ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Bloglar


የ ያሲን ኑሩ ሐዲሶች
Yasin Nuru
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራውን ሰው ያህል አጅር ያገኛል" ረሱል (ﷺ)
"የበጎ ስራ ምላሹ በጎ እንጂ ሌላ አይደለም "  
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሰራ ሰው ያገኘዋል :>> { አል -ዘልዘለህ 7}
This is not official
ለአስተያየት👇👇
@Hasabbbbot

ሀዲሶችን ከፈለጋችሁ👇👇
@yasin_nuru_hadis

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Bloglar
Statistika
Postlar filtri


🔖የጁምዓ ሰላት ሸሪዓዊ ብይኑና ማስረጃዎቹ🔖

🌂የጁምዓ ሰላት በያንዳንዱ ሙስሊም በሆነ ወንድ ላይ ግዴታ ነው፡፡

አላህ እንዲህ ይላል፡-

‹‹እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ፡፡ መሸጥንም ተዉ፡፡›› ጁምዓ 9

ነብዩም (ﷺ) እንዲህ ብለዋል

‹‹አቅመ አዳም በደረሰ በያንዳንዱ ሰው ጁምዓ ግዴታ (ዋጂብ) ነው››[ነሳኢይ 1371]

በሌላም ሐዲስ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል

‹‹ሠዎች ጁምዓን ከመተው የማይታቀቡ ከሆነ አላህ ልቦናቸውን ያሽግና ዝንጉዎች ይሆናሉ››[ሙስሊም 865]

☄ጁምዓ ግዴታ የሚሆንባቸው ሰዎች☄

ጁምዓ በእያንዳንዱ ወንድ፣ ከባርነት ነፃ በሆነ፣ አቅመ አዳም በደረሰ፣ የአእምሮ ጤነኛ በሆነና ወደ ጁምዓ የመምጣት ችሎታ ባለው ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው፡፡ በአንፃሩ በባሪያ፣ ሴት ልጅ፣ ያልደረሰ ልጅ፣እብድ፣ህመምተኛና መንገደኛ ላይ ግዴታ አይደለም፡፡ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል

‹‹ጁምዓን በህብረት መስገድ ከአራት ሰዎች በስተቀር በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው፡- ባሪያ፣ ሴት ልጅ፣ ህፃንና ህመምተኛ››[አቡዳውድ 1ዐ54]

መንገደኛ የሆነ ሰው ላይ ጁምዓ ግዴታ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ነብዩ (ﷺ) ባደረጓቸው ጉዞዎች ላይ አንድም ቀን ጁምዓ አልሰገዱም:: ነብዩ (ﷺ) ባደረጉት የመሰናበቻ ሐጅ ላይ ጁምዓ ገጥሟቸው ነበር ነገር ግን የሰገዱት ዙህርና ዓስርን በማቆራኘት እንጂ ጁምዓን አልነበረም፡፡ ይሁንና አንድ መንገደኛ ሙስሊምች ጁምዓ የሚሰግዱበት ቦታ ላይ በአጋጣሚ ቢገኝ ከነሱ ጋር አብሮ ጀምዓ መስገድ አለበት፡፡ ባሪያ፣ ሴት፣ልጅ፣ህፃን፣ህመምተኛ ወይም መንገደኛ ጁምዓ ተገኝተው ከሰገዱ ዙህርን መስገድ አይጠበቅባቸውም::

የጁምዓ ወቅት🌤

የጁምዓ ሰላት ወቅት ልክ እንደ ዙህር ፀሀይ ወደ ምዕራብ ዘንበል ካለችበት ወቅት አንስቶ የአንድ ነገር ከፀሐይ የሚያገኘው ጥላ በቁመቱ ልክ እስከሚሆን ድረስ ነው፡፡ አነስ ኢንብ ማሊክ እንዳሉት

‹‹ነብዩ (ﷺ) ጁምዓ የሚሰግዱት ፀሐይ ዘንበል ስትል ነበር››[ቡኻሪ 9ዐ4]

✔በዚህ ወቅት ጁምዓ መስገድ የሰሃቦች የተለመደ ተግባር እንደነበርም ተዘግቧል፡፡ በዚህ መሰረት ወቅቱ ከማብቃቱ በፊት አንድ ረከዓ የመስገጃ ያህል ጊዜ ላይ የደረሰ  ጁምዓን ይሰግዳል፡፡ ወቅቱ ያለፈበት ከሆነ ግን መስገድ ያለበት ዙህርን ነው፡፡

📔የጁምዓ ኹጥባ📚

ኹጥባ ነብዩ (ﷺ) በሰገዷቸው ጁምዓዎች ሁሉ የፈፀሙትና ትተውት የማያውቁ በመሆኑን የጁምዓ መሰረት ነው፡፡ ስለዚህ ጁምዓ ያለ ኹጥባ መሰረተቢስ ነው:: በጁምዓ የሚደረጉት ኹጥባዎች ሁሉት ኹጥባዎች(ሁለት ኹጥባዎች የሚባሉት ኢማሙ አንደኛውን ኹጥባ ካደረገ በኋላ በመሃል ተቀምጦ ለሁለተኛ ጊዜ ቆሞ የሚያደርጋቸው ናቸው)ሲሆኑ መስፈርቱም ከሰላት አስቀድሞ ማድረግ ነው፡፡

🔖የኹጥባ ሱናዎች🔖

ለሙስሊሞች ዱንያዊና ሀይማኖታዊ ጉዳዮች መስተካከልና ለመሪዎች ዱዓ ማድረግ የተወደደ ነው፡፡ ነብዩ (ﷺ) የጁምዓ ዕለት ኹጥባ ሲያደርጉ በጣታቸው ወደ ላይ እየጠቆሙ ዱዓ ሲያደርጉ ሰዎችም አሚን ይሉ ነበር፡፡

ኹጥባና ሰላት በአንድ ሰው ቢፈፀሙ ይወደዳል፤ ኹጥባ አድራጊው በተቻለ አቅም ድምፁን ከፍ ቢያደርግ የተወደደ ነው፤ ኹጥባን ቆሞ ማድረግ የተወደደ ነው፡፡

ጃቢር ኢብን ሰሙራ እንዳሉት

‹‹ነብዩ (ﷺ) ቆመው ኹጥባ ካደረጉ በኋላ በመሀል ተቀምጠው ከዚያ እንደገና ቆመው ያደርጉ ነበር››[ሙስሊም 862]

    ኹጥባን አጠር ማድረግና የሁለተኘውን ኹጥባ ከመጀመሪያው ይበልጥ አጠር ማድረግ፡፡ ዓማር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ይላሉ

‹‹የአንድ ሰው ኹጥባ አጠር ማለቱና ሰላቱን ረዘም ማድረጉ የአዋቂነቱ ምልክት ነው፡፡ ሰላትን አስረዝሙ ኹጥባን አሳጥሩ››[ሙስሊም 869]

ኹጥባ አድራጊው ወደ ህዝቦች ዞር ብሎ ሠላምታን ማቅረብ፡- ጃቢር እንዳሉት

‹‹ ነብዩ (ﷺ) ሚንበር[የኹጥባው መድረክ (ምኹራብ)] ላይ ሲወጡ ሠላምታ ያቀርቡ ነበር”

 አዛን አድራጊው አዛኑን እስኪያጠናቅቅ ሚንበር ላይ መቀመጥ  ኢብን ዑመር እንዳሉት ‹‹ነብዩ (ﷺ) በሚንበር ላይ ወጥተው አዛን አድራጊው አዛኑን እስኪጨርስ ሚንበር ላይ ይቀመጡና ሲጨርስ ተነስተው ኹጥባ ያደርጉ ነበር››

🔊በጁምዓ ክልክል የሆኑ ተግባራት🔊

    ✔ ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ መናገር አይፈቀድም፡፡  ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ይላሉ

‹‹በጁምዓ ቀን ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ የተናገረ መፅሐፍ እንደተሸከመ አህያ ነው››[አህመድ 1/23ዐ]

በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል

🌈‹‹ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ ለጓደኛህ ዝም በል ካልክ ከንቱ ንግግር ተናገርኽ››

🌈በተቀመጡ ሰዎች ትከሻ በኩል በመሸጋገር መተላለፍ :
✔ ነብዩ (ﷺ) የሰዎችን ትከሻ እየተሸጋገረ ሲያልፍ ለተመለከቱት ሰው ‹‹ተቀመጥ ሰውን አስቸገርክ›› ብለውታል:: በዚህ ተግባር ሰውን ማስቸገርና ኹጥባን የሚያደምጥን ማዘናጋትም ይፈጠራል:: ኢማሙ ግን የሠዎችን ትከሻ እየተሸጋገረ ካልሆነ ወደ ቦታው የሚደርስበት ሌላ አማራጭ ከሌለው ይህን ሊፈፅም ይችላል፡፡

ሁለት ሰዎችን በመለየት በመካከላቸው መቀመጥም አይፈቀድም፡፡ ነብዩ(ﷺ) እንዲህ ብለዋል

✔የጁምዓ ሰላት ገላውን ታጥቦ በጊዜ ወደ ጁምዓ የሄደ ከዚያ በኋላ በሰዎች መካከል ሳይለይ አላህ የወሰነለትን የሰገደ በዕለቱና በሚቀጥለው ጁምዓ መካከል የሚፈፀሙ ኃጢአቶች አላህ ይቅር ይለዋል።

[ቡኻሪ 91ዐ]

🔖ጁምዓ ላይ መድረስ የሚቻለው በምንድን ነው?

💡ከኢማሙ ጋር አንድ ረከዓ ከደረሰ ጁምዓን በማግኘቱ የቀረውን አንድ ረከዓ ይጠበቅበታል:: ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል ‹‹ከጁምዓ አንድ ረከዓን የደረሰ ሰላት ላይ ደርሷል›› ኢማሙ ላይ የደረሰው ግን ከአንድ ረከዓ ባነሰ ከሆነ መሙላት ያለበት ዙህር ሰላትን ነው፡፡

💡የጁምዓ ሱና ሰላት💡

✔ከጁምዓ በፊት የሚሰገድ መደበኛ ሱና የለም፡፡ ነገር ግን ወቅቱ ከመድረሱ በፊት መደበኛ ያልሆነ ሱና ቢሰግድ ምንም ችግር የለውም ምክንያቱም ነብዩ (ﷺ) በጥቅሉ ሱና መስገድን አበረታተዋል፡፡ ከጁምዓ በኋላ ግን መደበኛ የሆኑ ሁለት፣ አራት ረከዓ ወይም ስድስት ረከዓ ሱናዎችን እንደሁኔታው ሊሰገድ ይችላል፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ባስተላለፉት ሀዲስ

‹‹ነብዩ (ﷺ) ከጁምዓ በኋላ ሁለት ረከዓ ይሰግዱ ነበር››[ቡኻሪ 937 ሙስሊም 882]

በሌላ ሀዲስ ደግሞ ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል

‹‹ ከጁምዓ በኋላ አራት ረከዓ ሱናዎችን ስገዱ››[ሙስሊም 881]

ኢብን ዑመርም ከጁምዓ በኋላ ስድስት ረከዓዎችን ይሰግዱ እንደነበር ‹‹ነብዩ ይፈፅሙት ነበር››[አቡዳውድ 113ዐ]

✔እንዳሉ አቡዳውድ ዘግበዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከጁምዓ በኋላ የሚሰገድ መደበኛ ሱና ከፍተኛው ስድስት አነስተኛው ሁለት መሆኑን እንረዳለን::

🔖የጁምዓ ሰላት አሰጋገድ🔖

🎯የጁምዓ ሰላት ድምፅ ከፍ በመደረግ የሚሰገዱ ሁለት ረከዓዎች እንደሆኑ በነብዩ (ﷺ) ተግባርና በዑለማዎች ስምምነት የተረጋገጠ ነው፡፡ በመጀመሪያው ረከዓ ከፋቲሃ በኋላ ሱረቱል ጁምዓ በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ ሱረቱል ሙናፊቁን[ሙስሊም 877] ወይም በመጀመሪያው ረከዓ ከፋቲሃ በኋላ ሱረቱል አዕላ በሁለተኛው ሱረቱል ጋሺያ እንደሚነበብም ነብዩ (ﷺ) በተግባር አስተምረዋል፡፡[ሙስሊም 878]

@yasin_nuru @yasin_nuru

2.6k 0 32 12 71

አስተውል!

~ ሰዎች ዘንድ ለመወደድ ስትለፋ ጌታህ ዘንድ እንዳትጠላ ተጠንቀቅ።

~ ለምትወዳቸው ሰወች ክብር ስታበዛ የጌታህን ክብር እንዳትነካ ተጠንቀቅ።

~ ሰወችን በመውደድ ብቻ ስትጠመድ የጌታህን ውዴታ እንዳትነፈግ ፍራ! ጥላቸው ማለት አይደለም ውዴታህ በልክ ይሁን!

~ እውነት ለመናገር ከሰወች ጥቅምን አትፈልግ! ሰወችን ለማስደሰት አትዋሽ! ለህሊናህ እረፍት አስበህ እውነተኛ ሁን!

~ የራስክን ደስታ ለማሞቅ ለሌሎች ሃዘን ሰበብ አትሁን! በሌሎች ደስታ ተደሰት! ከምቀኝነት እራቅ!

~ ለጥፋት መሆንን እንጂ መባልን አትፍራ! ሆኖ ለመገኘት እንጂ ለመባል አትድከም።

~ ፍርድ ለመስጠት ከመወሰንህ በፊት ዳኛ ለመሆን አቅሙ እንዳለክ እራስክን ጠይቅ።

~ ለመውቀስ ከመቸኮል ለማጣራት ሞክር ! መልስ ከመስጠትህ በፊት ጥያቄውን አስተንትን!

~ ማንነትህን ለማሳወቅ በአፍህ ከመናገር ይልቅ ስራበት! ተግባርህ ያስረዳ!

~ መልካም ለመሆን አትምረጥ። ለሁሉም መልካም ሁን አትጎዳበትም።

~ ክብርን ለማግኘት ክብር ከሌለው ተግባር ተቆጠብ!

~ ሀቅን እንጂ ሰወችን አትከተል።

~ መኖርህን ስታይ መሞትህንም አትርሳ! ኖረህም የሚጠቅምህን ስትሞትም የሚከተልህን ስራ!!

JOIN: @yasin_nuru 
JOIN: @yasin_nuru  

4.6k 0 48 23 147

🖌በሀገረ እንግሊዝ የምትኖር አንዲት ሚስኪን ትውልደ ሶማሊያዊት ሙስሊም ሴት እርዳታን ለማግኘት ወደ ሬዲዮ ጣቢያ ደወለች። አምላክ የለም በሚለው እምነቱ የሚታወቀው ሰው የስልኩን እጀታ አነሳና አዳመጣት።

📍ፋጡማ ቤቷ የሚላስ የሚቀመስ አለመኖሩን በመንገር ለችግሯ መፍትሄ እርዳታ ያደርግላት ዘንድ ተማፅና ቁጥሯን እና አድራሻዋን ሰጥታ ስልኩን ዘጋችው።

✒️ምግብና ሌሎች እርዳታዎች ተዘጋጅተው ወደ አድራሻዋ እንዲያደርስ ለግል ጸሃፊው መመሪያ ሰጠ። እንዲህም አለ፡- 

💠"የእርዳታውን ምንጭ ከጠየቀችሽ ከሸይጣን የተሰጣት ስጦታ መሆኑን ንገርያት" በማለት ሴትየዋ ላይ እየተሳለቀ አዘዛት።

⏺ፀሐፊዋ የሚያስፈልጋትን ሁሉ ሸክፋ ወደ ሴትየዋ ቤት አቀናች።

❇️ምስኪኗ ሴት በደስታ እያነባች የተላከላትን ተቀብላ ወደ ውስጥ ለመግባት በመራመድ ላይ ሳለች ጸሃፊዋ
"የዚህን እርዳታ ምንጭ ማን እንደላከልሽ ማወቅ አትፈልጊምን?"  ስትል ጠየቀቻት።

🔰ይህች ማንበብና መጻፍ የማትችል ሙስሊሟ ፋጡማ የሰጠችው ምላሽ እምነት አልባውን ዶ/ር ቲሞሲ ቬንተርን አስተሳሰብ ቀይራ እስልምናን እንዲቀበል አደረገው ስሙንም ዐብዱልሀኪም ሙራድ ብሎ እንዲሰይም አስገደደው።
ምላሿ ይህ ነበር፡-

❤️ "ለማወቅ አልፈልግም ማንነቱም ግድ አይሰጠኝም። ጌታዬ አላህ አንድን ነገር ከፈለገ ሰይጣኖችም እንኳ ቢሆኑ ይታዘዙታልና"

#አላህ ሆይ" እምነታችንን አፅናልን!!

©️®ምንጭ"f.book.ድ/ገጽ

#ዘላለም_ኗሪ_አላህ_ነው

@yasin_nuru       @yasin_nuru

5.8k 0 49 41 297

💫መልካም አባባሎች
📖 እኔ ዘንድ በጣም የተወደደው ሰው ደካማ ጎኖቼን የሚነግረኝ ሰው ነው።
🖊 ዑመር አልኸጧብ(ረ. አ)

📖የበጎ ነገርና አላህን በመፍራትም ተረዳዱ ግን በሀጢአትና ወሰንን በማለፍ አትረዳዱ።
🖊 (5:2) ሱረቱል ማኢዳ

📖 ሙስሊም ባሪያውን በመርዳት ላይ ነው። ባሪያው ወንድሙንና እህቱን እስካልተባበረ ድረስ ።
🖊 ረሱል ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም

📖 ከሷሊህ ሰዎች ጋር ድንጋ መሸከም ከመጥፎ ሰዎች ጋር ከሚበሉት ምርጥ ምግብ ይጣፍጣል ።
🖊 ማሊክ ኢብኑ ዲናር

📖 ብዙ ጓደኛ አይቻለሁ ምላስን ከመጠበቅ የተሻለ ጓደኛ አላየሁም ። ብዙ ልብሶች አይቻለሁ አላህን ከመፍራት ያማረ ልብስ አላየሁም።

🖊 ኡመር አልኸጧብ(ረ. አ)

📖 ከመጥፎ ሰዎች ጋር ከመቀላቀል ለብቻ መሆን እረፍት ነው።
🖊 ኡመር አልኸጣብ(ረ. አ)

📖 ከስህተቶች ሁሉ ታላቁ ውሸት ነው። ምላሱ የሚዋሽ ሰው አይኑን ጆሮውን መላ አካሉን ያስዋሻል ።ያላየውን አየሁ ያልሰማውን ሰማሁ ይላል።
🖊 አብደላህ ኢብን መስኡድ (ረ .አ)

📖 አላህ የላይ ገፃችሁንና ገናዘባችሁን አይመለከትም ። ነገር ግን ቀልቦቻችሁንና ስራዎቻችሁን ይመለከታል።
🖊 ረሱል ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም ።

📖 አላህ ዘንድ የሚበላለጠው ስራ መብዛት ሳይሆን ቀልብ ውስጥ በተቀመጠው ነገር ነው።
🖊 ኢማሙ ኢብኑ ቀዩም

📖 በሚጠቅምህ ነገር ላይ ጉጉት ይኑርህ በአላህ ታገዝ ደካማና ስልቹ አትሁን አንድ ነገር ባጋጠመህ ጊዜ ይህን ነገር እንዲህ ባረገው ኖሮ አትበል።

ነገር ግን አላህ የወሰነውን ሆነ አላህ የፈለገውን ፈፀመ በል።እንዲህ ቢሆን ኖሮ የሚለውን ንግግር ለሰይጣን ስራ በር ይከፍታል።
🖊 ረሱል ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም።

📖 እኔኮ አንድን ሰው ማየት ያስጠላኛል በጣም ይከብደኛል ቢዚ ይሆናል የሆነበት ምክንያት ግን ለዲኑም ለዱንያውም በማይጠቅመው ነገር ምንም አላማ የለውም።

🖊 ኢማሙ ሻፊኢይ ናቸው ረሂመሁላህ።

🔗SHARE 🔗SHARE
╔════════════╗
☪ JOIN: @yasin_nuru         ☪
☪ JOIN: @yasin_nuru         ☪   ╚════════════╝

6.6k 0 68 13 114

📨20 ወንድማዊ ምክር ለውዷ እህቴ‼

1,በተውሒድ ላይ አደራ! ሽርክን ራቂ!!

2,, ሁሌ ቤት ውስጥ መቀመጥ ምርጫሽ ይሁን።ወጣ ወጣ አትበይ!!

3,,ተቅዋን(አላህን መፍራት) የውስጥ መዋቢያሽ ካደረግሽ ሀያእን ደሞ ውጫዊ መዋቢያሽ አድርጊው!!

4,,ከ ወንዶች እና ከካፊር ሴቶች ጋ ያለሽ ግንኝነት በጣም አስፈላጊ ሆኖ እስካላገኘሽው ድረስ ራቂ!!

5,,ሒጃብሽ ሰፋ ያለና ረዘም ያለ ይሁን!!

6,,አካሄድሽ ረጋ ያለና አደብ የተላበሰ ይሁን!!

7,,በየቀኑ ብታጠፊ በየቀኑ ወደ አላህ ተመለሺ!!

8,,በአለባበስሽና በሥነ-ምግባርሽ ለሌሎች ሴቶችና ለሴት ልጆችሽ ምሳሌ ሁኚ!!

9,,ያልተፈቀደልሽን ባዕድ ወንድም ሆነ ሊያገባሽ የሚፈቀድለትን የቅርብ ዘመድ አትጨብጭ!!

10,,ከላይ አላህን ሳይታዘዙ፤ ዉስጤ ንፁህ ነው አላህን ፈራለሁ ማለት ቅጥፈት ነው!!

11,ከባዕድ ወንድ ጋር ስታወሪ መቅለስለስ፤ በሽታ ያለበትን በሽታውን መቀስቀስ ነውና አደብ ይኑርሽ በንግግርሽ…!!

12,መስመር እየሳቱ የሚመስሉ የስልክ ወሬዎችንና ቻቶችን ከወድሁ ቁረጪ!!

13,እየተኳኳሉና እየዘለሉ አላህን እና መልዕክተኛዉን እወዳለሁ ማለት ዉሸት ነውና…

14,ሒጃብና ኒቃብ እየለበሱ መጥፎ መሥራት የኢስላምን ንጽሕት የሙስሊምን ሥም ጭምር ማጠልሸት ነውና… በቻልሽው አቅም አደብ ይኑርሽ!!

15,በሐራም መንገድ ገንዘብም ሆነ ትዳር ባገኙት አትቅኚ ፈፃሜው አያምርም እና!!

16,- ፀጉርሽን አትጎዝጉዢ(ከፍ አድርገሽ አትሰሪው) አትቀጥይውም፣ሽቶም ሆነ ዶድራንት አትቀቢ!!

17,ስትስቂ በስሱ፤ ሰታወሪ ድምጽሽ ዝቅ ይበል!!

18,በሥራ ቦታ እና በት/ት ቤት  ከሰዎች ጋር ባለሽ ግንኙነት ቀይ መስመር ይኑርሽ!!

19,,ከ እህቶችሽ ጋር ተግባቢ እና ትህትና ያለሽ ሁኚ!!

20,,የሸሪዓ እውቀትን በመፈለግ ላይ አደራ እስካሁን ለጠቀስኩት ምክሮች መሰረቱ ነው እና!!

[▫️አቡ ሡፍያን]

@yasin_nuru @yasin_nuru

7.9k 0 103 19 191





"ጁመዓ!
-----------------



በጁምዓ ክልክል የሆኑ ተግባራት።
,
ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ መናገር አይፈቀድም፡፡
,
   ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
,
በጁምዓ ቀን ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ የተናገረ መፅሐፍ እንደተሸከመ አህያ ነው››

      ,        አህመድ 1/23ዐ


   በሌላም ሀዲስ እንዲህ ብለዋል፦
ኢማሙ ኹጥባ እያደረገ ለጓደኛህ ዝም በል ካልክ ከንቱ ንግግር ተናገርክ››

   ቡኻሪ 394  ሙስሊም 851
,
በተቀመጡ ሰዎች ትከሻ በኩል በመሸጋገር መተላለፍ፦
,
ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) የሰዎችን ትከሻ እየተሸጋገረ ሲያልፍ ለተመለከቱት ሰው ‹‹ተቀመጥ ሰውን አስቸገርክ›› ብለውታል::
  ,
በዚህ ተግባር ሰውን ማስቸገርና ኹጥባን የሚያደምጥን ማዘናጋትም ይፈጠራል::
,
  ኢማሙ ግን የሠዎችን ትከሻ እየተሸጋገረ ካልሆነ ወደ ቦታው የሚደርስበት ሌላ አማራጭ ከሌለው ይህን ሊፈፅም ይችላል፡፡
,
ሁለት ሰዎችን በመለየት በመካከላቸው መቀመጥም አይፈቀድም፡፡
  ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
       እንዲህ ብለዋል ፦
,
የጁምዓ ሰላት ገላውን ታጥቦ በጊዜ ወደ ጁምዓ የሄደ ከዚያ በኋላ በሰዎች መካከል ሳይለይ አላህ የወሰነለትን የሰገደ በዕለቱና በሚቀጥለው ጁምዓ መካከል የሚፈፀሙ ኃጢአቶች ይሰረዝለታል››

            ቡኻሪ 910

©«አል ኢኽላስ የሙስሊሞች ጀመዓ»\

@yasin_nuru @yasin_nuru

9.2k 0 31 15 121

«She is   ቆንጆ ናት... አፍላ .... 20 አመቷ ነው።
ጎረምሶች ሲያዩዋት አይናቸው ይጎለጎላል። ጎልማሶች አይተው ይመኛታል። ወንዶች ይከጅሏታል። ሴቶች በቅናት እንደ ሽንኩርት ይልጧታል።

🧢  አንድ ቀን እንዲህ ስል ጠየቅኳት።

🧢በፍጥነት መለሰችልኝ
የተማረ መሆን አለበት፤ ማስተርስ ያለው ይመረጣል። ከተቻለ የግል ቢዝነስ የሚሰራ፤ ካልሆነ ግን አሪፍ ደሞዝ ሊኖረው
ግድ.ነው። መኖሪያ ቤቱ G+2 ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ከG+1 በታች ግን
አልፈልግም።

🧢መኪና በጣም ነው የምወደው። አሪፍ መኪኖች ቢኖሩት አሪፍ ካልሆነም
ከተጋባን በኋላ እኔ እንዲገዛ አደርገዋለሁ። ሙድ የገባው ቢሆን ደስ
ይለኛል። ሁሌ ግን የሚቅም መሆን
የለበትም። ጨዋታ የሚያውቅ ሁሌ የሚያስቀኝ!!!

🧢 ቁመቱ በጣም እንዲረዝም አልፈልግም። እኔ አጠር ስለምል በጣም
እንዳይበልጠኝ። ደረቱ ሰፋ ያለ ሆኖ ቦርጭ የሚባል እንዲኖረው
አልፈልግም።

🧢ጸጉሩ ፍሪዝ ቢሆን ደስ ይለኛል፤ ድሬድ ቢሆን ደግሞ ነፍስ ነው። አይኑ
የሚያምር፤ መልኩ ጸይም መሆን አለበት በጣም ቀይ ወይም በጣም ጥቁር
ወንድ አልወድም። አለባበሱ ዘናጭ መሆን አለበት። የሚወደኝ፤
የሚንከባከበኝ፤ ሮማንቲክ የሆነ፤ በሳምንት ቢያንስ ሁለቴ የሻማ
እራት ያለበት ሆቴል የሚጋብዘኝ፤ ፤.ከበዓላት እና  ቀን በተጨማሪ ስጦታ እያመጣ ስርፕራይዝ
የሚያደርገኝ፤ ፍቅር የሚያውቅ፤ በተለያየ ቁልምጫ ስም የሚጠራኝ እና
ታማኝ ከእኔ ውጪአንዲት ሴት የማያይ ...

🧢 >>ይበቃል አልኳት እንደማታቆም ስለገባኝ። እንዲህ አይነት ወንድ
ኢትዮጵያ ውስጥ ቀርቶ በ ዩኒቨርሱ ውስጥ እንኳን አይገኝም አልኩ
በውስጤ። ለሷ ግንአልነገርኳትም።


ከ5አመት በኋላ ሳገኛት 25 አመቷ ነበር። አላገባችም። ዩኒቨርስቲ
ጨርሳ.ስራ ይዛለች። አሁንም ታምራለች
እንደድሮው ግን የሰው ሁሉ አይን ማረፊያ አይደለችም። መልሼ ያንኑ ጥያቄ
ጠየቅኳት።

🧢
የማፈቅረው ሰው መሆን አለበት፤ ፍቅር ከሌለ ላገባው አልችልም።
ከማልወደው ሰው ጋር አንድ ቀን ላድር አልችልም። ታማኝ እንዲሆን
እፈልጋለሁ። እንዲያከብረኝ እፈልጋለሁ። ጥሩ ስራ ቢኖረው፤ ማንበብ
የሚወድና በሃሳብ የምንግባባ ቢሆን ደስ ይለኛል። ቆንጆና ሃብታም ከሆነ ጥሩ ነው፤ ካልሆነም ግን አብረን ሰርተን መለወጥ እንችላለን። ዋናው መግባባት ነው። በተረፈ ቤተሰቡን የሚወድ እና የማይዋሽ መሆን አለበት። ወንዱ ሁሉ
የማይታመን ሆነብን እኮ። ዋናው የሚታመን ከሆነ ሌላው ችግር
የለውም>>

ጊዜው ይሮጣል!!! ከ5አመት በኋላ ስንገናኝ አላገባችም። 30 አመት
እያለፋት ነበር። ደግሜ ያንኑ ጥያቄ ጠይቅኳት።


ትንሽ አሰብ አደረገኝና
አለችኝ
መልኩ፤ ጸጉሩ፤ ሃብቱ፤ እውቀቱስ አልኳት።
አለች እየሳቀች።

🧢ከ5 አመት በኋላ ሳገኛት አግብታ ሁለት ልጆች ወልዳ ነበር።ባሏ
አጭር፤ ጥቁር፤ መላጣ፤ የከባዳ መኪና ሾፌር አይነት ቦርጭ
ያለው፤ሱሪውን ቦርጩ መሃከል ላይ የሚታጠቅ፤ ሁልጊዜ መላጣውን
የሚያልበው  ነገር ነው

አልኳት





አለች ተከዝ ብላ።


አልኳት እያዘንኩ
አለች ፈገግ ብላ። በዛች ቅጽበታዊ ፈገግታ ውስጥ
የጊዜን ኃይለኝነት አየሁ።

በስተመጨረሻም የተረዳሁት ነገር

🧢 ሴት ልጅ የተጋነነ መስፈርቷ ጠላቷ እየሆነ ነው።»

يانساء ተማሩበት

ከኮመንት ማኅደር


@yasin_nuru @yasin_nuru

11.5k 0 195 55 355

ቁርጥ እርሣቸዉን የምትመስል ቆንጆ ናት፣ ዉብ ዕድሜዋ ለጋብቻ ሲደርስ ብዙ ሰዎች ሊጠይቋት እርሣቸው ጋር መጡ፤ ብዙ የተከበሩና ትላልቅ ሰዎች …

አንዲት ዐሊን የምትወድ የአንሷር ሴት ዐሊ ዘንድ ሄዳ
“ፋጢማን ብዙ ሰው እንደጠየቃት ታውቃለህ ግን?” አለችው፡፡
“አዎን” አላት፡፡
“አንተሰ ለምን ሄደህ አትጠይቅም፤ ለምን ዳሩልኝ አትላቸዉም፣ ትወዳት የለ?” አለችው፡፡
አንገቱን አቀረቀረ
“ድሃ ነኝ ምን አለኝና? በምንድነው የማገባት?” አላት፣
“ዝምብለህ ሂድና ጠይቅ፤ መልካም ነገር ልትሰማ ትችላለህ አብሽር፡፡” ብላ አሳመነችው፡፡

ሄደ፡፡ ፈራቸው፤ እርሣቸው ፊት ተቀምጦ መናገር ከበደው፡፡ እናም ዝም አለ፡፡
“ምነው ዐሊ ምን ሆነህ ነው? ምንድነው ያመጣህ ጉዳይ?” አሉት፤ አከታትለው ጠየቁት፡፡
ዐሊ አሁንም ዝም አለ፡፡
“ምናልባት ፋጢማን እንድሰጥህ ለመጠየቅ መጥተህ እንዳይሆን፡፡” አሉት፡፡
አዎን በሚል ሀሳብ ራሱን ነቀነቀ፤
“ታዲያ ጥሎሽ ይኖርሃልን?” አሉት፡፡
“ምንም የለኝም” አላቸው፡፡
“የሆነ ጋሻ እንዳለህ አስታውሳለሁ፡፡” አሉት፡፡
“አዎን አለኝ፣ ግን እሱ ምን ያደርጋል፣ ምን ዋጋ ያወጣል?” አላቸው፡፡
“ይጠቅማል ሽጠዉና ...፡፡” አሉት፡፡

ቤት ገዙላቸው፤ ጋብቻው ተፈፀመ፡፡

ዐሊ እንዲህ ይላል 
'ከዚያ በኋላ ፋጢማን እጅግ ወደድኳት፡፡ አንድም ቀን በስሟ ጠርቻት አላውቅም፤ “ የአላህ መልዕክተኛ ልጅ ሆይ” ነበር የምላት፡፡
ልክ እሷን ሳይ ሀሳብና ጭንቀቴ ሁሉ ይወገዳል፣ ልቤ እረፍት ይሰማዋል፣ አንድም ቀን አስቆጥቻት አላውቅም፣ አንድም ቀን አላስለቀስኳትም፣ አንድም ቀን አስቆጥታኝ፣ አንድም ቀን አስቸግራኝ አታውቅም፡፡ በአላህ አምላለለሁ አንድም ቀን ጀርባዬን ሰጥታችት አላውቅም፤ ሁሌም እጆቿን እንደሳምኳት …   

ፋጢማ ከአባቷ ከአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ.) ህልፈት ከስድስት ወር በኋላ ተከተለቻቸው፡፡ በሞተችም ጊዜ ባለቤቷ ዐሊ አጠባት፣ ከፈናትም፣  ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብሎም
      
“ፋጢማዬ እኔ ዐሊ ነኝ፡፡” አላት፡፡  

@yasin_nuru @yasin_nuru

10.7k 0 68 33 266

የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ሚስቶች_ስም

★زوجات الرسول ﷺ ﺇﻧّﻬﻦ ﺍﺛﻨﺘﺎ ﻋﺸﺮﺓ ﺯﻭﺟﺔً،
(١) ☜السيدة خديجة بنت خوليد
(٢)☜السيدة السودة بنت زمعة
(٣)☜السيدة عائشة بنت ابي بكر
(٤)☜السيدة حفصة بنت عمران
(٥)☜السيدة زينب بنت خزيمة
(٦)☜السيدة هند بنت أمية
(٧)☜السيدة زينب بنت جحش
(٨)☜السيدة جورية بنت الحارث
(٩)☜ السيدة ﻣﺎﺭﻳﺔ ﺍﻟﻘﺒﻄﻴﺔ  ﺑﻨﺖ ﺷﻤﻌﻮﻥ
(١٠)☜السيدة رملة بنت ابي سفيان
(١١)☜ السيدة صفية حيي بن اخطب
(١٢)☜السيدة ميمونة بنت الحارث

#የነብዩ_ሙሐመድ_ﷺ_ሚስቶች_12_ናቸው። እነሱም፦👇👇👇

①☞ ሰይደቲ #ኸዲጃ    ቢንቲ ኹይሊድ
②☞ ሰይደቲ #ሰውዳእ  ቢንቲ ዘመዐህ
③☞ ሰይደቲ #አዒሻ      ቢንቲ አቡበክር
④☞ ሰይደቲ #ሓፍሷ     ቢንቲ ዒምራን ልጅ
⑤☞ ሰይደቲ #ዘይነብ    ቢንቲ ኹዘይማህ
⑥☞ ሰይደቲ #ሂንድ       ቢንቲ  ኡመያህ
⑦☞ ሰይደቲ #ዘይነብ     ቢንቲ ጀሕሽ
⑧☞ ሰይደቲ #ጁወይሪያ ቢንቲ ሓሪስ
⑨☞ሰይደቲ #ማሪያ_አልቂብጢያ ቢንቲ ሸምዑን
10☞ ሰይደቲ #ረምላ       ቢንቲ አቡ ሱፍያን
11☞ ሰይደቲ #ሶፍያ       ቢንቲ ሓይይ
12☞ ሰይደቲ #መይሙና ቢንቲ ሓሪስ

@yasin_nuru @yasin_nuru

10.9k 0 114 30 165

🏷️የመልካም ተርቢያ ጸር የሆኑ
             10 ነገሮች

♻️ማንኛውም ወላጅ ልጆቹን ትክክለኛ አስተዳደግ ማሳደግ የሚችለው የተሳሳቱ የተርቢያ መንገዶችን አውቆ ሲርቃቸው ነው።
በዋናነት ከሚጠቀሱ የመጥፎ ተርቢያ መገለጫዎች ውስጥ:-

1/ ከመምከርና ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ከመሞከር ይልቅ በሁሉም ነገር ላይ ደረቅ ትችትና ወቀሳን መጠቀም፣ወይም ማብዛት

2/ በንግግርም ይሁን በተግባር ልጆች ላይ መጠንከርና ሁሌም ጉልበት መጠቀምን ማስቀደም፣

3/የልጆችን ሚስጥር ወይም ደካማ ጎኖቻቸውን ለሌሎች በማሳወቅ እንዲሸማቀቁና እንዲያፍሩ ምክንያትመሆ፣

4/ ልጆች ላይ በማሾፍና በመሳለቅ ሞራላቸው እንዲነካ ማድረግ፣

5/ ተፈጥአዊ በሆኑና የግድ ባልሆኑ ነገሮች ላይም ጭምር ልጆች ወላጆቻቸውን እንዲመስሉና በሁሉም ነገር ልክ እንደነሱ ሆነው እንዲያድጉ መፈለግና ጫና ማድረግ፣

6/ልጆች እንዲያደርጉት ወይም እንዳያደርጉት የምንፈልገውን ነገር በሙሉ ከገንዘብ ወይም ከሆን ጥቅም ጋር ማያያዝ (ብር... እሰጥሃለሁ እንዲህ... አድርሃለሁ ወዘተ) ማለት፣

7/ለአካላዊም ይሁን መንፈሳዊ ጤንነታቸው በቂ ትኩረት አለመስጠት፣

8/ለልጆች በቂ ጊዜ በመስጠት እነሱን አለማጫወትና የሚገጥሟቸው ችግሮችን አድምጦ መፍትሄ አለማበጀት፣

9/ በልጆች ጉዳይ ፍትሃዊ አለመሆን፣ (ለአንዱ በጎ ሆኖ ለሌላው መጥፎ መሆን፣ ለአንዱ የሚፈልገውን እያደረጉ ሌላኛውን ችላ ማለት ወዘተ)፣

10/ ወላጆች ልጆቻቸው ስርዓት እንዲይዙና ጥሩ እንዲሆኑ እየመከሩ እራሳቸው ግን  ከመልካም ነገሮች የራቁና ከዛም አልፈው ልጆቻችው ፊትም መጥፎ ነገሮችን ማድረግ ወዘተ መስለ የመልካም ተርቢያ ጸር የሆኑ ነገሮችን  አውቀን መራቅ ካልቻልን በስተቀር ለልጆች ጥሩ ተርቢያ መመኘትና  አንዳንድ ነገሮችን ማድረጋችን ብቻ ጥሩ ልጆችን ለማፍራት በቂ አይሆንም።

@yasin_nuru @yasin_nuru


#አምስቱ_የእስልምና_መሰረቶች

1.መመስከር :- ከአላህ ውጪ ሌላ አምላክ እንደሌለ እና ሙሀመድ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም መልዕክተኛ አንደሆኑ መመስከር

2.አምስቱንም ወቅት ሰላት ጠብቆ መስገድ

3.ዘካን መስጠት

4.ረመዳንን መፆም

5.ሀጅን ማድረግ


#ስድስቱ_የኢማን_መስፈርቶች

1.በአላህ ማመን

2.በመላኢኮች ማመን

3.በመፅሀፎች(በኪታቦች) ማመን

4.በመልዕክተኞች ማመን

5.በመጨረሻው ቀን ማመን

6.በቀዳ እና በቀድር(ባለፈው ነገር እና በሚመጣው ነገር) ማመን

Luhena

@yasin_nuru @yasin_nuru

11k 0 81 31 166

ብቸኛው ወደ ጀነት መግቢያ በር ተውሒድ ነው።

ሌሎች እንደ ሰላት፣ ጾምና ሰደቃ ወዘተ ያሉ ዒባዳዎች በሮች የሚገኙት ዋናውን የተውሒድ በር ካለፉ በኋላ ነው።

@yasin_nuru

10.5k 0 14 34 164

💠እራሳችንን እራሳችን በቁርኣን እናክም!

◻️ከቁርኣን መገለጫዎች መካከል አንዱ "ሺፋእ/ መድሃኒት" መሆኑ ነው።
ከፋቲሓ ስሞች መካከልም አንዱ "አሽ'ሻፊየህ/ፈዋሹዋ" የሚለው ነው።

◻️ቁርኣንና ነቢያዊ ዚክርና ዱዓዎች (ሩቃ) ለሁሉም አይነት በሽታና ችግሮች መፍትሄ ናቸው።
ማንኛውም በቁርኣን ፈውስነት የሚያምን ግለሰብ ፋቲሓንና አጫጭር (እራሱ በቀላሉ መቅራት የሚችላቸውን) ሱራዎች እንኳ ቢሆን እየቀራ ለራሱ ሩቃ ማድረግ ይችላል።

◻️ሩቃ ለማድረግ የግድ ሰው ጋር መሄድ ወይም ሰው መጥራት አይጠበቅብንም።
ለህጻናትና ራሱን ለማያውቅ(መቆጣጠር) ለማይችል ሰውም ቢሆን ሩቃ አድራጊ ፍለጋ ርቆ ለመሄድ ሳንገደድ፤ በቤተሰብ፣ የግድ ከሆነም በዘመድና ጎረቤት ማስደረግ ይቻላል።

◻️ዋናው ነገር ብዙ መቅራቱ ሳይሆን አላህን በሚፈራና ተወኩል ባለው ልብ፣ በቁርኣን ፈዋሽነት አምኖ ፋቲሓና እነ ቁል-አዑዙን ወዘተ.. እየደጋገሙ መቅራት በቂ ነው!። ነቢዩና ﷺ ሰሓቦቻቸውም በነዚህ ምእራፎች ሩቃ ያደርጉ ነበር።

◻️ታላቁ የዲን ሊቅም ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ "እንደ ተላላፊ በሽታ ያለበት ሰው ለሌላ ሰው ሩቃ ሲያደርግ "ቱ...ቱ.../እትፍ-ትፍ" ማለት እንደሌለበት" ተናግረዋል።

🔅በመሆኑም ሁሉም ለራሱ የሚችለውን የቁራኣን ሱራ ወይም አንቀጾችን በመቅራት ሩቃ ሊያደርግ ይገባዋል።ሁሉም የቁርኣን ሱራና አንቀጾ ለሙእሚኖች ፈውሶች ናቸውና!

@yasin_nuru @yasin_nuru

13k 0 48 37 158

🔖ዱዓችን መቅቡል እንዲሆን (ተቀባይነት) እንዲኖረው ...

▪️ዱዓእ የተከሱት ችግሮችን ያስወግዳል ያልተከሰቱትን ይከላከላል።

ከቀደር ጋር ሰማይ ላይ ትግል ገጥሞ መጥፎ ቀደርን ይመልሳል!

▫️አላህ በአግባቡ ዱዓእ የሚያደርጉ ሰዎችን በሙሉ ዱዓእ ይሰማል።
ስለሆነም ሳንሰላች ለዲን ለዱኒያ የሚበጁ ዱዓዎች አዘውተረን እናድርግ

▪️አሁን ላይ ደግሞ ብዙ ችግሮችን እያስከተለና ሀገራችን ላይም እየተባባሰ ያለውን  የኮሮና በሽታ አላህ እንዲያነሳልንም ሁላችንም ትክክለኛ ዱዓእ እናብዛ!

▫️ዱዓእ ተቀባይነት እንዲኖረው መሟላትና መጠበቅ ያለባቸው ዋና ዋና አደብና መስፈርቶች የሚከተሉት ናቸው

1/ ዱዓውን ሲያደርጉ አላህ እንደሚሰማ እርግጠኛ ሆኖና ተማምኖ በኢኽላስና በየቂን ዱዓእ ማድረግ፣

2/ ለአላህ መተናነስና ራስን ዝቅ ማድረግ፣

3/ ልብን መሰብሰና እጅን ወደ ላይ አንስቶ የአይንን እይታም ገታ በማደረግ መማጸን፣

4/ ዘውትር መልካም ስራ መስራትና ወንጀልን መተው፣

5/ ተውበትና ኢስቲግፋር ማድረግ፣

6/ አላህን በመልካም ስምና ባህሪያቱ መማጸን፣

7/ ምግብ፣ መጠጥና ልብስ ባጠቃላይ መገልገያና መተዳደሪያን ሐላል ማድረግ፣

8/ ዱዓእ/ልመናችን ውስጥ ወንጀል/ አላህ የሚጠላውን ነገር መጠየቅና ዝምድና መቁረጥን አለማካተት፣

9/ የዱዓችን ጅምርና መዝጊያ ላይ አላህን ማወደስና ነቢዩﷺላይ ሰለዋት ማውረድ፣
10/ ተስፋ ሳይቆርጡና ሳይቸኩሉ በትእግስት ደጋግሞ ዱዓእ ማድረግ ናቸው።

▪️የሚጠቅም እውቀት፣ የሚጠግብ አንጀት፣ የስራ ተቀባይነት፣ የዱዓእ ሙስተጃብነት፣ ሙሉ ጤንነት አላህ ይስጠን "ኣሚን"

@yasin_nuru @yasin_nuru

12.4k 0 52 46 169

የአላህ ባሪያዎች ሆይ...

🔹በሰማይም ይሁን በምድር ላይ የሚከሰት ነገር በሙሉ በአላህ ውሳኔና እርሱም ለሚያውቀው የላቀ ጥበብና ምክንያት ነው።አላህ የሚወስናቸው ውሳኔዎችም በሙሉ ለባሮቹ መልካምና በሁለቱም ዓለም (በገሃድ ሲታይ ጎጂ ቢመስሉም) ጠቃሚዎች ናቸው።

🔸የግልም ይሁን አጠቃላይ በሽታዎች (ወረርሽኞች) ከጥንት ጀምሮ በተለያዩ ምክንያቶች ይከሰታሉ፣ከምክንያቶቹም አንዱ ለበዳዮች ቅጣት ሲሆን ለምእምናን ደግሞ እዝነት፣ ወንጀል ማበሻና የሰምዓትነትን ማዕረግ ማግኛ መንገድ ነው።

🔹{በግፋቸው(የአላህን መልእክተኛ በማስተባበላቸው) ምክንያት እነሆ ቤቶቻቸው ፈራርሰው ባዶ ሆነዋል። በዚህም ውስጥ ለሚያውቁ ሰዎች ትልቅ ተአምር አለ።እነዚያ ያመኑና ጌታቸውን ይፈሩ የነበሩትን አዳናቸው!}ሱረቱ አን'ነም 51- 53

▪️ከበሽታዎች ለመዳን ሰበቦችን ከማድረስ ጋር ይበልጥ ደግሞ አላህን እንፍራ፣ ልንቶብትና ወንጀሎችንም ልንርቅ ይገባናል!
ዞሮ ዞሮ መሞትም ይሁን መታመም ቀድሞ የተቀደረ/ የተከተበ ነውና በቀደር አምነን እራሳችንን እናረጋጋ። ከበሽታ ይልቅ ብዙኃኑን የሚጎዳው ከልክ ያለፈ ጭንቀትና ስጋት ነው!
"አላህ የከተበልን ወይም የከተበብን ነገር እንጂ እኛ ላይ አይደርስም!"

🔸ከዚህም ጎን ለጎን በምንችለው ያክል እራሳችንና ቤተሰቦቻችን እንጠብቅ።
በበሽታው የተጠቃ ሰውም ሌሎችን ላለመጉዳት የሚችለውን ሁሉ ማድረግና የባለሙያዎችን ምክር መስማት ግዴታ ይሆንበታል!

🔹ይህ በእንዲህ እንዳለ በወረርሽኝ በሽታ መሞት ለሙእሚኖች *የሸሂድነትን ደረጃ* የሚያስገኝ በመሆኑም አማኞች ሆይ አብሽሩ !ሁሉም ለኸይር ነው!
ዳሩ ሞት እንኳ ቢሆን "ኣኺራ ለሙተቆች ከዱኒያ ትሻላለች!"
በበሽታ የተያዘ ሁሉ ይሞታል ማለትም አይደለም!
ደግሞስ ተውሒድና ሱንና ላይ ከሆኑ መሞት ምን ችግር አለው?!
ሆን ብሎ ራስን ላደጋ ማጋለጥ ግን በዲኑ የተከለከለ ነው።
በመልካም ስራም እድሜ መርዘሙ ሌላ መልካም ነገር ነው።

🗞️በተረፈ የጠዋትና የማታ እንዲሁም በአጠቃላይ ከጊዜና ከሁኔታዎች ጋር ተያይዘው የሚባሉ ዚክርና ዱዓዎችን እናብዛ።ችግሮችን በሙሉ ማስወገድ የሚችለው ጌታ አላህ የመጣውን በላ እንዲያነሳልንም ዱዓ እናዘውትር።

🔸በተጨማሪም የጤና ባለሙያዎችና የዘርፉ ተጠሪዎች የሚሰጧቸው መመሪያዎችን ከዲኑ እስካልተጋጩ  ድረስ በመከተል ከቀደር ወደ ቀደር እየሸሹ ራስንና ሌሎችንም መጠበቅ ተገቢ ነው እንላልን።

✍🏻ኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም

@yasin_nuru @yasin_nuru

11.8k 0 39 21 122

የዝሙት ሰበብና መዘዞች

   ዝሙት አላህ እጅግ የሚጠላው ከባድ ወንጀል ነው።ከኣኺራ በፊትም እዚሁ ዱኒያ ላይ ወንጀሉን ከሚፈጽሙት ግለሰቦች አልፎ  ለሀገርና ለዓለም የሚተርፉ ብዙ መዘዞች አሉት!

ለዚህም ነው አላህ ዝሙትን አትስሩ ሳይሆን "ዝሙትን አትቅረቡት" ያለው።
ኣይ ብሎ ዝሙትን የቀረበው ሰው ብዙ ጊዜ እራሱን ዝሙት ላይ ወድቆ ነው የሚያገኘው!

  የዝሙት መስፋፋት እና ወንጀሉ ላይ የመውደቅ ሰበብቦች ብዙ ሲሆኑ
ከነዚህም በጥቂቱ:-

1/ ስሜት ቀስቃሽ ምስሎችን ማየትና እንደዘፈን ያሉ ድምጾችን ማድመጥ፣

2/ በዲኑ ከማይፈቀድ ተቃራኒ ጾታ ጋር ተነጥሎ/ ተገልሎ መቆየት፣

3/ በወንድና በሴት መካከል የሸሪዓን ስርዓት የጣሰ ቀረቤታ እንዲሁም ቀልድና ጨዋታ መኖር፣

4/ "ልንጋባ ነው" በሚል ምክንያት ኒካሓ ሳይታሰር በፊት መቀራረብና ወሬ ማብዛት!

5/ ከላይ ሲታዩ ጥሩ የሚመስሉ ሰዎችን በማመን ቀርቦ ሳያጣሩ ራስንም ይሁን ልጅን ወይም እህትን ለነሱ በማይገባ መልኩ አሳልፎ መስጠት (መጠጋት)!

6/ ለሕክምና፣ ለሩቃ፣ ለትምህርት፣ ለስራና ወዘተ እያሉ ሴቶች ያለ አጃቢ ወንድ (ወሊይ) ባዕድ ወንድ ጋር መቅረብ!

7/ በቢሮ ስራ ምክንያት የሴትና ወንድ መቀራረብና አንዳምዴም አምሽቶ መግባት፣ ከዚህም አልፎ ከስራ አለቃ ጋር ክብርን ጥሎ መቀራረብ!

8/ ከተማ ውስጥም ይሁን ከከተማ ውጪ፣ ሀገር ውስጥም ይሁን ከሀገር ውጭ ሴት ልጅ ከባዕድ (መሕረም ካልሆነ) ወንድ ጋር በአንድ መኪና ውስጥ  መጓዝና  ወዘተ

♦️የዝሙት ወንጀል ላይ መውደቂያ ምክንያቶች ናቸው።

♦️እህቴ ሆይ፥ በምንም ምክንያት ከባእድ ወንድ ጋር አንድ ክፍል፣ አንድ ግቢ፣ አንድ መኪና ውስጥ ለአፍታ እንኳ ቢሆን እንዳትቆዪ!!

ይህን ምክር ያልተገበርሽ እንደሆነ በዋነኝነት የምትጎጂው አንቺው እራስሽ ነሽ።

🏷️ነቢዩ የሚከተለውን ብለዋል "ባዕድ ወንድና ባዕድ ሴት ለብቻቸው ተነጥለው አይቆዩም ሶስተኛቸው ሽይይጣን ቢሆን እንጂ!"ሽይጣን ደግሞ በመጥፎ ነገር ያዛል!

▪️ወንድሜ ሆይ ከእሳትና ከአውሬ ከምትሸሸው በላይ ከዝሙትና ከበሮቹ ሽሽ!
▪️እህቴ ሆይ ባልሽን ከእህትሽ፣ ከሰራተኛሽ ወዘተ ጋር ትተሽው አትሂጂ!

▪️ሀገር ውስጥም ይሁን ውጭ ሀገር ሰው ቤት በሰራተኝነት ተቀጥረሽ የምትሰሪ እህቴ ሆይ ከወንድ አሰሪሽም ጋር ይሁን ከልጆቹ ወዘተ ጋር ለአፍታም እንኳ ቢሆን ለብቻሽ እንዳትሆኚ ዲንሽም ዱኒያሽም እንዳይበላሽ ተጠንቀቂ!

አላህ በዱኒያ ከውርደት በኣኺይራእሳት ይጠብቀን

     ኣሚን

@yasin_nuru @yasin_nuru

12.5k 0 79 61 244



የደስታ ግማሹ ፣ " እናት " ነች ።

ቀሪው ግማሽ ደግሞ ፣ " የእናት ዱዓ " ነው ።

@yasin_nuru @yasin_nuru

12.8k 0 55 53 476
20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.