በፀጥታ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ ከ
7.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው አልተመለሱም፡፡ - የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)
በባሕር ዳር በመካሔድ ላይ በሚገኘው የአማራ ክልል የትምህርት ንቅናቄ መድረክ ላይ የተገኙ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)፤ በፀጥታ ችግር ምክንያት በኢትዮጵያ ከ
7.2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳልተመለሱ ተናግረዋል።
በአማራ ክልልሉ በዘንድሮው የትምህርት ዘመን
7 ሚሊዮን ተማሪዎችን መዝግቦ ለማስተማር ቢታቀድም፤ በፀጥታ ችግር ምክንያት የተመዘገቡት ተማሪዎች
2.8 ሚሊየን ብቻ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
ችግሩን ለመቅረፍ በትምህርት ዘመኑ በሁለት ዙር በተደረጉ ኢ-መደበኛ ምዝገባ
76 ሺህ ተማሪዎች ብቻ መመዝገባቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ገልፀዋል።
መድረኩ በክልሉ የትምህርት ዘርፍ በደረሰው ጉዳት ላይ በመምከር ቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ ይጠበቃል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ✅
✅ ተጨማሪ ትምህርታዊ መረጃ ለማግኘት ቻናላችን ይቀላቀሉ
🔻
https://t.me/Tmhrt_Ministers🔻
https://t.me/Tmhrt_Ministers