TIKVAH-ETHIOPIA


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ERMP 2024 List of Matched Candidates (1).pdf
947.6Kb
ERMP 2024 Max_Min Matching Results (1).pdf
486.1Kb
#MoH
#ERMP_2024_Matching

የጤና ሚኒስቴር የ2024 የብሔራዊ የህክምና ስፔሻሊቲ ስልጠና (ERMP) አመልካቾች ምደባ (Matching) ለቋል።

በምደባው ላይ ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በሚኒስቴሩ ነጻ የስልክ መስመር 952 በሥራ ሰዓት ብቻ እስከ የካቲት 21/2017 ዓ.ም ማቅረብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

" የተቋም/የፕሮግራም/የስፖንሰር ለውጥ አድርጉልኝ ጥያቄ እንደ ቅሬታዎች የማይወሰዱ በመሆናቸው ተቀባይነት የላቸውም " ብሏል።

Via @tikvahuniversity


#Update

በእግር ኳስ ተጫዋቹ አለልኝ አዘነ ግድያ የተከሱት ሚስቱና የእህቷ ባል የመከላከያ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ ፍርድ ቤቱ ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ሰጠ።

ባሳለፍነዉ ዓመት መጋቢት 17/2016 ዓ/ም የቀድሞ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንና የባህርዳር ከተማ ተጫዋች የነበረዉ አለልኝ አዘነ በአርባምንጭ ከተማ በድንገት ሕይወቱ ማለፉ በርካቶችን ያሳዘነ እንደነበር አይዘነጋም።

በተጫዋቹ አሟሟትና ሌሎች ሁኔታዎችን መነሻ አድርጎ ፖሊስ ሚስቱንና የእህቷን ባል በቁጥጥር ስር አዉሎ ክስ መመስረቱ የሚዘነጋ አይደለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ቀደምሲ ል በጉዳዩ ዙሪያ የተለያዩ መረጃዎችን ሲሰራ የቆየ ሲሆን ሰሞኑን ከጋሞ ዞን ፍትሕ መምሪያ ባገኘዉ መረጃ እስካሁን በነበረዉ ሂደት ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ክሱን ያስረዱልኛል ያላቸዉን የሰዉ፣ የሰነድና የምርመራ ማስረጃዎችን በማቅረብ ለፍርድ ቤቱ ክሱን አስረድቷል።

ጉዳዩን የያዘዉ የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ተከሳሾች የመከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርቡ ለየካቲት 10/2017ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ቢሆንም ተከሳሾች አሟልተዉ ማቅረብ ባለመቻላቸዉ ተለዋጭ የጊዜ ቀጠሮ ለመጋቢት 10/2017 ዓ/ም መሰጠቱን የጋሞ ዞን ፍትህ አካላት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

አርባ ምንጭ ከተማ በተለምዶ ልማት ሰፈር ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ ተወልዶ ያደገው አለልኝ አዘነ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ተስፋ ከተጣለባቸውና በኢትዮጵያ ፕሪሚዬር ሊግ በተለያዩ ቡድኖች ዉጤታማ እንቅስቃሴ የነበረዉ አማካይ ተከላካይ ነበር።

ተጫዋቹ ሕይወቱ እስካለፈበት ቀን ድረስ የባሕር ዳር ከተማ ቋሚ ተሰላፊ ተጫዋች የነበረ ሲሆን ከዚያ አስቀድሞ በሐዋሳ ከተማ እና በመቐለ 70 እንደርታ ዉጤታማ ጊዜ አሳልፏል።

ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል።

@tikvahethiopia


" የህግ ተጠያቂነት እስኪረጋገጥ ድረስ በአስቸኳይ ከአከባቢያችን ይልቀቁ " - ነዋሪዎች

" ተጠቅተናል " የትግራይ የሳምረ ሰሓርቲ ወረዳ 400 የህዝብ ተወካዮች ዛሬ የካቲት 14/2017 ዓ.ም ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት እና ምክትል ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ እና ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ በመቐለ ከተማ መክረዋል።

ተወካዮቹ የህግ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ እና ጥቃት አደረሰብን ያሉት የትግራይ ኃይል ክፍል ከአከባቢያቸው እንዲለቅ ጠይቀዋል።

በአካባቢው ያሉት ኃይሎች ህዝብን ከማስፈራት አልፈው ህዝብ ላይ መተኮሳቸው እጅግ እንዳሳዘናቸው በመግለፅ " የህግ ተጠያቂነት እስኪረጋገጥ ድረስ በአስቸካይ ከአከባቢያችን ይልቀቅልን " ሲሉ ጥሪ አቀረቡ።

ተወካዮቹ " ማህተም አስረክቡን " በሚሉ በአከባቢያቸው በሚገኙ የፀጥታ አካላት ግጭት መቀስቀሱ ጠቅሰው ራሳቸው በመረጡት እንጂ ሌላ በመረጠላቸው ሃይል ሆነ አካል መመራት እንደማይፈልጉ በምሬት ተናግረዋል። 

ስለሆነም ለደረሰባቸው ጉዳት ጊዚያዊ አስተዳደሩ አስቸኳይ ፍትህ እንዲሰጣቸው እና ጥቃት አድራሾቹ አከባቢያቸውን ለቀው እንዲወጡ ጠይቀዋል።

" በሰራዊት ስም ሽፋን የተወሰነ አካል ፍላጎት ለማሳካት በህዝብ ላይ እርምጃ የወሰዱት አካላት ስርዓት ባለው መንገድ ተጣርቶ የህግ ተጠያቂነት ይረጋገጣል " በማለት መልስ የሰጡት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ " ሰራዊቱ ከገለልተኝነት በወጣ መንገድ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ተቀባይነት የለውም " ሲሉ ተናግረዋል።

" ድርጊቱ ህዝብ እና ሰራዊት ለመከፋፈል ያለመ ነው ስለሆነም መቆም አለበት በድርጊቱ የተሳተፉ አካላት ሁሉ እንዲጠየቁ  ይሰራል " በማለት አክለዋል።

" ጥፋት ያደረሰ ማንኛውም አካል ከተጠያቂነት አያምልጥም " ሲሉ ምላሽ የሰጡት ምክትል ፕሬዜዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ " ጉዳዩ በአስቸኳይ ተጣርቶ በቅርብ ቀን ይፋ ይሆናል " ሲሉ ቃል ገብተዋል።

የካቲት 13/2017 ዓ.ም በሰሓርቲ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ገበሬ ማህበር እና በህዝብ እና በአከባቢው በሚገኙ የትግራይ ኃይል ታጣቂዎች መካከል ግጭት ተቀስቅሶ፤ በ20 ሲቪሎችና ቁጥራቸው በውል ባልታወቁ ታጣቂዎች ላይ ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሷል።

@tikvahethiopia


🎉⚡️ ቴሌ EV - Charging
እጅግ ፈጣን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ባትሪ መሙያ ጣቢያ!!


🚗 በሰከንድ 1 ኪሎ ሜትር ለመጓዝ የሚያስችል
🔌 በአንድ ጊዜ እስከ 32 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ቻርጅ የሚያደርግ
🤖 በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ የደንበኛን ትዕዛዝ የሚቀበል 
⏰ 24/7 አገልግሎት መስጠት ይችላል

👉 አገልግሎቱን ቴሌብር ሱፐርአፕ ላይ በሚገኝ መተግበሪያ ‘’ቴሌ EV – Charging’’ ጠይቀው ክፍያዎን በቴሌብር በመፈጸም በቀላሉ መስተናገድ ይችላሉ፡፡

🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ይጫኑ!

📍በአዲስ አበባ ከመገናኛ ወደ ቦሌ በሚወስደው አውራ ጎዳና ላይ ያገኙታል!

#teleEvCharging
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSuperApp #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia


ሕብረት ባንክ እንኳን ለ1446 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ በሰላም አደረሳችሁ እያለ፤ የሐጅ ጉዞ ክፍያዎን በአቅራቢያዎ በሚገኙ ቅርንጫፎቻችን በልዩ መስተንግዶ እንዲፈጽሙ በአክብሮት ይጋብዛል፡፡

በዚህ አጋጣሚ የሸሪዓውን መርህ መሰረት ያደረገ  ሕብር ሀቅ የተሰኘ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎታችን ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡

ሐጀን መብሩር!

ሕብር ሀቅ
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞  ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች  እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.me/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡


" ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን ይቀጥላል " -   የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

በኢትዮጵያ የተመረተ አዲስ ፓስፖርት ዛሬ ይፋ ሆኗል።

ፓስፖርቱ የግለሰቡን ባዮግራፊክ መረጃ ብቻ ሳይሆን የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል።

በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረተው ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተጠቅሷል።

ይህም ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገር አምራች ድርጅት እጅ የነበረውን ዲዛይን ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት እንዲሸፈን አድርጓል ተብሏል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በአዲስ የዘርጋው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ. አማካይነት የተሰራ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፤ ነበሩ ፓስፖርት የአገልግሎት ጊዜው እስኪያበቃ ጥቅም ላይ መዋሉን የሚቀጥል ሲሆን የዕድሳት ጊዜው ሲደርስ በኢ-ፓስፖርት ይተካል ተብሏል።

አገልግሎት መ/ቤቱ ፤ " 14 አዳዲስ ቅርንጫፎችን በመክፈትም አገልግሎቱን ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቋል " ያለ ሲሆን " ከአንድ ነጥብ 5 ሚልየን በላይ ኢ-ፓስፖርት ታትሞ ተዘጋጅቷል " ሲል ገልጿል።

አዲሱ የኢ-ፓስፖርት በነበረው ዋጋ ለተጠቃሚዎች ተደራሽ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን  ደንበኞች ባሉበት ፓስፖርታቸውን በፍጥነት ማግኘት እንዲችሉ ያደርጋል ተብሏል።

"  አዲሱን ኢ-ፓስፖርት በሁለት ወር ከ10 ቀን ማግኘት ይቻላል " ሲል አገልግሎቱ አሳውቋል።

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊ ዳዊት ፥ " አዲሱ ኢ-ፓስፖርት እስከአሁን ኢትዮጵያ ካላት ፓስፖርት በአይነቱና በደረጃው እጅግ ከፍ ባለ ጥረት የተዘጋጀ የጉዞ ሰነድ ነው " ብለዋል።


#EPA

@tikvahethiopia

205.7k 1 1.2k 2.1k

የቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች ሹመት ተሰጣቸው።

የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ኅብረተሰቡ ለተቀላቀሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ኃላፊነት ተሰጥቷል።

በዚህም መሠረት ፡-

1. አቶ ያደሳ ነጋሣ - በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የደኅንነት አማካሪ፣

2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ ተሰማ - የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ምክትል ኃላፊ፣

3. አቶ ቶሌራ ረጋሣ - የኦሮሚያ አስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

@tikvahethiopia


#NationalExam

" ፈተናው ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሁሉም ተማሪዎች በተማሩበት ሥርዓተ ትምህርት ይዘት እየተዘጋጀ እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ ፤ " የ2017 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ከ9ኛ - 10ኛ በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣ ከ11ኛ - 12ኛ ደግሞ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ብሏል።

" ነገር ግን በ2015 ዓ.ም በመላ ሀገሪቱ በናሙናነት በተመረጡ ት/ቤቶች የስርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራ ላይ የተሳተፉ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች 10ኛ ከፍልን በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ናቸው " ሲል ገልጿል።

በአማራ ክልል በ2016 የትምህርት ዘመን መፈተን ሲገባቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ሳይፈተኑ የቀሩና የ11ኛ ክፍልን በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት የተማሩ ት/ቤቶች ላይ የነበሩ ተማሪዎች በ2017 ዓ.ም የሚፈተኑ እንዳሉም ጠቁሟል።

በዚህም " የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ከላይ የተገለጹትን ሶስቱንም ነባራዊ ሁኔታዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ እና ሁሉንም የዘመኑን ተፈታኝ ተማሪዎች በማከለ መንገድ ስታንዳርዱን ፣ ደህንነቱንና ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ በመዘጋጀት ላይ ይገኛል " ሲል አሳውቋል።

የፈተና ዝግጅቱ፡-

1) ከ9ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከነባሩ ሥርዓተ ትምህርት፣

2) ከ10ኛ ክፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣

3) ከ11ኛ ከፍል በነባሩና በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ላይ ተመሳሳይ ይዘቶች፣

4) ከ12ኛ ከፍል ሙሉ በሙሉ ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት የሚዘጋጅ እንደሆነ ተገልጿል።

ከላይ የተዘረዘረው የዝግጅት ሂደት በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ላይ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚክስ የትምህርት ዓይነት ግን በስርዓተ ትምህርቱ አዲስ የተጀመረ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በ12ኛ ክፍል ይዘት ላይ ብቻ ተመስርቶ የሚዘጋጅ እንደሆነ ተመላክቷል።

በአጠቃላይ ሁሉም ተማሪዎች ከ9ኛ -12ኛ ክፍል በየተማሩበት የሥርዓተ ትምህርት ይዘት ላይ መመስረት ፈተናው እንደሚዘጋጅ አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አገልግሎት መ/ቤቱ አሳስቧል።

ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ወላጆች፣ መምህራንና መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ተላልፏል።

የዘንድሮ ሀገር አቀፉ የ12ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና መቼ እንደሚሰጥ እስካሁን የተወሰነ ነገር የለም።

@tikvahethiopia


#MoE

" በዚህ ዓመት 150 ሺህ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይን) ይወስዳሉ " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ባለፈው ዓመት ወደ ተግባር የገባው የኦንላይን ብሔራዊ ፈተና ዘንድሮም እንደሚቀጥል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ዓመት 150 ሺ የሚደርሱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናቸውን በበየነ መረብ (ኦንላይ ) እንዲወስዱ ቅድመ ዝግጅ እየተደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።

ይህንን ያሉት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምክክር መድረክ ላይ ነው።

ከዚህ ባለፈ በመድረኩ  " ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥራት ያለው ትምህርት በማግኘት ረገድ እኩል እድል እንዲኖረው ፤ በድሃና ሃብታም መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ ሥራ መስራት አለብን " ብለዋል።

" ይችን ሀገር መለወጥ የሚቻለው የትምህርት ሥርዓቱን መቀየር ሲቻል " ነው ሲሉም ገልጸዋል።

በመንግስት ትምህርት ቤቶች የተሻለ የመማር ማስተማር እንዲኖር ማድረግ ላይ መሥራት እንደሚገባና ' በትምህርት ለትውልድ ' የትምህርት ቤቶች መሠረተ ልማት ማሻሻል የተጀመረው ንቅናቄ ግለቱን ጠብቆ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የመምህራንን አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ከተመረቁ  ዜጎች ውስጥ ልዩ የማስተማር ሙያ (pedagogy) ስልጠና እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ሙያው እንዲገቡ እንደሚደረግ ይፋ አድርገዋል።

#MoE

@tikvahethiopia


🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ

🔴 “
የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች

➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ”  - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ

በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።

የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።

በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።

በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።

አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።

የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።

የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?

“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡

እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡

በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።

ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።

ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።

አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።

ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም  ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።

እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።

አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡

እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።

“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡

(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

10 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.