🔰 ካዕባን አናመልክም፣ወደ ካዕባ አቅጣጫ ለምን እንሰግዳለን ?🔰➸ በመጀመሪያ እኛ ሙስሊሞች የምናመልከው የምንሰግደው
ለአምላካችን አላህ ብቻ ነው። አላህ በቁርአኑ እንዲህ ይላል👇
فَاسْجُدُوا لِلَّهِ وَاعْبُدُوا
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡[📗
ነጅም 53:62]
أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ
وَبَشِيرٌ
(እንዲህ በላቸው)፡- «
አላህን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ እኔ ለእናንተ ከርሱ (የተላክሁ) አስፈራሪና አብሳሪ ነኝ፡፡»
[📗 ሁድ 11:2]➤➤ ከአንቀፆቹ ምንረዳው ከአላህ ውጭ ያሉ ነገሮች ማምለክ እና መስገድ እንደማይቻል ነው።
➸ እንድናመልከው የታዘዝነው የካዕባን
ጌታን አላህን እንጂ ካዕባን አይደለም።
فَلْيَعْبُدُوا رَبَّ هَٰذَا الْبَيْتِ
ስለዚህ የዚህን ቤት (
የከዕባን) ጌታ ይግገዙ፡፡[📗
የቁረሾች ምዕራፍ 106:3]
➸ ካዕባ ምንም መጥቀምም መጉዳትም የማይችል የተፈጠረ ነገር ስለሆነ
በካዕባ መማል ተከልክሏል።👇
" አንድ አይሁዳዊ ወደ ነቢያችን መጣና እንዲህ አለ "እናንተኮ ይሄ ነገር የሆነው
አንተና አላህ የሻችሁት ስለሆነ ነው ፣
በካዕባ እምላለሁ እያላችሁ
ሽርክ ትፈፅማላችሁ(በአላህ ላይ ታጋራላችሁ) አላቸው።
ነቢዩም ሶሀቦችን መማልን በፈለጉ ግዜ
በካዕባ ጌታ እምላለሁ እንዲሉ እና አላህ የሻው ከዚያም አንተ የሻሀው ነገር ነው እንዲሉ አዘዟቸው።
📚
ሱነኑ ነሳኢይ ሀዲስ 3773➤ ሀዲሱ ላይ በካዕባ መማል
መከልከሉ ለካዕባ አምልኮት መስጠት እንደማይቻል ያሳየናል።
➸ ካዕባ ምንም መጥቀምም መጉዳትም የማይችል የተፈጠረ ነገር ስለሆነ "
የካዕባ ባሪያ" ተብሎ መሰየም ተከልክሏል። -ዐብዱል ዓምር(የዐምር ባሪያ)፣
ዐብዱል ካዕባህ(የካዕባ ባሪያ) ወዘተ እያሉ ከአላህ ውጭ ላሉ አካላት ባርነት በመሰጠት የተሰየመ ስምን መጠቀም ክልክል በመሆኑ ላይ የኢስላም
ሊቃውንት ተስማምተዋል።
📘
መራቲቡል ኢጅማዕ 179📘
ኪታቡ ተውሒድ ገፅ 295📘
ፈታዋህ ኑሩን ዓላ ደርብ ቅጽ 18 ገፅ 240➤ ካዕባ አምልኮት የሚሰጠው ቢሆን ኖሮ የካዕባ ባርያ ማለትን ባልተከለከለ ነበር።
➸ በተጨማሪም በነቢያችን ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘመን ሀበሻዊው ቢላል ከካዕባ ላይ ወጥቶ አዛን ያደርግ እንደነበረ የታወቀ ነው።
ካዕባ ድንጋዩ አምላካችን ቢሆን ኖሮ
አምላኩ አናት ላይ ወጥቶ አዛን አደረገ ማለት አያስኬድም። አምላክ ብለው ቢያምኑ ኖሮ እላዩ ላይ ባልወጣ ነበር።🖐በእስልምና ካዕባ ምንም የማይጠቅም የማይጎዳ ድንጋይ ነው ብለን የምናምነው።
➸
ከአላህ ውጭ ማታመልኩ ከሆነ ወደ ካዕባ(መካ ላይ ያለ ድንጋይ) አቅጣጫ ለምን ትሰግዳላችሁ?? ከተባለ
እኛ ሙስሊሞች ወደ ካዕባ ዙረን ምንሰግደው
➸
ለስግደታችን አቅጣጫ ስለሆነ ነው። የምትሰግዱት ለአላህ ብቻ ከሆነ ካዕባን ማታመልኩት ከሆናችሁ
ለምን ወደ ሌላ አቅጣጫ ለምን አትሰግዱም? ከተባለ
መልሱ:- አላህ ለአቅጣጫችን ካዕባ ያደረገልን
የሙስሊሞችን አንድነት ለማስጠበቅ ብሎ ነው። ማለትም ወደ ፈለግንበት አቅጣጫ መስገድ የተፈቀደ ቢሆን ኖሮ
1.
ሙስሊሞች አንድ አይሆኑም ነበር(ይለያያሉ)። አላህ ደግሞ አንድ እንድንሆን አዞናል።
2.
በጀመዓ እንድንሰግድ የታዘዝነውን ሰላት መፈፀም አያስመችም።ለምሳሌ:- እኔ መስጂድ ገብቼ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ ብሰግድ ሌላው ደግሞ ወደ ሰሜን አቅጣጫ ቢሰግድ ሌላው ወደ ሌላ ከሰገደ በጀማዓ(
በህብረት) ስገዱ የተባለው ሶላት መስገድም አያስመችም። አንዱ ወደ ቀኝ ሌላኛው ወደ ግራ ዙረው ጀማዓ ሰላት አያስመችም።
2.
ሙስሊሞች አንድ አይሆኑም ጭቅጭቅ ወደዚህ አቅጣጫ ነው ምሰግደው..እያሉ መለያየት ይከሰታል።➸ አላህ ደግሞ አትለያዩ ብሎ መለያየትን ከልክሎናል።
وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ
የአላህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡
አትለያዩም፡፡
[ 📗ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 103 ]
🚩ስለዚህ ወደ ካዕባ ምንዞረው ለስግደታችን አቅጣጫ እንጂ ካዕባን ስለምናመልክ አይደለም።
አይ ወደ ካዕባ ዞራችሁ ስለምትሰግዱ ካዕባን እያመለካችሁ ነው ብለው ድርቅ ካሉ👇
➸ ነቢዩ ሙሀመድ ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ለ 16 ወራት ያህል
ወደ ቤይቱል መቅዲስ አቅጣጫ (ፍሊስጢን ላይ የሚገኘው መስጅድ) ሰግደዋል። ይህ ማለት መስጅዱን እያመለኩ ነበር ማለት ነውን?? በፍፁም የሶላት አቅጣጫቸው ነበረንጂ መስጂዱን እያመለኩት አልነበረም።
ነቢዩ ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም የሶላት አቅጣጫቸው ወደ ካዕባ እንዲቀየር ይፈልጉ ነበርና
አላህ ተቀብሏቸው ወደ ካዕባ እንዲቅጣጩ የሚያዝ የቁርአን አንቀፅ ወረደ።
አላህ እንዲህ ይላል
قَدْ نَرَىٰ تَقَلُّبَ وَجْهِكَ فِي السَّمَاءِ ۖ فَلَنُوَلِّيَنَّكَ قِبْلَةً تَرْضَاهَا ۚ فَوَلِّ وَجْهَكَ شَطْرَ الْمَسْجِدِ الْحَرَامِ ۚ وَحَيْثُ مَا كُنتُمْ فَوَلُّوا وُجُوهَكُمْ شَطْرَهُ ۗ وَإِنَّ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ لَيَعْلَمُونَ أَنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّهِمْ ۗ وَمَا اللَّهُ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ
የፊትህን ወደ ሰማይ መገላበጥ በእርግጥ እናያለን፡፡
ወደምትወዳትም ቂብላ እናዞርሃለን፡፡
ስለዚህ ፊትህን ወደ ተከበረው መስጊድ (ወደ ካዕባ) አግጣጫ አዙር፡፡ የትም ስፍራ ብትኾኑም (ስትሰግዱ)
ፊቶቻችሁን ወደርሱ አግጣጫ አዙሩ፡፡ እነዚያም መጽሐፉን የተሰጡት እርሱ ከጌታቸው ሲኾን እውነት መሆኑን ያውቃሉ፡፡ አላህም ከምትሠሩት ሥራ ዘንጊ አይደለም፡፡[📗በቀራህ 2:144]
☝️ካዕባ የሰላት አቅጣጫ እንጂ አምላካችን አይደለም።
➸በተጨማሪም አንድ መንገደኛ የካዕባ አቅጣጫ የት እንደሆነ ባያውቅ መጀመሪያ አቅጣጫውን ለማወቅ ይጥራል። ማወቅ ካልቻለ
ወደ ፈለገበት አቅጣጫ ይሰግዳል። ይህ ማለት ካዕባን ክዶ ለሌላ ይሰግዳል ማለት ነውን??በፍፁም
ምክንያቱ የምንሰግደው ለካዕባ ሳይሆን ለአላህ ስለሆነ ነው።
አላህ ደግሞ👇
وَلِلَّهِ الْمَشْرِقُ وَالْمَغْرِبُ ۚ فَأَيْنَمَا تُوَلُّوا فَثَمَّ وَجْهُ اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ وَاسِعٌ عَلِيمٌ
ምሥራቁም ምዕራቡም የአላህ ነው
(ፊቶቻችሁን) ወደ የትም ብታዞሩ የአላህ ፊት እዚያ ነው፡፡ አላህ ችሮታው ሰፊ ዐዋቂ ነውና፡፡[📗
በቀራህ 2:115]➸ በተጨማሪም የትኛውም ሙስሊም
ሲሰግድ አላህ እንጂ ካዕባ በልቡ ውል አትልም። ምክንያቱም ወደ ካዕባ ሚዞርበት አላማው
ለአቅጣጫ እንጂ እሷን ለማምለክ ስላልሆነ ነው።
➸ በእስልምና ቀደምት ነቢያት የሚቅጣጩበት ቦታ ነበራቸው። ለምሳሌ
ወደ ቤይቱል መቅዲስ(ፋሊስጢን ላይ ሚገኘው መስጂድ) ይቅጣጩ ነበር። ወደዛ መስጂድ መቅጣጨታቸው እሱን ያመልኩ ነበር ማለት ነውን? በፍፁም የሰላት አቅጣጫ እንጂ ለሷ አምልኮ እየሰጡ አይደለም። ነቢዩ ኢብራሂም(አብረሀም)፣ ልጃቸው እስማዒል እና ሌሎች ነቢያት ወደ ካዕባ ዙረው ይሰግዱ ነበር።
📚
መጅሙዕ አልፈታዋ ቅጽ 27 ገፅ 11☝️እና ቀደምት ነቢያት ወደ ካዕባ ዙረው ሲሰግዱ ካዕባን ያመልኩ ነበር ማለት ነውን? በፍፁም። የሰላት አቅጣጫ እንጂ ካዕባን እያመለኩ አይደለም።
https://t.me/iwnetlehullu1