Postlar filtri


" ፍፃሜውን ለማሸነፍ እንሄዳለን " ሩዲገር

የሎስ ብላንኮዎቹን የማሸነፊያ ግብ ያስቆጠረው አንቶኒዮ ሩዲገር ከባድ ጨዋታ እንደነበረ ከድሉ በኋላ ገልጿል።

“ ከባድ ጨዋታ ነበር በመጨረሻም ግብ አስቆጥሪያለሁ በጣም ደስተኛ ነኝ ይሄ ሪያል ማድሪድ ነው “ ሲል ሩዲገር ተናግሯል።

አክሎም " የፍፃሜ ጨዋታውን ለማሸነፍ ነው የምንሄደው " ሲል ተደምጧል።

የመጀመሪያውን ግብ ያስቆጠረው ኤንድሪክ በበኩሉ " ዋንጫውን ለማሸነፍ እንፋለማለን የምንሄደው ለማሸነፍ ነው “ በማለት ተናግሯል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


ሎስ ብላንኮዎቹ ለፍፃሜ ደረሱ !

ሪያል ማድሪድ ከሪያል ሶሴዳድ ጋር ያደረገውን የስፔን ኮፓ ዴላሬ ግማሽ ፍፃሜ የመልስ ጨዋታ 4ለ4 በሆነ አቻ ውጤት አጠናቋል።

የሪያል ማድሪድን ግቦች ኤንድሪክ ፣ ቹዋሜኒ ፣ ቤሊንግሀም እና አንቶንዮ ሩዲገር አስቆጥረዋል።

ለሪያል ሶሴዳድ ግቦችን ኦያርዛባል 2x ፣ ባሬኔቲ እና ዴቪድ አላባ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥረዋል።

ሎስ ብላንኮዎቹ የደርሶ መልስ ጨዋታውን 5ለ4 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ለኮፓ ዴላሬ ፍፃሜ መድረሳቸውን አረጋግጠዋል።

የ 21ዓመቱ ጁድ ቤሊንግሀም እስካሁን ባደረጋቸው ጨዋታዎች 125 የግብ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል።

ሪያል ማድሪድ በፍፃሜው የባርሴሎና እና አትሌቲኮ ማድሪድን አሸናፊ የሚገጥሙ ይሆናል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ የጉዳት ሁኔታቸው ነገ ይታያል “ አርቴታ

የመድፈኞቹ ዋና አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ በምሽቱ ጨዋታ የተጎዱ ተጨዋቾችን ጉዳት ሁኔታ አለማወቃቸውን ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

አሰልጣኙ አክለውም ጋብሬል ማግሀሌስ እና ጁሪየን ቲምበር በነገው ዕለት የህክምና ምርመራ ይደረግላቸዋል ብለዋል።

“ ቲምበር ጨዋታ ሲጀመር ጀምሮ ስሜቱ ነበረው መቀጠል አልቻለም ፤ ማግሀሌስ የጡንቻ ጉዳት ነው ያጋጠመው “ አርቴታ

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ቡድኑ መሻሻሉን አይቻለሁ " ሩበን አሞሪም

የቀያይ ሴጣኖቹ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪሞ ቡድኑ እየተሻሻለ መሆኑን በዛሬው ጨዋታ መመልከታቸውን አስረድተዋል።

" በጨዋታው ውስጥ የቡድኑን እድገት አይቻለሁ " ያሉት አሰልጣኙ ራሴን አልዋሽም ሰው የፈለገውን ማለት ይችላል የሆነ ጥሩ ነገር አይቻለሁ ብለዋል።

አክለውም " ነገርግን ጨዋታዎችን ማሸነፍ አለብን “ ሲል ቡድናቸውን አሳስበዋል።

" አንዳንድ ጊዜ ስትሸነፍ ተጋጣሚህ የተሻለ ነበር ብለህ ታስባለህ ለመቀበል ቀላል ነው ዛሬ ግን እኛ የተሻልን ነበርን " ሩበን አሞሪም

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


" ሲቲን ማሸነፍ አለብን " ዳሎት

የማንችስተር ዩናይትዱ የመስመር ተጨዋች ዲያጎ ዳሎት ቡድናቸው እየተሻሻለ መሆኑን ከምሽቱ ጨዋታ በኋላ ተናግሯል።

" እየተሻሻልን እንደሆነ ይሰማኛል በጨዋታው እኛ ነበርን የተሻልነው ጨዋታውን ተቆጣጥረነዋል “ ሲል ዳሎት አስተያየቱን ሰጥቷል።

አክሎም " የዛሬው ጨዋታ ጥሩ ነገር ለቀጣይ ጨዋታዎች መነሳሻ ይሆነናል “ ሲል ተደምጧል።

ስለ ቀጣዩ የማንችስተር ሲቲ ጨዋታ ያነሳው ዳሎት “ ደርቢ ነው ማሸነፍ አለብን ድባቡ የተለየ ይሆናል “ ሲል ገልጿል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe


ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል !

በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።

የኖቲንግሀም ፎረስትን የማሸነፊያ ግብ አንቶኒ ኢላንጋ በቀድሞ ክለቡ መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል።

ማንችስተር ዩናይትድ በውድድር ዘመኑ አስራ ሶስተኛ የፕርሚየር ሊግ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

ኖቲንግሃም ፎረስት በፕርሚየር ሊጉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለቱም የደርሶ መልስ የሊግ ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድን ማሸነፍ ችሏል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

3️⃣ ኖቲንግሃም :- 57 ነጥብ
1️⃣3️⃣ ማንችስተር ዩናይትድ :- 37 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ቅዳሜ - አስቶን ቪላ ከ ኖቲንግሃም ፎረስት

እሁድ - ማንችስተር ዩናይትድ ከ ማንችስተር ሲቲ

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe

21.7k 0 12 49 358

ባየር ሌቨርኩሰን ከውድድር ውጪ ሆነ !

ባየር ሌቨርኩሰን ከአርሚንያ ቤሌፌልድ ጋር ያደረገውን የጀርመን " DFB pokal " ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

የወቅቱ የቡንደስሊጋ አሸናፊ ባየር ሌቨርኩሰን በጀርመን ሶስተኛ ሊግ በሚወዳደረው አርሚንያ ቤሌፌልድ ተሸንፎ ከውድድሩ ተሰናብቷል።

አርሚንያ ቤሌፌልድ በፍፃሜው ከሌፕዚግ እና ስቱትጋርት አሸናፊ ጋር የሚጫወቱ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


መድፈኞቹ ወሳኝ ድል አሳክተዋል !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ከፉልሀም ጋር የፕርሚየር ሊግ መርሐግብር 2ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የመድፈኞቹን የማሸነፊያ ግቦች ቡካዩ ሳካ እና ሚኬል ሜሪኖ ሲያስቆጥሩ ለፉልሀም ሙኒዝ ከመረብ አሳርፏል።

በጉዳት ለወራት ከሜዳ ርቆ የቆየው ቡካዩ ሳካ ወደ ሜዳ በተመለሰበት ጨዋታ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

አርሰናል ማሸነፉን ተከትሎ ከሊጉ መሪ ሊቨርፑል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ዘጠኝ ማጥበብ ችሏል።

በሌላ ጨዋታ ዎልቭስ ከዌስትሀም ዩናይትድ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

2️⃣ አርሰናል :- 61 ነጥብ
8️⃣ ፉልሀም :- 45 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ቅዳሜ - ኤቨርተን ከ አርሰናል

እሁድ - ፉልሀም ከ ሊቨርፑል

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


90+4 '

አርሰናል 2-1 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ ⚽ ሙኒዝ
⚽ ሳካ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

75 ' ኖቲንግሃም 1-0 ማንችስተር ዩናይትድ

⚽ ኢላንጋ'

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


90 '

አርሰናል 2-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ
⚽ ሳካ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

75 ' ኖቲንግሃም 1-0 ማንችስተር ዩናይትድ

⚽ ኢላንጋ'

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


#TikvahGoal

በአሁን ሰዓት እየተካሄዱ በሚገኙ ጨዋታዎች የሚቆጠሩ ግቦችን እና አጫጭር ቪዲዮችን በጎል ቻናላችን መከታተል ይችላሉ።
    
የጎል ቻናላችን 👉 https://t.me/+rbdEU4UaEdQxYWFk

@tikvahethsport            @kidusyoftahe


66 '

ኖቲንግሃም 1-0 ማንችስተር ዩናይትድ

⚽ ኢላንጋ'

82 ' አርሰናል 2-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ
⚽ ሳካ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


80'

አርሰናል 2-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ
⚽ ሳካ

- ከሶስት ወራት ጉዳት በኋላ ወደ ሜዳ የተመለሰው ቡካዩ ሳካ ተቀይሮ በገባ ሰባት ደቂቃ ውስጥ ለአርሰናል ግብ አስቆጥሯል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


73'

አርሰናል 2-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ
⚽ ሳካ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

45 ' ሪያል ማድሪድ 1-1 ሪያል ሶሴዳድ ( ኮፓ ዴላሬ )

⚽ ኤንድሪክ

ድምር ውጤት :- 2-1

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


52 '

ኖቲንግሃም 1-0 ማንችስተር ዩናይትድ

⚽ ኢላንጋ'

71 ' አርሰናል 1-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

44 ' ሪያል ማድሪድ 1-1 ሪያል ሶሴዳድ ( ኮፓ ዴላሬ )

⚽ ኤንድሪክ

ድምር ውጤት :- 2-1

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


62'

አርሰናል 1-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

35 ' ሪያል ማድሪድ 1-1 ሪያል ሶሴዳድ ( ኮፓ ዴላሬ )

⚽ ኤንድሪክ

ድምር ውጤት :- 2-1

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


52'

አርሰናል 1-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

25 ' ሪያል ማድሪድ 0-1 ሪያል ሶሴዳድ ( ኮፓ ዴላሬ )

ድምር ውጤት :- 1-1

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


እረፍት

ኖቲንግሃም 1-0 ማንችስተር ዩናይትድ

⚽ ኢላንጋ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


41 '

ኖቲንግሃም 1-0 ማንችስተር ዩናይትድ

⚽ ኢላንጋ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


እረፍት

አርሰናል 1-0 ፉልሀም

⚽ ሜሪኖ

ዎልቭስ 1-0 ዌስትሀም

⚽ ላርሰን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.