Postlar filtri


አል ነስር ሽንፈት አስተናግዷል !

በሳውዲ አረቢያ ሊግ ሀያ አንደኛ ሳምንት መርሐ ግብር አል ነስር ከአል ኢቲፋቅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3ለ2 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።

ለአል ኢቲፋቅ የማሸነፊያ ግቦችን ጆርጂንዮ ዊናልደም 2x ፣ ፋቲል በራሱ ግብ ላይ ማስቆጠር ችለዋል።

የአል ነስርን ግቦች አይማን ያህያ እና መሐመድ አል ፋቲል ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።

አል ነስር ከተከታታይ ዘጠኝ ጨዋታዎች ያለመሸነፍ ጉዞ በኋላ ሽንፈት ገጥሟቸዋል።

በጨዋታው ኮሎምቢያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ጆን ዱራን ቀይ ቀርድ ተመልክቷል።

የሊግ ደረጃቸው ምን ይመስላል ?

4️⃣ አል ነስር :- 44 ነጥብ
8️⃣ አል ኢቲፋቅ :- 28 ነጥብ

ቀጣይ መርሐግብር ?

ማክሰኞ - አል ዌህዳ ከ አል ነስር

ረቡዕ - አል ኢቲፋቅ ከ አል ታዎን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


“ አላማችን አራት ውስጥ መጨረስ ነው “ ማሬስካ

የሰማያዊዎቹ ዋና አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ የቡድናቸው የዚህ አመት አላማ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ ቦታ ማግኘት መሆኑን ገልጸዋል።

“ አብዛኛውን የውድድር ዘመን አራት ውስጥ ነበርን “  ያሉት ማሬስካ ስለዚህ በቀሪ አስራ ሶስት ጨዋታዎች አላማችን አራት ውስጥ መጨረስ ነው።“ ብለዋል።

“ እዚህ ያለሁት ጨዋታዎች ለማሸነፍ እና ቡድኑን የዋንጫ ተፎካካሪ ለማድረግ ነው ከጅምሩ ሀሳቤ ቡድኑን ትልቅ ቦታ ማስቀመጥ ነው።“ ማሬስካ

ሰማያዊዎቹ በሊጉ አርባ ሶስት ነጥቦችን በመሰብሰብ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠው ይገኛሉ።

እንዲሁም በአውሮፓ ኮንፈረንስ ሊግ ምንም ጨዋታ ያልተሸነፉ ሲሆን በጥሎ ማለፉ ከዴንማርኩ ክለብ ኮቤንሀቨን ጋር ተደልድለዋል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


የመልስ ጨዋታው በሜዳችን አሸንፈን እናልፋለን “ ሎዛ አበራ

⏩ “ ጥቃቅን ስህተት እንድንሸነፍ አድርጎናል “ ዮሴፍ ገብረወልድ

የሉሲዎቹ አምበል ሎዛ አበራ ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ በሜዳው አሸንፎ የማለፍ አቅም እንዳለው ከጨዋታው በኋላ ተናግራለች።

“ ጨዋታውን ተሸንፈናል ነገር ግን የመጨረሻ አይደለም “ ያለችው ሎዛ “  የመልስ ጨዋታው በሜዳችን ነው አሸንፈን እናልፋለን “ ስትል ተደምጣለች።

“ ዩጋንዳ ጠንካራ ናቸው ነገር ግን እኛ አቅሙ አለን የመልሱን ጨዋታ አሸንፈን ወደ ቀጣዩ ዙር እንደምናልፍ ሙሉ ተስፋ አለኝ “ ሎዛ አበራ

ሎዛ አበራ አክላም " ደጋፊው ላደረገልን ድጋፍ እናመሰግናለን “ ስትል ለመልሱ ጨዋታ ሁሉም ሰው ጠንካራ ድጋፍ ያድርግልን ስትል ጠይቃለች።

የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ዮሴፍ ገብረወልድ በበኩላቸው “ ጨዋታው በጣም አሪፍ ነበር ጥቃቅን ስህተት ነው እንድንሸነፍ ያደረገን “ ሲሉ ተናግረዋል።

አሰልጣኙ አክለውም “ በቀጣይ የዛሬውን ስህተት አርመን ለማሸነፍ ወደ ሜዳ እንገባለን " ብለዋል።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


WANAW SPORT WEAR dan repost
#Wanaw_x_Dessie_FC
የካቲት 15 በጣም ታላቅ ቀን ነው...ታዲያ እርሶስ ዝግጁ ነዎት በዚህ ታላቅ በደስታ እና ፌሽታ የተሞላ ቀን ለመታደም ይህን በማድረግ ብቻ በነጻ መታደም የታሪክ ተቋዳሽ መሆን ይችላሉ!

የዚህን ጥያቄ መልስ ኮመንት ላይ ያስቀምጡ!
ዋናው ምን ማለት ነው ለእርሶ በአንድ ቃል?
✅ለ5ሰው ይህን ፖስት ያጋሩ
✅የዋናውን ቴለግራም ገፅ መከተል https://t.me/wanawsportwear
ብዙ ላይክ ላገኙ ለ5 ሰዎች የምንሸልም ይሆናል ‼️

🛒 ለመግዛት አዲስ አበባ
📍አድስ አበባ - 22 ማዞሪያ ኖሃ ሪልስቴት 11ኛ  ወለል ግዕዝ  ስቲዲዮ ላይ
📞ኤርሚያስ - +251914414001
📞አቶ እያሱ - +251910332331

🛒 ለመግዛት ደሴ
📍ሸል ~ ቢኒ  ፑልና የስፖርት ትጥቅ መደብር
📍በፒያሳ- ሳንቾ ስፖርት ትጥቅ መሸጫ
📍ፈሲካ ሆቴል  ከፍ ብሎ  -2H  Gym
📍ወሎ ባህል አምባ ~ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ቢሮ

📞 ለበለጠ መረጃ
+251972425242
+251918350126 ላይ ይደውሉ

✨ዋናው ስፖርትም የዚህ ታላቅ ዝግጅት የመጀመሪያ ደረጃ ስፖንሰር ስለሆነ ክብር ይሰማዋል! ✨

🔗 ማህበራዊ ገጾቻችን🔗
Instagram|Facebook |TikTok |X|Youtube
በኩሩ አፍሪካውያን የተመረተ
⭐️ዋናው ወደፊት⏩⏩⏩


ፍቅር  ከቅመም ጋር! 🥰

💨⚡️ለብዙ ሰአት ከምትወዱት ጋር እንድታወሩ የሚያስችላችሁን 3000 mah የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡️
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#SafaricomEthiopia


ሀላንድ ለሊቨርፑል ጨዋታ ይደርሳል ?

የማንችስተር ሲቲው የፊት መስመር ተጨዋች ኤርሊንግ ሀላንድ ለሊቨርፑል ጨዋታ መድረሱ እስካሁን አለመታወቁን አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ተናግረዋል።

" በጨዋታው መድረሱን እስካሁን አላውቅም " ያሉት ፔፕ ጋርዲዮላ ነገ አይተነው የምንወስን ይሆናል እስካሁን ልምምድ አልሰራንም ብለዋል።

በሌላ በኩል ጆን ስቶንስ እና ማኑኤል አካንጂ በጉዳት ለረጅም ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቁ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አረጋግጠዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ሉሲዎቹ ሽንፈት አስተናግደዋል !

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ አቻው ጋር ያደረገውን የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ ተሸንፏል።

ሉሱዎቹ ከሜዳቸው ውጪ ያደረጉትን የመጀመሪያ ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት ተረተዋል።

ብሔራዊ ቡድኑ ከ 90ኛው ደቂቃ በኋላ በተቆጠረበት ሁለት ግብ ሊሸነፍ ችሏል።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች የመልስ ጨዋታ በሚቀጥለው ሳምንት ረቡዕ በአዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚካሄድ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


90+3'

ዩጋንዳ 2 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


90'

ዩጋንዳ 1 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


83 '

ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


68 '

ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


56 '

ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


እረፍት

ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


34 '

ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


13 '

ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


ተጀመረ | ዩጋንዳ 0 - 0 ኢትዮጵያ

ጨዋታውን ለመከታተል :- https://www.youtube.com/live/Ju99OKz6SCI?si=C9Rpo1_WeesLkwmz

@tikvahethsport @kidusyoftahe


የዩሮፓ ሊግ ተጋጣሚዎች ተለይተው ታውቀዋል !

የዩሮፓ ሊግ አስራ ስድስቱን የተቀላቀሉ ክለቦች የጥሎ ማለፍ ተጋጣሚዎቻቸውን ከደቂቃዎች በፊት በወጣ የእጣ ማውጣት ስነስርዓት አውቀዋል።

በዚህም መሰረት :-

- ማንችስተር ዩናይትድ ከ ሪያል ሶሴዳድ

- አልክማር ከ ቶተንሀም

- አትሌቲክ ቢልባኦ ከ ሮማ

- ፌነርባቼ ከ ሬንጀርስ

- FCSB ከ ሊዮን

- አያክስ ከ ፍራንክፈርት

- ቦዶ/ጂልምት ከ ኦሎምፒያኮስ

- ቪክቶሪያ ፕሌዘን ከ ላዝዮ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe


የጨዋታ አሰላለፍ !

10፡00 ዩጋንዳ ከ ኢትዮጵያ

@tikvahethsport @kidusyoftahe


#TeamEthiopia 🇪🇹

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከዩጋንዳ አቻው ጋር ለሚያደርገው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ መርሐ ግብር ጨዋታው የሚደረግበት ስታዲየም ደርሷል።

ሉሲዎቹ የመጀመሪያውን ጨዋታ ከሰዓታት በኋላ 10:00 ሰዓት ላይ በ ናኪቭቡ ሀምዝ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

@Tikvahethsport       @kidusyoftahe


የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ምን ይመስላሉ ?

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ተጋጣሚዎች ከደቂቃዎች በፊት በወጣ እጣ ማውጣት ስነስርአት ተለይተዋል ታውቀዋል።

በሩብ ፍፃሜው እናማን ይገናኛሉ ?

- የሪያል ማድሪድ እና አትሌቲኮ ማድሪድ አሸናፊ ከ አርሰናል እና ፒኤስቪ አሸናፊ ጋር

- የሊቨርፑል እና ፒኤስጂ አሸናፊ ከ ከክለብ ብሩጅ እና አስቶን ቪላ አሸናፊ

- የባየር ሌቨርኩሰን እና ባየር ሙኒክ አሸናፊ ከ ፊኖርድ እና ኢንተር ሚላን አሸናፊ ጋር

- የዶርትመንድ እና ሊል አሸናፊ ከባርሴሎና እና ቤኔፊካ አሸናፊ በሩብ ፍፃሜው የሚገናኙ ይሆናል።

@tikvahethsport            @kidusyoftahe

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.