TIKVAH-ETHIOPIA


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


#RemedialExam

የ2017 ትምህርት ዘመን የሪሚዲያል ተማሪዎች ከማዕከል የሚሰጥ ፈተና ከግንቦት 26 እስከ ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሜጄና (ዶ/ር) በቀን መጋቢት 15/2017 ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጻፉት ሰርኩላር፤ የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ግምገማ ከ100% ከማዕከል እንደሚሆን አስታውሰዋል፡፡

የሪሚዲያል ተማሪዎች ከዚህ በፊት 70% በማዕከል እና 30% በተቋማት የሚዘጋጁ ምዘናዎችን ይወስዱ የነበረ ሲሆን፤ ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ከ100% ከማዕከል እንዲሰጥ በጥቅምት 2017 ዓ.ም መወሰኑ ይታወሳል፡፡

በዚህም የ2017 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች በሚማሩበት ተቋም የሚሰጥ የተከታታይና የማጠቃለያ ፈተና ውጤት ለትምህርት ሚኒስቴር የሚላክ ይሆናል፡፡ ከዛም በማዕከል በሚሰጥ ፈተና የተማሪዎቹ መቀጠል እና አለመቀጠል የሚወሰን ይሆናል፡፡

(ከላይ የተያያዘውን ሰርኩላር ትክክለኛነት ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል፡፡)

Via
@tikvahuniversity


#Mekelle : በመቐለ ከተማ ሰሜን ክፍለ ከተማ ላጪ ተብሎ በሚጠራ ቀበሌ መጋቢት 16/2017 ዓ.ም ሌሊት ባጋጠመ የእሳት አደጋ ወላጅ እናት ከሁለት ልጆችዋ ጋር ህይወታቸው አልፏል።

በቤት ውስጥ የተቀመጠ ቤንዚን ተቀጣጥሎ ነው አሰቃቂ የሞት አደጋ ያስከተለው ተብሏል።

ቤንዚኑ በጀሪካን በቤት የተቀመጠ ነበር ያለው የከተማው ፖሊስ ቃጥሎውን ተከትሎ እናት እና ልጆቿ ህይወታቸው እንደጠፋ አመልክቷል።

በአደጋው ምክንያት ወላጅ እናት ዕድሚያቸው 5 ወር እና 4 ዓመት ትኩል ከሆኑ ልጆቻ ጋር ነው ህይወቷ ያለፈው።

ቤተሰቡ ለማዳን ጥረት ያደረገው አባት ሳይሳካለት ቀርቶ ከባድ ጉዳት ደርሶት ሆስፒታል ገብቶ ክትትል እዘየተደረገለት ይገኛል።

የአሰቃቂ የቃጠሎ አደጋውን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ፓሊስ ማጥራቱን መቀጠሉ አስታውቋል።

ህብረተሰቡ ቃጠሎ የሚያባብሰሱ ነገሮች በመኖሪያ ቤት ከማስቀመጥ እንዲቆጠብ መልእክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia


" ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት ይደረጋል፤ መንገዱ ክፍት የሚደረገው ግን የፀጥታ መዋቅር በሚያስቀምጠው የሰዓት ገደብ ነው " - አቶ ወገኔ ብዙነህ

በደቡብ ኢትዮጵያ እና ኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት አዋሳኝ አካባቢዎች የሚታየውን የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለ የፀጥታ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ መካሄዱ ተሰምቷል።

በምክክር መድረኩ ህዝብ መካከል ያሉ የተደራጁ ንብረት ዘራፊዎች እና ነፍስ አጥፊዎች ላይ የህግ የበላይነት ማስከበር እንዲሁም ሀገር መከላከያ ሠራዊት ኦፕሬሽን አድርጎ አካባቢውን ለማፅዳት የሚሰራውን ስራ ማገዝ ከዛ ባለፈ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እዲጠናከርና ሰላም እንዲፀና መስራት ይገባል ተብሏል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች እነማን ነበሩ ?

- የሀገር መከላከያ ሰራዊት
- የኮሬ ዞን
- የቡርጂ ዞን
- የምዕራብ ጉጂ ዞን
- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሠላምና ፀጥታ

ምን ተባለ ?

የኮሬ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ታረቀኝ በቀለ ፤ መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለመጀመር ወሳኝ እና ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።

በኮሬ ዞን በኩል እየተሰራ ባለ የህግ የበላይነትን የማስከበር ስራ የፀጥታው ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱን ጠቁመዋል።

የቡርጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ኣቶ ዳኜ ሂዶ ፤ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር ሁሉ። መዋቅሮች ኃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የምዕራብ ጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አዱላ ህርባዬ ፤ መድረኩ አላማው የተሳሳቱ አመለካከቶችን ማስተካከል ጥርጣሬ በማስወገድ ግልፀኝነት መፍጠር እንደሆነ ገልጸዋል።

በቀጣይ የቀበሌ እና የወረዳ አመራሮች የእርስ በእርስ ግንኙነት በማጠናከር ቅንጅታዊ ኦፕሬሽን ማድረግ፣ ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማጠናከር ላይ ይሰራል ብለዋል።

ሶስቱም ዞኖች በጋራ ሆነው የቆመው የፍስሃ ገነት - ኬሌ - ነዳሌ የአስፋልት መንገድ እንዲጀመር መጠየቅ ያስፈልጋል ብለዋል።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት 37ኛ ክፍለ ጦር አዛዥ ኮሎኔል ካሳዬ ተገኝ ፤ ቀጠናው ዘላቂ ሰላም እንዲያገኝ ከቀበሌ አንስቶ የህዝብ አመለካከት ላይ ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ህዝቡ ወንጀለኞችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ ማድረግ ፣ ፀረሰላም ኃይሎች የሚንቀሳሰቁባቸውን ቀበሌያት ወሰን አካባቢ ህዝባዊ ሰራዊት እና ሚሊሻ ማደራጀት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በሰላም ግንባታ ላይ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ሚናቸውን እንዲጫወቱ ጠይቀዋል።

መከላከያ ለሚሰራው ኦፕሬሽን አዋሳኝ ቀበሌያት ያለው ህዝብ እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ ፥ " የተጀመረውን የአመራር ለአመራር እርስ በእርስ ግንኙነት ለማደናቀፍ የሚሰራ ፀረ ሰላም አለ " ብለዋል።

በመሆኑን የፀጥታ መዋቅሩ በተጠንቀቅ መቆም አለበት ሲሉ አስገንዝበዋል።

ሁለቱም መዋቅር አመራርና ፀጥታ አካላት እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት በጋራ ተስማምተው በሚያስቀምጡት የሰዓት ገደብ መሰረት ከኬሌ - ዲላ መንገድ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ገልጸዋል።

" ከዛሬ ጀምሮ በቀጠናው የሰው ነፍስ የሚያጠፉ ንብረት የሚዘርፉ በኮሬ፣ ቡርኪና ጉጂ ስም የሚነግዱ ህገወጦች ወደ ቤት ግቡ " ሲሉ አሳስበዋል።

#KooreZone #BurjiZone #WestGujii #FDREDefenseForce

@tikvahethiopia


#DStvEthiopia

የአውሮፓ ሻምፕየንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ የደረሱት 8 ቡድኖች መካከል መድፈኞቹ ከሪያል ማድሪድ ጋር በኤመሬትስ ስታዲዮም የመጀመሪያውን ጨዋታ ይደርጋሉ!

ማን ወደ ግማሽ ፍፃሜ ይደርሳል?

👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

👉ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ደንበኝነትዎን ሲያሳድጉ... እኛም ቀጣዩን ፓኬጅ ለአንድ ወር እንጋብዝዎታለን!

ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/48oVhj8

#ChampionsLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvSelfServiceET #StepUp


At Jasiri, we empower entrepreneurs to launch impactful startups, gain expert mentorship, and connect with a powerful network of like-minded innovators.

Cohort 8 is NOW OPEN for aspiring entrepreneurs from Ethiopia!

Apply using this link 👉 https://bit.ly/40Ai4oR

For more information @jasiri4africa


" በኬንያ እና ኢትዮጵያ ድንበር አዋሳኝ በቱርካናና ዳሰነች አከባቢ ዳግም በተቀሰቀሰዉ ግጭት የሰዎች ሕይወት ጠፍቷል " - የዳሰነች ወረዳ አስተዳደር

🚨" በመጀመሪያዉ ግጭት ወቅት የሞቱ 11 ሰዎች አስከሬን እስካሁን ከቱርካና ሀይቅ አልተገኘም !!! "

ባሳለፍነው የካቲት ወር በሰሜናዊ ኬንያ ቱርካና ግዛትና በኢትዮጵያ ደቡባዊ ክፍል በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በአሳ ማስገሪያ መረብና ጀልባዎች ስርቆት የተቀሰቀሰው ግጭት ለበርካቶች ሞት ምክንያት መሆኑን አይዘነጋም።

ሰኞ እለት ደሞ በአከባቢው አስተዳደር " ለበቀል የተደረገ ትንኮሳ " በሚል በተገለፀው ዳግመኛ ግጭት የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ታደለ ሀቴ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የአሁኑ ግጭት ምክንያት በባለፈዉ ቤተሰብ የሞተባቸዉ ወጣቶች በቱርካና በኩል የበቀል ጥቃት በማድረሳቸው ነዉ ያሉት አቶ ታደለ በጥቃቱ ከኢትዮጵያ በኩል 4 ሰዎች ሲሞቱ 3 መቁሰላቸውንና 9 ከብቶችም በኬንያ አርብቶአደሮች መወሰዳቸዉን ገልፀዋል።

" በየካቲቱ ግጭት ወቅት በሁለቱም በኩል የሰዉ ሕይወት ጠፍቶ ነበር " ሲሉ ያስታወሱት አስተዳዳሪው ከኢትዮጵያ በኩል 13 ሰዎች መሞታቸዉንና ግጭቱ በአብዛኛዉ በቱርካና ሐይቅ ላይ ስለነበር እስካሁን የ2ቱ አስከሬን ብቻ መገኘቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

" የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እና የሰሜናዊ ኬንያ ቱርካና ግዛት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በተደረገዉ ዉይይት መሰረት የኬንያ አርብቶ አደሮች ከኢትዮጵያ በኩል የወሰዷቸዉን 120 የአሳ ማስገሪያ መረብ፣6 ጀልባዎች፣ 1 የአርብቶአደር  መሳሪያ እንዲመልሱና በአንፃሩ የዳሰነች አርብቶ አደሮች ከኬንያ በኩል የተወሰዱ120 የሚሆኑ መረቦች፣ 15 ጀልባዎች እና አንድ የአርብቶአደር መሳሪያ እንዲሁም አንድ ሞተር ሳይክል ለመመለስ ከስምምነት ላይ ቢደረስም ከኬንያ በኩል ምንም የተመለሰ ነገር የለም " ብለዋል።

የኛ አርሶ አደሮች ግን ከ15 ጀልባዎች 9ኙን በመመለስ 6ቱን በራሳቸዉ ስድስት ጀልባዎች ምትክ ከመያዛቸዉ ወጪ ሁሉንም ንብረቶች ማስረከባቸውን አስረድተዋል።

" የንብረት መረካከቡ ቀሪ ስራዎች አሉ " የሚሉት አስተዳዳሪዉ አከባቢውን ወደ ቀደመ ሰላሙ ለመመለስ በኬንያ በኩል ከአከባቢው ባለስልጣናት ጋር ለመነጋገር ቀጠሮ ተይዟል ሲሉ አሳውቋል።

በኬንያ ቱርካና በኩል ከዚህ ቀደምም ንብረት በመመለስ በኩል ከፍተኛ ችግሮች መኖራቸዉንና ለአብነትም በ2012 ዓ/ም ከ1400 በላይ ከብቶች ተወስደዉ እንዳልተመለሱ አስታዉሰዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia


🔈 #የነዋሪዎችድምፅ

🔴 “ የቤት ኪራይ ለመክፈል ይቅርና የዕለት ዳቦ መግዣ የለንም።  የሥራ ቦታችንን ወረዳው አፈረሰብን ” -  አረጋዊያንና አካል ጉዳተኞች

➡️ “ ደብዳቤው በዚህ ወር ነው የመጣልን ‘በሦስት ቀናት ውስጥ አስረክቡ ነው’ የሚለው፤ ከመፍረሱ ከ15 ቀናት በፊት ነው የመጣው ” - ወረዳው 

ወደ 30 የሚሆኑ አካል ጉዳተኞችና አረጋያውን በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 10፣ “ አጣና ተራ ቴሌ ጀርባ ” በተባለ አካባቢ በተለያዬ ዘርፍ ተሰማርተው ሲሰሩባቸው የነበሩ ቤቶችን ወረዳው እንዳፈረሰባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።

ቅሬታ ያሰሙት 3 ማኀበራት ሲሆኑ፣ ከነዚህም ውስጥ  ' ቢያድግልኝ የአካል ጉዳተኞች ማኀበር '፣ 11 አካል ጉዳተኞች  ሲተዳደሩባቸው የነበሩ 11 የንግድ ሱቆች እንደፈረሱባቸው ባለፈው ሳምንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጾ ነበር።

ሰሞኑን ደግሞ፣ በስሩ 10 አባዎራዎች ያሉት ‘ዓርዓያ የህዝብ መጸዳጃ አገልግሎት' ፣ ሌላ በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ዘጠኝ እናቶች በሥሩ ያሉት ማኅበራት መስሪያ ቦታዎች እንደፈረሱባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

እሮሮ አቅራቢዎቹ በሰጡን ቃል በዝርዝር ምን አሉ ?

“ የቤት ኪራይ ለመክፈል ይቅርና የዕለት ዳቦ መግዣ የለንም። የሥራ ቦታችንን ወረዳው አፈረሰብን።

እኛ የመጸዳጃ ቤት አገልግሎት ላይ ተደራጅተን ነበር ቦታውን የሰጡን። በአካባቢው ሌላ የውጪ መጸዳጃ ቤት የለም። የኛን ነበር ህዝቡ የሚጠቀመው ከእኛ በላይ ህዝቡን ነው ጉድ ያደረጉት። 

ምን እንደሆነ አልገባንም አፈረሱት። 'ለመልሶ ማልማት ተሰጠ' ነው ያሉን። ቢያንስ አንዳንድ እቃዎች አሉ እስከናጣራበት እንኳ ጊዜ ስጡን ብንልም አልፈቀዱልንም። አፍርሰው ለባለሀብት ሸጡት።

አካል ጉዳተኞች ነን፤ በወቅቱ ብዙ ቦታ ሮጠናል፣ ሮጠንም አልቻልንም። የነበሩ ኮንቴነሮችንም አፍረሱብን። የሦስት ማህበራት ነው የፈረሰው።

በ'ዓርዓያ የህዝብ መጸዳጃ በማህበር' 10 ሰዎች አሉ። አንድ ሙሉ ግቢ የነበረ መጸዳጃ ቤት ነበር። ከዛ በምናገኘው ገቢም ነበር የምንተዳደረው።

ወረዳው 'አፍርሱ የሚል ደብደቤ አለ' አለ። እሱንም ማስረጃ ማወቅ ይገባናል ስንለው  ፈቃደኛ አልሆነም።

በአንድ ማኀበር ያሉትን የ10 አካል ጉዳተኞችን፣ የሌላ የ11 አካል ጉዳተኞችና የዘጠኝ አረጋዊ እናቶችን የሥራ ቦታ ቤት አፈረሱብን።

እናቶችን፣ 'ተለዋጭ ቦታ ይፈለግላቸዋል፤ ራሳቹ  አፍርሱና አስረክቡን' አሏቸው። እኛ ግን አናፈርስም ጊዜ ይሰጠን አልናቸው። 'እቢተኛ ናቹ' ብለው በግብረ ኃይል እቃችንን ሳናወጣ ፍርድ ቤት በሄድንበት አፈረሱብን" ብለለዋል።

ወረዳው ምን አለ ?
 

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ቅሬታውን ይዞ ምላሽ የጠየቃቸው የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ዋና ስሬ አስፈፃሚ አቶ አበራ ግርማ፣ የቦታው ለልማት እንደሚፈለግና እንዲፈርስ ትዕዛዝ በመውረዱ መፍረሱን ገልጸዋል።

የትዕዛዝ ደብዳቤ የመጣው ከየት ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄም፣ “ደብዳቤው በዚህ ወር ነው የመጣልን ‘በሦስት ቀናት ውስጥ አስረክቡ ነው’ የሚለው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ኃላፊው አክለው፣ ደብዳቤው ቦታው “ከመፍረሱ ከ15 ቀናት በፊት ነው የመጣው” ያሉ ሲሆን፣ የፈረሰባቸው ሰዎች ምትክ ቦታ እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ታዲያ ከ15 ቀናት በፊት ከመጣ እንደ ወረዳ አስተዳደር ሰዎቹ ከስራ ሳይፈናቀሉ፣ ለቤት ኪራይ የሚከፍሉት ሳያጡ ቀድማችሁ ለምን ምትክ ቦታ አልሰጣችኋቸውም ? ሲል ኃላፊውን ጠይቋል።

እሳቸውም “ 29 ግለሰቦች ናቸው ለ29ኙም ተመሳሳይ የሆነ ቦታ ላናገኝ እንችላለን። ለምሳሌ አንድ ቦታ 3 ሰዎች፣ ሌላ ቦታ 2 ብቻ የሚይዝ ቦታ ሊኖር ይችላል። የተከፋፈለ ስለሆነ አንድ ወጥ የሆነ ቦታ አይኖርም ” ብለዋል።

“ እንዲያውም ደካማ ለሆኑ እናቶች ቦታ የሰጠናቸው አሉ። ግን ለመስጠት በስራና ክህሎት ተመዝግቦ የስራ እድል ተፈጥሮላቸው ነው ያን ቦታ መውሰድ ያለባቸው ” ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ለምሳሌ በንግድ ቤት የተሰማሩ 11 የአካል ጉዳተኞች ቦታ አንዳልተሰጡ ገልጸዋልኮ፤ ስንላቸው፣ “እኔ ጋር መጥተው ተነጋገርን ቦታ እንደማመቻችላቸው ተግባባን፤ ከዛ ቀድመው ፍርድ ቤት ሄዱ ፍርድ ቤትም እግዱን አነሳባቸው፤ ከዛ በኋላ ወደ እኔ መጥተው አያውቁም” ነው ያሉት።

ኃላፊው፣ ወደ 30 ለሚሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ምትክ ቦታ እንደሚሰጣቸው የጠቆሙ ሲሆን፣ መቼ ይሰጣቸዋል? ብለን ስንጠይቃቸው፣ አካል ጉዳተኞቹ ወደ ወረዳው አለመሄዳቸውን በመጥቀስ መቼ እንደሚሰጣቸው ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ ፍ/ቤት የእግድ ደብዳቤ ካወጣላቸው በኋላ መልሶ፣ ' ልማት አላደናቅፍም ' እንዳላቸው፣ ከወረዳው ኃላፊ ሲሄዱም ቢሮ እንደተዘጋባቸው የሚያሳይ ቪዲዮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ልከዋል።

(ጉዳዩን እስከ መጨረሻው የምንከታተለው ይሆናል።)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#SafaricomEthiopia

🌐 እጅግ ፈጣን ዋይፋይ በአዲስ ቅመም! ሊያውም ከጉርሻ ጋር 🤗

💨⚡️ እስከ 6 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም!

🍰  ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😊

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡️
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#SafaricomEthiopia


መቅረዝ የጥራት ፈርጥ !

በጤናዎ አንደራደረም !

በስፔሻሊስት ሐኪሞች የሚከናወን ጥራት ያለው ሕክምና ፤ ለእናንተ ለውድ ደንበኞቻችን በቀን 24 ሰዐት በሳምንት 7 ቀናት ለማገልገል ዝግጁ ነን። በማንኛዉም ሰአት ይምጡ ፤ በፍቅር እንቀበሎታለን።

ለበለጠ መረጃ በ0952272727 ወይም በ 0921636465 ላይ ይደውሉ።

መቅረዝ የጥራት ፈርጥ !
ቴሌግራም = @MeQrezGH
ቲክቶክ= https://www.tiktok.com/@meqrezhealthservices?_t=ZM-8uyvqH4gLck&_r=1
ኢንስታግራም= https://www.instagram.com/meqrez?igsh=YjdyemNwemFiNTN3
ፌስቡክ= https://www.facebook.com/share/1FAMkQvHnd/
በይነ-መረብ= meqrezhealth.com/


#Islam

ለነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዓ.ወ) ተከታዮች ብቻ የተሰጠችው ከሺህ ወራት በላጯ ሌሊት !

(በሴራን ታደሰ)

የኢስላም ሃይማኖት ምሁራን እንደሚሉት፥ ከነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዓ.ወ) መላክ አስቀድሞ በምድር ላይ ኖረው ያለፉ ሕዝቦች ዕድሜያቸው ረጅም ነበር፤ በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ዓመታትን በሕይወት የመቆየት ዕድል ነበራቸው።

በአንፃሩ የነቢዩ (ሰ.ዓ.ወ) ተከታዮች ዕድሜ በአማካይ ከ60 እና ከ70 ዓመት የማይዘልና በጣም አጭር ነው። በመሆኑም የነቢዩ ተከታዮች በአምልኮም ሆነ በበጎ አድራጎት ተግባራት በሚያስመዘግቡት ምንዳ ከቀድሞዎቹ ሕዝቦች ጋር ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉበት ዕድል አልነበራቸውም።

አላህም ይህን ሊያካክስላቸው ከረመዳን ሌሊቶች አንዷን በምርታማነቷ ከሺህ ወራት ጋር ተመጣጣኝ እንድትሆን አደረገላቸው። ይህች ሌሊት ለይለቱል ቀድር ወይም የመወሰኛዋ ሌሊት በመባል ትታወቃለች። የረመዳን ወርን ክብር ካላቁት ነገሮች አንዷም ይህችው ለይለቱል ቀድር ናት።

ነቢዩ (ሰ.ዓ.ወ) ለይለቱል ቀድርን ከመጨረሻዎቹ 10 የረመዳን ቀናት በተለይ ኢ-ተጋማሽ በሆኑት ውስጥ ተጠባብቃችሁ ፈልጓት ብለዋል። ይህም በረመዳን 21፣ 23፣ 25፣ 27፣ እና 29 መሆኑ ነው። አብዛኛዎቹ የሃይማኖቱ ምሁራን ወደ 27ኛዋ ሌሊት ቢያደሉም፣ለዚህ ቁርጥ ያለ ማስረጃ ወይም ማረጋገጫ የለም።

አላህ ሌሊቷ ተለይታ እንዳትታወቅ ያደረገበት የራሱ ምስጢር አለው ይላሉ የኢስላም ምሁራን። ምዕመናን ሌሊቷ የቷ እንደሆነች ለይተው ቢያውቁ ኖሮ፤ በዚያች ሌሊት ብቻ ሥርዓተ አምልኮን በመፈጸም ረመዳንን ላይጾሙ፣ ዓመቱን ሙሉ ፈጣሪያቸውን ላያመልኩ ይችሉ ነበር። ያ እንዳይሆን ለመከላከል አላህ ለይለቱል ቀድርን ድብቅ ሌሊት አደረጋት።

ለይለቱል ቀድር ከሌሎቹ ሌሊቶች የምትልቀው ቁርዓን የወረደባት እና የመወሰኛ ሌሊት በመሆኗ ነው። የምዕመናን ዓመታዊ ጉዳዮች አላህ ዘንድ ቀርበው ውሳኔ የሚያገኙት በዚህች ሌሊት ነው።በመሆኑም በዚህች ሌሊት ምዕመናን የአላህን ምህረት፣ ጸጋ እና ውዴታ ለማግኘት የአምልኮ ተግባራትን ከወትሮው በበለጠ ትጋት እና ትኩረት ያከናውናሉ።

በሌላ አባባል፥ በዚህች ሌሊት የሚከናወን አምልኮተ ሥርዓት ከረመዳን ዉጪ ለ1 ሺህ ወራት ወይም ለ83 ዓመት ከ3 ወር ከሚከናወነው ጋር ተመጣጣኝ የሆነ ምንዳን ያስገኛል።

በመሆኑም በዚህች ሌሊት ምዕመናን ሥርዓተ አምልኮን እና በጎ−ምግባራትን ከወትሮው በበለጠ መጠን እና ጥራት ያከናውናሉ፤ለአብነትም፥ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን ይከውናሉ፣ ቁርዓን ይቀራሉ፣ የሌሊት ሶላት ይሰግዳሉ፣ ዱዓ ያደርጋሉ (ፈጣሪያቸውን ይለምናሉ)። በዚህች ሌሊት ከሚደረጉ ተወዳጅ ዱዓዎች መካከልም፥ "አላህ ሆይ፥ አንተ ይቅር ባይ ነህ፤ ይቅር ማለትን ትወዳለህ፤ ይቅር በለን!" የሚለው ተጠቃሽ ነው።

Credit - Ethiopian Broadcasting Corporation (Seran Tadesse)

@tikvahethiopia


#TPLF

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጥሪ ተቋወመ።

ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ ፥ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚነንስትር  ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) የትግራይ ህዝብ  ለቀጣይ አንድ ዓመት ስልጣኑ የሚራዘመውን የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚመራ ፕሬዜዳንት እንዲጠቁም አስመልክቶ ያወጡትን መልዕክት " የተናጠል ውሳኔና ተግባር " ሲል ተቃውሟል።    

" የፕሪቶሪያ ሥምምነት ከተፈረመ ሁለት ዓመት ተኩል ሆኖታል " ያለው የደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት " ስምምነቱ በሙሉነት ተተግብሮ ትግራይ በህዝብ የተመረጠ መንግስት ሊኖራት ይገባ ነበር "  ብሏል። 

" የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በሙሉነት ያልተተገበረው የፌደራል መንግስት በስምምነቱ አፈፃፀምና አተገባበር በተከተለው የተሳሳተ አካሄድና ፓለቲካዊ ቀውስ እንዲፈጠር በመስራቱ ነው "  ሲልም ክስ አሰምቷል።

" በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አንቀፅ 3 መሰረት ተዋዋይ ወገን ሌላውን በቀጥታ ይሁን በተዘዋዋሪ በፕሮፓጋንዳ ማጥቃት ይከለክላል  ይሁን እንጂ ይህንኑ የስምምነቱ አካል በፌደራል መንግስት በተደጋጋሚ እየተጣሰ ነው " ብሏል።

" የፌደራል መንግስት ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መንፈስና ይዘት በወጣ አካሄድ አግባብነት በሌላቸው 359/1995፤ ደንብ 533/2015 ህግና አዋጆች እንዳሻው እየወሰነ ይገኛል " የሚል ወቀሳም አቅርቧል።

" የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አንቀፅ 10 የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በህወሓትና በኢትዮጵያ መንግስት መግባባት እንዲቋቋም ያዛል " ያለው የደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት " የኢትዮጵያ መንግስት የተናጠል ውሳኔ መወሰን አይችልም " ብሏል።    

" ህወሓት ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ከስልጣን ማስነሳቱ ተከትሎ ፤ ጀነራል ታደሰ ወረደ ፕረዚደንት እንዲሆኑ ማእከላይ ኮሚቴ ወስኖ የኢትዮጵያ መንግስት ተቀብሎታል " ያለም ሲሆን " ይህንን ወደ ጎን በመተው በጠቅላይ ሚንስትሩ የተናጠል ውሳኔ በሚያስመስል  መልኩ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የሚጥስ አካሄድ ተቀባይነት የለውም " ሲል ገልጿል።

" የፌደራል መንግስት ህዝብን ከሚጎዱ ግልፅ ተግባራት በመቆጠብ ዘላቂ ጥቅምና የጋራ ሰላም በሚያረጋግጡ ተግባራት እንዲያተኩር ጥሪ እናቀርባለን " ያለው የደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት " የተናጠል ውሳኔዎች እንዲቆሙ " ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia 


" ተቋሙ የተገኘበትን የኦዲት ግኝት ማስተካከያ ለማድረግ ዝግጁነት የለውም " - የፌዴራል ዋና ኦዲተር

🚨 " ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የበጀት ጉድለት ተገኝቶበታል !! "

" የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አላግባብ የህዝብና የመንግሥት ሀብት እንዲባክን አድርጓል " ሲል በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሰታወቀ።

ቋሚ ኮሚቴው ይህን ያለው የሚኒስቴሩን የፕሮጀክት ውልና የሰው ሀብት አስተዳደር አፈፃፀም የክዋኔ ሪፖርትን በገመገመበት ወቅት ነው።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ (ዶ/ር) ፤ " ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ወደ ትግበራ ከመግባታቸው በፊት የቅድመ አዋጭነት ጥናት ግምገማ ተደርጎላቸው እንዲከናወኑ አልተደረገም " ብለዋል።

" በመንግሥት በጀትና በዓለም አቀፍ ድጋፍና ብድር የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች የትግበራ ቅደም ተከተል ተሰጥቷቸው ለምክረ ሀሳብ ለሚመለከታቸው አካለት አለማቅረቡ ተገቢነት የሌለው ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

በተያዘላቸው ጊዜ ያላለቁ ፕሮጀክቶች ወቅታዊ ሁኔታ የማይታወቅ ሲሆን፣ የፋይናንስና የፊዚካል አፈፃፀማቸው የተስማሚነት ችግር እንዳለበት አሳውቀዋል።

በተጨማሪም ፕሮጀክቶች ሳይጠናቀቁ አቋርጦ በጀቱን ወደ ሌላ ፕሮጀክት የማዘዋወር ሂደት ረገድ የህግ፣ የመመሪያ፣ የአሰራር ጥሰት የታየበት በመሆኑ ሊታረም እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

" ለትራንስፖርት ኪራይ፣ ለዳታ ማዕከል ግንባታ፣ ለሳይንስ ካፌና ለሰራተኛ ደሞዝ ያለአግባብ የወጣውን ወጪ ኦዲት በማድረግ በ15 ቀናት ውስጥ ለቋሚ ኮሚቴው ሪፖርት እንዲያደርግ " ሲሉም አሳስበዋል።

ከሰው ሀብት ጋር ተያይዞም መስሪያ ቤቱ ሰራተኞችን #በሪኮመንዴሽን_የሚቀጥርበት ሁኔታ ህግና ስርዓት ያልተከተለ በመሆኑ ሰራተኞችን አወዳድሮ ሊቀጥርና አሰራሩ ሊታረም እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ከንብረት ማስመለስ ጋር በተያያዘም ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የለቀቁና ጡረታ የወጡ ሰራተኞች ያልመለሷቸውን በጥቅል ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን የመንግስትና የህዝብ ሀብት በአግባቡ የማስመለስ ስራ መስራት አለበት ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ከግማሽ ቢሊዮን ብር በላይ የበጀት ጉድለት እንደተገኘበት በማመልከት የአሰራር ሂደቶችን በማረምና ለጉድለቱ መንስኤ የሆኑ ግለሰቦችን የህግ ተጠያቂ በማድረግ ለምክር ቤቱ እንዲያሳውቅ ቋሚ ኮሚቴው አሳስቧል።

የፌዴራል ዋና ኦዲተር ወይዘሮ መሰረት ደምጤ ፤ " ተቋሙ የተገኘበትን የኦዲት ግኝት ማስተካከያ ለማድረግ ዝግጁነት የለውም " ሲሉ ተናግረዋል።

" ተጀምሮ ላልተጠናቀቀ ፕሮጀክት ገንዘብ ወጪ ተደርጓል " ብለዋል።

" የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሰው ሀብትና የንብረት አስተዳደር ሂደቱ ደካማ ነው " ብለው " ከህግ አግባብ ውጪ የተከፈሉ ክፍያዎች ላይ በፍጥነት የእርምት እርምጃ መውሰድ ይጠበቅበታል " ሲሉ ተናግረዋል።

በኦዲት ክፍተቶች ላይ የፌዴራል ፀረ ሙስና ኮሚሽን ክትትል በማድረግ የህግ ተጠያቂነት ማስፈን እንደሚጠበቅበት ተመላክቷታ።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ምን መለሱ ?

በለጠ (ዶ/ር) ፤ " ተቋሙ የሚሰራቸው ሥራዎች ዘርፈ ብዙ በመሆናቸው በአንዳንድ ዘርፎች የኦዲት ጉድለት ተከስቷል " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ችግሮቹን ለመፍታት የድርጊት መርሐግብር በማዘጋጀት የተወሰዱ እርምጃዎችን ለቋሚ ኮሚቴው እናቀርባለን " ብለዋል።

" ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025ን ተግባራዊ ለማድረግ ከዓለም ባንክና ከአጋር አካለት ጋር የሚሰሩ ሥራዎች በአይነትና በቁጥር በርካታ ናቸው " ያሉት ሚኒስትሩ " የተስተዋሉ የኦዲት ክፍተቶችን ለማረም ዝግጁ ነን " ብለዋል። #EPA #HoPR

@tikvahethiopia


#ETEX2025 : ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ ልታዘጋጅ ነው።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ በመሆን የሚያዘጋጁት ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (Ethiopian Tech Expo - ETEX 2025) ከግንቦት 8 እስከ 10/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ፣ አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል፡፡

ዛሬ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ትዕግስት ሃሚድ እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በጋራ በመሆን ሁነቱን በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
 
የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ (Ethiopian Tech Expo - ETEX 2025) በ5 ዋና ዋና መስኮች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።

እነዚህም፦
- በሳይበር ደህንነት፣ 
- በሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI)፣ 
- ፋይናንስ ቴክኖሎጂ (FinTech)፣ 
- ስማርት ከተማ (Smart City)፣
- በቴክኖሎጂ ትምህርት (Tech Education) ናቸው።

ይህም ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ እና ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳ 2063 ጋር ተጣጣሚነት ያለው ተብሏል።

ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ኤክስፖ የመጀመሪያው የመክፈቻ ቀን ከሳይበር ደህንነት ጋር የተያያዙ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑ ተገልጿጻ።

በሁለተኛው ቀን በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ መርሃ ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል ተብሏል።

በሦስተኛው ቀን አጠቃላይ ለሕብረተሰቡ ለጉብኝት ክፍት የሚሆን ሲሆን ሌሎች የመዝጊያ መርሃ ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል፡፡

ያንብቡ
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-03-26

#INSA #EthiopianArtificialIntelligenceInstitute

@tikvahethiopia

13 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.