ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Bloglar


የ ያሲን ኑሩ ሐዲሶች
Yasin Nuru
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራውን ሰው ያህል አጅር ያገኛል" ረሱል (ﷺ)
"የበጎ ስራ ምላሹ በጎ እንጂ ሌላ አይደለም "  
የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሰራ ሰው ያገኘዋል :>> { አል -ዘልዘለህ 7}
This is not official
ለአስተያየት👇👇
@Hasabbbbot

ሀዲሶችን ከፈለጋችሁ👇👇
@yasin_nuru_hadis

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Bloglar
Statistika
Postlar filtri


የነብዩ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ታሪክ ✍

❶) ጥያቄ፦የነብያችን (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ስም ማን ይባላል ?

መልስ፦ ሙሃመድ ኢብኑ ዐብደላህ ኢብኑ ዐብደል ሙጠሊብ ኢብኑ ሀሺም ፡ሀሺም (ከቁረይሽ ጎሳ ሲሆኑ)፡ ቁረይሾች ደግሞ ከአረብ ናቸዉ አረቦች ደግሞ ከነብዩላህ ኢስማዒል(አለይሂ ሰላም) ዝርያ ናቸዉ።

❷), ጥያቄ፦ነብያችን(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) መቼ ቀን ነዉ የተወለዱት ?

መልስ፦ ሰኞ ቀን ተወለዱ።

➌), ጥያቄ፦ ነብያችን(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱት የት ሀገር ነዉ ?

መልስ፦የተወለዱት ሀገር(መካ) ነዉ።

➍),ጥያቄ፦ የነብያችን(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) አባት የሞተዉ መቼ ነበር ?

መልስ፦ አባታቸዉ የሞተዉ በእናታቸዉ መህፀን ዉስጥ ሳሉ ነዉ።

➎), ጥያቄ፦ የነብያችን(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቀልብ (ልብ)የተቀደደዉ መቼ ነበር ?

መልስ፥ ልባቸዉ የተቀደደዉ የአራት አመት ህፀን ሳሉ ነበር።

❻), ጥያቄ፦የነብያችን(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) እናት የሞተችዉ መቼ ነበር ?

መልስ፦እናታቸዉ የሞተችዉ(የስድስት)አመት ህፀን ሳሉ ነበር)።

❼),ጥያቄ፦የነብያችኝ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እናት ከሞተች ቡሃላ አሳዳጊያቸዉ ማን ነበረ ?

መልስ፦አያታቸዉ(ዐብደል ሙጠሊብ)ከዚያ ኡሱ ከሞተ ቡሃላ አጎታቸዉ (አቡ ጧሊብ)።

➑),ጥያቄ፦ነብያችንን(ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) አላህ ነብይ አድርጎ የላካቸዉ መቼ ነበር ?

መልስ፥ በአርባ አመታቸዉ።

❾) ጥያቄ፦የነብያች(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)
ልጆች ስንት ናቸዉ ? ስማቸዉስ ?

መልስ፦ ሰባት ናቸዉ። ስማቸዉም፦

❶.ቃሲም
❷.አብደላህ
➌.እብራሂም
➍.ዘይነብ
❺.ሩቂያ
❻.ፋጢማ
❼.ኡሙ ኩልሱም...ይባላሉ


#ረመዳን_8_ቀናቶች_ይቀሩታል። 14/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

3.7k 0 85 15 172

            ከእኩዮቹ ተነጥሎ🥺🥺
           ያህፃን ሲያለቅስ ቁጭ ብሎ💔

ቢያዩት  የዐለሙ ጀማል🤗🤗
ነቢ አሉት ምንስ ሁነሃል👀👀

              ህፃኑም አለ ለዘይኔ❤️❤️
               አባቴ ሞቶብኝ እኔ 😭😭

ሌላ ባል አግብታ እናቴ🤷‍♂🤷‍♂
አባሮኝ የእንጀራ አባቴ 🤔🤔

         ምበላውም ምለብሰው የለኝ😔😔
          እህት  የለኝ ወንድምም የለኝ😔😔

ሚጫወቱት ልጆች በሙላ🏃‍♀‍➡️🏃‍➡️
አባት አላቸው በጠቅላላ 👨‍🍼🧑‍🍼


         ይህ ማልቀሴ  የኔ ማንባቴ🥹🥹
         ትዝ ቢለኝ ነው እኮ አባቴ💔💔

ይህንን ሲል እጁን ይዘውት💞💞
እኔ አባትህ አለሁህ አሉት❤️‍🔥❤️‍🔥


#ረመዳን_9_ቀናቶች_ይቀሩታል። 13/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

5.3k 0 87 38 245

#የ25ቱ_ነቢያት_ስም_እና ቁርዓን_ላይ_የተጠቀሱበት_ቦታ

👉ካነበባችሁ በኋላ ለሌሎች ማስተላለፍ አትርሱ👈

#1 አደም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#2 ኢድሪስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#3 ኑሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ30 ሱራዎች በ50 አንቀጾች ውስጥ 50 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#4 ኢብራሒም(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ25 ሱራዎች በ63 አንቀጾች ውስጥ 69 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#5 ሉጥ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ14 ሱራዎች በ27 አንቀጾች ውስጥ 27 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#6 ኢስማዒል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ8 ሱራዎች በ12 አንቀጾች ውስጥ 12 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#7 ኢስሐቅ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ12 ሱራዎች በ16 አንቀጾች ውስጥ 17 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#8 የዕቁብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ10 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 16 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#9ሁድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 3 ሱራዎች በ7 አንቀጾች ውስጥ 7 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#10 ሷሊሕ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ9 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#11 ሹዐይብ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ10 አንቀጾች ውስጥ 11 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#12 ሙሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ34 ሱራዎች በ131 አንቀጾች ውስጥ 136 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#13 ሀሩን(ዐለይሂ ሰላም)፡-  ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ13 ሱራዎች በ20 አንቀጾች ውስጥ ለ 20 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#14 ዳዉድ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርአን ውስጥ በ9 ሱራዎች 16 አንቀጾች ውስጥ ለ 16 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#15 ሱለይማን(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ7 ሱራዎች 16 አንቀጾች ውስጥ ለ 17 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#16 ኢልያስ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 1 ሱራ በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#17 አዩብ( ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#18 ዩኑስ(ዐለይሂ ሰላም)፡-  ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#19 ዩሱፍ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ 3 ሱራዎች በ26 አንቀጾች ውስጥ ለ 27 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#20 በአል-የሰዕ(ዐለይሂ )፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ 2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#21 ዙል-ኪፍል(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ  በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ2 ሱራዎች በ2 አንቀጾች ውስጥ ለ ስም2 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#22 ዘከሪያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ6  ውስጥ ለ 7 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#23 የሕያ(ዐለይሂ ሰላም)፡- አንቀጾችይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ5 አንቀጾች ውስጥ ለ 5 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#24 ዒሳ(ዐለይሂ ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ11 ሱራዎች በ25 አንቀጾች ውስጥ ለ 25 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#25 ሙሐመድ❤️❤️(ዐለይሂ ሶላቱ ወስ-ሰላም)፡- ይህ ስም በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ በ4 ሱራዎች በ4 አንቀጾች ውስጥ ለ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፡፡

#ረመዳን_10_ቀናቶች_ይቀሩታል። 12/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

6.4k 0 153 60 149

#ለበጎ_ነው

በአንድ ወቅት አንድ ወጣት ለፈጣሪው ፀሎት ለማድረስ ራቅ ወዳለ ስፍራ ይሄዳል ፣

በዚህም ወቅት ወደ ፀሎት ቦታ የሚሄዱት ተሳፋሪዎች በጉዞ መሀል ምሳ ለመብላት ወደ አንድ ካፌ ይወርዳሉ ።

ወጣቱም ከነሱ ጋር አብሮ በመውረድ ምግብ አዞ መመገብ ይጀምራል ።

ተመግቦም ከጨረሰ በኃላ ሂሳብ ለመክፈል ወደ ኪሱ ሲገባ ዋሌቱን ያጣዋል

ለ ሆቴሉ ማናጀርም ዋሌቱ እና ብሩ በሌባ መሰረቁን ያስረዳዋል ፣

ከዛም ከተማ ላለው ጓደኛው ደዉሎ የሆነውን ይነግረዋል ።

ጓደኛውም ገንዘብ ይልክለትና አመስግኖ ሂሳቡን ከፍሎ ሲወጣ ባሱ ስለቆየበት ጥሎት ይሄዳል ።

ከዛም በጣም አዝኖ ወደ ጓደኛው ዘመድ ቤት ያቀናል፣

እነሱም ጋር ለ 2 ቀን አድሮ ወደ ፀሎት ቦታው እንዲሸኙት ይጠይቃቸዋል ፣

እነሱም ያሳፍሩታል! ፀሎት ቦታውም ጋር ለ 2 ቀን አድሮ ወደ ቤቱ ወዳጁ ያሳፍረዋል ፣

ወደ ቤቱም ሲገባ እያለቀሱ ከቤቱ የሚወጡ ሰዎች ችን ይመለከታል ። ከዛም ፈጠን ብሎ ወደ ቤት ሲገባ ሰዎቹ እንዳለ በፍርሀት እና ድንጋጤ ይጮሀሉ።

እሱም ማን እንደሞተ እያለቀሰ ይጠይቃቸዋል ፣

ከጎረቤቱም አንዱ ጠጋ ይልና > ይለዋል፣

ወጣቱም ስላጋጠመው ችግር በሰከነ መልኩ ያስረዳቸዋል ።

በአደጋውም ከባድነት የሰዎች መልክ ባለመለየቱ ያንተን ዋሌት በኪሱ ይዞ ስናይ አንተ መስለከን ከቀበርነው ዛሬ 4ኛ ቀናችን ነው ይለዋል🥹🥹

ለካ በወጣቱ ቦታ የተሳፈረው የወጣቱን ዋሌት የሰረቀው ሰው ነበር -


#ረመዳን_11_ቀናቶች_ይቀሩታል። 11/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

7.5k 0 82 27 213

#ልብ_የሚነኩ_የአለማችን_ሙስሊም_ወገኖቻችን_4_ንግግሮች:-

1- በሶሪያ ጦርነት የቆሰለው ህፃን ለዶክተሩ

«እኔ ወደ ፈጣሪ መሄዴ ነው የሆነውን ሁሉ እነግረዋለው!»😢

2-ኢራቅ ሞሱል ውስጥ ቆስላ እየሮጠች ካሜራማኑ ሲቀርፃት

«አጎቴ እባክህ ቪዲዮ አትቅረጸኝ ምክንያቱም ሂጃብ አለበስኩም!»😭

3- አንድ ህፃን በፍልስጤም እጅግ በጣም ይራብና

«ፈጣሪ ሆይ እባክህ በቶሎ ወሰደኝ አንተ ከወሰድከኝ በጀነት ውስጥ አልራብም እዛ እበላለሁ»😔

4- በአፍጋኒስታን ጦርነት እጁ ክፉኛ የቆሰለው ህፃን ለሕክምና ዶክተር ጋር ወስደውት ለዶክተሩ

«ዶ/ር እጄን ስትቆርጠው ልብሴን አትቁረጠው ተጠንቀቅ ምክንያቱም እኔ ሌላ ልብስ የለኝም እና» አለው። 😢


#ረመዳን_12_ቀናቶች_ይቀሩታል። 10/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

7.9k 0 62 35 322

በዚህ✨#ረመዳን✨አላህ🥰 ያላሰባችሁትን✨ሪዝቅ✨ይስጣችሁ ✨✨✨✨


#ረመዳን_13_ቀናቶች_ይቀሩታል። 9/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

8.1k 0 25 175 402

#እኛስ_በ20_አመታችን❓

🔖#ዐምር ኢብን ሰለማ ገና በ7 አመቱ ቁርኣን በመሀፈዙ ብቻ ታላላቅ ሰሐቦችን ጭምር #ያሰግድ ነበር።

🔖#አብደላህ ኢብኑ አባስ ነብዩን እግር በእግር እየተከተለ በሄዱበት አብሯቸው እየሄደ "#ጌታዬ ሆይ በዲን ውስጥ አዋቂ አድርገው የነገሮችንም ፍቺ #አሣውቀው" የሚለውን ዱዓ ከሳቸው ሲወስድ ገና የ13 አመት #ታዳጊ ነበር።

🔖#ነብዩላህ ኢብራሂም የሙሽሪኮችን #ጣዖቶች ሲጨፈጭፋና ተይዘው ወደ እሳት ሲወረወሩ 16 #አመታቸው ነበር።

🔖ነብዩ #ኢስማኤል የአባቱን የነብዩላህ ኢብራሂምን እና የጌታውን ቃል #በማክበር እንደ በግ ለመስዋትነት #ሲጋደም 15 አመት አልሞላውም ነበር።

🔖#ኡሳማ ኢብን ዘይድ በ18 አመቱ እነ አቡበክርን ጨምሮ ታላላቅ ሰሀቦች የነበሩበትን #ጦር እንዲመራ በረሱል ሰለላሁ ዐለይህ ወሰለም #ተሾመ።

🔖#ሙዓዝ ኢብን ጀበል ገና በ20 አመቱ ለኢስላም ተልዕኮ ወደ የመን #በአምባሳደርነት ተላከ።

🔖#አስማዕ ቢንት አቡበክር አስሲዲቅ ረሱል ሰለላሁ ዐለይሂ  ወሰለም እና አባቷ #ከቁረይሾች በዋሻ ውስጥ በተደበቁ ጊዜ በየቀኑ 5 ኪሜ ያህል #ተጉዛ ስንቅ ስታመላልስ ገና የ23 አመት ኮረዳና የ7 ወር ነፍሰ #ጡር ነበረች።

🔖#ሰዐድ ኢብን ሙዓዝ በ30 አመት ሰልሞ ለ6 አመታት ብቻ በእስልምና ኖረ ሲሞት ግን #የአርረህማን ዐርሽ ተንቀጠቀጠለት። ምን #ቢሰራ ነው❓

🔖#ኢማም አሻፊዒ ገና በ6 አመታቸው ቁርኣንን #ሀፈዙ በ15 አመታቸው #ሙፍቲ ሆኑ።

#አሁን አኔ አንተ አንቺ #ባለንበት የእድሜ ደረጃ #በኢላለማዊ ዕውቀታችን #በኢስላማዊ እሴታችን እውን በተግባሮቻችን ለኢስላም በመስራት እውን #ኢስላም ከኛ የሚፈልገውን ያህል ሰርተናልን?!
#ፍርዱን_ለህሊናችን_እንስጠው


✨✨✨✨

#ረመዳን_13_ቀናቶች_ይቀሩታል። 9/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

8.9k 0 86 9 153

ቅደም ተከተል‼️
=========
ሙስሊም የቡኻሪ ተማሪ ነው፣
⬇️
ቡኻሪ የኢማሙ አህመድ ተማሪ ነው፣
⬇️
ኢማሙ አህመድ የሻፊዒ ተማሪ ነው፣
⬇️
ሻፊዒ የማሊክ ተማሪ ነው፣
⬇️
ማሊክ የናፊዕ ተማሪ ነው፣
⬇️
ናፊዕ የአዕረጅ ተማሪ ነው፣
⬇️
አዕረጅ የአቡ ሁረይራ ተማሪ ነው፣
⬇️
አቡ ሁረይራ የረሱል (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ተማሪ ነው።

ሰሉ አለ ነቢይ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም

#ረመዳን_14_ቀናቶች_ይቀሩታል። 8/6/2017


@yasin_nuru @yasin_nuru

9.8k 0 134 40 256

ፈገግተኛው ጀናዛ
****


(
ምን ብታይ ይሆን እንዲህ ፈገግ ያልከው)
ጌታዬ ሆይ! ብዕሬን እንደ ኻሊድ ኢብኑል ወሊድ ሠይፍ የሰላ
አድርግልኝ

መዲነቱል ሙነወራ ውስጥ ጀናዛ በማጠብ ሥራ ላይ የተሠማራ አንድ ግለሠብ በሬሳ አጠባ ወቅት ከገጠሙት ድንቅ ነገሮች መካከል አንዱን እንዲህ ሲል ይተርክልን ይዟል…

"ተክለ ሰውነቱ ከሲታ ሲበዛ የቀጨጨ አካሉ በተበጫጨቀ ልብስ የተሸፈነ ካገኘ በልቶ ካጣም ባዶ ሆዱን የሚያድር የአላህ ባርያ።

ለሊት ለተሀጁድ ቆሞ የጌታውን ቁርአን
እያነበነበ የሚያነጋ። ከሰዎች አይቀላቀልም ብቸኝነት የህይወት ጌጡ ናት። በተበጫጨቀ ጨርቅ የተሸፈነ ጀናዛውን ወደ ማጠቢያ ክፍሉ ይዘነው ገባን በተዘረጋው የጀናዛ ማጠቢያ እንጨት ላይ አስተኝተን ልብሱን አወለቅንለት።

ጆሯችን መልካም ይሰማ ዘንድ በማሰብ ቁርአን በስፒከር ከፍ አድርገን ከፍተን ማጠብ ጀመርን።

ነፍሴ በእጄ በሆነችው ጌታ እምላለሁ ጀናዛው የቁርአን አንቀፆቹን ሲሰማ ፈገግ አለ ከፈገግታው የተነሳ ጥርሶቹ ተከፍተው ድዶቹ ይታዩ ጀመር።

ቁርአኑን ስንዘጋው የተከፈቱት ነጫጭ ጥርሶቹ ይከደናሉ የቁርአኑን ድምፅ ከፍ ስናደርገው
ፈገግታና ሳቅ ከፊቱ ላይ ይታያል። በግርምት ተውጠን የሱን መልካም ኻቲማ እንዲወፍቀን አላህን እየተማፀንን አጥበን ጨረስን" ይሉናል
የታሪካችን አቅራቢ።

ገጠመኙን እንዲህ በማለት ቀጠሉት "ከተቀበረ ከአስራ ሁለት አመታት በኋላ የመቃብሩ ስፍራ ለልማት ተፈለገና ተለዋጭ ቦታ ተሰጠን በቅርብ ጊዜ የሞቱትን አፅማቸውን አውጥተን ወደ አዲሱ የመቃብር ስፍራ ወሰድን።

ከቀናት በኋላ ተጠራንና ወደቦታው አቀናን ከአንድ ጉድጓድ አጠገብ ስራውን ያቆመ አንድ ዶዘር ወዳለበት አካባቢ ስንጠጋ ደስ የሚል ጠረን ይሸተን ጀመር ወላሂ ከፈኑ እንኳ አልበሰበሰም ሰውነቱም አልተቀየረም ከሰአታት በፊት የተቀበረ አዲስ ጀናዛ ነበር የሚመስለው አፈር አካሉን መብላትን እንቢ አለች ቁርአንን ታቅፎ የኖረን ሰውነት ለመብላት እንዴትስ ያስችላታል?!

ከፈኑን ስንገልጠው ያ ቁርአን ሲሰማ የሚንቀሳቀሰው ጀናዛ ነበር"

«የውመል ቂያማ ለቁርአን ባልደረባ አንብብ ደረጃውንም ከፍ ብለህ ውጣ ያንተ ማረፊያ የመጨረሻ አንቀፅ ቀርተህ በቆምክበት ስፍራ ላይ ነው ይባላል»

እውነተኛ ታሪክ እንጂ ልቦለድ አይደለም
አንብቦ ለሌላ ባካፈለ ሰው ላይ ሁሉ የአላህ እዝነት ይስፈንበት


#ረመዳን_15_ቀናቶች_ይቀሩታል። 7/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru

13.2k 0 279 31 207

🔰 ካዕባን አናመልክም፣ወደ ካዕባ አቅጣጫ ለምን እንሰግዳለን ?🔰

➸ በመጀመሪያ እኛ ሙስሊሞች የምናመልከው የምንሰግደው ለአምላካችን አላህ ብቻ ነው
አላህ በቁርአኑ እንዲህ ይላል👇
فَاسْجُدُوا لِلَّهِ وَاعْبُدُوا
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡
[📗 ነጅም 53:62]

أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ
وَبَشِيرٌ
(እንዲህ በላቸው)፡- «አላህን እንጂ ሌላን አትገዙ፡፡ እኔ ለእናንተ ከርሱ (የተላክሁ) አስፈራሪና አብሳሪ ነኝ፡፡»
[📗 ሁድ 11:2]
➤➤ ከአንቀፆቹ ምንረዳው ከአላህ ውጭ ያሉ ነገሮች ማምለክ እና መስገድ እንደማይቻል ነው።
➸ እንድናመልከው የታዘዝነው የካዕባን ጌታን አላህን እንጂ ካዕባን አይደለም

فَلْيَعْبُدُوا رَبَّ هَٰذَا الْبَيْتِ
ስለዚህ የዚህን ቤት (የከዕባን) ጌታ ይግገዙ፡፡
[📗 የቁረሾች ምዕራፍ  106:3]

➸ ካዕባ ምንም መጥቀምም መጉዳትም የማይችል የተፈጠረ ነገር ስለሆነ በካዕባ መማል ተከልክሏል።
👇
" አንድ አይሁዳዊ ወደ ነቢያችን መጣና እንዲህ አለ "እናንተኮ ይሄ ነገር የሆነው አንተና አላህ የሻችሁት ስለሆነ ነውበካዕባ እምላለሁ እያላችሁ ሽርክ ትፈፅማላችሁ(በአላህ ላይ ታጋራላችሁ) አላቸው። ነቢዩም ሶሀቦችን መማልን በፈለጉ ግዜ በካዕባ ጌታ እምላለሁ እንዲሉ እና አላህ የሻው ከዚያም አንተ የሻሀው ነገር ነው እንዲሉ አዘዟቸው።
📚 ሱነኑ ነሳኢይ ሀዲስ 3773

➤ ሀዲሱ ላይ በካዕባ መማል መከልከሉ ለካዕባ አምልኮት መስጠት እንደማይቻል  ያሳየናል።

➸ ካዕባ ምንም መጥቀምም መጉዳትም የማይችል የተፈጠረ ነገር ስለሆነ "የካዕባ ባሪያ" ተብሎ መሰየም ተከልክሏል።

  -ዐብዱል ዓምር(የዐምር ባሪያ)፣ዐብዱል ካዕባህ(የካዕባ ባሪያ) ወዘተ እያሉ ከአላህ ውጭ ላሉ አካላት ባርነት በመሰጠት የተሰየመ ስምን መጠቀም ክልክል በመሆኑ ላይ የኢስላም ሊቃውንት ተስማምተዋል
📘መራቲቡል ኢጅማዕ 179
📘ኪታቡ ተውሒድ ገፅ 295
📘 ፈታዋህ ኑሩን ዓላ ደርብ ቅጽ 18 ገፅ 240
➤ ካዕባ አምልኮት የሚሰጠው ቢሆን ኖሮ  የካዕባ ባርያ ማለትን ባልተከለከለ ነበር።

➸ በተጨማሪም  በነቢያችን ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘመን ሀበሻዊው ቢላል ከካዕባ ላይ ወጥቶ አዛን ያደርግ እንደነበረ የታወቀ ነው።
ካዕባ ድንጋዩ  አምላካችን ቢሆን ኖሮ አምላኩ አናት ላይ ወጥቶ አዛን አደረገ ማለት አያስኬድም። አምላክ ብለው ቢያምኑ ኖሮ እላዩ ላይ ባልወጣ ነበር።
🖐በእስልምና ካዕባ ምንም የማይጠቅም የማይጎዳ ድንጋይ ነው ብለን የምናምነው።
ከአላህ ውጭ ማታመልኩ ከሆነ ወደ ካዕባ(መካ ላይ ያለ ድንጋይ) አቅጣጫ ለምን ትሰግዳላችሁ?? ከተባለ

እኛ ሙስሊሞች ወደ ካዕባ ዙረን ምንሰግደው
ለስግደታችን አቅጣጫ ስለሆነ ነው።
የምትሰግዱት ለአላህ ብቻ ከሆነ ካዕባን ማታመልኩት ከሆናችሁ
ለምን ወደ ሌላ አቅጣጫ ለምን አትሰግዱም? ከተባለ
መልሱ:- አላህ ለአቅጣጫችን ካዕባ ያደረገልን የሙስሊሞችን አንድነት ለማስጠበቅ ብሎ ነው። ማለትም ወደ ፈለግንበት አቅጣጫ መስገድ የተፈቀደ ቢሆን ኖሮ
1. ሙስሊሞች አንድ አይሆኑም ነበር(ይለያያሉ)። አላህ ደግሞ አንድ እንድንሆን አዞናል
2. በጀመዓ እንድንሰግድ የታዘዝነውን ሰላት መፈፀም አያስመችም።
ለምሳሌ:-  እኔ መስጂድ ገብቼ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ ብሰግድ ሌላው ደግሞ ወደ ሰሜን አቅጣጫ ቢሰግድ ሌላው ወደ ሌላ ከሰገደ በጀማዓ(በህብረት) ስገዱ የተባለው ሶላት መስገድም አያስመችም። አንዱ ወደ ቀኝ ሌላኛው ወደ ግራ ዙረው ጀማዓ ሰላት አያስመችም።
2. ሙስሊሞች አንድ አይሆኑም ጭቅጭቅ ወደዚህ አቅጣጫ ነው ምሰግደው..እያሉ መለያየት ይከሰታል።
➸ አላህ ደግሞ አትለያዩ ብሎ መለያየትን ከልክሎናል።

وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ
የአላህንም (የማመን) ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡
[ 📗ሱረቱ አሊ-ዒምራን - 103 ]

🚩ስለዚህ ወደ ካዕባ ምንዞረው ለስግደታችን አቅጣጫ እንጂ ካዕባን ስለምናመልክ አይደለም።
  አይ ወደ ካዕባ ዞራችሁ ስለምትሰግዱ ካዕባን እያመለካችሁ ነው ብለው ድርቅ ካሉ👇
➸ ነቢዩ ሙሀመድ ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ለ 16 ወራት ያህል ወደ ቤይቱል መቅዲስ አቅጣጫ (ፍሊስጢን ላይ የሚገኘው መስጅድ) ሰግደዋል። ይህ ማለት መስጅዱን እያመለኩ ነበር ማለት ነውን?? በፍፁም  የሶላት አቅጣጫቸው ነበረንጂ መስጂዱን እያመለኩት አልነበረም።
ነቢዩ  ሰላሏሁ ዐለይሂ ወሰለም የሶላት አቅጣጫቸው ወደ ካዕባ እንዲቀየር ይፈልጉ ነበርና
አላህ ተቀብሏቸው ወደ ካዕባ እንዲቅጣጩ የሚያዝ የቁርአን አንቀፅ ወረደ።
አላህ እንዲህ ይላል
قَدْ نَرَىٰ تَقَلُّبَ وَجْهِكَ فِي السَّمَاءِ ۖ فَلَنُوَلِّيَنَّكَ قِبْلَةً تَرْضَاهَا ۚ فَوَلِّ وَجْهَكَ شَطْرَ الْمَسْجِدِ الْحَرَامِ ۚ وَحَيْثُ مَا كُنتُمْ فَوَلُّوا وُجُوهَكُمْ شَطْرَهُ ۗ وَإِنَّ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ لَيَعْلَمُونَ أَنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّهِمْ ۗ وَمَا اللَّهُ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ
የፊትህን ወደ ሰማይ መገላበጥ በእርግጥ እናያለን፡፡ ወደምትወዳትም ቂብላ እናዞርሃለን፡፡ ስለዚህ ፊትህን ወደ ተከበረው መስጊድ (ወደ ካዕባ) አግጣጫ አዙር፡፡ የትም ስፍራ ብትኾኑም (ስትሰግዱ) ፊቶቻችሁን ወደርሱ አግጣጫ አዙሩ፡፡ እነዚያም መጽሐፉን የተሰጡት እርሱ ከጌታቸው ሲኾን እውነት መሆኑን ያውቃሉ፡፡ አላህም ከምትሠሩት ሥራ ዘንጊ አይደለም፡፡[📗በቀራህ 2:144]
☝️ካዕባ የሰላት አቅጣጫ እንጂ አምላካችን አይደለም።
➸በተጨማሪም አንድ መንገደኛ የካዕባ አቅጣጫ የት እንደሆነ ባያውቅ መጀመሪያ አቅጣጫውን ለማወቅ ይጥራል። ማወቅ ካልቻለ ወደ ፈለገበት አቅጣጫ ይሰግዳል። ይህ ማለት ካዕባን ክዶ ለሌላ ይሰግዳል ማለት ነውን??በፍፁም
ምክንያቱ የምንሰግደው ለካዕባ ሳይሆን ለአላህ ስለሆነ ነው።
አላህ ደግሞ👇

وَلِلَّهِ الْمَشْرِقُ وَالْمَغْرِبُ ۚ فَأَيْنَمَا تُوَلُّوا فَثَمَّ وَجْهُ اللَّهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ وَاسِعٌ عَلِيمٌ

ምሥራቁም ምዕራቡም የአላህ ነው (ፊቶቻችሁን) ወደ የትም ብታዞሩ የአላህ ፊት እዚያ ነው፡፡ አላህ ችሮታው ሰፊ ዐዋቂ ነውና፡፡[📗በቀራህ 2:115]
➸ በተጨማሪም የትኛውም ሙስሊም ሲሰግድ አላህ እንጂ ካዕባ በልቡ ውል አትልም። ምክንያቱም ወደ ካዕባ ሚዞርበት አላማው ለአቅጣጫ እንጂ እሷን ለማምለክ ስላልሆነ ነው።

➸ በእስልምና ቀደምት ነቢያት የሚቅጣጩበት ቦታ ነበራቸው። ለምሳሌ ወደ ቤይቱል መቅዲስ(ፋሊስጢን ላይ ሚገኘው መስጂድ) ይቅጣጩ ነበር። ወደዛ መስጂድ መቅጣጨታቸው እሱን ያመልኩ ነበር ማለት ነውን? በፍፁም የሰላት አቅጣጫ እንጂ ለሷ አምልኮ እየሰጡ አይደለም። ነቢዩ ኢብራሂም(አብረሀም)፣ ልጃቸው እስማዒል እና ሌሎች ነቢያት ወደ ካዕባ ዙረው ይሰግዱ ነበር።
📚መጅሙዕ አልፈታዋ ቅጽ 27 ገፅ 11

☝️እና ቀደምት ነቢያት ወደ ካዕባ ዙረው ሲሰግዱ ካዕባን ያመልኩ ነበር ማለት ነውን? በፍፁም። የሰላት አቅጣጫ እንጂ ካዕባን እያመለኩ አይደለም።
https://t.me/iwnetlehullu1


ታዋቂው አሜሪካዊው የቅርጫት ኳስ ተጨዋች ሻኪል ኦኔል፣“ትልቁ  ሻክ” በመባልም ይታወቃል፤ በትውልድ ከተማው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የተማረበትን ትምህርት ቤት ለመጎብኘት ይሄዳል።

ሻኪል ኦኔል የተማረበትን ትህምርት ቤት ሲጎበኝ የቅርጫት ኳስ መጫወቻው ቦታ ሲደረስ ጎደኛውን ጋሪ ኩፐርን አስታወሰው፤ በጣም ይወደው ነበረ፣ የነበራቸው ፍቅርና አንድነት ትዝ አለው።አሁን ግን የት እንዳለ አያውቅም ።

ሻክ በትህምርት ቤቱ ውስጥ አንድ ያልጠቀው ነገር ገጠመው።

ሻክ  የድሮ  የትህምርት ቤት ጎደኛውን ጋሪ ኩፐርን አብረው በተማሩበት ትምህርት ቤቱ ግቢ ውስጥ አገኘው። ለረጅም ግዜ ስላልተገናኙ ተቃቅፈው ሰላም ተባባሉ።ጋሪ በጣም ተጎሳቅሎና ያለእድሜው አርጅቷል።

ጋሪ እዛው ትህምርት ቤት ውስጥ የ 4ኛ ክፍል አስተማሪ ነበር። ጋሪ በአንድ ታዋቂ የቅርጫት ኳስ ተጫዋች የመሆን ህልም ነበረው። ምኞቱ ልክ እንደ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪው  ጓደኛው ሻኪል ኦኔል መሆን ነበረ ።

ጋሪ በኮሌጅ እየተማረ ከባድ  የመኪና አደጋ  ጉዳት ስለደረሰበት ታዋቂ የቅርጫት ኳስ ተጨዋች እውን የማድረግ ምኞቱ  አከተመ።

ጋሪ ብዙ ችግሮች አጋጥመውታል ፤ንግድ ጀምሮ ከሰረ፣ ትዳሩ ፈረሰ ፣ቤቱን አጣ ። በሚያስተምርበት ትህምርት ቤት መጠላያ ቤት ውስጥ  ነው የሚኖረው ።

ሻክ ኦኔል ስለ ድሮው ጎዳኛው ጋሪ የደረሰበትን ችግርና አሁን በትምርህት ቤቱ ውስጥ መጠለያ እንደሚኖር  አወቀ።

የጋሪን ሁኔታ ማየቱ የሻክ አይን እንባ አፈሰሰ፣ ጎደኛውን ለመርዳትም ተዘጋጀ ፣ ከጋሪ ስልክ ተቀብሎ ሄደ።

አንድ ቀን ጠዋት  የትምህርት ቤቱ መጠለያ  ስራ አስኪያጅ የሆነች አንዲት ሴት ድሃ አስተማሪውን ጋሪን በመኪና ይዛ በመውሰድ ወደ አንድ የሚያምር ባለ ሁለት ክፍል አፓርታማ አደረሰችው። ሴትየዋ ለጋሪ ብዙ ቁልፎቹን ሰጥታ አፖርታማው የአንተ ነው በማለት ጠረጴዛው ላይ ወዳለው ፖስታ እየጠቆመች በፈገግታ “ይህም ያንተ ነው” አለችው።

ጋሪ እጆቹ እየተንቀጠቀጡ ፖስታውን ከፈተው። ከፖስታ ውስጥ “ከልጅነት ጓደኛህ ቢግ ሻክ” የሚል ማስታወሻ ነበረ።

ከማስታወሻው ጋር  በጋሪ ስም የተመዘገቡ የአፓርታማው ንብረት ሰነዶች እና የ 5 ሚሊዮን ዶላር ቼክ አገኘ።ጋሪ በስሜት ተውጦ ፣ተንበርክኮ እንባው በፊቱ እየፈሰሰ ፣ ሻክን ደውሎ ሲያመሰግነው ሻክም እንዲህ አለው።

"እራስህን ብቻ ተንከባከብ ፣አስታውስ  ደውልልኝ ሁሌም ከአጠገብህ ነኝ።"

ጋሪ ኩፐር በቴክሳስ ውስጥ ስኬታማ ነጋዴ ነው፤  ብዙ ጊዜ ህይወቱን ስለለወጠው የሻኪል ኦኔል ደግነትን ያወራል።

የኛትኩረት ከሚል ገጽ ያገኘሁት ያስተምራል ብዬ ስላሰብኩኝ አጋራዋችሁ❤❤❤❤🙏🙏🙏🙏

#ረመዳን_16_ቀናቶች_ይቀሩታል። 5/6/2017

@yasin_nuru    @yasin_nuru


✨ለዉስጣዊ ሰላም አራት(4) አስፈላጊ ነገሮች✨

💎 #ተወኩል - በሱ በመመካት ጉዳዬን ሁሉን ቻይ ለሆነው የዓለማት ጌታ አስረክቤያለሁ። ወደሱ ተጠግቻለሁ ።

💎 #ሪዷ - አላህ የፃፈልኝና የመረጠልኝ እኔ ከማስበዉና ከምመርጠው የተሻለ ነው። ሁሌም ቢሆን እሱ በኔ የሚያደርገው ነገር መልካም ነው።

💎 #ተፋኡል - በአላህ ፈቃድ መጪው ጊዜ ምርጥ እና የተሻለ ነው። በኔ እጅ ካለው በላይ ከርሱ ዘንድ ያለዉን አምናለሁ ፤ ተስፋ አደርጋለሁ ።

💎 #ተስሊም - አላህ ወሰነው የሻውንም አደረገ። ለሁሉም መሻቶቹ ያለምንም ቅሬታ እጅ ሠጥቻለሁ።


#ረመዳን_17_ቀናቶች_ይቀሩታል። 5/6/2017

@yasin_nuru @yasin_nuru

10.5k 0 131 11 169

ሰላትን መስጂድ ሄዶ

የመስገድ ጠቀሜታዎች

1. የበለጠ አጅር እናገኛለን

ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፡-

''በጀማዓ የሚሰገደው ሰላት አንድ ሰው ብቻውን ከሚሰግደው ሶላት ሃያ ሰባት እጥፍ ይበልጣል።''

(ቡኻሪና ሙስሊም)

2. አላህ ጀነትን ያዘጋጅልናል


ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፡-

''በጧትም ሆነ በማታ ወደ መስጂድ የሄደ ሰው አላህ በሄደበት ቁጥርጀነት ነት ውስጥ ቦታ ያዘጋጅለታል።''

(ቡኻሪና ሙስሊም)

3. ወደ መስጂድ በተራመድንበት እርምጃ ልክ አጅር እናገኛለን

ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፡-

''በቤቱ ውስጥ (ውዱእ በማድረግ) ራሱን ያነፃና ከዚያም ወደ አላህ ቤቶች የግዴታ ሰላት ለመስገድ የሄደ ሰው እያንዳንዱ እርምጃ ወንጀሉን ያብስለታል እና በጀነት ያለውን ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።''

(ሙስሊም)

4. የአላህን ትእዛዝ አክባሪ እንሆናለን

''ሶላትንም ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም (ግዴታ ምጽዋትን) ስጡ፡፡ (ለጌታችሁ) ከአጎንባሾች ጋርም አጎንብሱ፡፡''

ሱራቱ አል-በቀራ 2:43

''አላህ እንድትከበርና ስሙ በውስጧ እንዲወሳ ባዘዘው ቤቶች ውስጥ (አወድሱት)። በውስጧ በጧትና በማታ ለእርሱ ያጠራሉ።''

ሱራቱ አን-ኑር 24:36

5. መላኢካዎች ዱዓ ያደርጉልናል

ነቢዩ

صلى الله እንዲህ ብለዋል፡-

''አንድ ሰው መስጂድ ውስጥ በሚሰግደው ቦታ ላይ እስካለ ድረስ (ከመስጂድ እስካልወጣ ድረስ) መላኢካዎች አላህን ምህረትን ይለምኑለታል። ''አላህ ሆይ ይቅር በለው አላህ ሆይ እዘንለት'' (በማለት ይለምኑለታል)

(አል-ቡኻሪ)

6. ፈጅር እና ዒሻን በመስጂድ ውስጥ መስገድ ከሙናፊቅነት ይጠብቀናል

ነቢዩ እንዲህ ብለዋል፡-

''በሙናፊቆች ላይ በጣም የከበደችው ሰላት ፈጅር እና ኢሻእ ናቸው። በነሱ ውስጥ ያለውን (ምንዳቸውን) ቢያውቁ ኖሮ (በደረት) መሳብ ቢገባቸው እንኳን ይመጡ ነበር።''

(ቡኻሪና ሙስሊም)


#ረመዳን_17_ቀናቶች_ይቀሩታል። 5/6/2017

@yasin_nuru @yasin_nuru

10.6k 0 92 19 152

ጨረቃ

እንደ ልብ ወዳጅ ሌት ተቀን ተናፍቃ
እንደ እናት ጉርሻ በስስት ተጠብቃ
ምድሩን አፍክታ ሰማዩን አድምቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ!

ምንዳዬን አብዝቶ ኃጢያቴን አክስሞ
ከሲዖል ‘ሚያነፃኝ ሩሄን አለምልሞ
ከቤቱ መራቄ ሽሽቴ እንዲያበቃ
አቅፎ አድራሼን ይዛ ብቅ አለች ጨረቃ።

ሳይሰስት ‘ሚያድለኝ ከሰነቀው ፀጋ
‘ሚያቆመኝ ከደጁ እዝነቱን ፍለጋ
በስክነት ተውቦ ምህረትን ተኩሎ
እነሆ ብቅ አለ በጨረቃ ታዝሎ።

አህለን ያረመዳን
አህለን ቢከ ያረመዳን
አህለን ያረመዳን
አህለን ቢከ ረመዳን
**********

እንደ ልብ ወዳጅ ሌት ተቀን ተናፍቃ

እንደ እናት ጉርሻ በስስት ተጠብቃ
ምድሩን አፍክታ ሰማዩን አድምቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ!

ነፍሴ እንዳትሰንፍብኝ ለስጋዬ አድልቼ
ፅድቁን እንዳልረሳ ለእኩይ ተረትቼ
በክብር ‘ሚያስጠራኝ ተቅዋን አጎናፅፎ
የኃጢአቴን ሸክም ከላዬ አራግፎ።

እዝነትን የቸረኝ ከስስት አርቆ
የመስጠትን ዋጋ ያሳየኝ አልቆ
ብቅ አለ ረመዳን የበጎነት ማሳ
ሳይጎድል ትውስታው ጣዕሙ ሳይረሳ።

አህለን ያረመዳን
አህለን ቢከ ያረመዳን
አህለን ያረመዳን
አህለን ቢከ ረመዳን
********

እንደ ልብ ወዳጅ ሌት ተቀን ተናፍቃ

እንደ እናት ጉርሻ በስስት ተጠብቃ
ምድሩን አፍክታ ሰማዩን አድምቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ
ብቅ አለች
ብቅ አለች ጨረቃ!

ተራዊህ ሙናጃው የሌሊት ሹክሹክታ
ሪዷውን ሽቶ የኸልዋ ቆይታ
አዝካር ሶለዋቱ የዱዓው ትውስታ
የወንድም ናፍቆት መሃባው ትዝታ።

ያንተ ትብስ አንተ ወጋችን ማሰሪያ
የመተጋገዣ ያብሮነት ማደሪያ
ተቅዋን ሊያላብስ የተኛን ሊያነቃ
የእዝነቱ ወር መጣ ብቅ አለች ጨረቃ።

በኢባዳ ወዝተው ደምቀው በአዝካሩ
ከቁርአን ሸንጎ ተርቲብ እየቀሩ
በመላእክት አክናፍ ዙሪያቸው ተከቦ
ሩሃቸው ይጠግባል ስጋቸው ተርቦ።

ኸይሩን ሚን አልፊዋን ማግኘት እየጓጉ
ሌሊቱን በስቲግፋር በዱዓ እያነጉ
የሊቃውን ፀጋ በረካውን ሽተው
ሲያነቡ ይፈጅራል የከርሞውን ናፍቀው።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የካቲት 23/2012 ተፃፈ
********

#ረመዳን_18_ቀናቶች_ይቀሩታል 4/6/2017

@yasin_nuru @yasin_nuru

11.6k 0 108 17 196

🕌አስተማሪ ታሪክ ላካፍላችሁ🕌

ጠራራ ፀሀይ ላይ ከመቃብሮች መሀል ባህሉል የተባለ የከተማው ዕውቅ እብድ ቁጭ ብሏል።

ጊዜው 160 አመተ ሂጅራ ነው በጊዜው የሙስሊሙን አለም ሲያስተዳድር የነበረው ሀሩነ-ረሺድ ድንገት ከመቃብር መሀል የተቀመጠውን እብድ ይመለከተዋል።

ንጉስ ሀሩን የማፌዝ ገፅታ እየተነበበበት፦ «አንተ ባህሉል! አንተ ቆይ መች ነው ሰው ምትሆነው?» ብሎ ጠራው።

ከመቃብሮች መሀል ብድግ አለ። ዙርያውን በአይኑ ቃኘ'ና ከአጠገቡ ከምትገኝ ዛፍ ላይ በርጋታ ወጥቶ፦ «አንተ ሀሩን! አንተ ቀውስ! ቆይ ግን መች ይሁን ሰው ምትሆነው?» ብሎ ጮኸበት።

ንጉስ ሀሩን የተቀመጠባትን ፈረስ በዝግታ እየጋለበ መጥቶ ከዛፏ ስር ቆመ።

እዝያው ፈረሱ ጀርባ ላይ ተንደላቅቆ፦ «እንዴ! እኔ ነኝ እብድ ወይስ በዚ ጠራራ ፀሀይ መቃብሮች ላይ ምትቀመጠው አንተ ነህ እብድ?»

«እኔማ ጤነኛ ነኝ» አለ ባህሉል፤ ሙሉ መተማመን ፊቱ ላይ እየተስተዋለበት።

«እንዴት ሆኖ...?» ሀሩን የማሾፍ ስሜት የተቀላቀለበት ጥያቄ ጠየቀ።

ባህሉልም ወደ ንጉሱ ቤተ-መንግስት እያመላከተ፦ «ያኛው ጠፊ እንደሆነ አውቃለሁ። ይኸኛው ደግሞ (መቃብር) ዘውታሪ እንደሆነም አውቃለሁ። ስለዚህ እኔ ይኸኛውን ከዝያኛው አስበልጬ ገንብቸዋለሁ። አንተ ደግሞ እንደሚታወቀው ያኛውን ብቻ ገንብተህ ይኸኛውን አፍርሰኸዋል።

ምንም እንኳን ከገነባኸው ህንፃ ተነቅለህ ወዳፈረስከው መቃብርህ ወራጅ እንደሆንክ ብታምንም ግን መሄድን አትሻም» ብሎ በአውላላ የትካዜ ሜዳ ላይ ንጉሱን አደናገረው።

ባህሉል ንግግሩን ቀጥሏል፦ «ታድያ ከኔ እና ካንተ ማናችን ነን እብድ መባል ያለብን...»

ካማረው ፈረስ ላይ በክብር ቁጭ ያለው ንጉስ ከጉንጮቹ እንደ ጅረት የሚፈሰው እንባው ፂሙን አረጠበ።

ንጉስ የሀፍረት ስሜት ውስጥ ሆኖ፦ «ባህሉል ሆይ! ወላሂ አንተ ትክክል ነህ። እባክህ ትንሽ ምክር ጨምርልኝ» አለው።

«ቁርአን ይበቃኻል፤ ምክሮቹን ጠበቅ አድርገህ ያዝ» አለው

ባህሉል። «እሺ ምትፈልገውን ንገረኝ'ና ልፈፅምልህ» አለው ንጉስ ከግዛቱ ሊያስጠቅመው።

«አዎን! 3 ምፈልገው ነገር አለ። ከፈፀምክልኝ አመሰግንሃለሁ» አለው ባህሉል ከዛፉ ላይ ቁጭ ብሎ።

ንጉስም፦«ጠይቀኝ» አለ፤ ሙሉ መተማመን ፊቱ ላይ እየተነበበ።

ባህሉል፦«እድሜዬን ጨምርልኝ»

ንጉስ፦ «ይኸንን እንኳን አልችልም»

ባህሉል፦ «ከመለከል መውት ጠብቀኝ»

ንጉስ፦ «ኧረ አልችልም»

ባህሉል፦ «እሺ ከእሳት ታድገኸኝ ጀነት አስገባኝ»

ንጉስ፦ «በምን አቅሜ...!»

ባህሉል፦ «አየህ አንተ ባርያ እንጂ ገዢ አይደለህም፤ እኔም ባንተ የሚፈፀምልኝ ምንም ጉዳይ የለኝም» አለው ይባላል።
-------------------------------------------------------------
ምንጭ፦
ﻛﺘﺎﺏ ﻋُﻘﻼﺀ ﺍﻟﻤﺠﺎﻧﻴﻦ

@yasin_nuru       @yasin_nuru

12.4k 0 139 33 260

ረሱል (ሰ,አ,ወ) ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ እንዲህ ብለዋል የአላህን 99
ስሞች በቃሉ የሀፈዛቸው እና የተገበራቸው ጀነት ይገባል በለዋል።

ቁርዓን እና ሀዲሶችን የተከታተለ ሁሉንም ማግኘት ይችላል።

ስለዚህ የአላህን ሰም በቃላችን ሀፍዘን ጀነት ብንመኝ ምን ይመስላቹሀል?

#አላህ _አምላክ

አረህማን— በጣም አዛኝ

#አረሂም— በጣም ሩህሩህ ♥

አል መሊክ— ንጉስ

#አል_ቅዱስ— ከጉድለት የጠራ

አሰላሙ— የሰላም ባለቤት

#አል_ሙእሚኑ— ፀጥታን ደህንነትን ሰጭ

አል ሙሀይሚኑ— በሰሮቹን ጠባቂ

#አል_አዚዙ— አሸናፊ

አል ጀባሩ— ሀያል ጠጋኝ ♥

#አል_ሙተከቢሩ— ኩሩ

አል ኻሊቁ— ፈጣሪ

#አል_ባሪኡ— ከምንም ያስገኘ ፈጣሪ

አል ሙሶውሩ— ለሻው ነገር የሻውን ቅርፅ ሰጭ

#አል_አወሉ— ፊት ያለ የመጀመሪያ

አል አኺሩ— ኋላ ቀሪ የመጨረሻ

#አል_ዟሂሩ— ግልፅ

አል ባጢሉ— ስውር

#አል_ሰሚኡ— ሰሚ

አል በሲሩ — ተመልካች

#አል_መውላ— ወዳጂ ረዳት ♥

አል ነሲሩ— ድል ሰጭ

#አል_አፍው— ይቅር ባይ

አል ቀዲሩ— በነገሮች ቻይ

#አል_ለጢፍ — ሩህሩህ

አል ኸቢሩ— ውስጥ አዋቂ

#አል_ዊትሩ— ብቸኛ

አል ጀሚሉ— መልካሙ ♥

#አል_ሐዪዩ— አክባሪ ትሁት

አል ሲትሩ— ሸፍኝ

#አል_ከቢሩ— ትልቅ

አል ሙተ— አሊ የላቀ

#አል_ወሂዱ— አንዱ

አል ቀሀሩ— አሸናፊ

#አል_ሀቁ— እውነቱ

አል ሙቢኑ— ሁሉን ግልፅ አድራጊ♥

#አል_ቀውዩ— ሀይለ ብርቱ

አል መቲኑ— እጂግ ብርቱ

#አል_ሀዩ— ህያ

አል ቀዩሙ— ራሱን ቻይ

#አል_አሊዩ— የሁሉ የበላይ

አል አዚሙ— ታላቅ

#አል_ሽኩሩ— ውለታን መላሽ

አል ሐሊሙ— ሲበዛ ታጋሽ♥

#አል_ዋሲኡ— ችሮታው ሰፊ

አል አሊሙ— አዋቂ

#አል_ተዋቡ — ንስሀን ተቀባይ

አል ሀኪሙ— ጥበበኛ

#አል_ገኒዩ— ሀብታሙ

አል ከሪሙ — ቸሩ

#አል_አሀዱ— ብቸኛ

አል ሶመዱ— ሁሉን አስጠጊ

#አል_ቀሪቡ— ቅርብ

አል ሙጂቡ— ልመናን ጥሪን መላሽ ፣ተቀባይ

#አል_ገፍሩ— መሀሪ

አል ወዱዱ— ተወዳጂ ፣ወዳድ

#አል_ወልዩ— ወዳጅ

አል ሀሚዱ— ምስጉኑ

#አል_ሐፊዙ— ተጠባባቂ

አል መጂዱ— ለጋስ

#አል_ፈታሁ— የሚከፍት ፣ድልን አጎናፃፊ

አል ሸሂዱ— ተከታታይ

#አል_ሙቀዲሙ— አስቀዳሚ ፣የሚያቀርብ

አል ሙአኺሁ— አዘግይ ፣የሚያርቅ

#አል_መሊኩ— ንጉስ

አል ሙቅተድሩ— የችሎታ ያዥ

#አል_ሙሰኢሩ — ወጋ ሰጭ

አል ቃቢዱ— ሲሳይን ያዥ

#አል_ባሲጡ— ሲሳይን የሚዘረጋ

አል ራዚቂ— መጋቢ

#አል_ቃሂሩ— አሸናፊ

አል ደያኑ— አሸናፊ,

#አል_ሻኪሩ— አመስጋኝ

አል መናኑ— ለጋስ ፣ችሮታው ሰፊ ሰጭ♥

#አል_ቃዲሩ — ሁሉን ቻይ

አል ኸላቁ— ፈጣሪ♥

#አል_ማሊኩ— ንጉስ

አል ረዛቁ— ሲበዛ ለጋስ

#አል_ወኪሉ— ተወካይ♥

አል ረቂቡ— ተጠባባቂ

#አል_ሙህሲኑ— በጎን ወይ

አል ሀሲቡ— ተሳሳቢ ፣ተቆጣጣሪ

#አል_ሻፊ— ፈዋሽ

አል ረፊቁ— አዛኝ

#አል_ሙዕጢ— ሰጭ

አል ጀወሰዱ— ቸር♥

#አል_ሱቡሁ— የጠራው

አል ዋሪሱ— ወራሽ ብቻውን ቀሪ

#አል_ረቡ— ጌታ ፣ተንከባካቢ

አል አእላ— ከሁሉ በላይ♥

#አል_ኢላሁ— አምላክ

የአላህ (ሰ, ወ) 99 ስሞች በቃሉ የሀፈዘ ጀነት ገባ ብለዋል ረሱል (ሰ, አ,ወ)

#ረመዳን_20_ቀናቶች_ይቀሩታል። 2/6/2017

@yasin_nuru      @yasin_nuru

13.4k 0 247 21 213

••በታሪክ ትልቁ ሶላት አልጀናዛ••

ኢስላማዊ ታሪክን የምትወድ ከሆነ የዚህን ምርጥ የአላህ ባርያ ታሪክ አንብብ...

•••••••••••√√√√√•••••√√√√•••••••
ሱልጧን ሱለይማን አልቃኑኒ ከእለታት በአንዱ ለሊት አንድ ህልም አዩና ተደናግጠው ከእንቅልፋቸው ተነሱ

የቅርብ ዘባቸውን ተጣርተው ፈረስ እንዲያዘጋጅላቸውና ሲነጋ ጎዳና ላይ ወጥተው የህዝቡን የቀን እንቅስቃሴ ማየት እንደሚፈልጉ አስረዱት

ከነጋ በኋላ በተዘጋጀላቸው ፈረስ ብቻቸውን ጎዳና ላይ በመውጣት የህዝቡን እንቅስቃሴ መቃኘት ጀመሩ

በዚህ መካክል አንድም ሰው ያልተከተለው አንድ አስከሬን በጎዳናው ላይ ሁለት ሰዎች ብቻ ወደ መቃብር ሲወስዱት ተመለከቱ

ሱልጧን ሱለይማንም ቀረብ ብለው ይሄ ብቻውን ወደ መቃብር የሚሸኘው አስከሬን የማነው? ብለው ሲጠይቁ

ይሄማ ዝሙተኛና ኸምር ጠጪ ከሚስቱ ውጭ ልጅም ሆነ ቤተሰብ የሌለው ግለሰብ አስከሬን ነው ስለዚህ የዚህን ዝሙተኛ እና መጠጥ ጠጪ አስክሬን ማንም ሰው ሊሸኘውና ሊሰግድበት ፍቃደኛ የሆነ ሰው የለም ይሏቸዋል🥹

ሱልጣን ሱለይማንም በጣም ይቆጡና ይሄማ እንዴት ይሆናል የሙሀመድ ኡመት አይደለምን? ይሉና አስከሬኑን ተሸክመው ወደ ባለቤቱ ይመልሱታል እዛም እንደደረሱ ባለቤቱ እጅግ አዝና ታነባለች😭

ሱልጣኑም በመገረም እንዴት እንደዚህ ታለቅሻለሽ ባለቤትሽ ዝሙተኛና ጠጪ አልነበረም አንዴ? ይሏታል

የሟች ሚስትም የሚጠይቃት ሰው ሱልጣን ሱለይማን መሆናቸውን አታውቅም ባለቤቴ አላህ ይዘንለትና አላህን የሚፈራ ነበር ልክ እንደሱ አላህን ፈሪ ልጅ ይመኝ ነበር ነገር ግን ሞት ቀደመው ትላቸዋለች💔

ሱልጣኑም ባለቤትሽ ከዝሙተኝነቱና ከጠጪነቱ ውጭ ምን የተለየ ነገር ይሰራ ነበር ? ይሏታል

ሚስትም ባለቤቴ ሁልጊዜም በየመንደሩ እየዞረ መጠጥ ወደሚገኝበት ቦታ በመሄድ መጠጦችን በብዛት በመግዛት ወደ ቤት ያመጣና ግቢ ውስጥ ባዘጋጀው ጉድጓድ ውስጥ ይደፋውና አልሀምዱሊላህ ዛሬ ለብዙ ሙስሊም ወጣት ወንድሞቼ ብዙ ወንጀልን ቀነስኩላቸው እያለ ጌታውን ያመሰግን ነበር💞💞

በማስከተልም ሁልጊዜ ምሽት በሆነ ቁጥር ወደ ሴተኛ አዳሪዎች መንደር በመጓዝ ለብዙ ሴተኛ አዳሪዎች ዝሙት ሰርተው የሚጋኙትን ሙሉ የቀን ገቢያቸውን ክፍያ ከሰጣቸው በኋላ ወደቤታቸው እንዲመለሱ ያደርግና ቤቱ መጥቶ አልሀምዱሊላህ ዛሬ ለብዙ ሙስሊም ወጣት ወንድሞቼ የዚናን ወንጀል ቀነስኩላቸው እያለ ጌታውን ያመሰግን ነበር😢😢

እኔም ሰዎች ከላይ የምትሰራውን ብቻ ነው የሚመለከቱት አንድ ቀን መሞትህ አይቀርም ያኔ ጀናዛህን አጥቦ ሶላተል ጀናዛ የሚሰግድብህና የሚቀብርህ አንድም ሰው አታገኝም እለው ነበር🥺

እሱም እየሳቀ ጀናዛየን ሱልጣን ሱለይማን አጥቦ በጀናዛየ ላይም ሱልጣን ሱለይማን ከእነ ሰራዊቱ ከእነ ምኒስትሮቹና ከታላቅ የሀገሪቱ ሼኮች ጋር ሆኖ የሀገሪቱ ሁሉም ሙስሊሞች ሲሰግዱብኝ ታያለሽ እያለ ይነግረኝ ነበር በማለት የባሏን የህይወት ታሪክ አጠገቧ ለቆመው ሰው ትነግረዋለች🥰🥰

ሱልጣን ሱለይማንም ከልቡ በማልቀስ አዎ ልክ ነው እኔ ሱልጣን ሱለይማን ነኝ እኔው እራሴ ጀናዛውን አጥበዋለሁ ይልና

የዚህን ምርጥ የአላህ ባሪያ ጀናዛ እራሱ ካጠበ በኋላ ለሀገሪቱ ሙሉ ሰራዊት ለሀገሪቱ ሙሉ ባለስልጣናት ለሀገሪቱ ሙሉ መሻኢኾች ለሀገሪቱ ሙስሊሞች በሙሉ ትዕዛዝ በማስተላለፍ በዚህ የአላህ ባሪያ ጀናዛ ላይ እንዲገኙ በማድረግ🤗🤗

ሱልጧን ሱለይማን አልቃኑኒ በታሪክ ትልቁን ሶላተል ጀናዛ በዚህ ድንቅ የአላህ ባርያ ላይ አሰገዱ።

ውጭ ላይ ለእኛ በተገለጠልን ነገር ላይ ብቻ ተመርኩዘን የአላህን ባሮች መለካት መመዘን ደረጃን መስጠት ከባድ ነገር ነው ከእኛ እውቀትም ውጭ ነው።


#ረመዳን_21_ቀናቶች_ይቀሩታል 1/6/2017

@yasin_nuru @yasin_nuru

13.7k 0 118 28 225

Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
#ጁምዓ_እኮ_ነው

🍃እናንተ ያመናችሁ ሆይ በአርብ ቀን ወደ ስግደት  በተጠራ ግዜ አላህን ወደ ማውሣት ሂዱ  መሸጥንም ተው ይህ የምታውቁ ከሆነ ለናንተ በላጭ ነው።
,  《ሡረቱል ፦ አል ጁሙአህ》

ሰሉ አለ ነቢ🥰🥰

#ረመዳን_22_ቀናቶች_ይቀሩታል❤

@yasin_nuru @yasin_nuru 

12.4k 0 32 45 215

አስራሚ እውነተኛ ታሪክ
የታሪኩ ረእስ☘ የተቅዋ ጠቀሜታ☘

አንድ እውቀት ፈላጊ ተማሪ እና እርሱን የሚያስተምሩት አንድ አሊም ነበሩ። እኝህ አሊም ከለታት አንድ ቀን ለዚህ ተማሪና ለጎደኞቹ የሚከተለውን ምክር መከሯቸው ከሰው ዘንድ ለማኝ ከጃይ እንዳትሆኑ። አሊም የሆነ ሰው እሲ ስጡኝ ብሎ እጁን ወደሰው የሚዘረጋ ከሆነ ምንም ኸይር አያገኝም። ለራሱም ለድኑም ውርደት ነው የሚከናነበው። ስለዚህ እናነተ ወዳባቶቻችሁ ሂዱና አባቶቻችሁ የሚሰሩትን ስራ ስሩ ወይም አግዞቸው። ታዳ በምትሰሩት ስራ ሁሉ አላህን ፍሩ። ከዚህ ቡሀላ ተማሪወቹን ወደ የጉዳያቸው አሰናበቱአቸው።
ይህ ወጣት ተማሪ ወደ እናቱ ሄደና አባቴ የሚሰራው ምን አይነት ስራ ነበር ብሎ ጠየቃት። እናቲቱም የአባቱን ስራ ለመንገር በጣም ተቸገረች። እንደገና ቡሀላ አባት ወደ አኼራ ሂዲአል የእርሱ ስራ ላንተ ምን ያደርግልሀል አለችው። ልጁ ካልነገርሽኝ ብሎ አስጨነቃት። ጥያቄ ሲያበዛባት አባትህ ሌባ ነበር አለችው።

ልጅየውም ሸይኻችን አባታችን የሚሰራውን ስራ እንድንሰራ ነገር ግን አላህ መፍራት እንዳለብን መክረውናል አላት። እናቲቱም ምን ማለትህ ነው? እየሰረክ እንዴት ነው አላህን የምትፈራው? ስትል የግርምት ጥያቄዋን ጠየቀችው። እናትና ልጅ በሀሳብ ሳይግባቡ ተለያዩ። ልጁ ግን ወደ አንድ ቦታ ሂዶ የአሰራረቅ ዘደወችን ተማር።

በሌብነት ስልቶች ከተካነ ቡሀላ ትምህርቱንም የሸህየውን ምክርም ተግባራዊ ለማድረግ ወሰነ። የኢንሻን ሶላት ሰግዶ ሰው እስኪተኘ ድረስ አድፍጦ ጠበቀ። ከዚያም ከቤቱ ወጣ በቅድሚያ ወደአንድ ጎረቢት ቤት ወስጥ ገብቶ ለመስረቅ ነበር ያሰበው። ነገር ግን የሸህየውን አላህ ፍሩ ተግሳጽ  አስታወሰ ጎረቢትን ማስቸገር አላህ ከመፍራት አይደለም አለና ይህንን ቤት አልፎ ወደሌላ ቤት ተሻገረ። ይህ ቤት ደግሞ የየቲሞች ነው ለነፍሱም ይህ ቤት የየቲሞች ቤት ነው። አላህ ደግሞ የየቲሞችን ገንዘብ መብላት እርም ( ሀራም) አድርጎታል አለ።

ይህንኛውንም ቤት ትቶ ወደቀጣዩ ቤት አለፈ። እንድህ እንድህ እያለ ወደ አንድ ሀብታም ነጋደ ቤት ደረሰ ቤቱም ዘበኛ አልነበርውም ።  ይህ ሀብታም ብዙ ገንዘብ እንዳለው ሰው ሁሉ ያውቃል ከአስፈላጊ በላይ ትርፍ ገንዘብ እንዳለው ይታወቃል እዚህ ቤት ነው መግባት ያለብኝ ብሎ በተመሳሳይ ቁልፍ በሩን ከፍቶ ወደ ቤት ውስጥ ገባ።
ሰፊ ግቢና ብዙ ክፍሎች ያሉት ቤት ነው። ወደዋናው ቤትም ገብቶ ካዝናውን ከፍቶ ሲመለከት,,,,,


ወርቅ እና አልማዝ እንድሁም ብዙ ገንዘብ አገኘ። ያገኘውን እቃ ይዞ ለመውጣት ሲል ሁሉንም መውሰድ የለብኝም ምክንያቱም ሽይሀችን አላህ ፍሩ ብለውናልና ምን አልባት ይህ ነጋዴ ዘካ ያላወጣ ከሆነ መጀመሪያ ከገንዘቡ ዘካ ማውጣት አለበት አለ ።

ካዝናው አጠገብ ተቀምጦ ያገኘውን መዝገብ ፊኖስ አብርቶ መመርመር ጀመረ። እንዳጋጣሚ በሂሳብ ጎበዝ ነበርና ገንዘቡን ቆጥሮ ዘካውን አሰበ። ሂሳቡን ሲያሰላ ብዙ ሰአት ወስዶበት ኖሮ የፈጅር (የሱብሂ) ሶላት ደርሷል። አላህን የመፍራት መጀመርያው ሶላት መስገድ ነውና ወደመታጠቢያ ክፍል ውስጥ በመግባት ውዱእ አደረገ። ለሶላት አዛን አደረገ።

የቤቱ ባለቤት አዛን በቤቱ ውስጥ ሲሰማ ግራ በተጋባ ስሜት እና ድንጋጤ ተነሳ ሚስቱም ተከትላዋለች። የሚያስገርም ነገር ነበር የተመለከተው ፋኖሱ በርቱአል የገንዘብ ማስቀመጫው ሳጥኑ ወለል ብሎ ተከፍቷል በአቅራቢአው አንድ ሰው አዛን ይላል። ሚስቱ በአላህ እምላለሁ እየሆነ ያለው ነገር ምንም አልገባኝ አለች። አዛኑን ከጨረሰ ቡሀላ ሰውየው ወደልጁ ቀርቦ ሰውየው ምን አይነት ጉደኛ ነህ ማነህ አንተ ሌባ አለው።

ልጁም ፈርጠም ብሎ መጀመርያ ሶላት እንስገድና ከዛ ቡሀላ እናወራለን ይለዋል። ባለቤቱም ውዱእ አደረገ ልጁም ለባለቤቱ በል ቅደም ቅደምና አሰግደን ኢማምነት ለባለቤት ነውና አለው። ባለቤቱም ምን አልባት መሳርያ ይኖረዋል ብሎ ስለፈራ ኢማም ሁኖ አሰገደ። እንደት እንደሰገደ ግን አላህ ብቻ  ነው የሚያውቀው። ሶላት ሰግደው እንደጨረሱ ባለቤቱ ወደልጁ በመዞር ማነህ ምን እያደረክ ነው ያለኸው? ጉዳይህ ምንድነው ሲል የጥያቄ ውረጅብኝ አወረደበት። ልጁም,,,,,,,,,,


ልጁም ያላወጣኸውን የዘካ ገንዘብ ሂሳብ እያሰላሁልህ ነበር የስድስት አመት ዘካህን አስቤ ጨርሸልሀለሁ ይህን የዘካ ገንዘብ ለሚገባቸው ሰወች እንድትሰጣቸው ለብቻ አስቀምጨልሀለሁ አለው።

ባለቤቱም በመገረም ሌላ ጥያቄ ጠየቀ ለመሆኑ አንተ እብድ ነህ? ልጁም ይህን ያደረገበትን ምክንያት ከመጀመርያው ጀምሮ ለባለቤቱ አጫወተው። ነጋደውም የልጁን ታሪክ ካደመጠ ቡሀላ ሂሳቡ ትክክል እና ምንመ ያልጎደለው መሆኑን አረጋግጦ ወደሚስቱ ሄደ። የልጁንም ታሪክ በዝርዝር አጫወታት።

ይህ ነጋዴ አንድት ልጃገረድ ልጅ ነበረችውና ወደሌባው ልጅ ተመልሶ እንድህ አለው : ልጀን ብደርህና  እና የሂሳብ ሰራተኛየና ፀሀፊየ ባደርግህ እናትህንም ደግሞ እኔ ጋር ባስቀምጣት እንድሁም አንተን በተጨማሪ በንግድ ሽርክና ባስገባህ ደስ ይልሀል? ልጁም እሽ እቀበላለሁ አለ። እንደነጋም ነጋዴው ምስክሮችን ጠራና ኒካሁን አሰር የጋብቻ ስነስረአት ተደረገ። የነጋደው ሴት ልጅና ሌባው ተጋቡ።

አላህን በቁረአኑ አላህን የፈራ እሱ መውጫ ያበጅለታል። እርዚቅም ካላሰበበት ያመጣለታል ይለናል። ለዚህም ነው ይህ ወጣት አላህን ፈራ ካላሰበበት እርዚቅ አመጣለት። በማጭበርበር በስርቆት በማታለል እሚመጣ ነገር የለም ቢመጣም ለግዜው ይመስለናል እንጅ መጨረሻው ውርደት ነው አላህ የተቅዋ ሰወች ያድርገን


ፀሀፊ✍ አረቡ ዩሱፍ

       ✍ምንጭ ቀሶስ ኢማኒያት ከሚለው
                     መፅሀፍ የተወሰደ

#ረመዳን_23_ቀን_ቀረው🥰


@yasin_nuru    @yasin_nuru

14.3k 0 121 21 236

🔰 ለእያንዳንዱ ሙስሊም በጀነት 72 ሚስት ይኖረዋልን??🔰
➸ አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ በዚህ ቅርቢቷ ዓለም የፈጠረን እሱን ብቻ አምልከን ጀነት እንድንገባ ነው።

➸ አላህ እንዲህ ይላል👇
"ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡
(📗ሱረቱ አል-ዛሪያት - 56)

➸ ከሴትና ከወንድ በአላህ አምኖ አላህን ብቻ የሚያመልክና  መልካም ስራ የሚሰራ ሰው በጀነት አይን አይታው፣ጆሮ ሰምታው፣ልብ ላይ ውል ብሎ የማያውቅ ትልቅ ፀጋ ያገኛሉ።
(📗ሱረቱ አል-ሰጅዳህ፣ - 17)
[📚ኢማም ቡኻሪይ ሐዲስ 3244]
እነዚህ ፀጋዎች ለሁለት ይከፈላሉ
1. መንፈሳዊ ፀጋ ሲሆን ጀነት ውስጥ ከሚያገኛቸው ፀጋዎች ትልቁ ፀጋ  የአላህን ፊት ማየት ነው።
2. ሥጋዊ ጸጋዎች ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ደግሞ አላህ ለምዕመናን ያዘጋጀላቸውን (ታይተውም ሆነ ተቀምሰው) የማይታወቁትን ፍራፍሬዎች መብላት፣ ከሚስታቸው ጋር የመኖር ፀጋ ወዘተ ናቸው።
ዛሬ የምናየው የጀነት ሰዎች ስለሚያገኟቸው የጀነት ሚስቶች ነው።
ለሴቶችስ ምን አለላቸው ለሚለው ጥያቄ በኡለሞች የተሰጠውን መልስ👇👇
https://t.me/iwnetlehullu1/357
☝️☝️ ተጭነው ይመልከቱ☝️☝️
ስለ ሌላ ዝርዝር ነገሮች ሌላ ግዜ እናያለን ኢንሻአላህ  አሁን ለእያንዳንዱ ወንድ 72 ሚስት ይሰጠዋል ስለሚለው እናያለን ኢንሻአላህ።
➸ሀዲሱ ኢብኑ ማጃህ ላይ የሚገኝ ሲሆን አላህ እያንዳንዳችሁን 72 ሚስት ያጋባችኃል ይላል።
ይሄ ሀዲስ በትክክል ከነቢያችን ﷺ ተረጋግጧል ወይስ ዶዒፍ(ደካማ) ሀዲሰ ነው የሚለውን እናያለን

➸በሀዲስ ጥናት ላይ ጎልተው ከወጡት እና ከሱ በኃላ አምሳያው እንዳልተነሳ የሚመሰከርለት ሀፊዝ ኢብኑ ሀጀር የሶሂሁልቡኻሪይ ሸርህ በሆነው ፈትሁል ባሪ ኪታባቸው ላይ
"እያንዳንዱ ሙእሚን 72 ሚስቶች ይሰጠዋል፣ከመቶ ሴቶች ጋር ይገናኛል፣5000 ወይም 4000ሚስቶች ወዘተ የሚሉ ሀዲሶችን እየጠቀሰ ሀዲሶቹ ሰነዳቸው ላይ ችግር ድክመት ስላለባቸው ዶዒፍ(ደካማ) መሆናቸውን ጠቅሷል። ደካማ የሆኑበትን ምክንያት እዛው ጠቅሷል።
ወደ 4000 ወይም 5000 ሚስቶች የሚለው ደግሞ በሰነዱ ላይ ስሙ ያልተጠቀሰ ዘጋቢ ስላለ ዘገባው ዶዒፍ ደካማ ነው።
ከዚያ በኃላ የታላቁ ኢማም ኢብኑል ቀይም ንግግር አስከትሎ አመጣና
ኢማሙ " የጀነት ሰዎች በጀነት ሚስቶች አሏቸው ከሚለው ሀዲስ ውጭ ከሁለት ሚስት በላይ ይሰጣቸዋል የሚል ሶሂህ(ትክክለኛ) የሆነ ዘገባ የለም። 
- ትክክለኛው" ለእያንዳንዱ ሙእሚን ሁለት ሚስት አለው የሚለው ነው። ብለዋል
📚ፈትሁልባሪ ሸርህ ሶሂህ አልቡኻሪይ ቅጽ 7 ገፅ 544

ሐፊዝ አቡ ኑዐይም አልአስባሃኒይ
"72 ሚስት ያገኛሉ የሚለው ሀዲስን በጠቀሰበት ላይ ሀዲሱ የመጣበት ሰነድ(ሰንሰለቱ) ላይ ኻሊድ ኢብኑ የዚድ የሚባል ዶዒፍ(ደካማ) የሆነ ዘጋቢ ስላለበት ሀዲሱ ضعيف جدا በጣም ዶዒፍ ነው።የሚል እናገኛለን
📚 ሲፈቱ ሶላት ሊአቢ ኑዐይም አልአስባሃኒይ ገፅ 205 ሀዲስ 370

ከኪታቡ በቀጣይ ገፁ ላይ "73 ሚስት ያገኛሉ የሚለውን በጠቀሰበት ላይ ሀዲሱ የመጣበት ሰነድ(ሰንሰለቱ) ላይ ሐጃጅ ኢብኑ አርጠአህ የሚባል ስህተተ ብዙ እና ሙደሊስ የሆነ ዘጋቢ ስላለበት የሀዲሱ ሰነድ ضعيف ዶዒፍ ደካማ ነው። ኢማሙ ዘሀቢይ "ዘጋቢው ሙንከር የሆኑ(በጣም ደካማ የሆኑ) ሀዲሶችን የሚዘግብ ነው። የሚል እናገኛለን
📚 ሲፈቱ ሶላት ሊአቢ ኑዐይም አልአስባሃኒይ ገፅ 206 ሀዲስ 372
➸ ታላቁ የሀዲስ ሊቅ ኢማሙል አልባኒይ የሶሂህነት መስፈርት ያላሟሉ(ዶዒፍ ሀዲሶችን በሰበሱበት ኪታቦቻቸው ላይ
" 72 ሚስት የሚለውን ሀዲሱን ከጠቀሱ በኃላ "ሀዲሱ ضعيف جدا በጣም ደካማ የሆነ ሀዲስ ነው" ብለዋል
📚 ሲልሲለቱል አሃዲስ አድዶዒፋህ ወልመውዱዓህ ቅጽ 9 ገፅ 456 ሀዲስ 4473
በኢብኑ ማጃህ የተዘገበው 72 ሚሰት የሚለውን ሀዲሱን ዶዒፍ ብለውታል
📚 ዶዒፍ ሱነን ኢብኑ ማጃህ ገፅ 364 ሀዲስ 5002
➸ ታላቁ ኢማም ኢብኑል ቀይም በኪታባቸው ላይ 
- ስለ 72 ሚስት የሚያወራው ሀዲስ የመጣበት ሰነድ(ሰንሰለት) ላይ ኻሊድ ኢብኑ ዘይድ የሚባል ዘጋቢ አለ።
ይህን ዘጋቢ ከሰለፎች ታላላቅ ኡለሞች ዶዒፍ(ደካማ) መሆኑን ተናግረዋል።
*ያህያ ኢብኑ መዒን* ደካማ ነው
*ኢማሙ ነሳኢይ* ታማኝ አይደለም ብሏል።
*ኢማሙ አድዳረቁጥኒይ* ዶዒፍ ነው ብሏል።
* ኢብኑ ዓዲይ" ደግሞ ይሄ ስለ 72 የሚወራው ሀዲስ ሙንከር ተደርጎበታል ብሏል።

-73 ሚስት ይሰጣቸዋል የሚል ሀዲስ ላይ ደግሞ አሕመድ ኢብኑ ሐፍስ የሚባል ዘጋቢ አለ። ይሄ ዘጋቢ ብዙ ሙንከር(ተቀባይነት የሌላቸው) የሆኑ ዘገባዎች አሉት
📚ሐዲ አልአርዋሕ ኢላ ቢላዲል አፍራሕ ገፅ 501-502

- በቀን መቶ ሴትን ይገናኛሉ የሚለው ሀዲስ ሰነድ ላይ ሑሴን አልጁዕፊይ የሚባል ዘጋቢ አለ። ይህንን ሀዲስ ኡለሞች ኢንካር ያደረጉበት የሆነ ሀዲስ ነው። ኢማም ኸጢብ አልበግዳዲይ ሀዲሱ ዶዒፍ ነው ብሏል
📚 ሐዲ አልአርዋሕ ኢላ ቢላዲል አፍራሕ ገፅ 503
☝️ኢማም ኢብኑል ቀይም እነዚህ ሀዲሶች ዶዒፍ መሆናቸውን ከጠቀሱ በኃላ
"ትክክለኛ ዘገባ የመጣው ሁለት ሚስት እንደሚሰጣቸው ነው ከሁለት ሚስት በላይ ይሰጣቸዋል የሚል ሶሂህ(ትክክለኛ) የሆነ ዘገባ የለም። 
📚 ሐዲ አልአርዋሕ ኢላ ቢላዲል አፍራሕ ገፅ 505

➸ ከዚህ ምንረዳው ካፊሮች እያንዳንዳችሁ 72 ሚስት ታገኛላችሁ እያሉ የሚያመጧቸው ሀዲሶች ዶዒፍ ደካማ መሆናቸውን እንረዳለን። ያመጧቸው ሀዲሶች ለነሱ ማስረጃ ሊሆኑላቸው አይችሉም። ምክንያቱም ሀዲስን ማስረጃ አድርጎ ለማቅረብ ያ ሀዲስ ከነቢዩ ﷺተረጋግጦ የመጣ መሆን አለበት
📚 ሸርህ መንዙመቱል በይቁንያህ ኢብኑ ዑሰይሚን ገፅ 21

ከላይ እንዳየነው ሀዲሶቹ ዶዒፍ(ደካማ) ናቸው።
ባለፈው ርዕሳችን ላይ እንዳየነው ሰለፎች ዘንድ ዶዒፍ የሆነን ሀዲስ ማስረጃ ሊደረግ እንደማይችል አይተናል።
በተጨማሪ👇
📚ሸርህ መንዙመቱል በይቁንያህ ኢብኑ ዑሰይሚን 60
📚 ሙስጠለሁል ሀዲስ ኢብኑ ዑሰይሚን ገፅ 16
ለእያንዳቸው ከ 2 በላይ ሚስቶች ይሰጣቸዋል የሚለው ሀዲስ ዶዒፍ(ደካማ) ከሆነ ስንት ነው የሚሰጡት ከተባለ👇
ኡለሞች ትክክለኛነቱ ላይ የተስማሙበት የሆነ በቡኻሪይ እና ሙስሊም ሌሎች ኪታቦች ላይም በተዘገበ ሀዲስ ላይ
" ለእያንዳንዳቸው ሁለት ሚስት ይሰጣቸዋል"
📚ሶሂህ አልቡኻሪይ ሀዲስ 3245 እና ሀዲስ 3246
e፣ ሶሂህ ሙስሊም 2834 መፅሐፍ 53, ሀዲስ 20
የሚል ሶሂህ ሀዲስ እናገኛለን።
➸ አንዳንድ 72 ሚስት የሚለው ሀዲስን ሶሂህ ያደረጉ ኡለሞች ሁለት ሚስት የተባለው ከዱንያ(ከዚህ ዓለም) የሆኑ ሴቶች ሲሆኑ ሰባዎቹ ደግሞ ከሁረል ዓይን ናቸው ቢሉም ይሄ አያስኬድም። ምክንያቱም ሶሂህ በሆነ ሀዲስ ላይ
" ለእያንዳንዳቸው ከሁረል ዓይን የሆኑ ሁለት ሚስቶች ይሰጣቸዋል"
📚ሶሂህ አልቡኻሪይ ሀዲስ 3254
የሚል ስላለ ትክክለኛው እና ሶሂህ ማስረጃዎች የሚደግፉት ለእያንዳንድ ሙዕሚን ሁለት ሚስቶች ይኖረዋል የሚል ነው።

ኢብኑ ረጀብ ረሂመሁላህ እንዲህ ይላሉ
"ለእያንዳንዱ ሰው ሁለት ሚስት ይሰጣቸዋል። በደረጃቸው ልክ ከሁለት በላይ የሚኖራቸው ቢኖሩም ( 72፣73፣100 እንደሚባለው) የሴቶቹ ብዛት በቁጥር የሚገድብ ሶሂህ የሆነ ማስረጃ የለም
📚 አትተኽዊፍ ሚን አንናር ገፅ 268
➤አልሃምዱሊላሂ ረቢል ዓለሚን➤

ከላይ የጠቀሰኳቸውን ማስረጃዎች ከኪታብ በማስረጃ ከፈለጉ ይህንን ይጫኑ👇👇
https://t.me/iwnetlehullu1/460?single
☝️☝️☝️☝️☝️

14.1k 0 52 17 121
20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.