Postlar filtri


ነህምያ ስለ ሕዝቡ መከራና ስለ ኢየሩሳሌም ጥፋት በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ያዘነውም ለእግዚአብሔር ሕዝብ እጅግ ስለሚያዝን እና በጸሎት ሀይል እጅግ ስለሚያምን ነው።
ሀዘኑም ደግሞ አጭር አልነበርም ለአያሌ ቀናት ነበር።ከማዘን ይልቅ
በሰማይ አምላክ ፊት ጾምና ጸለየ ወደ እግዚአብሔርም ተመለሰ። ጾም እና ጸሎት በእግዚአብሔር ላይ የመታመን ምልክት እንደሆነም ገብቶታልና!
ዛሬ አንተም ምንም አይነት ነገር ቢገጥምህ በእግዚአብሔር ፊት ብትጾምና ብትጸልይ መፍትሄ ከእርሱ ይሆንልሀል!

ነህምያ 1:4፤ ይህንም ቃል በሰማሁ ጊዜ ተቀምጬ አለቀስሁ፥ አያሌ ቀንም አዝን ነበር፤ በሰማይም አምላክ ፊት እጾምና እጸልይ ነበር፥
#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እምነት በስጋት እያነከስክ የምትሄድበት ጉዞ ሳይሆን የምትፀልየው ፀሎት መመልስ መሰረት ነው፡ ያለ እምነት የሆነ ፀሎት ውጤት የለውም::
በጌታ ላይ ልብን በመጣልና በእርሱ በመታመን ልመናህ ሁሉ ያደረግልሀል::

ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። ማርቆስ 11፥24

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


ሳታቋርጥ ወደ እግዚአብሔር መፀለይ ከእርሱ ጋር ዘላቂ ግንኙነት እና ህብረት እንዲኖርህ ያደርጋል፤ ሳታቋርጥ መፀለይ የእርሱን ሀሳብ የህይወትህ መመሪያ አድርገን እንድትኖር ያቀልልሀል። በአስቸጋሪም ሆነ በማይመች ሁኔታ ውስጥ እንኳን፣ ምስጋና ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ግንኙነት ና ህብረት ይፈጥርልሀል:: በፈተናና በመከራ ውስጥም ቢሆን በእያንዳንዱ በምታልፍበት ቀን ሳታቋርጥ ወደ እግዚአብሔር በመቅረብ ከእግዚአብሔር ጋር ህብረትህን አጠንከር:: እያንዳንዱ ፈተና በፀሎት ወደ እርሱ የሚያቀርብህ ይሁን። በምታደርገው ነገር ሁሉ፣ በእያንዳንዱ እርምጃህ ሁሉ፣ እግዚአብሔርን በማመስገን እና በፀሎት ይሁን:: ይሄ ቀን ወደ እርሱ እንድትቀርብ ተሰጥቶሀልና::

1 ተሰሎንቄ 5:17-18፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው:: ጸሎትን እና ልመናን ለመስማት ቅርብ ነው:: እግዚአብሔር በእውነተኛ የልብ ጩኸት ብትጠራው ምላሽን ይሰጣል::
በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሆነህ የእግዚአብሔርን መገኘት መፈለግ ተግዳሮቶችን ቢያጋጥሙህም እንድትበረታ ያደርግሀል:: ወደዚህ ጌታ መቅረብ ትፈልጋለህ? እርሱ ጭንቀትህ፣ ፀሎትህን ለመስማት: ሁልግዜም ቅርብ ነው ::
መዝሙር 145:18፤ እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፥ በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


አንዳንድ ፀሎቶችህ ምላሽ የማያገኙት እግዚአብሔርን የምትፈልገው ሀሳብህን እንዲፈፅምልህ እንጂ ፈቃዱን ለማድረግ በተዘጋጀ ልብና መንፈስ ስላልሆነ ነው!!! ፍላጎቶችህ ላይ ብቻ እግዚአብሔር እንዲናገርህ ሳይሆን የእርሱ ፈቃድ ህይወትህ ላይ ምን እንደሆነ ለማወቅ እና እንደፈቃዱ ለመለመን ወደ እግዚአብሔር ፊት መቅረብ ፀሎቶችህ ምላሽ ይኖራቸዋል። መልስ ማለት የምንትፈልገውን ብቻ መስማት አይደለም!

በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል።1 ዮሐንስ 5 ፡14


#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


ኢየሱስ በድካምህ የሚራራልህ ታላቅ ሊቀ ካህን ነው። በክርስቶስ ኢየሱስ ስራ በማመን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ምህረትን ከእርሱ ዘንድ እንድትቀበል ይረዳሀል። በዚህ የጾም እና የጸሎት ጊዜህ በሚያስፈልግህ ሁሉ ወደ ሚረዳህ አምላክ ልትቀርብ ትወዳለህ?

ዕብራውያን 4:16፤ እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እውነተኛ ጸሎት የግል ማጽናኛን ወይም ለራስ ጉዳይ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ብቻ አይደለም። ይልቁንም የተጨቆኑትን ነጻ ማውጣትን፣ እንጀራህን ለተራቡት ማካፈል እና የተቸገሩትን ማቀፍ እንደሆነም የእግዚአብሔር ቃል ይነግረናል።

እግዚአብሔር አምላክህን ደስ ማሰኘት ከፈለግህ ፀሎትህን ለራስህ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም በመማለድ እንዲሁም በመልካም አካሄድህ ቃኘው።

ኢሳይያስ 58:6፤ እኔስ የመረጥሁት ጾም ይህ አይደለምን? የበደልን እስራት ትፈቱ ዘንድ፥ የቀንበርንስ ጠፍር ትለቅቁ ዘንድ፥ የተገፉትንስ አርነት ትሰድዱ ዘንድ፥ ቀንበሩንስ ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን?

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


የህይወትህን መርህ ለማግኘት፣ በእርሱ ፈቃድ ለመመራት በእግዚአብሔር ፊት ተግቶ መቆየት፣ መፀለይ እና መጾም ዋነኛው ነገር ነው። በአንጾኪያ ያሉ መሪዎች በአምልኮ፣ በጸሎት እና በጾም በእግዚአብሔር ፊት ይቆዮ ነበር። እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ እና ሲጾሙም ነበር ። በዚህም የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማግኘት ችለዋል።

ዛሬ አንተም እግዚአብሔርን በመፈለግ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ በህይወትህ ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ ኖሮትህይወትህን እንዲመራው ትፈቅዳለህ?

ሐዋ. ሥራ 13:2፤ እነዚህም ጌታን ሲያመልኩና ሲጦሙ መንፈስ ቅዱስ፦ “በርናባስንና ሳውልን ለጠራኋቸው ሥራ ለዩልኝ፡” አለ።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እንደ ፈሪሳውያን ያሉ የሃይማኖት መሪዎች ሆን ብለው በጾም ወቅት ደካማ፣ የተጎዱ እና ጾመኝነታቸው በሰው ሁሉ ፊት እንዲታወቅላቸው ይጥራሉ: አንዳንዶች ደግሞ የአምላክንም ትኩረት ለመሳብ በሚመስል መልኩ ራሳቸውን ያገረጣሉ፤ እኝህ ሰዎች ዋና አላማቸው እውነተኛውን ጾም በእግዚአብሔር ፊት ከመጾም ይልቅ በሰው ዘንድ ታይታ መፈለግ ነው። ይህ አይነት ጾም ከእግዚአብሔር ዘንድ ምንም ዓይነት ሰማያዊ ሽልማትን አያስገኝም።
ዛሬ በጾም ላይ ላለኽው ወንድሜ ይሄን እውነት እነግርሀለሁ፤ ጾምህን በትሕትና እና በቅንነት እንደ እግዚአብሔር ቃል ማከናውን እና እውነተኛው ጾም በአንተ እና በእግዚአብሔር መካከል ብቻ መሆኑን በመረዳት የሚደረግ ስርዓት እንጂ ለሌሎች ታይታ አይደለም። አንተ ከእግዚአብሔር ጋር በድብቅ የምታደርገውን የሚያይና ዋጋ የሚሰጥ አምላክ ነው።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እግዚአብሔር ርሁሩህ እና መልካም አምላክ ስለሆነ ህዝቡ ከጥፋት እንዲመስ ወደ እውነተኛ ንስሐ ይጠራል። ንስሐ ደግሞ በሚታይ ድርጊቶች ላይ ብቻ ሳይሆን በቅንነት፣ በጾም፣ በልቅሶ፣ ራስን በቅዱሱ እግዚአብሔር ፊት በማዋረድ ለኃጢአት ጥልቅ ንስሀ በመግባት እና ከኃጢአት በእግዚአብሔር ፀጋ ለመራቅ ፈቃደኛ መሆን ነው።
በዚህ በጾም ወቅት እግዚአብሔር ዛሬ አንተንም እየጠራህ ነው ። በፍጹም ልብህ ወደ እርሱ እድትመለስ፣ ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን ወደ ጎን በመተው በጸሎት እራስህን ዝቅ በማድረግ እና በቅንነት ፈልገው። እግዚአብሔር ለሚመለስ እና በምህርቱ በሚታመን ሰው ይደሰታል።
ኢዮኤል 2:12፤ አሁንስ፥ ይላል እግዚአብሔር፦ በፍጹም ልባችሁ፥ በጾምም፥ በልቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ።


#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


የሁሉ ፈጣሪ በሆነው በእግዚአብሔር ፊት መጾም ማለት:- ለሰውነትንህና ስሜትህ ድሎት እና ምቾት ከሆኑ ነገሮች ለጊዜው በመራቅ እና ስጋን በማድከም በፊቱ የፈለከውን ልመናህን በትህትና ወደ እግዚአብሔር ይዞ መቅረብ ማለት ነው።
ዕዝራና ሕዝቡ ወደ እግዚአብሔር አጥብቀው ጸለዩ፣ ጾሙ፣ ከምግብ ተከለከሉ። ይህንንም ሲያደርጉ በትሕትና በጸሎት ነበር። እርሱም ተለመናቸው፤ ጸሎታቸውንም ሰምቶ መለሰላቸው። ጾም በትህትና እና በጸሎት ሲሆን እግዚአብሔር የሚሰማ እና የሚመልስ አምላክ ነው። በራስ አቅም፣ በራስ ጾም እና በራስ ጸሎት ከመታመን ይልቅ በእግዚአብሔር መታመን ልመናህን እንዲሰማህ እና እንዲመልስልህ ያደርገዋል።
እግዚአብሔር በቅንነት ለሚሹት የሚገኝ እና የሚመልስ ፃድቅ አምላክ ነውና።
ዕዝራ 8:23፤ ስለዚህም ነገር ጾምን፥ ወደ እግዚአብሔርም ለመንን፤ እርሱም ተለመነን።


#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እንደ ቃሉ በእግዚአብሔር መንገድ ለሚሄዱ ለእነርሱም ሆነ ለዘሮቻቸው የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ የሚያሟላላቸው እግዚአብሔር ብቻ ነው። እግዚአብሔር ሁልጊዜ በእርሱ ለሚታመኑት ታማኝ ነው፣ እና ይህን ዛሬ አንተም ብታምን በህይወትህ ውስጥ የሚሰራ እውነት ነው። በህይወት ምልልስህ እየታገልክ እንደሆነ ከተሰማህ ወይም የወደፊት ህይወትህን እርግጠኛ መሆን ከከበደህ ፣ እግዚአብሔር ያያል አይጥልህም እግዚአብሔር፣ ይደግፋል አይተውም። እርሱ እስከ እርጅና ድረስ ታማኝነቱን እየገለጠ የሚያኖ አምላክ ነው።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እግዚአብሔርን መፍራት ማለት ለህጉ መገዛት፣ በቅድስና መኖር ማለት ነው:: በእግዚአብሔር ምህረት መታመን ማለት በየትኛውም አይነት በደል እና ሀጢአት ውስጥ ብትሆን ከዛ ሊያወጣህ እንደሚችል፣ ምህረት እንደሚያደርግልህ ማመን ማለት ነው:: በምሕረቱ እና በጸጋው ብትታመን እርሱ ይቅር ሊልህ፣ ምህረትን ሊያደርግልህ ይወዳል:: እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በፅድቅ፣ በቅድስና በማያልቀው ምህረቱ በመታመን ለመኖር ትፈልጋለህ?

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የእርሱ አቅርቦት፣ ጥበቃ፣ ምሕረት፣ የማይጠፋ ፍቅሩ፣ ጸጋው ሁልጊዜ ከአንተ ጋር እንዲሆን ትፈልጋልህ? የአሁኑን እና ዘላለማዊ ህይወትህን ተስፋን ሁሉ የሚቀይረውን የእግዚአብሔርን ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስን የህይወትህ ጌታ እና አዳኝ አድርገህ ልትከት ይገባሀል።
ይሄን ውሳኔ ዛሬ ብትወስን በእግዚአብሔር ቤት ለዘላለም ትኖራለህ!

መዝሙር 23:6፤ ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።


#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


እግዚአብሔር በሀዘንህ ጊዜ መፅናናትን የሚሰጥ፣ በፍርሃት ጊዜ መረጋጋትን የሚሰጥ፣ በሰጋህባቸው ሁኔታዎችህ ሁሉ ምህረቱ እንዴት እንደሚረዳህ ነግሮሀል። መከራ ምንም ከባድ ቢመስል በመከራህውስጥ ያለው መፅናናት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ እንደሆነ ልታውቅ እና በምህረቱ ልትታመን ይገባል። ወደዚህ ጌታ ብትቀርብ መከራ ከሆኑብህ ነገሮች ሁሉ ሊያድንህ: ሊረዳህ: ሊያፅናናህ ይችላል::

መዝሙር 94:19፤ አቤቱ፥ ለልቤ እንደ መከራዋ ብዛት፡ ማጽናናትህ ነፍሴን ደስ አሰኛት።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


ሰው ተስፋ ካለው የማይታየውን እንዳየ ሆኖ ይረዳል፡፡ እምነት ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር የምንገልጥበት፣ እርሱን ደስ የምናሰኝበት ጥበብ ነው፡፡ ስለዚህ በተስፋ: በእምነት እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ህይወት መኖር ትፈልጋለህ ልንረዳህ ዝግጁ ነን !
#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


በእግዚአብሔር መታመን ማለት በኃይሉ፣ በቸርነቱ እና በሉዓላዊነቱ ማመን ማለት ነው። በራስህ ጥንካሬ ወይም ባለህ ነገር ከመታመን ይልቅ በእርሱ ብትታመን የሚያስጥል፣ የሚታደግ አባት ነው። እግዚአብሔርን በእውነት ለማውቅ ብትወድ፣ እርሱን ብትፈልግ፣ ከክፉ ሁሉ ይጋርድሀል። በእውነት ለሚወዱት፣ ለሚታመኑት እና ለሚሹት ታማኝ ወደሆነው አምላክ ልትመጣ ትወዳለህ? ልንረዳህ ዝግጁ ነን !
#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads  |  Pinterest


የሌባው አላማ ማታለል እና ሰዎችን ወደ ጥፋት መምራት ነው።
ኢየሱስ ግን የመጣው እውነተኛ፣ የዘላለም ሕይወት ለመስጠት እና ርቀህ የነበርከውን አንተን ከእግዚአብሔር ጋር ለማስታረቅ ነው። በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ሌባው ሊሰርቀው የማይችለው የዘላለም ሕይወት፣ የተትረፈረፈ ሰላም ቀርቦልሀል።
ይህንንም ሕይወት ለመኖር ዛሬ ብትወስን ከክርስቶስ ጋር ባለው ግንኙነት እስከ ዘለአለም ድረስ የእረፍት ህይወትን ትኖራልህ።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads | Pinterest


መዳን እና መጠራትህ እንዲሁም ከክርስቶስ ኢየሱስ ጋር ያለህ ግንኙነት በእግዚአብሔር ታማኝነት ላይ የተመሰረተ እንጂ በሰው ጥረት አይደለም። እግዚአብሔር በጸጋው ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ህብረት እንድታደርግ ጠርቶሀል።

1 ቆሮንቶስ 1:9፤ ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው።

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads | Pinterest


እግዚአብሔር ብርሃኑና ማዳኑ ለሆነ ሰው ማንም ሆነ ምንም አያስፈራውም። እግዚአብሔር የሕይወቱ መጠጊያ እና መሸሸጊያ ያደረገ ሰው ያለስጋት ነፍሱ ታርፋለች። እግዚአብሔር ጠባቂ ከክፉም መሸሸጊያ ነውና። ወደ እርሱ ብትመጣ ከጠላትን፣ ከፍርሀት ታርፋለህ።

እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር የሕይወቴ መታመኛዋ ነው፤ የሚያስደነግጠኝ ማን ነው?
መዝሙር 27:1፤

#tesfa #hope

Follow Tesfa on:
Instagram | Facebook | Telegram | TikTok | Youtube | Threads | Pinterest

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.