sunday, February 9
📍 Venue: Kaleb Hotel (Next to Harmony Hotel) 
Time: 2:00 AM – 8:00 AM (Local Time) 
 
🎓 No Pre-Payment Required
📜 No English Proficiency Exam
✅ 100% Admission Guarantee


🇺🇸 USA – 66% Scholarship + 34% Covered by Student Loan
🇨🇳 China – Full Scholarship + Pocket Money Allowance

🎯 Apply for: 
- Bachelor’s Degree 
- Master’s Program 
- PhD Programs 

📦 Our Packages Improve Your Visa Chances!

🔗 Secure Your Spot – Register Now!👇🏾 
https://forms.gle/aWzxNFkQJS8ozaLU7




#ExitExam

176 ሺሕ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸው ተገለጸ

👉ፈተናው ከጥር 26 እስከ 30 ድረስ ይሰጣል

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ 176 ሺሕ ተማሪዎች መመዝገባቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ፈተናውን በድጋሚ የሚወስዱትን ጨምሮ በጠቅላላው 176 ሺሕ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጀና #ለአሐዱ ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የሚገኙ በሁሉም የኒቨርሲቲዎች ፈተናው የሚሰጥ ሲሆን፤ ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ያልሆነው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጭምር በዚህ ፕሮግራም ተካታች መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የግል ኮሌጆችን በሚመለከት አሐዱ ላቀረበላቸው ጥያቄ ትምህርት ሚኒስቴር የግል ኮሌጆች ላይ ገብቶ ለመፈተን የሚያስችል መዋቅር እንደሌለው በማንሳት፤ ነገር ግን ተማሪዎች በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመንግስት ተቋም በኩል መፈተን እንደሚችሉ ገልፀዋል።

የፈተና ቀኑ በተለያዩ ምክንያቶች ዘግይተው ትምህርት የጀመሩትን ዩኒቨርሲቲዎች ታሳቢ ያደረገና በቂ ዝግጅት ማድረጋቸው ከተረጋገጠ በኋላ መወሰኑን ተናግረዋል።

ፈተናውን ለመስጠት ታቅዶ የነበረው ጥር 14 እና 15 የነበረ ቢሆንም፤ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እኩል ትምህርት ባለመጀመራቸው ወደ ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም. እንዲሸጋገር መደረጉን ገልጸዋል፡፡

በዚህ የፈተና ፕሮግራም ተንቀሻቃሽ ስልክና የወረቀት ፅሁፍ ይዞ መገኘት ፈፅሞ #የተከለከለ መሆኑን የገለጹት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ "ተፈታኞች መታወቂያ መያዝና ከፈተና ፕሮግራሙ 30 ደቂቃ ቀድሞ ቦታው ላይ መድረስ ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል፡፡ የወጣው ፈተናም ከተማሩት በመሆኑ ሳይጨነቁ በተረጋጋ መንፈስ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የዘንድሮው የዩኒቨርስቲዎች የመውጫ ፈተና ከዚህ በፊት ይሰጥ እንደነበረው ሙሉ ለሙሉ በኦንላይን የሚካሄድ ሲሆን፤ ከጥር 26 እስከ 30 ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት አምስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

የተማሪዎች ፈተና እንደተጠናቀቀ ቅዳሜ ማለትም የካቲት 1 ቀን የመምህራንን ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ መምህራን ፈተና ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

[ዘገባው የአሃዱ ሬድዮ ጣቢያ ነው]

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


የሐኪሞች የስራ አጥነት ቁጥር እየጨመረ ከመምጣቱ በተጨማሪ በተለያዩ በሽታዎች ተይዘው የህይወት ዋጋ እየከፈሉ ነዉ ተባለ፡፡

በህክምና የተመረቁ ስራ አጥ የህክምና ባለሙያዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር አስታዉቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ሕክምና የሚያስፈልጋቸው ሐኪሞች ተገቢውን ሕክምና በፍጥነት ባለማግኘታቸው የሕይወት ዋጋ እየከፈሉ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

ማህበሩ ሀኪሞች ብዙ ጫናዎችን ተቋቁመው ስራ እየሰሩ ቢሆንም የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ሳይከፈላቸዉ የሚቆዩባቸዉ ክልሎች መኖራቸዉን አንስቷል፡፡

ክፍያ የሚጠይቁ ሐኪሞችም ለእስር የሚዳረጉበት ሁኔታዎች የታዩበት ዓመት ነበር ሲል ማህበሩ ገልጿል፡፡

እንደሕክምና ማህበር ከሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ጋር ምክክር ለማድረግ ቢሞከርም፤ አሁንም ከችግሩ ስፋት አንጻር ለብዙዎች ችግር ምላሽ መስጠት አልተቻለም ነዉ ያለዉ፡፡

ከዚህ ቀደም ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተግባር ይግዛዉ ፤ በአገራችን ያሉ የሀኪሞች ቁጥር ወደ 17ሺህ ነዉ ያሉን ሲሆን፤ ከዚህ መሃል ወደ 40 በመቶ የሚሆነዉ ወይም 1ሶስተኛዉ ብቻ የማህበሩ አባል መሆኑን አንስተዋል፡፡

የሙያ ማህበር መቅጠር አይችልም ፤ማድረግ የሚችለዉ ጉዳዩን ማሳወቅ ነዉ ያሉት ዶ/ር ተግባር፤ከጤና ሚኒስቴርም ሆነ ከክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በጉዳዩ ላይ መነጋገራቸዉን በወቅቱ አንስተዉ ነበር፡፡

ዘንድሮ 61ኛውን ዓመታዊ የሕክምና ጉባኤና ዓለም አቀፍ የጤና አዉደ ርእይ ከየካቲት 14 – 15/2017ዓ.ም ለማካሄድ ማቀዱንም ማህበሩ አስታዉቋል፡፡
በጉባዔዉ በሃገር ውስጥ እና በውጭ ሃገር የሚኖሩ የህክምና ባለሙያዎች ያላቸውን እውቀት፣ የምርምር ግኝቶችን እና የህክምና ልምዶችን በማቅረብ የዓመቱን መሪ ቃል መነሻ በማድረግ የፓናል ውይይቶች እንደሚካሄዱም ለማወቅ ችለናል፡፡

ማህበሩ ከተመሰረተበት 1940 ዓ.ም ጀምሮ በህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት፣  ደህንነት እና በአጠቃላይ በህክምናው ዘርፍ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡

#EthioFM

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete


ጥንቃቄ #CBE

አደገኛ መተግበሪያ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ መሆኑን ንግድ ባንክ አስታወቀ‼️

ከጫናችሁ ያለፈቃድ ገንዘብ ይቆረጥባችኃል!

ደንበኞች በዋትስ አፕ እና በቴልግራም የሚሠራጭ Pharma+/CBE Vacancy መተግበሪያን እንዳይጭኑ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሳስቧል።

ባንኩ ባስተላለፈው የማስጠንቀቂያ መልዕክት፤ ባደረገው ምርመራ መሠረት አደገኛ መተግበሪያ ማግኘቱን ገልጿል።

ይህ Pharma+/CBE Vacancy የተሰኘ አሳሳች መተግበሪያ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በሰፊው እየተሰራጨ እንደሆነ በመጥቀስ፤ ይህ መተግበሪያ በቴሌግራም እና ዋትስአፕ ወደ ደንበኞቹ እየደረሰ መሆኑን ጠቁሟል።

መተግበሪያው በስልክ ላይ ከተጫነ ያለ ፈቃድ ገንዘብ ማስተላለፍ እንደሚችልም አሳውቋል።

ባንኩ ከዚህ አይነት አደጋ ለመጠበቅ ከቴሌግራም ወይም ዋትስአፕ መተግበሪያዎችን አታውርዱ ብሏል። ደንበኞች መሰል ተግባራት ሲገጥሟቸው በ951 ነጻ የስልክ መስመር ደውለው እንዲያሳውቁ አሳስቧል።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የትምህርት በቤቴ ቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ!

https://t.me/temhert_bebete
https://t.me/temhert_bebete

17 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.