ዩናይትድ ሽንፈት አስተናግዷል !
በእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐግብር ማንችስተር ዩናይትድ ከኖቲንግሃም ፎረስት ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።
የኖቲንግሀም ፎረስትን የማሸነፊያ ግብ አንቶኒ ኢላንጋ በቀድሞ ክለቡ መረብ ላይ ማሳረፍ ችሏል።
ማንችስተር ዩናይትድ በውድድር ዘመኑ አስራ ሶስተኛ የፕርሚየር ሊግ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።
ኖቲንግሃም ፎረስት በፕርሚየር ሊጉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሁለቱም የደርሶ መልስ የሊግ ጨዋታዎች ማንችስተር ዩናይትድን ማሸነፍ ችሏል።
የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?
3️⃣ ኖቲንግሃም :- 57 ነጥብ
1️⃣3️⃣ ማንችስተር ዩናይትድ :- 37 ነጥብ
ቀጣይ መርሐግብር ?
ቅዳሜ - አስቶን ቪላ ከ ኖቲንግሃም ፎረስት
እሁድ - ማንችስተር ዩናይትድ ከ ማንችስተር ሲቲ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe