“ የመልስ ጨዋታው በሜዳችን አሸንፈን እናልፋለን “ ሎዛ አበራ
⏩ “ ጥቃቅን ስህተት እንድንሸነፍ አድርጎናል “ ዮሴፍ ገብረወልድ
የሉሲዎቹ አምበል ሎዛ አበራ ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ በሜዳው አሸንፎ የማለፍ አቅም እንዳለው ከጨዋታው በኋላ ተናግራለች።
“ ጨዋታውን ተሸንፈናል ነገር ግን የመጨረሻ አይደለም “ ያለችው ሎዛ “ የመልስ ጨዋታው በሜዳችን ነው አሸንፈን እናልፋለን “ ስትል ተደምጣለች።
“ ዩጋንዳ ጠንካራ ናቸው ነገር ግን እኛ አቅሙ አለን የመልሱን ጨዋታ አሸንፈን ወደ ቀጣዩ ዙር እንደምናልፍ ሙሉ ተስፋ አለኝ “ ሎዛ አበራ
ሎዛ አበራ አክላም " ደጋፊው ላደረገልን ድጋፍ እናመሰግናለን “ ስትል ለመልሱ ጨዋታ ሁሉም ሰው ጠንካራ ድጋፍ ያድርግልን ስትል ጠይቃለች።
የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ በበኩላቸው “ ጨዋታው በጣም አሪፍ ነበር ጥቃቅን ስህተት ነው እንድንሸነፍ ያደረገን “ ሲሉ ተናግረዋል።
አሰልጣኙ አክለውም “ በቀጣይ የዛሬውን ስህተት አርመን ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንገባለን " ብለዋል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe