Postlar filtri


ቀድሞ የሚሞላው ስንት ቀጥር ነው?






ባለፈው ቅዳሜ ምሽት በጥይት ተደብድበው የተገደሉት የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ ግድያቸው የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎችን እና የህክምናውን ማኅበረሰብ አስደንግጧል።
"በስንት ዘመን አንዴ የሚፈጠር ልጅ ነው" ሲሉ ዶ/ር አንዱዓለምን የሚገልፆቸው አብሮ አደጋቸው እና የሙያ አጋራቸው፤ ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ ሦስት ዩኒቨርስቲዎችን ባዳረሰው የሕክምና ትምህርታቸው ተሸላሚ እንደነበሩ ያነሳሉ።
"በዘመን እና በጊዜ መሀል ብቅ ከሚሉ ዓለም አቀፍ ጭንቅላቶች አንዱ ነው" ሲሉ የሚገልፆቸው ሌላ የቅርብ ጓደኛቸው፤ ምድር ላይ ከኖሩበት 37 ዓመታት 26ቱን ትምህርት ላይ ማሳለፋቸውን ገልፀዋል።
ቢቢሲ ያነጋገራቸው የዶ/ር አንዱዓለም ወዳጆች እና ባልደረቦች ከግላዊ ሰብዕናቸው ጀምሮ አንቱታን ያተረፉ ሐኪም እንደሆኑ ይመሰክራሉ።
"ሕክምና ማንን ይመስላል ከተባለ ዶ/ር አንዱዓለምን ነው የሚመስለው" ሲሉም የሙያቸው ቁንጮ እንደሆኑ የሚያሰምሩ አንድ አብሮ አደጋቸው እና የሙያ አጋራቸው፤ በሁሉም ዘርፍ የተካኑ ነበር ይላሉ።
"ክፉ የማይወጣው፤ ታካሚዎቹን በሙሉ በእንክብካቤ የሚያክም" ሲሉ ሰብዓዊነታቸውን የሚገልፁት ወዳጃቸው "ታካሚዎችን በመንከባከብ፤ በማከም ብቻ ሳይሆን አንድ ሐኪም ከዕውቀት ባለፈ ታካሚዎችን የሚይዝበት መንገድ ምን ይመስላል ከተባለ ዶ/ር አንዱዓለምን ነው የሚመስለው" ብለዋል።
ዶ/ር እንዱዓለም ዳኜ በኢትዮጵያ የላቀ የካንሰር ቀዶ ሕክምና ማዕከል ማቋቋም ህልማቸው እንደነበር የጥበበ ጊዮን ሆስፒታል ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር የሺጌታ ገላው ተናግረዋል።
በካንሰር ለሚሰቃዩ ሕሙማን "ጥራት ያለው ሕክምና ከሰብዓዊ ግልጋሎት ጋር" መስጠት የሚችል ማዕከል በማቋቋም ከሕክምና ባለፈ ለታካሚዎች እና ለቤተሰቦቻቸው ተስፋ፣ ድጋፍ እና ሰብዓዊ ክብር እንዲያገኙ ሩቅ አልመው በቅርብ መቅረታቸውን ጠቁመዋል።
"ካለው ሰብዕና፣ ከሚሰጠው አገልግሎት እና ካለው ተቀባይነት አንፃር" ግድያው እንደረበሻቸው ያልደበቁ ሌላ ባልደረባቸው፤ ግድያውን "የሙያን ድንበር የጣሰ" ብለውታል።
"ከባህሪ እስከ እውቀት" ተክነዋል የተባሉት ሐኪም ቅዳሜ ጥር 24/2017 ዓ.ም. ከባሕር ዳር ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ ቆሼ በተባለ አካባቢ ደረታቸውን በጥይት ተመተው ሕይወታቸው ያለፈ ሲሆን፤ ግድያው ከፍተኛ ድንጋጤን ፈጥሯል።
"[ሞትን] እሱ ላይ የምጠብቀው አልነበረም። ምናልባት ብዙዎቻችን ካለቅን በኋላ፤ መጨረሻ ላይ ለሞት ይታጫል ብለን የምናስበው ሰው በእንደዚህ ዓይነት አደጋ መሞቱ. . ." አስደንጋጭ መሆኑን ተናግረዋል።
ዶ/ር አንዱዓለም በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ስር የሚገኘው ጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የጉበት፣ የቆሽት ሰብ እና የሃሞት ከረጢት ስፔሻሊት ሐኪም፣ ተመራማሪ እንዲሁም መምህር ነበሩ።
በዩኒቨርስቲው ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር አንዷለም ዳኜ የጉበት፣ የሀሞት ከረጢት እና የቆሽት ሰብ ስፔሻላይዜሽን ትምሕርታቸውን ባለፈው ዓመት ነበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቁት።
በባሕር ዳር ከተማ በትርፍ ሰዓት ከሚሠሩበት አፊላስ ሆስፒታል ሥራቸውን ጨርሰው ከከተማ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው (የሆስፒታሉ ባለሞያዎች መኖሪያ) እየተመለሱ ሳለ ነበር አመሻሽ 12፡30 አካባቢ የተገደሉት።

ዶ/ር አንዱዓለም ከመገደላቸው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ሌላ ሐኪም ተመሳሳይ ጥቃት ተፈጽሞባቸው ማምለጣቸውን ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የታጠቀ እና "ሲቪል" የለበሰ ግለሰብ ወደ መንገድ ገብቶ ሐኪሙን ሊያስቆማቸው ሲሞክር በድንጋጤ ማምለጣቸውን አንድ የሙያ አጋራቸው ተናግረዋል።
"አንገቱን ቀርቅሮ ነዳጁን ተጭኖ መኪናዋን ነዳት። መኪናዋ በሦስት ጥይት ተመታች። እንደ አጋጣሚ ሆኖ [ሐኪሙ] አልተመታም። እንደዚያ ሆኖ አመለጠ" ብለዋል።
ይህ በሆነ በደቂቃዎች ልዩነት አካባቢው ላይ የደረሱት ዶ/ር አንዱዓለም ማንነታው ባልታወቁ ታጣቂዎች እንደተገደሉ የልጅነት ጓደኛቸው እና የሥራ ባልደረባቸው ለቢቢሲ ገልፀዋል።
"የቤት መኪና ይዞ የሚንቀሳቀስ ማንም የለም። በዚያች መስመር የቤት መኪና ይዘው የሚሄዱት ሐኪሞች ናቸው" የሚሉት ግለሰቡ፤ ጥቃቱ ግን ዝርፊያ እንዳልነበር ተናግረዋል።
"የተወሰደ ነገር የለም። ስልኩም እዚያው ነው የተገኘው። ምንም የተዘረፈ ነገር የለም" ያሉት የሟች ጓደኛ፤ ጥቃቱ ዶ/ር አንዱዓለም ላይ ያነጣጠረ ነው ለማለት እንደሚቸገሩ ጠቁመዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ ሥራ ኃላፊ ዶ/ር አንዱዓለም ያሽከረክሩት የነበረው መኪና እና ንብረታቸው ባለመዘረፉ ጥቃቱ እሳቸው ላይ ያነጣጠረ ነው ብለው እንደሚያምኑ ለቢቢሲ ገልፀዋል።
'ግድያው የተቀነባበረ ነው' ብለው የሚያምኑት የሥራ ኃላፊው "ቀጥታ ረሽነውት ነው የሄዱት። ሞባይሉ አልተነካ፤ መኪናው አልተነካ፤ ጥለውት ነው የሄዱት" በማለት ግድያው ተራ ግድያ አይደለም ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።
ቢቢሲ ከዚህ ቀደም የሆስፒታሉ ባለሙያዎች ላይ በሚደርሱ ተደጋጋሚ ጥቃቶች፣ ዝርፊያ እና ዛቻ "የደኅንነት ዋስትና" በመጠየቅ ለቀናት ሥራ እንዳቆሙ መዘገቡ ይታወሳል።
ከሳምንታት በፊትም የሆስፒታሉ የጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ ሆስፒታሉ ውስጥ መገደላቸውን ባለሙያዎቹ ተናግረዋል።
ለሁለተኛ ጊዜ የሆነው በዶ/ር አንዱዓለም ላይ የተፈጸመው ግድያ በሕክምና ማኅበረሰቡ ከፍተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ እንደፈጠረ ባለሙያዎች ገልጸዋል።
"የሚችል ሰው ጓዙን ጠቅልሎ ከዚያ ጊቢ ለመውጣት እያሰበ ነው። ለመሥራት ምንም አይነት ዋስትና የለም። የሆነ ነገር ሲፈፀምም የሚደርስ አካል የለም። ከተፈጸመ በኋላም አጣርቶ ፍትሕ የሚሰጥ የለም። በመሀል የሕክምና ባለሙያው ነው እየተጎዳ ያለው" በማለት አንድ ሐኪም ድባቡን ተናግረዋል።
ሌላ የዩኒቨርስቲው ሠራተኛ በበኩላቸው "ተረጋግተው የሕክምና አገልግሎት እንዳይሰጡ እየተደረገ ነው" ሲሉ በሆስፒታሉ ባለሙያዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ጥቃት ውጤት ተናግረዋል።
በአማራ ክልል ያለው ግጭት እና የፀጥታ ሁኔታ ዳፋ ተደርጎ የታው የዶ/ር አንዱዓለም ግድያ፤ የክልሉ ነባራዊ ሁኔታ ለሕክምና ባለሙያዎች መጠቃት "ክፍተት" እንደፈጠረ አንድ ሐኪም ጠቁመዋል።
ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት የሆኑት ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜ የቀብር ሥነ ሥርዓት እሁድ ጥር 25/2017 ዓ.ም. በባሕር ዳር መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን ተፈፅሟል።
እስካሁን ከዶክተሩ ግድያ ጋር በተያያዘ የተጠረጠረም ሆነ የተያዘ ሰው የለም። የባሕር ዳር ከተማ ፖሊስ ግድያው "ባልታወቁ ኃይሎች" እንደተፈፀመ በመግለጽ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን አሳውቋል።

Via BBC Amharic




በሜታ ወልቂጤ በአንዲት ታዳጊ ህጻን ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሜታ ወልቂጤ ወረዳ አንዲት ህጻን ከቤት ተወስዳ ከተደፈረች በኋላ ተገድላ መገኘቷ ቁጣ ቀስቅሷል። “በኛ የደረሰ በማንም አይድረስ” የሚሉት የተጎጂ ቤተሰብ በታዳጊ ልጃቸው ላይ ለደረሰው ቀሰቃቂ ወንጀል ፍትህ እንሻለለን ብለዋል።

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች፡፡ የስምንት (8) ዓመት ታዳጊ ህጻን ናት፡፡ የአንደኛ ክፍል ተማሪ፡፡ በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንት ባለፈ ረቡዕ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ከትምህርት ቤት ተመልሳ ምሳ እንደበላች ከመኖሪያ ቤቷ የደረሰችበት ሳይታወቅ ቀርቷል ፡፡ በዕለቱ ፍለጋ የወጣው ቤተሰብ ታዳጊዋን ከነሙሉ ጤንነትና በህይወት ለማግኘት ግን አልታደሉም፡፡

ሮጣ ያልጠገበች ታዳጊዋ ለአዕምሮም በሚከብድ ሁኔታ ከተደፈረች በኋላ “እንዳትናገር በሚል” ከመኖሪያ ቤታቸው ጀርባ በቅርብ ርቀት ላይ ህይወቷ አልፎ መገኘቱን አንድ የቤተሰቧ አባል ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል። ታዳጊዋ ከተገደለች በኋላ ተሰቅላ መገኘቷን የገለጹት የቤተሰብ አባሉ “ጫማዋን ያወለቁባትና የሰቀሏት ቦታ አንድ አይደለም የ50 ሜትር ገደማ ርቀት አለው” ብለዋል።

በወረዳው የኤላ ከተማ በታዳጊዋ ላይ የተፈጸመው ጥቃት አባት የመንግስት ሰራተኛ መሆናቸው እና በስራ ቦታ መሆናቸው እንዲሁም እናት የ2 ወር እመጫት በመሆናቸው አጋጣሚውን በመጠቀም እንደነበር የቤተሰቡ አባል ተናግረዋል።...

Via DW


ማህበራዊ ሚድያ ላይ ትችት በማቅረብ የሚታወቀው ሰመረ ካሳዬ (ሰመረ ባርያው) ታሰረ

በቅርብ አመታት ማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚለቀቁ ቪድዮዎችን መነሻ በማድረግ ትችት እና ሽሙጥ በማቅረብ የሚታወቀው ሰመረ ካሳዬ (ሰመረ ባርያው) በትናንትናው እለት በፀጥታ አካላት አዲስ አበባ ውስጥ ተይዞ እንደታሰረ ታውቋል።

ሰመረ ትናንት እኩለ ቀን ገደማ ምሳ ከጓደኞቹ ጋር በልቶ እየወጣ በነበረበት ወቅት በፀጥታ አካላት ተይዞ ተወስዷል።

ሰመረ ብዙውን ግዜ ትችት የሚያቀርበው በማህበረሰቡ ዘንድ ጥያቄ በሚያስነሱ እና አነጋጋሪ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ሆኖ ሳለ ለእስር መዳረጉ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ስራዎቹን በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ሲያቀርብ እንደነበር ይታወሳል።

Via መሰረት ሚዲያ


















Please የWollo Addis ቤተሰቦች ይህን የተቀደሰ የቢዝነስ አይዲያ Bejai Nerash Naiker ፓስት ስር Suleiman Muhye በሚል ስም የተቀመጠ Commente ላይ እየገባችሁ Like በማድረግ አሸናፊ እንሁን" የዛሬን ልናስቸግራችሁ ወደድን ከጎናችን ሁኑ🙏
https://web.facebook.com/vijai.naiker/posts/9093745984036262?comment_id=949844830046275¬if_id=1737130755813937¬if_t=feedback_reaction_generic&ref=notif

🛑የዲርጂት ስም፦ Digitals Discovery One Member PLC
👉ሀሳብ፦ የዲጂታልስ ጤና(Digitals Health)ፕላትፎርም ማዘጋጀት
🔖በራሱ ፕላትፎርምና በተለያዩ የዲጂታል ሚዲያ አማራጮች በተለይ በውጭው ዓለም በስደት ለሚገኙት ትውልደ ኢትዮጵያዊያንና በሀገራችንም በአካል ተገኝተው አገልግሎት ማግኘት ለማይችሉት በተመጣጣኝ የህክምናና የማማከር አገልግሎት እንዲያገኙ ለማስቻል ይረዳል።
🔖በዚህም ላይ ከብዙ የጤና ሴክተሮች ጋር ለምሳሌ ከነ Dr Feysel Dermatology Speciality Clinic, ከ Lucy MultiSpeciality የማርኬቲንግ ባለሙያዎችና ሀኪሞች ጋር ባደረኩት ውይይት ለሀገርም ለህዝቡም አዋጭ መሆኑን አረጋግጫለሁ💚
www.digitalsdiscovery.com
+251946960000






ሎሬት “የትነበርሽ ንጉሴ” በአንድ ወቅት ይህን አለች



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.