💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


🇪🇹 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  አስተምህሮ ና ስርአትን የጠበቁ ቆየት ያሉና አዳዲስ👇👇
👏 የቸብቸቦ መዝሙራት 🎻 የበገና መዝሙራት  
👑 የቅዱሳ መዝሙራት ⛪️ የንግስ መዝሙራት
💍 የሠርግ መዝሙራት 🌦 ወቅታዊ መዝሙራት መገኛ

📢ለ ማስታወቂያ ስራዎች @Miki_Mako

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


⁉️በሙስሊሙ ወገን ብዙዎች ስለ ክርስትና ይፅፋሉ ስለ ክርስትናም ይነቅፋሉ።

ብዙዎች ከቤተክርስትያን እየወጡም ይገኛሉ።ክርስቶስ አንዲቱን በግ ሊፈልግ መጥቶዋል እኛም ከሙስሊም ለሚወረወሩ ጥያቄዎችን ከበቂ መልስ ጋር መጥተናል ቻናሉን ይቀላቀሉት
       👇👇👇
https://t.me/+Swgevc_okHzlBREl
https://t.me/+Swgevc_okHzlBREl




✞መቼ ነው ጌታ✞

መቼ ነው ጌታ መቼ ነው
ልቤ ለቃልህ የሚገዛው
መቼ ነው ጌታ መቼ ነው
አንተን በፍርሃት የማመልከው

ያ የቀደመው ኑሮ ለቤትህ ያለኝ ናፍቆት
ዛሬ ከልቤ ጠፍቷል አንቆታል የዓለም ፍትወት
አመጸኛ ሆኛለሁ አንዷን መክሊት ቀብሬ
እንዳነበረ ሆኗል ያ የቀድሞ ፍቅሬ
    አምልኮቴ እንዲሆን በእውነት እና በመንፈስ
    እርዳኝ አግዘኝ አባቴ ወደ ኋላ አልመለስ
       አዝ= = = = =
ቃልህን መመስከሬ በአደባባይ መጥራቴ
እኔን መቼ ሰበረኝ ጠዋት ማታ ስግደቴ
በበረሃ እንደሚዞር እንደተጠማ ዋልያ
ናፍቆቴ ጥማት ሆኗል ለማረፍ በአንተ ጥላ
    አምልኮቴ እንዲሆን በእውነት እና በመንፈስ
    እርዳኝ አግዘኝ አባቴ ወደ ኋላ አልመለስ
       አዝ= = = = =
በክፉ ሰዎች ምክር በአመጸኞች ጎዳና
በኃጢአተኞች ወንበር ተመኝቼ ልጽናና
ነፋስ እንደሚወስደው እንደሚበተን ትቢያ
መደፊያ አጣሁኝ ለነፍሴ ማሳረፊያ
    አምልኮቴ እንዲሆን በእውነት እና በመንፈስ
    እርዳኝ አግዘኝ አባቴ ወደ ኋላ አልመለስ

        መዝሙር
     መቅደስ ማርዬ

"እግዚአብሔር ጻድቅንና ኅጥእን ይመረምራል፤ ዓመፃን የወደዳት ግን ነፍሱን ጠልቶአል።"
                   መዝ፲፩፥፭
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ሁሉም ያልፋል✞

ሁሉም ያልፋል እግዚአብሔር ያሳልፋል(፪)
ልጆቹን መቼ ይረሳል

ብርሃን ይመጣል ጨለማው ተገፎ
ደስታ ይሆናል መከራው አልፎ
/የምስራች ቃል ይሞላል በአፋችን
ሐዘናችን ጠፍቶ ይፈካል ፊታችን/(፪)
አዝ= = = = =
በትር ነው ምርኩዝ እሱን ላመኑበት
ባህር ውቅያኖሱን ከፍለው የሚያልፉበት
/በእሳት መካከል በግፍ ለተጣሉ
ውሃ አየሆናቸው በድል ይወጣሉ/(፪)
       አዝ= = = = =
ማስተዋል ጥሩ ነው ትዕዛዛቱን ማክበር
ያኖራል በሕይወት በሰማይ በምድር
/የማያልፍ ቀን የለም ታሪክ የማይሆን
በአምላክ አንድ ቀን ነው አንድ ሺ ዘመን/(፪)
       አዝ= = = = =
ይቅርታ እንዲሰጠን በደልን ሳይቆጥር
ማረን እንበለው ስለሆነ ፍቅር
/ነገ ቀን ሲመጣ ብርሀኑ ሲያበራ
ፊታችን እንዳይዞር ወደ ክፉ ስራ/(፪)

             መዝሙር
   ዲያቆን አቤል መክብብ

"እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፥"
               መዝሙር ፻፭፥፩
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞አምላኬ እግዚአብሔር✞

እግዚአብሔር አይተወኝም
ወድቄም አልቀርም

ለመንገዴ ብርሃን ለእግሬ መብራት
እረኛዬ እርሱ ነው አምላክ ምህረት
ጠርቶ ያሣደረኝ በለመለመ መስክ
አምላኬ እግዚአብሔር መንግሥቱ ትባረክ
       አዝ= = = = =
በእረፍት ውሃ ዘንድ ነፍሴን የሚመራ
ያድነኛል እርሱ ከጭንቅ ከመከራ
መታመኛዬ ነው የሚያሣጣኝ የለም
እርሱ ከእኔ ጋር ነው ወድቄ አልቀርም
       አዝ= = = = =
በትርና ምርኩዙ እኔን ያፅናኑኛል
ምህረት ቸርነቱ ሁሌ ይከተሉኛል
ኃጢአት ከፍቶብኝ ሰዎች ቢጠሉኝም
አምላኬ አይተወኝም ወድቄ አልቀርም
    
     መዝሙር
  ተስፋዬ ኢዶ
መዝሙር ፳፫፥፩-፬
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ንስሐ እንግባ✞

ንስሐ እንግባ(፪)
ንስሐ እንግባ  ሲኦል እንዳንገባ

የበደልነው በደል ያጠፋነው ጥፋት(፪)
ይወገድልናል ንስሐ በመግባት
ተመርምሮ እራስን ነግሮ ለካህኑ(፪)
ነገ ዛሬ ሳንል መቅረብ አሁኑኑ
       አዝ= = = = =
ለኛ የነገረን ጌታችን በወንጌል (፪)
ይቅር ብዬሀለው ከእንግዲህ አትበድል
ይህንኑ ቃሉን አምነን ብንቀበል(፪)
ይሰጠናል እና ሰማያዊ አክሊል
       አዝ= = = = =
ሞት እንደው አይቀርም ዙሮ ተዟዙሮ(፪)
ሲመጣ መጓዝ ነው የለውም ቀጠሮ
እድፋችን ይታጠብ በንስሐ ውሃ(፪)
ንዑ እና  ሑሩ ሲል ለመዳን አሜሃ
                    
          ሊቀ መዘምራን
     ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ

"መንግስተ ሰማያት ቀርባለችና
ንስሐ ግቡ"

                   ማቴ ፫፥፪
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


መቼስ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ የ ኖት ኮይንን ዜና ሰምታችሁ ምነው ታብ ታብ ባደረግኩኝ እንዳላችሁ አልጠራጠርም:: ያኔ በሚሊዮን ቤት ታብ ታብ አድርገን የሰበሰብንውን ኮይን የመጨረሻዎቹን ሶስት ዜሮዎችን ዲጂት አጥፍቶ በኖት አስቀምጦልናል:: ማለትም ያኔ 5.000.000 ኮይን ሰብስበን ከነበር ሶስቱን ዜሮዎች አጥፍቶ አሁን ላይ በ 5000not አስቀምጦልናል::
መነሻ ተብሎ የታሰበው የ 1$not ዋጋ 0.012 Ton ነው:: ያ ማለት ደግሞ

5000 ኖት * 0.012 Ton = 60 Ton ይሆናል ማለት ነው:: 1 Ton ደግሞ 7 ዶላር ነው :: እንግዲህ ወደ ቶን የቀየረላችሁን Amount  በ 7 አባዙት😋 ወደ ዶላር መቀየር ምትችሉት April 20 ነው::

   እና በ ኖት ኮይን የተቆጫችሁ በ Tap swap ራሳችሁን ካሱት:: ልክ እንደ not coin ታብ ታብ በማድረግ ኮይን መሰብሰብ ነው.. ከ ኖት ኮይን በፊት የነበረ የኮይን ሲስተም ስለሆነ እና ማብቂያው  እየተቃረበ ስለሆነ እታች በማስቀምጥላችሁ ሊንክ ቴሌግራም ላይ እየገባችሁ ታብ ታብ በማድረግ ኮይን ሰብስቡ :: ባይሳካም ምንም ምትከስሩት ነገር አይኖርም :: እውን ሲሆን ግን አስቡት😋

https://t.me/tapswap_bot?start=r_259635251

🎁 +2.5k Shares as a first-time gift


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በአንድነቱ በሦስትነቱ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ የሚመሰገን እግዚአብሔር በባሕሪው ንጉሥ ሲሆን እንደ ባሪያ ሆኖ ትሕትናውን አሳየን  ስለዚህ ጌታ ሆይ እናመሰግንሃለን ።

     ✞ሥላሴ አምባዬ✞

ሥላሴ አምላኬ ብዬ እዘምራለሁ
ሥላሴ እምባዬ ብዬ እቀኛለሁ
ሰማይና ምድር ደመና ሳይቀሩ
አእዋፍ አዝርዕት በሱ ተፈጠሩ

ብርሃን ጨለማ እንዲሆን በተራ
በዓለሙ ሁሉ ፀሐይ እንዲያበራ
እንድትሰለጥን ጨረቃ በለሊት
ሥላሴ አስውቦ ፈጠረ ከዋክብት
       አዝ= = = = =
በእግር የሚሄዱ በክንፍ የሚበሩ
በምድር ላይ ያሉ በጥልቅ የሚኖሩ
በሥላሴ ዘንድ ውላቸው ታውቀዋል
በከሃሊነቱ ፍጥረት ተፈጥረዋል
       አዝ= = = = =
አስቀድሞ ያለ ዓለም ሳይፈጠር
ሥላሴ ነበረ ዘመን ሳይቆጠር
ዘመን አሳልፎ ዘመን የሚያመጣ
ልክፉው ለደጉ ፀሐይ የሚያወጣ

             መዝሙር
          አቤል ተስፋዬ

"የእግዚአብሔር ቸርነት ምድርን ሞላች
በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ
ሠራዊታቸውም ሁሉ በአፉ እስትንፋስ"


           መዝ ፴፫ ፥፭-፮
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ገብር ኄር✞

እግዚአብሔር የሰጠህ መክሊትህ የታለ
ድንገት ቢመጣብህ ምን ታሳየዋለህ
አንድ ከተሰጠው ያንን ከቀበረው
አንተ ከገብረ ሐካይ ብልጫህ ምንድን ነው

አደራ ጠባቂው የጸና በእምነቱ
ታማኙ ገብር ኄር ባለ አምስት መክሊቱ
ወጣ ወረደና ረርቶ አተረፈበት
ጌታው በመጣ ቀን በእጥፍ መለሰለት
    ወደ ደስታው ገባ ክብርን ተሸለመ
    በጥቂቱ ታምኖ በብዙ ተሾመ
       አዝ= = = = =
ሊሠራ እንዳቅሙ ሁለት የተሰጠው
ሌላ ሁለት አትርፎ ጌታውን ጠበቀው
ሊቆጣጠራቸው ዳግመኛ ሲመጣ
የመክሊቱን ዋጋ ከነትርፉ አመጣ
    ወደ ደስታው ገባ ክብርን ተሸለመ
    በጥቂቱ ታምኖ በብዙ ተሾመ
       አዝ= = = = =
አንድ መክሊት ብቻ የተሰጠው ሐካይ
ምድር ሥር ደበቀው አኖረበት ድንጋይ 
የአደራ መክሊቱን መቅበሩ ሳያንሰው
ጨካኝ ክፉ ብሎ ጌታውን ሰደበው
    መክሊቱን ተቀማ አሥር ላለው ሰጡት
    ለቅሶ ወዳለበት ጨለማ ስር ጣሉት

መዝሙር
ሲስተር ሕይወት ተፈሪ

ማቴ ፳፭፥፲፬-፴
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

መዝ፲፬፥፩-፭

✞የዳዊትን ገርነቱን✞

የጎልያድ ትምክህት
በዳዊት ወንጭፍ ተመታ
አንገቱን ቆርጦ አነሳው
የእግዚአብሔርን እጅ እረዳው
       አዝ= = = = =
ቀድሞ በነቢያት ትንቢት መነገሩ
ወልደ ዳዊት ተብለህ ስትገኝ ከዘሩ
ብዙ አንስቶችን በዙሪያው ሰብስቦ
ድንግሊቱን ዳዊት ሊያገኛት አስቦ
       አዝ= = = = =
ለጽዮን ሲዘምር ዳዊትን የናቀች
ሜሊኮል ንግሥቲቱ መካን ሆና ቀረች
የዋህ ስለሆነ ዳዊት በሕይወቱ
ከዙፋኑ ወርዶ ሰግዷል ለታቦቱ
       አዝ= = = = =
የዝሙት እንግዳ ቢመጣ ከቤቱ
ከዙፋኑ ቆሞ ከቤተ መንግሥቱ
መቶ በግ እያለው እንዳይጎድሉ ሳስቶ
አንዷን የኦሪዮን አስገባት ጎትቶ

ጸሐፌ ትዕዛዝ
  ዲያቆን ታዴዎስ ግርማ
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


የዐቢይ ጾም ፮ኛ ሳምንት #ዘገብር_ኄር #ሰንበት በቅዳሴ ጊዜ

   #ምንባባት
፪ጢሞ ም ፪÷፩-፲፯
፩ጴጥ ም ፭÷፩-፲፪
ግብ ሐዋ ም ፩÷፮-፱

    #ምስባክ
መዝ ፴፱÷፰
ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ
ወሕግከኒ በማዕከለ ከርሥየ
ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ
     #ትርጉም
አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ፥ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው።
በታላቅ ጉባኤ ጽድቅን አወራለሁ።

      #ወንጌል
የማቴዎስ ወንጌል ም ፳፭፥፲፬-፴፩
      #ቅዳሴ
ቅዳሴ ባስልዮስ

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


💛 የ መዝሙር ግጥሞች 💛 dan repost
​​"ጌታውን ደስ ያሰኘ ታማኝና ቸር አገልጋይ ማነው?"ቅዱስ ያሬድ

በዲያቆን ግዛው ቸኮል
መጋቢት ፴ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም

ክፍል ሁለት
በዚህ ዘመን ለምንኖር አገልጋዮች አገልግሎታችንን የሚያዳክሙ ነገሮች ምንድን ናቸው?

፩.የመንፈሳዊ ሕይወታችን መዛል፡-

መንፈሳዊ ዝለት በሁለት መንገድ ሊፈጠር ይችላል፡፡ አንደኛው ያለ አቅም የተጀመረን መንፈሳዊ ተግባር ቀስ በቀስ ማቋረጥና ወደቀድሞው ሥጋዊ ሕይወት መመለስ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ቀስ በቀስ ያደገን መንፈሳዊ ሕይወት የሚጠይቀውን መንፈሳዊ አኗኗር ከመሰልቸት የሚመጣ ነው፡፡

በሁለቱም መንገድ በሕይወቱ ወደኋላ የተመለሰ ሰው ለአገልግሎት (ለመታዘዝና ለመታመን) የነበረው ፍቅር ይቀንስና ሁልጊዜ መጸጸትን ብቻ ሥራው ያደርጋል፤ "የነበርኩ" ሕይወትንም ይለማመዳል፡፡

፪.ምቹ ሁኔታዎችን መሻት፡-

ሰዎችን መርጦ መታዘዝና ማገልገል ቀላል ነው፤ሰው ሲመቸው ማገልገል ሳይመቸው ከቤተክርስቲያን መቅረትንም ገንዘቡ ያደረጋል፡፡

ነገር ግን እስከ መጨረሻው ጸንቶ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ ደግሞ በየትኛውም ጊዜና ቦታ ሁሉ ሰማዕትነትን መክፈል ያስፈልጋል፡፡

ካልሆነ የአገልግሎትን ጣዕም አንረዳውም፡፡"በዝግታ ቆመህ በጊዜውም ያለጊዜውም ቃሉን ስበክ፤ በሁሉም እየታገሥህና እያስተማርህ፥ ገሥጽ፤ ዝለፍ፤ ፈጽመህ አጽናና፤" ያለውን የሐዋርያውን ቃል ማሰብ ጠቃሚ ነዉ፡፡ ፪ኛ ጢሞ. ፬፥፪

፫.ዓላማን መርሳት፡-

መታዘዝም ሆነ መታመን ትርጒም የሚኖረው በዓላማ ሲፈጸም ነው፡፡ ኃላፊነትን መርሳት ከመስመር ያርቀናልና ሁልጊዜ የመጣንበትን ዓላማ ማሰብ ተገቢ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ነገር ግን ከተመሠረተው በቀር ሌላ መሠረት ሊመሠርት የሚችል የለምብሎ እንደተናገረው መሰባሰባችንን ለሌላ ዓላማ መጠቀምም ሆነ ማሰብ ተገቢ አለመሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ፩ኛ ቆሮ. ፫፥፲፩

፬.ባላገለግልም እጸድቃለሁ ብሎ ማሰብ፡-

በእርግጥ ለጽድቅ የሚያበቃን የእግዚአብሔር ቸርነት እንጂ የእኛ በጎ ምግባር ብቻ እንዳልሆነ እናውቃለን፡፡ ነቢዩ ኤርምያስም ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምናበማለት ተናግሯል፡፡ ባላገለግልም እጸድቃለሁ ብሎ ማሰብ ራስ ወዳድነት ከመሆኑም በላይ ድርሻንም አለመገንዘብና አለማወቅም ጭምር ነው፡፡

ባለአንዱ መክሊት ድርሻውን ስላልተወጣ የተፈረደበት ለዚህ ነው፡፡ "በብዙ ድካምና መከራ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት እንገባ ዘንድ ይገባናል" በማለት መጽሐፍም ያስረዳናል፡፡
ሰቈ ኤ. ፫፥፳፪፣ ሐዋ ፲፬፥፳፪

በጎ አገልጋይ ለመሆን ምን እናድርግ?

፩. መታዘዝ፡-

የሰው ልጅ በፈጣሪው አርአያና አምሳል ሲፈጠር የሚያዝም የሚታዘዝም ሆኖ ነው፡፡

አገልግሎት (መንፈሳዊነት) መታዘዝ ነው ስንል እንደ ባለአምስቱና ባለሁለቱ አገልጋዮች ያለምንም ማጉረምረም ከኃጢአት በስተቀር ሁሉንም ተቀብሎ ማከናወን ማለት ነው፡፡

አብርሃም "ልጅህን ሠዋልኝ" የሚለውን የእግዚአብሔርን ጥያቄና ትእዛዝ የተቀበለው በጸጋም በደስታም ነው፡፡

ነቢያት፣ ሐዋርያት ኃላፊውን ዓለም በማይታየው ዓለም ለውጠው መንፈሳዊ ተልእኮን እንዲወጡ ለእግዚአብሔር ቃል ሲታዘዙ በደስታ ነበር፡፡ ስለዚህ እኛም የአባቶቻችንን መታዘዝ መታዘዛችን ልናደርግ ይገባናል፡፡

፪.በትጋት ማገልገል፡-

ከዘመነ አበው ጀምሮ የእግዚአብሔር ወዳጆች እየተባሉ የሚጠሩ ሁሉ የፍቅረ እግዚአብሔር መገለጫቸው ትጋታቸው ነበር፡፡

መንፈሳዊ ሕይወት ከትጋት ውጭ መለኪያ የለውም፡፡ ሐዋርያት ለስብከተ ወንጌል አገልግሎት የተመረጡት ከሥራ ቦታቸው ነው፡፡

ጌታችን ሲመርጣቸውም እጅግ በጣም ትጋትን ለሚጠይቅ ተልእኮ ነበር፡፡ ዋጋን ለመቀበል ከጠዋት እስከ ማታ በአገልግሎት መትጋት ያስፈልጋል፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞንም በምሳሌ "በሥራው ታካች የሚሆን የሀብት አጥፊ ወንድም ነው"በማለት ትጋት የመንፈሳዊ ዋጋ መጠበቂያ መሆኑን አስረድቷል፡፡
ማቴ. ፲፥፩-፲፬፣፳፥፩-፲፪፣ ምሳ.፲፰፥፱

፫. በተስፋ የተመላ ትጉህ አገልጋይ መሆን፡-

የሰው ልጅን በተለይም በመንፈሳዊ ሕይወት የሚመሩ የእግዚአብሔር ወዳጆችን ከሌላው ሥነ-ፍጥረታት የተለዩ የሚያደርጋቸው ተስፋ ነው፡፡

የተወለደው የማደግ ተስፋ፣ ያደገው የመኖር ተስፋ፣ በኃጢአት የወደቀው በንስሓ የመነሣት ተስፋ፣ ቤተክርስቲያንን የማገልገል ተስፋ፣ መንግሥተ ሰማያትን የመውረስ ተስፋ ለሰው ልጆች በተለይም ለእኛ ለክርስቲያኖች የተሰጠን ተስፋችን ነው፡፡

ነቢያትን በትንቢት ያጸናና መከራውን እንዲታገሡ ያደረጋቸው፣ ሐዋርያትን በሐዋርያነት ያጸናና በሰማዕትነት ያጠነከራቸው፣ ከዘመነ አበው እስከ ዕለተ ምጽአት ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር አስተሳስሮ የሚኖር ኅቡእ ሰንሰለት ተስፋ ነው፡፡አባቶቻችን "የሙታንንም መነሣት ተስፋ እናደርጋለን" ሆኖ መገኘት የግድ ነው፡፡

በአጠቃላይ እኛም ኦርቶዶክሳውያን በመንፈሳዊ አገልግሎት ነግደን እንድናተርፍበት ከጌታችን የተሰጠንን መክሊት በግዴልሽነት፣ በትዳር፣ በትምህርት እና በቦታ ርቀት ምክንያት አንዳችን ካንዳችን ባለመስማማት ለራሳችን ሰበብ እየፈጠርን እንደ ባለአንዱ አገልጋይ ከቀበርነው ቆይተናል፡፡

ጌታችንም የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት ስለማናውቅ ከቀበርንበት አውጥተን ልናተርፍበት ይገባናል።

"እነሆ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን ዛሬ ነው"እንዳለ ሐዋርያው አትርፎ መገኘት ለእኛ ለክርስቲያኖች የግድ ያስፈልገናል፡፡
፩ኛ ቆሮ. ፮፥፪

ሊቁ ቅዱስ ያሬድም "መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይረክቦ እግዚኡ በምግባረ ሠናይ፤ በጎ ሥራ እየሠራ ጌታው ያገኘው ቸርና ታማኝ አገልጋይ ማነው?"እንዳለ ታማኝነት እና መታዘዝ ከሌለን፣ ከመንፈሳዊ አገልግሎት ከራቅን፣ በጌታችንም ፊት መሾም መሸለም፣ ወደ ዘለዓለማዊ ደስታ መግባት አይኖረንም፡፡

ስለዚህ በተሰጠን ስጦታ፣ ሀብት፣ አቅም፣ ጊዜ፣ ቦታና ዕድሜ ሥጦታውን ለሰጠን እግዚአብሔር ታምነንና በአገልግሎት ጸንተን ወጥተው ወርደው አትርፈው ከተሾሙት ወገን እንዲደምረን አምላካችን እግዚአብሔር በቸርነቱ ይፍቀድልን፤
አሜን።

ቃለሕይወት ያሰማልን
~ተፈጸመ~
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯


✞የማይሻር ሥልጣን✞

የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው
የምሕረትን ጠል ከሰማይ ያወርዳል
ሕያው ቃልኪዳኑ ዓለምን ያድናል የአምላክ ባለሟል ዝናው የገዘፈ
በሰማያት መዝገብ ስሙ የተጻፈ

ቅሩበ ሥላሴ ርዕሰ ባሕታዊ ገብረ መንፈስቅዱስ ጻድቅ ሰማያዊ የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው
ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው


የኃጥአን ተስፋ ጌታ ያከበረው የነፍስ ደስታዋ ለአጋንንት ፍርሃት ነው
የጻድቃን ነቢያት የሐዋርያት ዘመድ
የሰው ልጆች ወዳጅ ከአምላክ የሚማልድ

ቅሩበ ሥላሴ ርዕሰ ባሕታዊ ገብረ መንፈስቅዱስ ጻድቅ ሰማያዊ የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው
ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው


የመላእክት ወዳጅ ዕጹብ ባሕታዊ
በተጋድሎ ጽናት ሆነ ሰማያዊ
የበረሃው መናኝ ወንጌልን የኖረ
ገብረ መንፈስቅዱስ ሰይጣን ያሳፈረ

ቅሩበ ሥላሴ ርዕሰ ባሕታዊ
ገብረ መንፈስቅዱስ ጻድቅ ሰማያዊ
የማይሻር ሥልጣን ከአምላክ የተሰጠው
ገብረ መንፈስቅዱስ መፍቀሬ አምላክ ነው


            መዝሙር
         ፍስሐጽዮን ካሳ

"የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው"
              ምሳ፲፥፱
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
@yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ወደ ማን እንሄዳለን✞

ከአንተ ወደ ማን ወደ የትስ እሄዳለሁ
ከአንተ ወደ ማን ወደ የትስ          እደርሳለሁ
ልኑር ከአንተ እለምንሃለሁ
ከአንተ ጋር ልኑር እማጸንሃለሁ

እንዳስለመድከኝ በሠርክ
ጠራኸኝ አዳም እያልክ
ተሸሽጌያለሁ ፈርቼ
የጸጋ ልብሴን አጥቼ
ከሰማይ መጣህ ፍለጋ
አባቴ አልፋ ዖሜጋ
እንደምትወደኝ በፍጹም
አምናለሁ ጌታ ዘለዓለም
    አዝ= = =
እየጎተቱህ በገመድ
ተሳለቁብህ በመንገድ
ለእኔ እንዲሆንልኝ ክብር
ተከተልካቸው በፍቅር
በጥፊ መትተውህ ሲያበቁ
ማን መታህ አሉ እየሳቁ
በቁስልህ ተፈውሻለሁ
ትዕግስህን እኔ አደንቃለሁ
      አዝ= = =
አምላኬ ሲያስሩህ በክፋት
ተፈታሁ እኔ ክእስራት
ልብስህን ሲገፉህ ያኔ
ጸጋ አለበስከኝ መድህኔ
ሞትን ገደልከው ስትሞት
ለእኔ ሆንክልኝ ሕይወት
ተጠማሁ ስትል ረካሁ
ዘመኔን ሁሉ ባረከው

        መዝሙር
ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

 "...ጌታ ሆይ፥ወደ ማን እንሄዳለን?..."
ዮሐ ፮፥፷፰
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✞ብጹዕ ውእቱ✞

ብጹዕ ውእቱ ዘገብረ ተዝካርከ ወዘጸሐፈ መጽሐፈ ገድልከ መጽሐፈ ገድል
አነ እሁቦ ሕይወተ ዘለዓለም ወ አወርሶ መንበረ ክብር ይቤሎ እግዚአብሔር ለያሬድ ካህን

ንዑድ ነው ክቡር ነው ያደረገ ተዝካርህን
የጻፈ ገድልህን ያጻፈ ገድልህን
እኔ እሰጠዋለሁ የዘላለም ሕይወትን አወርሰዋለሁ መንግስተ ሰማያትን ብሎታል እግዚአብሔር ለያሬድ ካህን

   ፦
መጋቢት አምስት ቀን የሊቁ ኢትዮጵያዊ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ልደቱ ቀን ነው።

╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ንዑኬ ጉባዔ ማኅበራ ለቤተክርስቲያን
እስመ ትስምዕዎ ለዮሐንስ ወንጌላዊ ክቡር

ዮሐንስ ታዖሎጎስ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ
ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ


  ✞ለወዳጅህ ያኔ✞

ለወዳጅህ ያኔ የተናገርከው ቃል
በማዕከለ ምድር ስቃይ ስትቀበል
እነኋት እናትህ ብለህ የሸለምከው
ዮሐንስ መስቀሉን በመከ በመከተሉ ነው

ወደ ቤቱ ይዟት በዚያን ሰዐት ሄደ
በጌታው መከራ ልቡ እየነደደ
ከእናቱ ጓዳ አንጥፎ ጎዝጉዞ
አገልግሏት ኖሯል በአምላክ በአምላኩ ታዞ


ጌታ የሚወደው የተባለለት ሰው
ማርያምን ሽልማት ጌታችን ከሰጠው
ይኄ ልጅሽ ነው ብሎ ዛሬ ሠጣት
ጌታ ቢፈቅድ ነው በእውነት በእውነት ያለ ሐሰት

ወደ ቤትህ ትግባ በረድኤት ማርያም
ነፍስህ እድታገኝ ፀጥታና ሰላም
ከረድኤት ቤትህ ተራቁቶ እዳይገኝ
ድንግል  ጓዳሕ ትግባ ጓዳሕ ትግባ ህይወትህን ትጎብኝ


ዮሐንስ መስቀሉን ስለተከተለ
ሳይለይ ከጌታው በሐዘን እንደዋለ
ልቡ ከኢየሱስ ጋር ቢወገር ቢሰቀል
በጽናቱ ብዛት ማርያምን እናት ተሸልሟል

ምን ተነጋገርካት ዮሐንስ ጻድቁ
ምስጢራችሁ ለሰው መራቁ መርቀቁ
በምን ቃል አፅናንታህ ተረጋጋህ አንተ
ነፍስህ በጌታ ፍቅር እንደዛ እንዲያ እየዋተተ


         ሊቀ መዘምራን
         ይልማ ኃይሉ

          "እናትህ እነኋት"
                ዮሐ፲፱፥፳፯
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


✝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ መዝሙር ይፈልጋሉ?


✞ዓለምን ለማዳን✞

ዓለምን ለማዳን የተሰቀለው
ኢየሱስ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው

ጌታችን ተሰቅሎ ሲያዩት መላእክት
በዝማሬ ፈንታ አለቀሱለት
ሚካኤል ዝም አለ ገብርኤል ገረመው
አምላኩ እርቃኑን ተሰቅሎ ስላየው
       አዝ= = = = =
ነፍሱን ለወዳጁ የሚሰጥ ቢገኝም
ለጠላት የሚሞት በጭራሽ አይኖርም
ጠላቶቹ ስንሆን ለኛ የሞተው
በመስቀል የዋለው በፈቃዱ ነው
       አዝ= = = = =
እውርን ቢያበራ የሞተ ቢያስነሳ
በመመስገን ፈንታ ሆነበት ወቀሳ
ከመከራ ሊያድን ቢገለጥ በሥጋ
የእሾህ አክሊል ደፋ ቀኝ ጎኑ ተወጋ
       አዝ= = = = =
በጸሎተ ሐሙስ ዕለት እራት የሆነው
አርብ በመስቀል ላይ የተሰቀለው
ፍቅር አስገድዶት ለኛ የሞተው
መልካሙ እረኛችን መድኃኒዓለም ነው(፪)

             ዘማሪት
          ፋንቱ ወልዴ

"ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ ....በዚያም ሰቀሉት፥"
                ዮሐ፲፱፥፲፯-፲፰
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯


የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ትምህርቶች dan repost
ስለእውነት ምን ይሻላል?✞✞

እውነትን ለማወቅ የሚፈልግ የለም እንጅ እውነትን ለማወቅ ሁሉም ደፋ ቀና እያለ ነው። ስለ እውነት የሚጠይቁ የማይቆጠሩ ናቸው። ሰለ እውነት የሚመራመሩትስ ቢሆን! ስለ እውነት የሚዋኙ አሉ። ስለ እውነት የሚከንፉም እልፍ! ስለ እውነት የሚቆፍሩም ትእለፊት ናቸው። እውነት ግን በዚህ ሁሉ የለችም። ምክንያቱም እውነት አይፈልጓትም እንጅ አጠገባቸው አለችና። እውነት ልሳኗ እስኪዘጋ በረጅም ጩኸት አየጮኸች አቤት የሚላት የለም። ለእውነት ጆሮውን የደፈነው ሁሉ ግን ስለ እውነት ተመራማሪ ነው። አንድ ቀን አይቷት ቀርተቶ ሲያልፍ ድምጿ ጭር ያላለችበት ሁሉ የእውነት የልብ ወደጅ ነኝ ብሎ ስለ ራሱ ድርሰት ያስነብባል። እውነት ታማ አጠገባቸው እየረገጡ ወደ ውሸት ሠርግ እየሄዱ የእውነት ጠበቃ ይሆናሉ። ነብርን የፍየል፥ ጅብን የአህያ፥ ፍየልን የቅጠል፥ ቀበሮን የበግ ፥ዶሮን የጥሬ ፤ውሻን የቅቤ ጠበቃ የሚያቆማቸው ማን ነው? አንድ ሚ'ገርመኝ ነገር አለ። ድመትን ነምር ቢያባርራት። ድመትን አስጥሎ ራሱ ለመብላት ነው እንጅ እውነት ሳንባን ከድመት ለመጠበቅ ይሆናልን?

እውነት ቤት ውስጥ አለች ነገር ግን ሰዎች ከቤት ያስወጧት ዘንድ ሌሊት ከቀን እየጎሰሟት ስለ እውነት ግን ደግሞ በአደባባይ ይሰብካሉ። በውሸት ሻማ እውነትን ይፈልጋሉና የእድሜ ነፋስ ሻማውን ያጠፋውና እውነትን ሳያዩ ያሸልባሉ። አንገቱን ያቀረቀረ ሰማይን አያይም፤ ሥግብግብነት ያጎበጠው ሰውም በእውነት ሰማይ ላይ የሚያበራውን ጸሐይ አያይም። መድኀኒቱን በመርዝ ዕቃ ቢጠጡት ይገድላል እንጅ አያደንም። እውነትንም በውሸት መመርመር አይቻልም እውነትን እየሰቀሉ እውነትን ይመረምራሉ። በውሸት በሚኖሩም የውሸት መሞት ግን አይቻልም።

በእውነት ላይ ፍርድ እየፈረዱ እውነት ምንድን ነው ቢሉት ምን ዋጋ አለሁ? ይህቺ ዓለም
ስለ እውነት እየጠየቅን መልሱን ሳንሰማ እንድንወጣ በሁከቷ እድል ትነሳናለች።"ጌታ ኢየሱስም መልሶ እኔ ንጉሥ እንደሆንሁ አንተ ትላለህ። እኔ ስለ እውነት ልመሰክር ስለዚህ ተወልጃለሁ ስለዚህም ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ከእውነት የሆነ ሁሉ ድምፄን ይሰማል አለው። ጲላጦስም እውነት ምንድን ነው አለው ይህንንም ብሎ ዳግመኛ ወደ አይሁድ ወጥቶ እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኘሁበትም።"ዮሐ፲፯፰፥፴፯
ጰላጦስ ስለ እውነት ጠይቆ ሳይመለስለት ለእውነት ጥብቅና ሊቆም ወጣ። ሳይጸናበትም ቀረና እውነትን ሰቀለ። እርሱ በጌታ ላይ በደል አለማግኘቱ ብቻ መስሎታል እውነት! ጌታ ግን የሌለበት ብቻ ሳይሆን ኃጢአትትን የሚደመስስ እውነተኛ አምላክም ነበር። ይህ ግን እሰከ ጊዜው ድረስ አልገባውም ነበር። እውነትን እሽ በጎ ላለማለት እድል የሚነሱት ገንዘብና ሥልጣን መጣበት ናቸው። ዓለም ለእውነት መኖር በሚፈልጉ ሰዎች ላይ ፈጥና ጉሮሯቸው ላይ ትቆማለች ወዲያውም የህልውና ጉዳይ አይደል ምን ይደረግ ታስብላቸዋለች። ማራጭ በማያቀርቡለት ኑሯቸው ለይ ትመጣለች። እነርሱም እውነትን ሳይውጧት ይቀራሉ። ጲላጦስ በከፊሉም ቢሆን ስለ እውነት ሲከራከር አይሁድ"እንግዲያውስ የቄሳር ወዳጅ አይደለህም" ነበር ያሉት። ያን ጊዜ ተብረከረከ። በሹመቱ መጡበታ!

ችግሩ ምንድን ነው። እውነት በጥልቀት ሳትገባው ስለ እውነት መቆሙ። ሳይገባው የወደደ ሳይገባው ይጠላል። ሳይገባው ያመነ፡ሳይገባው ይክዳል። እውነት ክርስቶስ ነው። ቄሳር የጲላጦስ ንጉሥ ቢሆንም ክርስቶስ ግን የቄሳር ፈጣሪ ነው። ስለዚህ ይህ ቢገባው አይሸበርም ነበር።
ሁለተኛ ስለ እውነት ሲኖር ይህ እንደማይቀርለት ማወቅ ነበረበት። ነገር ግን ይህ ሁሉ ባይቀርም በእውነት ነጻ መውጣቱ ደግሞ አይቀርም! ወተአምርዋ ለጽድቅ ወጽድቅኒ ታግዕዘክሙ=እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል" ዮሐ፰፥፴፪
ስለ እውነት እንድናውቅ እውነት እንዲገባን
ስለ እውነት ለመኖር እውነት እንዲመራን
እውነተኛው አምላክ በእውነት ይጠብቀን!
አባ ገብረ ኪዳን
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan


✞አንተ እንደ ጠራኸኝ✞

አንተ እንደ ጠራኸኝ ከምርጦችህ ልሁን(፪)
አምላክ ለዘላለም ልፈጽም ፍቃድህን

በሲኦል የሚያመሰግንህ የለምና
ከሞት ልዳን ልጥራህ በምስጋና(፪)
       አዝ= = = = =
ልቤ አንተን እያለ በሲኦል አተተወኝ
በረቀቀ ጥበብ ከሞት መንደር አውጣኝ(፪)
       አዝ= = = = =
ከመንፈስ ጀምሬ በብርታት
በሥጋ እንዳፈጽም እርዳኝ የኔ አባት(፪)

         መዝሙር
  ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ

"እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፥"
መዝሙር ፻፭፥፩
╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮
   @yamazemur_getemoche
╰══•ೋ•✧๑♡๑✧•  ══╯

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.