የፍቅር ቴሌግራም ❤️‍🔥™


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


𝐖𝐞𝐥𝐜𝐨𝐦𝐞 t̑̈ȏ̈ የፍቅር ቴሌግራም™ ❤
💙በዚ 𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥 ላይ
💜ድርሰቶች
💚የፍቅር ግጥሞች
💛ጣፋጭ ታሪኮች
❤️ምክሮች ...
አልፎ አልፎ ቀልዶች ይለቀቁበታል 😂

Since 2016 e.c
❤️ከናተ ሚጠበቀው 𝐉𝐨𝐢𝐧 to request በማረግ ብቻ መከታተል ነው ❤️
👇👇👇

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ወላሂ ለአዚም አላህ ሽሀዳዬ ነው ይሄንን ቻናል  ተቀላቅዬ 87455ብር በልቺያለሁኝ ,ሰዎችን ሁሉ ሀብታም እያደረገ ነው።
👉ገንዘብ ለጠረረባቹህ ብቻ አሪፍ መፍትሄ በቀላለሉ ገንዘብ ለማግኘት ምርጥ ቻናል
💯💯💯💯💯💯💯💯💯💯💯
ቶሎ ከስር ቻናሉን ለመቀላቀል ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃‍♀️🏃‍♂️




💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስራ ስድስት 1⃣6⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን



የአባትዋ ሞት ተከትሎ ወንድምዋ እናቱን እና ብቸኛ እህቱን ትግስትን ለመውሰድ ወደ አዲስ አበባ መጥቷል
ነገር ግን ትግስት ወደ ከሚሴ የመሄድ ሀሳብም ፍላጎትም አልነበራትም ከናንተ ጋር መኖር አልፈልግም ከሀዲዎች ናቹ የአባቴ ሞት ተጠቀማቹበት። አልወዳችሁም እያለች ብትጮህባቸውም እነሱ ሊተዋት አልቻሉም።በተለይ እናትዋ ዘይነባን እስከዛሬ ድረስ አባቴን ስትደልዪ ኖረሻል አፈቅርሀለው ብለሽ አታለሽዋል አባቴን ክደሽዋል ገና ከመሞቱ ሙስሊም ሆንሽ እያለች ነጋ ጠባ ትሰድባታለች።

ወንድሟም ወደ ከሚሴ ልውሰዳቹ ትምህርትሽን እዛ መቀጠል ትችያለሽ አሪፍ ሀገር ነው ለሙስሊምም ለክርስትያንም የሚሆን ሀገር ነው።ሁሉ ነገር አስተካክያለው የራሴንም ቤት ገዝቻለው ቢላትም አሻፈረኝ አላችው።


ትምህርት በጀመርንበት ወር አዲስ ለገቡት ለዘጠነኛ ክፍሎች የ well come ( የ እንኳን ደህና መጣቹ ) ፕሮግራም አዘጋጀን። well come ፕሮግራም አላማው ለአዲስ ገቢ ተማሪዎቹ ጀመአውን እና የመስገጃው ቤት ማስተዋወቅ ነው። ያለንን አዋጥተን ኩኪስ እና ለስላሳ እንዲሁም ቴምር ገዝተን የ ዌልካም ፕሮግራሙን አዘጋጀን። አልሀምዱሊላህ ብዙ ተማሪዎች ተገኝተዋል።ትግስትንም የተለየ ነገር የለውም ብለን አባብለን ወደ ጀመአው ወሰድናት። ብቸኛዋ ሂጃብ ያለበሰች ሴት ስለነበረች የተማሪዎቹ አይን ቢያስፈራትም ተቋቁማው ፕሮግራሙን ከኛ እኩል ተካፍላለች። ሀዲስ ከሰማን በኋላ የጀመአው ጄነራል አሚር አቡበከር ትንሽ ንግግር አድርጎ ፕሮግራሙ ተቋጨ።

እኔና ዘቦም የጀመአው (የዳእዋ) ጥርያችንን እያቀላጠፍን ነው።በየክፍሉ እየዞርን የማይሰግዱትን ተማሪዎች እንዲሰግዱ የጀመአውን ቤት የማያውቁትን እያሳየን ጥሪ እናስተላልፍለን። ሂክማ(የፍይናንስ ዘትፍ አሚር) ለጀሙአው እርዳታ የሚያደርግ ሰው ልታገኝ ባለመቻልዋ አዝናለች። የምታውዋቸው የጠየቀቻቸው ሀብታም ናቸው ያለቻቸው ሰዎች ነገ ነይ ሳምንት ነይ እያሉ ያመላልሱዋታል እንጂ አይስጥዋትም።እኔም ላግዛት በማሰብ የማውቃቸውን ሰዎች ስጠይቅ አንዴ ደብዳቤ ፃፊ ይሉኛል ደብዳቤውን ፅፌ ስመለስ ደሞ ማህተም የለውም ይሄ የውሸት ጀመአ ነው ይሉኛል።

እኛ ደሞ ጀመአችን ከትምህርት ቤቱ እውቅና ውጪ ስለሆነ በትምህርት ቤቱ ስም ማህተም መጠቀም አንችልም። የሂክማ ስራ ከባድ እንደሆነ ስሰራው ነው የተረዳሁት። ግን ወላሂ ከሁሉም ስራ ተማሪን ወደ ጀመአው መጥራት ይከብዳል።ከ ሀ እስከ ፐ ማንነታችንን ያውቃሉ። እነዚህ ጨቅጫቃዎች መጡ እያሉ ይጠሩናል።አሰላሙ አለይኩም ስንላቸው የሚያፌዙብን ሴቶች ቁጥራቸው ብዙ ነው።ወአለይኩም ሰላም ከማለት ወአለይኩም ኩርኩም እያሉ ያላግጡብናል።አንዳንዶቹም ሰላም ይንሳቹ ሳይሉን አይቀሩም። አስተያየታቸው ግልምጫቸው ተስፋ ያስቆርጣል ሆኖም ግን የተሰጠን ሀላፊነት ከባድ ስለሆነ ፊታቸው እየገረፈን እየተመላለስን እንዲሰግዱ እንማፀናለን። እሺ ኢንሻ አላህ ነገ እመጣለሁ፤ሀይድ ላይ ነኝ፤ወደ ቤት ልሄድ ነው ፤እዚህ ነው የምሰግደው .......እያሉ የሚዋሹን ብዙዎች ናቸው።

የጊቢው ሰቃይ ተማሪም ሙስሊም ናት ሀናን ትባላለች። ውሎዋ ጊቢ ውስጥ ነው።ሶላት እንድትሰግድ ጥሪ ባደረግንላት ጊዜም እኔ ከትምህርት ከወጣሁ በኋላ ቤቴ ነው የምሰግደው አለችን።ከዚህ እስክትሄጂ አሱር ያዝናል እኮ ለምን እዚህ ከኛጋ አትሰግጂም ??ስንላት
..... እኔ ቀስሬ ነው ምሰግደው ምሳ ሰአቴን ላይብረሪ ነው ማሳልፈው ብላ በፈጣጣ መልሳልናለች።ከኛ ድክመት ይሁን ከተማሪው ስንፈት ባላውቅም ከለት ወደየ እለት ጀመአው ቤት እየሄዱ የሚሰግዱት ሴቶች ቁጥር በጣም ቀንሷል። ቤቱ ጠቦን ምንሰግድበት ቦታ አጥተን ለሁለት ጀመአ ተከፋፍለን በየተራ እንዳልሰገድን አሁን አሁን ቤቱም እየሞላ አይደለም።እንዳውም አንዳንድ ጊዜ አንድ ሰልፍ ሰጋጆች ብቻ የሚኖሩበት ጊዜ አለ። ወላሂ እኛ የጀመአው አባላት ወደዛች ቤት ለመሄድ ምክንያት አንፈልግም ነበር ጁምአ ጁመአ ቅዳሜ እና እሁድ አልፎ ሰኞ እስኪደርስ እንጓጓለን። እርስ በራሳችን እንዋደዳለን ። ሀይድ ላይ ብንሆንም ባንሆንም ወደዛች ቤት መሄዳችንን አናቆምም ይናፍቀናል።

ምሳ የያዝን ምሳችንን ካልያዙት ጋር ተካፍለን ነው የምንበላው። ከ እህትማማቾች በላይ ነው ፍቅራችን።አንዳንዶቹ እዛች ቤት ላለመሄድ ስበብ ይደረድራሉ። ሰአዳም እንዲህ እንዲህ እያለች ነው የጀመአው ቤት መሄድ ያቆመችው። ውሎዋ ከነ እየሩስ እና ትግስት ጋር ነው። አሚራ ድሮውንም የምትሰግደው ቤትዋ ነው።በነገራችን ላይ 10 ክፍል ከገባሁ በኋላ አንዲት አዲስ ልጅ ክፍላችን ገብታለች መርየም ትባላለች ሲበዛ እብድ ናት።

#Part 1⃣7⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል 1️⃣7️⃣7️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስራ አምስት 1⃣5⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን



አመቱ ማብቂያ ደረሰ ግንቦት ወር ላይ ሁሉንም ሙስሊም ተማሪ ያካተተ ሹራ በጀመአው ቤት ተደረገ።ጉዳዩ አሚር መረጣን በተመለከተ ነበር። አስረኛ ክፍሎች ማትሪክ ከተፈተኑ በኋላ ትምህርት ቤቱ ላይ ምንም ማድረግ ስለማይችሉ መምጣትም ስለማይፈቀድላቸው የስልጣን ሽግግር ያደርጋሉ። አሚር ተደርገው የሚመረጡት ዘጠነኛ ክፍል የሆኑት(ወደ 10 የሚሸጋገሩት) ነው። ዘጠነኛ ክፍል የነበሩትም 10 ገብተው ማትሪክ ሲፈተኑ በተመሳሳይ ሁኔታ ስልጣናቸውን ያስረክባሉ። በዚህ ጉዳይ ነበር ለሹራ የተሰባሰብነው።


ሹራው ተጀመረ።ጀመአው ሲመሰረት ከነበሩት ተማሪዎች መካከል የነበረው ፈትሁዲን ንግግር ጀመረ። ወንድ እና ሴት በመጋረጃ ስለተለያየ ፊቱን ማየት አልቻልኩም ግን ንግግሩ የንዴት እንደሆነ ድምፁ ያስታውቃል። ይሄ ቤት እኮ! አለ ድምፁን ከፍ አድርጎ።ይሄ ቤት እኮ መስዋትነት የከፈልንበት ቤት ነው ትምርታችንን ያጣንበት ለእስር የተዳረግንበት የተደበደብንበት አፈር ድሜ የበላንበት ቤት ነው ይሄ ቤት እኮ ለናንተ ለማስተላለፍ ለናንተ ለማበርከት እንቅልፍ ያጣንበት ያለቀስንበት ቤት ነው።እናንተ ግን የጥቂት ሰዎች ሰላት መስገጃ ብቻ አደረጋችሁት። ጀመአው ፈርሶዋል ማለት ይቻላል በኛ ጊዜ እኮ ቀጣይ ወር የሚደረገውን የዳእዋ ፕሮግራም አስቀድመን ነበር ምናዘጋጀው እናንተ ግን ብዙ ጊዜ ፕሮግራማቹን አይቻለው እንዳልተዘጋጃችሁበት ያስታውቃል። ጀመአውን ካልፈለጋችሁት ለሌሎች ስጡት ቤቱ ብዙ ነገር ሊሰራበት ይችላል፡፡ ጊቢው ውስጥ ካለው ከ 1000 በላይ ሙስሊም ተማሪዎች መካከል እዚህ የተገኘው 200 እኳን የማይሞላ ነው ይህ የሆነው የዳእዋ ጥሪ በተገቢው መንገድ ባለመደረጉ በደንብ ባለመሰራቱ ምክንያት ነው።

አላማ ይኑራችሁ goal ይኑራችሁ ዝም ብላችሁ አትነዱ።የራሳቹን ታሪክ ስሩ።እኛ ይሄን ቤት አስተካክለን ሰጠናችሁ እናንተ ደሞ ለቀጣዩ ትውልድ ሌላ አዲስ ነገር ፍጠሩ........ንግግሩን ቋጨ።

የጀመአዋ የሴቶች አሚር ሀናን ከዘጠነኛ ክፍል ሴት ተማሪዎች አሚር ለመሆን ጀመአው ላይ ለማገልገል ፍቃደኛ የሆነ እጁን ያውጣ አለች። ማንም እጁን አላወጣም።በርግጥ አሚር መሆን ማለት በጣም ከባድ ነው ለሰዎች አርአያ መሆን ማለት ነው አሚር መሆን ማለት ሌሎችን ሰዎች መምራት ማለት ነው አሚር መሆን ማለት ከራስ አልፎ ሌሎች ሰዎችን ማስተማር ሌሎች ሰዎችን ማስተዳደር ነው። እኛ ደግሞ እራሳችንን ማስተካከል ያልቻልን ሰዎች ነን። አሁንም በድጋሚ ጠየቀች ምላሽ አጣች
.....በስተመጨረሻም እራሴ የማውቃቸውን እሾማለሁ ብላ ስም ጠራች። ኢማን ጄኔራል አሚር(ዋና አሚር) ዘቢባ ሱልጣን እና ዘቢባ ነጃ የዳእዋ ዘርፍ(ተማሪዎችን ወደ ጀመአው መጥራት) አሚር፤ ሂክማ የፍይናንስ ዘርፍ አሚር ፤........... እያለች በፍላጎትዋ መደበች።ከጄነራል አሚርዋ ኢማን ጀምሮ ሁላችንም ደስተኛ አልነበርንም።

ዘቢባ ሱልጣን እና ዘቢባ ነጃ ማለት እኔና ዘቦ ጋደኛዬ ነን። በተለይ እኔ በፍፁም ለአሚርነት በቂ አልነበርኩም።ትልቅ ሀላፊነት እንደተሸከምኩ ተሰማኝ እራሴንም ማስተካከል እንዳለብኝ ወሰንኩ። በወንዶቹም በኩል አቡበከር ጄነራል አሚር ተደርጎ ተመረጠ።ከኢማን (ሴቶች ጄነራል አሚር) ጋር የአንድ ክፍል ተማሪዎች ናቸው።ከዛን ቀን ጀምሮ ማርፈድ አቁሜ በሰአቱ መግባት ጀመርኩ።

እንዳውም አንድ ቀን ለታ ሰልፍ ላይ ተገኝቼ ዳይሬክተሩ ሲመለከተኝ አንቺ ከመጣሽ የቀረ የለም ማለት ነው ብሎ መሳቂያ አድርጎኛል። አመቱ አለቀ አሚሮቹም ወጡ እኛም 10ኛ ክፍል ገባን።እኛ አስር 7 እነ ኢማን አስር 12 ናቸው።


ትምህርት ገና ከመጀመራችን የትግስት አባት ፍራኦል ሞት ተሰማ። ሀዘንዋ መጠን አልነበረውም።እናትዋ ዘይነባም የባልዋን ሞት ተከትላ መስለምዋ ደግሞ ይበልጥ እንድታዝን አድርጓታል።እስዋን ለማፅናናት ብዙ ጊዜ ፈጅቶብናል በሁለት እግርዋ እንድትቆም ለማድረግ ብዙ ጥረናል።

የአባትዋ ሞት ተከትሎ ወንድሟም እናቱን እና ብቸኛ እህቱ ትግስትን ለመውሰድ ወደ አዲስ አበባ መጥቷል።

Part
😀6️⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል

🔻ክፍል 1️⃣6️⃣7️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስራ አራት 1⃣4⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን

በመስለሙ ምክንያት ትግስትም በጣም ስለተበሳጨች ስሙን እንኳን መጥራት አትፈልግም።

ጀመአችን በራሱ መዋጮ የሚያስተዳድራቸው 30 የቲም ልጆች አሉት።ልብስ እና ዩኒፎርም እንዲሁም ደብተር የመሳሰሉትን ይሸፍንላቸዋል። አሚሮቹ በአጠቃላይ የ 10ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው እኛ ደግሞ ቀጣይ ስልጣን የምንይዘው እኛ ስለሆንን የሴቶች አሚር የሆነችው ሀናን ሁል ጊዜ .......አደራ አደራ እኛን አይቶ የሚበላሽ ብዙ ሰው ስላለ ቅድሚያ እራሳችንን እናስተካክል የዘንድሮ ዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎች በጣም ትንንሽ ናችሁ ከናንተ በኋላ የሚመጡት ደግሞ ይበልጥ ትንንሾች ናቸው እኛን እያዩ ክፍት እና ብልግና እንዳይማሩ እያለች ትመክረናለች።

ይሄ ንግግርዋ ዳይሬክተራችንም ሲናገር ሰምቼዋለው የዘንድሮ ተማሮዎች በጣም ልጆች ናችሁ በዛውም ልክ ጋጠወጥ ናቹ አልበሰላቹም ከናንተ በኋላ የሚመጡትም እናንተን እያዩ ነው የሚማሩት ጥሩ ከሆናቹ ጥሩ ይሆናሉ መጥፎ ከሆናቹም መጥፎ ይሆናሉ ብሎ ሲጨቃጨቅ ሰምቼዋለው።
የጀመአው አሚሮች ተማሪውን ወደ ጀመአው ለመጥራት በጣም ይደክማሉ። ጊቢው ውስጥ እየዋሉ ሰላት ሳይሰግዱ የሚውሉ ብዙዎች ናቸው። ይሄንን ለመቅረፍ በየክፍሉ እየዞሩ ምክር ይሰጣሉ።አንዳንዶቹም መጡ ደግሞ እያሉ እንደጠላት ሲያዩቸው ተመልክቻለው እኛ ክፍልም ብዙ ተማሪዎች እንዳያዩያቸው ብለው ሲደበቁ ተመልክቻለው። ትምህርት ቤቱ ስመ ገናና ስለሆነ ቁጥጥር ያበዛሉ።

ቤቴ ቅርብ ቢሆንም ልምድ ሆኖብኝ ሳላረፍድ ክፍል ገብቼ አላውቅም። ሪከርድ ተይዞብኝ ተባርሬ ሳምት ከተቀጣሁ በኋላ ወላጅ አምጥቼ ምህረት ተደርጎልኝ ተመልሻለው። ያው የልምድ ነገር አይለቅም አይደል የሚባለው? ማርፈዴን አላቆምኩም። ጊቢው እጅግ በጣም ሰፊ ስለሆነ ከአንዱ በር ወደ ሌላኛው በር ለመጓዝ 20 ደቂቃ ያክል ይፈጃል። ዳይሬክተራችንም ወላጅ ማስመጣት እና ማባረር ስለሰለቸው እኔን የሚቀጣኝ በአንዱ በር ወተሽ በአንድኛው በር ተመለሺ ብሎ ነው። በአንዱ በር ወቶ በሌላኛው መመለስ ከ 25 እስከ 30 ደቂቃ ይፈጃል። ይሄ የለት ተእለት ተግባሬ ሆኖዋል። ለመድከት መሰለኝ ቅጣቱም አይከብደኝም።

ትምህርት ቤቱን ለምጄዋለው በጣም ወድጄዋለው። ትብብራቸው ደስ ይላል። አንድ ተማሪ ቀርቶ መምህሩ አቴንዳንስ ሲይዝ ሌላኛው ተማሪ የጓደኛቸውን ድምፅ አስመስለው አቤት ይላሉ።አስተማሪውም ሳይነቃ መምጣቱን ራይት በማድረግ ይመሰክራል። ፈተናም ስንፈተን የቀረ ተማሪ ካለ በሱ ስም ተፈትነው ከራሳቸው ጋር ደባልቀው ይሰጡታል። አስተማሪውም ሳይነቃ አርሞ ይመልሳል። አንድ ተማሪም ያለ ጥፍቱ አስተማሪ ሲመታው ካዩ አስተማሪውን ለማስቆም ሁሉም ተማሪ ከተቀመጠበት ተነስቶ ይጮሀል ያምፃል።
አመቱ ማብቂያ ደረሰ ምኑንም ለይቼ ሳላውቀው ግንቦት ወር መጨረሻ ደረሰ።በዚህም ወር ሁሉንም የጊቢው ማለትም የትምህርት ቤቱ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ ተጠርተው ሁሉንም ያካተተ በጀመአው ቤት ሹራ ተደረገ።...

Part
😀5️⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል 1️⃣5️⃣7️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስራ ሶስት 1⃣3⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን
በISALMIC SCHOOL ቻናል የተዘጋጀ

ቀስ በቀስ ሁላችንም የየራሳችንን ጓደኞች አፈራን
ኬቢ(ኬብሮን) ራሄል የተባለች ጓደኛ ስታፈራ እኔ ደሞ ዘቢባ፣እየሩስ፣ትግስት፣ሰአዳ እና አሚራ የተባሉ ጓደኞችን አፍርቻለው። በባህሪዬ ሰው ለመግባባት ጊዜ ስለማይፈጅብኝ እነሱን ለመተዋወቅ አልተቸገርኩም።

...ሙስሊም ጓደኛ ኑሮኝ ስለማያውቅ አሚራን ሰአዳን እና ዘቢባን ከሌሎቹ በተለየ በጣም ነበር የምወዳቸው። በተለይ ደሞ ለዘቢባ ያለኝ ፍቅር ልዩ ነበር። ብዙ ነገሬን ቀይራዋለች አለባበሴን ስርአቴን እናም ሌሎች ባህሪዎቼን አስተካክላዋለች።

ቂርአቴ ላይ ጊዜ እንድወስድ ሶላት በሰአቱ እንድሰግድ ብዙ ነገር አስተምራኛለች።እኔ ዘቦ እና ሰአዳ ምሳ ይዘን ስለምንሄድ ምሳ ሰአታችንን ትምህርት ቤት ነው የምናሳልፈው አሚራ ምሳ ስለማትይዝ ወደ ቤትዋ እየሄደች ትመገባለች።እኔ ሰአዳና ዘቦ ምግቦቻችንን በየተራ ከተመገብን በኋላ ሶላት ለመስገድ ወደ ግቢያችን ጀመአ ቤት እናመራለን።


ትምህርት ቤታችን የሙስሊም ተማሪዎች ጀመአ እንዳለው የሰማሁት ከዘቦ ነው። ከዛን በፊት ጀመአ ምን እንደሆነ እራሱ በቅጡ አላውቅም ነበር። የትምህርት ቤቱ ጀመአ 14 አመት አስቆጥሯል። ብዙ ኡስታዞች መተው አስተምረውበታል ብዙ ዳእዋዎች ተደርገውበታል።ጀመአውን ትምህርት ቤቱ ስለማይፈቅደው ብዙ ተማሪዎች ብዙ ፈተና ደርሶባቸዋል።ከመባረር እስከ መታሰር ደርሰዋል።

ጀመአው በሊላሂ የተሰጠው አንድ ሰፋ ያለ ክፍል ቤት አለው።ምሳ ሰአት ላይ ሴቶች ይሰግዱበታል።በሳምንት ጁመአ ደግሞ አሚሮቹ ተሰብስበው ሹራ ያደርጉበታል።በየ ወሩ ደግሞ ሙሉ የጊቢው ሙስሊም ተማሪዎች ተጠርተው የዳእዋ ፕሮግራም ይሰጥበታል ። ከአሱር እስከ መግሪብ ደግሞ የሰፈሩ ህፃናት ቁራን ይቀሩበታል።ወንዶች ሰላት የሚሰግዱት መስጂድ ነው።የጀመአው ቤት ለሶላት ትንሽ ቢርቅም ሌላ አማራጭ ስለሌለ የግድ እንሄዳለን።
አልፎ አልፎም መንገዱ ሲሰለቸን እንዲሁም እየሩስ እና ትግስት አብራችሁን ዋሉ ብለው ሲለምኑን ክፍል ውስጥ የዩኒፎርም ሹራባችንን አንጥፈን አስተማሪ እንዳይደርስብን በሩን በውስጥ ቆልፈን እየሩስ እና ትግስት ከውጭ የሚመጣውን ሰው እየጠበቁልን እንሰግዳለን።


እየሩስ የምትኖረው ከአንዲት አሳዳጊዋ ጋር ነው እናትም አባትም የላትም ቢኖራትም የት እንደሚኖሩ ምን እንደሚመስሉ አታውቅም እነሱም ፈልገዋት አያውቁም። ለነገሩ እየፈለጓት ቢሆን እንኳን ያያቸው የለም። አሳዳጊዋ ያገኘቻት ቆሻሻ ውስጥ ተጥላ እንደሆነ ነግራታለች።የሰፈሩ ሰዎችም ይሄንን ታሪክ ስለሚያውቁ ምን በላሽ? ምን ጠጣሽ? የት ነሽ የት ዋልሽ? እያሉ ይንከባከብዋታል። በተለይ ደግሞ አሳዳጊዋ hiv ስላለባት እንድትጠነቀቅ ይመክሩዋታል።

ሌላኛው ከጎዳና አንስታ ያሳደገችው ልጅ ዳግምም ምንም እኳን አብረው ቢያድጉም ሴትነትዋን እንዳይነካ ያስጠነቅቁታል።ምክንያቱም ዳግም ብር ወዳድ እና ውለታ ቢስ ሰው ነው። አሳዳጊውንም መቃሚያ ብር ካልሰጠችው ይደበድባታል።


ትግስት ደግሞ የምትኖረው ከእናት እና አባትዋ ጋር ነው። ታላቅ ወንድም ቢኖራትም እስልምናን በመቀበሉ ምክንያት ከአባቱ ጋር ተጣልቶ ከሚሴ የምትባል ሀገር ሂዶ የራሱን ህይወት መኖር ጀምሯል። የትግስት እናት ዘይነባ ትባላለች የሙስሊም ልጅ ብትሆንም የትግስትን አባት ፍራኦልን በማፍቀሯ ምክንያት ሀይማኖቷን ቀይራ አግብታዋለች። የ ትግስት ታላቅ ወንድም መላኩ ከሰለመ በኋላ ስሙ አማር ሁኗል።

በመስለሙ ምክንያት ትግስትም በጣም ስለተበሳጨች ስሙን እንኳን መጥራት አትፈልግም።

Part 1⃣4⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል 1️⃣4️⃣7️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

6.9k 0 22 10 106

💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስራ ሁለት 1⃣2⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን


   ለማግባት ዝግጁ እስካልሆንኩ ድረስ ከወንድ ጋር የሀራም ግንኙነት ላልጀምር በአላህ ቃል ቁርአን መትቼ ማልኩ

አመቱ ማብቂያ ደረሰ ሀምሌ ወር መጨረሻ ላይ ነን። የሚኒስትሪ ውጤት ወጣ። ይወድቃሉ ተብለን ስማችን ይጠራ የነበረው ዮናታን ዩሴፍ እና እኔ በተርታ 91.5 ,92.4 እና 93.6 አመጣን። ትምህርት ቤታችንም ሁላችንም የተፈተነዉ ተማሪዎች አልፈናል። ከዚህም ባሻገር ሁሉም ተማሪ ከ 77.3 በላይ በማምጣቱ ምክንያት ትምህርት ቤቱ ከ ኢትዮጵያ ትምህርት ሚኒስቴር የዋንጫ እና የማበረታቻ ሰርተፊኬት ሽልማት አግኝቶዋል። 4 ተማሪዎችም 99.9 በማምጣት በ ኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስቴር የምስክር ወረቀት ተሸልመዋል። ከድርም 99.9 አምጥቶ ማለፉን ከሰፈሩ ልጆች ሰምቻለው። ደስ የሚል እና የሚያሳዝን አመት የማይረሱ ትዝታዎች ብዙ ነገር ተፈጥረዋል።

በከድር ፍቅር ታውሬ ዋናውን ነገር ረሳሁት። ሰባተኛ ክፍል መጨረሻ አካባቢ ማለትም የረመዳን ወር ላይ እነ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፤ ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ፣ኡስታዝ ያሲን ኑሩ፤ልጅ አቡበከር አደም...........የመሳሰሉት በአሸባሪነት ስማቸው ተነስቶ ታስረዋል።


ለ እስልምናዬ ቦታ መስጠት የጀመርኩት እነ አቡኪ (አቡበከር አህመድ) ፤ አህመዲን ጀበል እና እነ ያሲን ኑሩ የመሳሰሉትን ኡስታዞቻችን አሸባሪ ናቹ ተብለው የታሰሩ ጊዜ ነው። እምነት ማለት ምን እንደሆነ የገባኝ ያን ጊዜ ነው። ሰላትም መስገድ የጀመርኩት በዛ ምክንያት ነው።

በተለይ ደግሞ የዛን ጊዜ የረመዳን ወር ፆም ማብቂያ የኢድ ሰላት ላይ በተደረገው ተቃውሞ ምክንያት በተነሳው ረብሻ ፖሊሶች ህዝቡን በፍልጥ ሲያደቁ እኔንም በደረሰኝ አንድ ዱላ እና የጉልበት መላላጥ አማካኝነት ነው ይበልጥ እስልምናዬን እንድወድ መንገድ የከፈተልኝ።እድሜዬ 13 ወይም 14 አመት ገዳማ ይሆነኝ ነበር።እድሜያችን በጨመረ ቁጥር አዳዲስ ነገሮችን አብረን እንማራለን አይምሮአችንም ማገናዘብ ይጀምራል።በተለይ ደግሞ ከ elementary ትምህርት ቤት ወደ hign school ስንሸጋገር መቆሚያው እና መቀመጫው ይጠፍናል። dv ደርሶት አሜሪካ የሚሄድ ሰው እንኳን የኛን ያክል አይደሰትም።

የትምህርት ጥግ የደረስን እስኪመስለን ድረስ ደስታችን ወደር አይኖረውም።ይሄ ስሜት ሳይሰማው ያለፈ አንድም ተማሪ የለም።እኔም በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኜ ነው ዘጠነኛ ክፍልን ድላችን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የገባሁት። ከ 1 እስከ 8 የተማርኩበት ትምህርት ቤት የግል ቢሆንም የሚኒስትሪ ውጤት ከወጣ በኋላ የሚመድበው ግን የመንግስት ትምህርት ቤት ባልቻ አባነፍሶ የሚባል ትምህርት ቤት ነው። እኔም የተመደብኩት ባልቻ ቢሆንም ካለሁበት ሰፈር ትንሽ ርቀት ስላለው አቅራቢያዬ ወዳለው ድላችን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ ጓደኛዬ አባት አማካኝነት ተመዘገብኩ።


ጓደኛዬ ኬብሮን ትባላለች ፕሮቴስታንት(ጴንጤ) ናት ኢለመንተሪም አብረን ነው የተማርነው። ከተመዘገብንም በኋላ ክፍል ተመደብን። ብዙ ተማሪ ስለነበር ዘጠነኛ ክፍል ብቻ 23 ክፍሎች ነበሩ።ዘጠኝ 1 ፤ ዘጠኝ 2 ፤ ዘጠኝ 3............ እየተባለ ነው ሚጠራው። እኔ የደረሰኝ ዘጠኝ 7 ሲሆን ኬብሮን የደረሳት ዘጠኝ 5 ነበር። ሁሉም ተማሪ ለኛ እንግዳ ስለነበር በ እረፍት እና በ ምሳ ሰአታት እየተገናኘን ብቻችንን እንቀመጣለን። ተማሪዎች ሲጫወቱ ሲላፉ እኛ ተመልካች ነን። ትምህርት ቤቱ በጣም ደብሮናል። ላይናችን ያስጠሉናል።


እኔም የሀብታሞቹ ልጆች ባህሪ ተጋባብኝ መሰለኝ ተማሪዎቹ ሊያናግሩን ሲሞክሩ ኩራት ኩራት ይለኛል። ገና ከትውውቃችን ስም ከተለዋወጥን በኋላ ቀጣዩ ከየት ትምህርት ቤት ነው የመጣሽው?? የሚል ጥያቄ ስለሆነ ይኬንን ጥያቄ እንዳቀረቡልኝ ስለ ትምህርት ቤቴ ዝና እና ስም እንዲሁም የልጥጥ ትምህርት ቤት እንደሆነ ክፍያውም ምን ያክል እንደሆነ ኮራ ብዬ በጋንኜ ቅመም ጨምሬ እነግራቸዋለው።
.....ቀስ በቀስ ሁላችንም የየራሳችንን ጓደኞች አፈራን

Part 1⃣3⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል 1️⃣3️⃣7️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

7.4k 0 22 13 92

💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስራ አንድ 1⃣1⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን


ሚኒስትሪ ልንፈተን 2 ወራት ብቻ ቀርተውናል።ከድሬ ሳናግረው ይሸሸኛል። ያቺን የለመድኳት ፍቅሬን የምታሳየኝ ፖልም ብቻዋን ተገትራ ነው የማገኛት። አንዳንዴም እኔ በተራዬ ድንገት ከመጣ ብዬ ፖሉን ተደግፌ እቆማለው። እየሩስ ይሄ ተግባሬ ያናድዳታል ። ወንድ ልጅ ኮራ ስትይበት ነው የሚወደው ትለኛለች። አብረን እንድንተኛ እንደጠየቀኝ ግን አልነገርኳትም። ናፍቆቱ ሲበረታብኝ አላስችል ብሎኝ ነገርኳት።
.....እዩ መፍትሄ ብዙ ናት ምክንያት ሰበብ እና ዘዴ አታጣም።ሁል ጊዜ እስዋ ጋር የችግር ቁልፍ አለ። አሁን ግን ለኔ ምንም ልታገኝልኝ አልቻለችም።ገና በዚ እድሜሽ ሴክስ ከጀመርሽ መጨረሻሽ ሴተኛ አዳሪ ነው የምትሆኚው እውነት የሚያፈቅርሽ ከሆነ በራሱ ጊዜ ይታረቅሻል የማያፈቅርሽ ከሆነ ግን ብትርቂው ነው የሚሻልሽ ለስሜቴ ነው ማለት ነው ሚፈልግሽ ብላ ተስፍ አስቆረጠችኝ።
.....ያፈቀረ እና ያበደ አንድ ነው አይደል የሚባለው ንግግርዋን ከምንም አልቆጠርኩትም ። እንደተለመደው ከትምርህት ቤት ወጥተን ወደ መድረሳ ስሄድ ከድሬ ፖሉን ተደግፎ ቆሞ ጠበቀኝ። ሳላቅማማ ወደርሱ አመራሁ። ናፍቀከኛል ለምን ጠፋህብኝ?? ስልክስ ለምንድነው የማታነሳው ??በተለያየ ስልክ ደውዬልሀለው ግን አታነሳም አልኩት።
.....እሱም ንግግሬን ካዳመጠ በኋላ ወደ ገደለዉ እንግባ የጠየኩሽን ምን ወሰንሽ ??አለኝ
.......ማለት አልገባኝም ??አልኩት
.......ባለፈዉ የጠየኩሽን ፍቃደኛ ነሽ አይደለሽም ???ብሎ ጠየቀኝ
......ምንም የተለወጠ ነገር እንደሌለ በባለፈዉ አቋሜ እንደሆንኩ ነገርኩት።
....ከድር ጥሎኝ ወደቤቱ ገባ። እዛው ፖሉ ጋር ሆኜ አነባሁ።ያየኝ ሁሉ ሰዉ ምን ሆንሽ ልጄ የምታለቅሽዉ?? እያለ ይጠይቁኛል።
....እየሩስም እንባዬን ጠራርጋ ተነሽ በቃ ዛሬ መድረሳ ይቅርብሽ ወደቤት እንሂድ በጌታ እያለች ለመነችኝ
......ግን አይሆንም አላህ ፊት ቆሜ ማንባት ነው የምፈልገው ሂጅልኝ ብዬ ትቻት ወደ መድረሳ ሄድኩ። ግን አላህ ያለው መድረሳ ብቻ ነው እንዴ? አይ ልጅነት ይገርማል ንግግር እንኳን አናውቅም።

መድረሳ ሄጄ ቁርዐኔን ከፍቼ እየቀራሁ አነባሁ።እንባዬ ቁርዐኔን አርሶ አበላሸብኝ።
......ኡስታዛም ምን ነክቶሽ ነው አይዞሽ እያለች አባበለችኝ። የሆንኩትን ለማንም ሳልናገር ወደ ቤቴ ሄድኩ። ከዛም መግሪብ ከሰገድኩ በኋላ እራቴን ሳልበላ መስገጃዬ ላይ ቁጭ ብዬ የሙሀመድ አወል ሳላህን መስገጃሽ ላይ ታገሺ የሚለውን ነሺዳ እየሰማሁ እያነባሁ እንባዬንም እየጠረኩ ኢሻ እስኪያዝን ጠበኩ። ኢሻም አዛን ካለ በኋላ ሰላቴን ሰግጄ ዱአ አደረኩ። ከዛም አላህዬ ከድር የወደፊት አጋሬ ነው አይደለም? ለኔ ሀላሌ ነው አላህዬ? አሁን ምንም ብናደርግ ችግር የለውም? አላህዬ አሳውቀኝ እያልኩ አፍ እንዳልፈታ ህፃን ልጅ እየተንተባተብኩ ዱአዬን ጨርሼ ሰላተል እስቲሀራ ሰግጄ ስለከድሬ የሆነ ነገር እንዲያሳየኝ ለምኜ ተኛሁ።

ግን አላህ ምንም ያሳየኝ ነገር አልነበረም። በማግስቱም ሱብሂ ከሰገድኩ በኋላ አልፎም አላህዬ እሺ ከድር ለኔ የማይሆን ከሆነ ከልቤ አውጣልኝ ከዚህ ስሜት አስወጣኝ ብዬ ተንሰቅስቄ አለቀስኩ። ያለወትሮዬ ሰላቴን በሰአቱ መስገድ ጀመርኩ በዱአም በረታሁ። ባላሰብኩት ፍጥነት ከከድር መራቅ እንዳለብኝ ልቤ ተሰማው። ከዛሬ ጀምሮ ከድሬን ላለማናገር እና በፍቅር ላለማሰብ ወሰንኩ ።ከዛም ቀን ጀምሮ ፖሉን ተደግፎ ቆሞ ሲጠብቀኝ ባይም ባላየ ማለፍ ጀመርኩ። አልፎ ሲናፍቀኝ አይኔን አጣምሜ ሰርቄ አየዋለው ግን አላናግረውም።


የሚኒስትሪ ፈተና ከወሰድን አንድ ወር አለፈን። የሚኒስትሪ ውጤት ተለቀቀ የሚል የሀሰት ወሬ ብዙ ጊዜ ይሰራጭ ስለነበር በሰማን ቁጥር ለማረጋገጥ እኔና እዩ ትምህርት ቤት እንሄድ ነበር። አንድ ቀንም ይሄንን የሀሰት ወሬ ሰምተን ለማረጋገጥ ስንሄድ ከድሬን አገኘሁት።
.....ዘይባ ዘይባ እያለ ጠራኝ። አላስችል ብሎኝ ላናግውረ ወደርሱ ሄድኩ።
....ጠፋሽ ምን ሆነሽ ነው?? ናፈቅሽኝ እኮ ለምን አትደውይም?? እያለ ጥያቄ አዘነበብኝ።
.....ያን ሁሉ ያሳለፍኩትን መከራ ረስቼ ስልክ ስላላገኘሁ ነው ካሁን በኋላ እደውልሀለው አልኩት።

አሁንም ጥያቄውን ቀጠለ። ከኔጋ የጠየኩሽን ለመፈፀም ዝግጁ ሆንሽ ? ብሎ የረሳሁትን ጥያቄ ድጋሚ ጠየቀኝ።
..... የማውቀውን እና ይገባዋል ያልኩትን ስድብ በሙሉ ሰደብኩት ለሱ ያለኝ ስሜት ከዛን ቀን ጀምሮ ሞተ።ለማግባት ዝግጁ እስካልሆንኩ ድረስ ከወንድ ጋር የሀራም ግንኙነት ላልጀምር በአላህ ቃል ቁርአን መትቼ ማልኩ


Part
1️⃣2️⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል

🔻ክፍል 1️⃣2️⃣6️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

7.1k 0 24 6 109

💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አስር 🔟

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን



ፊት ለፊቱ ቆሜ አይኔን ከአይኑ ገጥሜ ጥርሴን ከጥግ እስከጥጉ ከፍቼ ከድሬ አልኩት። እሱም ያንን የሚያፈዘው ፈገግታውን ተጠቅሞ ልቤን እያቀለጠ ወዬ ዘቢ አለኝ።
......ታፈቅረኛለህ? ስል ጠየኩት።
.......እሱም ትጠራጠሪያለሽ እንዴ?? አለኝ
.......እኔም እሺ ለኔ ያለህን ስሜት ንገረኝ እስቲ በራስህ አንደበት እኔን ግለፀኝ ??? አልኩት።
......እሱም ሰምቼው በማላውቀው ንግግር አንቺ ማለት ለኔ ህይወቴ እናቴ እህቴ ሚስቴም ጭምር ነሽ በ እናቴ ያላገኘሁትን ፍቅር ያገኘሁት ባንቺ ነው። ካንቺ ሌላ ያፈቀርኩትም የተመኘሁትም የምመኝውም ሴት የለም።አንቺ ማለት ልቤ ውስጥ ልዩ ቦታ ያለሽ ብቸኛ ሴት ነሽ አንቺ ማለት የልጆቼ እናት አጋሬ ሀላል ሚስቴ ነሽ አለኝ።...ያለኒካ ሀላል አለ እንዴ? ወይ እኔ ሞኝ እኮነኝ የነገሩኝን ሁሉ አምናለው።

ከንግግሩም አስከትዬ የዚህን ያክል የምታፈቅረኝ ከሆነ አንተም አንድ ውለታ ዋልልኝ ...ዚና መስራት አልፈልግም ከኒካ በፊት ከማንም ጋር መተኛት አልፈልግም አላደርገው አልኩት።

ፊቱ ሲቀያየር ታየኝ።ያ የሚያምረው ቀይ ፊቱ እንደወረቀት ተጠቅልሎ ጭምድድ ብሎ ሲኮሰታተር አየሁት። ተረጋጋ ከድሬ ብዬ በጥርሴ ልደልለው ሞከርኩ።ጥያቄዬን ቀጥልኩ።
.....ከድሬ ከኔ ሌላ ሴት አትጨብጥም ማለት ነው? አልኩት
.......እሱም እያወቅሽ ለምን ትጠይቂኛለሽ እኔ አጂ ነብይ የሆነችኝን ሴት አልጨብጥም አንቺንም ስለማፈቅርሽ ነው አለኝ።
.......ለምንድነው የማትጨብጠው ?? ብየ ጠየኩት።
......እሱም መድረሳ የምትመላለሺው ዝም ብለሽ ነው እንዴ ይሄንን አታውቂም? ለኛ እኮ አልተፈቀደልንም ሀራም ነው ለምን እናደርገዋለን ሌሎቹም እኮ የአላህን ህግ ጥሰው እንጂ ተፈቅዶላቸው አይደለም ሀራም ነው መቼም ከሚስቴ ውጪ አልጨብጥም አልነካም ብሎ መለሰልኝ። ግን እኔ ሀራምነቱን ሳላውቅ ቀርቼ ሳይሆን የጠየቀኝን የዚና ጥያቄ ለማስቀየር ነው ጥረቴ።
......አሁንም ንግግሬን ቀጠልኩ።ታዳ ዚና መስራትስ ሀላል ነው እንዴ? ከ መጨበጥ እና ያለኒካ ከመተኛት የትኛው ነው የሚከብደው የትኛው ነው ትልቅ ወንጀል??? ብዬ ሌላኛውን ጥያቄ ጠየኩት።
......እሱም ይሄን ሁሉ እንቢ ለማለት ነው??? ሀራምነቱ ጠፍቶኝ አይደለም አንቺን ግን ስለማገባሽ ስለማፈቅርሽ ነው እናድርግ ያልኩሽ እንደዚህ ልትሆኝ አይገባም።ካሁን በኋላ ተስማምተሽ ከኔጋ ለመተኛት ካልወሰንሽ አጠገቤ እንዳደርሺ ብሎ ጥሎኝ ሄደ።

ምድር ከሰማይ ተደበላለቀብኝ ቀኑ ጨለመብኝ። ምነው አላህዬ ለምን ታሳጣኛለህ?? ብዬ ወቀስኩት። በርግጥ የዚና ጥያቄውን ያልተቀበልኩት አላህን ፈርቼ አልያም ሀራም ነው ብዬ አልነበረም።ጥያቄውን የተቀበልኩት ወንድሜ ጭንቅላቴ ውስጥ በቀረፀው ንግግሩ ምክንያት ነው። ታላላቆቻችን የሚያስተምሩን ጥሩም ይሁን መጥፎ ነገር ለኛ ለታናናሾች ትርጉም አለው።

ይሄንን ብቻ አይደለም ወንድሜ ያስተማረኝ
ከ እንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የ ማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊ ነው እኔም ልክ እንደሱ የዩናይትድ ደጋፊ ነኝ።ጨዋታ ባለው ጊዜም እየተከታተልኩ አያለው።
በ ስፔን ላሊጋ ደግሞ የሪያል ማድሪድ ደጋፊ ነው እኔም የሪያል ማድሪድ ደጋፊ ነኝ።
ከሀገር ውስጥም ቡናን ይደግፍል እኔም እንደዛው።ምን ቸገራቹ ባጭሩ የወንድሜ ደጋፊ ነኝ።ልዩ የሆነ የግጥም ችሎታ አለው።ይኸው እኔም በሱ ወጥቼ ፈለጉን ተከትዬ የወጣልኝ ገጣሚ እና ደራሲ ሆኛለሁ😜 እንዳውም በከድሬ አሳብቤ የገጠምኩትን ግጥም ልበልላቹ

........እማማ ትሙት...........
ያ የኔ ሽምጋይ
የልቤ አታላይ
በአስመሳይ ጥርሱ
በቅቤ ምላሱ
እንደሚወደኝ አስበልጦ ከርሱ
እማማ ትሙት! እያለ ምሎ
እመኚኝ ግድ የለም ወደድኩሽ ብሎ
ቃላትን ቀምሞ
ሲነግረኝ ከርሞ
እውነቱን ነው ብዬ
ቃሉን ተከትዬ
መሀላው አምኜ

እማማ ትሙት! እማማ ትሙት!
አሁንም ትሙት ደጋግማ ትሙት!
ሺ ጊዜ ሺ ጊዜ ገሎ በመሀላ
በዘረጋው ወጥመድ ከጣለኝ በኋላ
እንዳልገባኝ ገባኝ ያኔ እውነቱ
ሰንበትበት እንዳለ ከሞተች እናቱ


.......ከጅምሩ.......
ያኔ ስንገናኝ ከጅምሩ
እጆቻችን ሲያወሩ
ሬት ሳይልህ እኔነቴ
ስንባባል ያባረርከው
ድንበር ዘለው ልቦቻችን
ሲገናኙ አይኖቻችን
እያዜሙ የፍቅር ዜማ
ሊያበሩ የድል ሻማ
ወየው ዛሬ በነበረ
ትላንህናን ባልቀበረ
ድንገት ደርሰህ ስትለወጥ
አሁን ታየኝ ልቤ ሲሰምጥ
ሀ ብለህ ያስጀመርከው
ፐ ብለህ ሳጨርሰው
ለጋው ፍቅሬ ተሰበረ
ገና ሳያድግ ረገፈ
ውዴ ሲልህ ያባረርከው
ብሎ ቆሟል ትመጣ እንደው
.
.
ለ ከድር


ይሄ ነገሩ አድጎ ይኸው ከዚና ጠብቆኛል። ወንድሜ ባያስተምረኝ ኖሮ ዛሬ ከከድር ጋር በሀራም በተጨማለኩ ነበር

Part 1⃣1⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል1️⃣1️⃣6️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ ዘጠኝ 9⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን

ስልኩም እንደተላከ ሰው ላጥ ብሎ የሽንት ቤቱ ቀዳዳ ውስጥ ገባ......
ወይኔ ጉዴ ብዬ እዛው እንዳለሁ ጮህኩ። አጯጯሄ የሆነ ዱብዳ የመጣበት እንጂ ስልክ የገባበት አይመስልም ነበር።
.....አባዬም ደንግጦ ምን ሆንሽብኝ?? ብሎ መጣ።
......እኔም ስልኬ ሽንት ቤት ገባብኝ አልኩት።
......እሱም ጦስሽ ይውሰድ እኔ ሌላ የተሻለ እገዛልሻለው ይሄ ሊያሳስብሽም ሊያስደነግጥሽም አይገባም ብሎ አረጋጋኝ። ወደቤት አስገብቶኝ ትንሽ ከቆየን በኋላ እንዳዲስ ሽንት ቤት ስልክ ይዘሽ ምን አስገባሽ ??ብሎ ተቆጣኝ በተጨማሪም የትምህርት ውጤቴ እያሽቆለቆለ በመምጣቱ ለትንሽ ጊዜ ስልክ መያዝ እንደሌለብኝ ወሰነ።

በዚህም ምክንያት ከከድር ጋር የምገናኝበት ጊዜ አጥሮዋል። ልክ እንደድሮው እዛቹ ፖል ተደግፎ ይጠብቀኝ ጀመር። ሁል ጊዜ ከመድረሳ ስወጣ ጠብቆኝ የኛን እና የነሱን ሰፈር ማለትም አብነትን ከሰባተኛ ወይም ልደታ ክፍለ ከተማን ከ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የሚለየው ድንበር የሆነው የሚገነጥላቸው ዋነኛ አስፓልት ማለትም አብነት አደባባይ የሚባለውን አስፓልት ድረስ ሸኝቶኝ አባት ልጁን እንደሚያሻግረው እጄን ይዞ አሻግሮኝ ወደቤቱ ይመለሳል። አስፓልቱን ሳያሻግረኝ ተለያይተን አናውቅም ድንገት ዞር ስል መኪና ቢገጭሽስ እያለ በሚያሳሳ አስተያየት ይመለከተኛል።

ከ 15 ቀን እረፍት መልስ እኔም ትምህርቴን በስርአቱ መከታተል ቀጠልኩ እናም ለሚኒስትሪ ፈተና እራሴን ማዘጋጀቱን ተያያዝኩት።ትምህርት ቤቱ 31 ተማሪ ነው ሚኒስትሪ የሚያስፈትነው ።ከሰላሳ አንዱም እኔ ዮናታን እና ዮሴፍ ከክፍሉ ሰነፍ ተማሪዎች እንዲሁም ሚኒስትሪን አያልፉም ተብለው ከሚታሰቡ ተማሪች መካከል ዋነኞቹ ነበርን፡፡ እናም ላለመውደቅ እራሴን መታገል ጀመርኩ።
ከድርም ሰቃይ ተማሪ ስለሆነ ብዙ ጊዜ እየተገናኘን ያስጠናኛል። እንኳን አስረድቶኝ ዝም ብሎ ሲመለከተኝም ይገባኛል። አላህዬ ሰርጋችንን ዛሬ አድርገው እያልኩ ሁል ጊዜ ዱአ አደርጋለው። ከድሬም ከአንቺ አትለየኝ ብሎ ሁል ጊዜ ዱአ እንደሚያደርግ ነግሮኛል። በአለም ላይ እንደኔ ደስተኛ ያለም አይመስለኝም መሳቅ መደሰት ብቻ ነው የሚታየኝ።

እንደተለመደው አንድ ቀን ሊያስጠናኝ ገዳመ እየሱስ መዝናኛ ሄድን እና እንደወትሮው ጥናታችንን ቀጠልን።ከብዙ ጥናት በኋላም እረፍት ማድረግ እንዳለብን ወስነን መቀላለድ ጀመርን።
..... ከድሬም ድንገት ሳላስበው ልክ እንደባለፈው ሳመኝ።
.....እኔም ኮስተር ብዬ ምን መሆንህ ነው ??አንተ እኮ ሴት የማትጨብጥ ሰው ነህ ከ ትዳር በፊት እንደዚህ መሆን የለብንም ብዬ ተኮሳተርኩ።
..... ከድርም አኩርፎ ወደቤት እንሂድ ብሎ ትቶኝ ወጣ። ከዛን ቀን ጀምሮ ለኔ ያለው ፍቅር እየቀነሰ መጣ እናም አንድ ቀን ለምንድነው የምትርቀኝ?? እያልኩ በግልፅ ጠየኩት
...... እሱ አልራኩሽም አሁንም አፈቅርሻለሁ አለኝ ያኔ ልቤ እንዳዲስ አንሰራራ።በተለይ ደሞ የስኳር በሽተኛ ስለሆነ በቻልኩት አቅም እሱን መንከባከብ ጀመርኩ። ለሱ ያለኝ ፍቅር ከለት ወደየለት በበርሜል እንደሚያጠራቅሙት ውሀ እየጨመረ እየጨመረ መቶዋል።

አንድ ቀን ዛሬ ትምህርት ስንለቀቅ የምነግርሽ አለ አለኝ
....እኔም ምን ይሆን የሚነግረኝ እያልኩ ብቻየን ማሰብ ሁኗል ትምህርት ሰአት መምህሮቹ ቢያስተምሩም ምንም ማዳመጥ አልቻልኩም፡፡

ትምህርት ተለቀቅን ከድርም ያለምንም ማፈር አብረን ማደር እንዳለብን ነገረኝ
.....እኔም በጭራሽ አይሆንም አልኩት
.......ከድርም አንቺ እኮ ሚስቴ ነሽ ምን ችግር አለው?? ዛሬም ሆነ ነገ ለውጥ የለውም ነገ ስንጋባ ማድረጋችን አይቀርም ስለዚህ እናድርግ አለኝ።
....እኔም ቆሜ ማሰብ ጀመርኩ።ግራ መጋባቴን ሲመለከት
...... እንዳውም እንቢ የምትይኝ ከሆነ ይሄ እኔን አለማፍቀርሽ ነው የሚያሳየው እንቢ ምትይኝ ከሆነ ፍቅራችንን ማቋረጥ እና መለያየት እፈልጋለው ብሎ ወሽመጤን ቆረጠው።አስከትሎም የምታፈቅሪኝ ከሆነ ይሄን ውለታ ብትውይልኝ ምን ችግር አለው?? አለኝ።

የከድር እንደዚህ መናገር አስደንግጦኛል በሚስተካከለው መልኩም አናዶኛል።አፈቅርሻለው እያለ ለጆሮዬ የነገረኝንም ደጋግሜ እያስታወስኩ በመሀል ፈገግ እላለው።እሱን አጥቼ መኖር አልችልም እሱ ማለት ለኔ ደስታዬ ተስፍዬ ኩራቴም ጭምር ነው ከሱ ተለይቼ መኖር አልችልም እሱ ከሌለ ኑሮዬ ጨለማ ነው አለም ለኔ ጨለማ ትሆናለች። እሺ ብዬ ላስደስተው ብዬ አሰብኩ ፍቅሬን ላሳየው ብዬ ልቤ አመነታ ትንሽ እንደተራመድኩም ግን ለምንድነው ይሄንን የምንፈፅመው ??? ገና እኮ 15 አመቴ ነው እያልኩ ከራሴ ጋር ታገልኩ ከብዙ ትግል ከብዙ ማሰብ እና ከብዙ ጭንቀት በኋላ ውሳኔዬን ላሳውቀው ወደ ከድሬ አመራሁ።
........ ፊቱ ቆሜ አይኔን ከአይኑ ገጥሜ ጥርሴን ከጥግ እስከጥጉ ከፍቼ ከድሬ አልኩት


Part 🔟
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል አስር ከ6️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

7.4k 0 35 17 84

💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ ስምንት 8⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን


ከድርም ያለምንም ማቅማማት ጥያቄዬን እንደተቀበለው በፈገግታ አጅቦ ነገረኝ። በደስታ ሰከርኩ።ምንም ቃል ሳልተነፍስ ወደ እደሩስ አመራሁ እናም ይሆነውን ሁሉ አስረዳኋት እስዋም ደስታሽ ደስታዬ ነው ብላ ሳቅዋን አቀለጠችው።

ጊዜያት ነጎዱ ከከድር ጋም ከትምህርት ሰአት ውጪ ክላስ እየቀጣን ሰው ዝር የማይልበት አካባቢ መገናኘት ጀመርን ግን አንድም ቀን አቅፎኝ ወይም ነክቶኝ አያውቅም። ጊዜው ነጎደ 7ተኛ ክፍልን ጨረስን።ብዙ ተማሪዎች ወደ 11 የሚጠጉ ተማሪውምች 7ተኛ ክፍልን ወድቀው ደገሙ እኛም 8ተኛ ክፍል ገባን።በዚህ አመት ስልክ ተገዛልኝ። ከድርም ስልክ ስለነበረው ተለዋውጠን ማታ ማታ በድብቅ ሽንት ቤት ውስጥ ቁጭ ብዬ አውርቼው እተኛለሁ።

በዛ መሀል ሲናፍቀኝም ሚሴጅ እልክለታለው። ከለት ወደየለት ፍቅሩ እየጨመረብኝ መጥቷል።እሱም በስስት ያየኛል።ድንገት ትምህርት የቀረሁ ለትም ዛሬ ሳላይሽ ላድር ነው ማለት ነው ??ብሎ ያኮርፈኛል።በትምህርቴ በጣም እየደከምኩ ነው እንደድሮ አይደለሁም።ሰባተኛ ክፍልንም 2 ትምህርት ከ 50 በታች አምጥቼያለው።


ከድርን እንደማገባው እና የወደፊት አጋሬ እንደሆነ 100% እርግጠኛ ሁኛለው። ባገኘሁት ቁጥር ነብስያዬ እቀፊው ሳሚው እንደልብሽ ሁኚበት ይለኛል ነገር ግን ወንድሜ ያለኝን ንግግር ሳስታውስ ወደ ቀልቤ እመለሳለው።ወንድሜ ከልጅነቴም ጀምሮ ከትዳር በፊት ፍቅረኛ ምናምን ብሎ ነገር መያዝ እንደሌለብኝ ከአላህ መንገድ እንደሚያስወጣኝ እና ክብሬን መጠበቅ እንዳለብኝ በፍፁም በወንድ ተታልዬ ከማንም ጋር ዚና መስራት እንደሌለብኝ።አላህ ዘንድ የዚናን ያክል ከባድ ወንጀል እንደሌለ ሴት ልጅ ክብርዋን በሀራም ካስወሰደች ማንም እንደማያከብራት እና ሂወትዋ እንደሚበላሽ ብዙ ጊዜ ነግሮኛል።

ምንም እንኳን ካዱኩ በኋላ አላህ ዘንድ ከሁሉም ወንጀል ከባዱ በእርሱ በአላህ ላይ ማጋራት ወይም ማሻረክ እና ዚና እንደሆነ ነው አይምሮዬ የፃፈው ። እንደተለመደው ክላስ ቀጥተን ተደዋውለን ሁል ጊዜ ምንፎርፍባት ገዳመ እየሱስ የሚባለው መናፈሻ ቦታ አመራን እዛም ሳሩ ላይ ጫማችንን አውልቀን ተንደላቀን ቁጭ አልን።

ከድሬም ከኪሱ አንድ ነገር አወጣና ይሄ ላንቺ ነው አለኝ። ረጅም ቸኮላት ነበር እናም ለመብላት ጓጓሁ።ስጠኛ ብዬ አይኔን አቁለጨለጭኩ።ከድሬም እንዲ በቀላሉማ አልሰጥሽም አህያ ነኝ በይና እሰጥሻለው አለኝ እኔም ለመብላት ካለኝ ጉጉት የተነሳ አህያ ነኝ አልኩት ቀጥሎም አይ ውሻ ነኝ በይ አለኝ። እኔም አስከትዬ ውሻ ነኝ ስጠኝ በቃ አልኩት።እሱም ውሻ ከሆንሽ እንደ ውሻ በአፍሽ ተንጠራርተሽ ውሰጂ አለኝ
....እኔም እንዴት አድርጌ ስለው ቸኮላቱን ከፈተውና በአፉ ይዞ ይኸው እንዲ እይዝልሻለው አንቺ እየገመጥሽ ብይ አለኝ።
......እኔም ሳላቅማማ በሀሳቡ ተስማምቼ አንድ ሁለት ሶስት እያልኩ በአፌ ከአፉ ላይ እየወሰድኩ ተመገብኩ።አንዴ በጎረስኩ ቁጥር ወደ ከንፈሩ እየተጠጋሁ ነው።አንድ ጊዜ ምትጎረስ ያክል ስትቀር ልጎርሳት ስጠጋው ቸኮላቱን እራሱ ጎርሶት ከንፈሬን ከከንፈሩ አገናኘው። የሰርጋችን ቀን ዛሬ የሆነ መሰለኝ። ደስ አለኝ ከንፈሬ ከከንፈሩ ሳይላቀቅ ነገን ማለም ጀመርኩ። ልቤ ከአካሌ ተንሸራታ ስትወድቅ ተሰማኝ። ድንገት የወንድሜ ንግግር ትዝ ሲለኝ ከእንቅልፍ እንደነቃ ህፃን ብንን ብዬ ተነሳሁ።
......ከድሬንም ቻው እንኳን ሳልለው በፍጥነት ወደቤት አመራሁ። ህልም ያየሁ መሰለኝ ከንፈሬ ኪሎ የጨመረ እስኪመስለኝ ድረስ ከበደኝ። ከዛን ቀን በኋላ ከከድሬ ጋር መተፍፈር አቆምን። እዛዉ መነፈሻ በተደጋጋሚ እየሄድን ነዉ ከሄድንም በኋላ እቅፍፍፍፍፍ አድርጎ ጉንጬን ይስመኛል ደረቴ ላይ ተኝቶም ስላንዳንድ ነገሮች ያወራኛል።
ሁለታችንም ተጋብተን ልጆች የምንወልድባቸውን ቀናቶች ናፍቀውኛል በጉጉት እየጠበኩትም ነው።


የመጀመርያው መንፈቅ አመት የማጠቃለያ ፈተና ከመድረሱ በፊት የሚኒስትሪ ተፈታኝ ተማሪዎች እንደመሆናችን መጠን ሞዴል ተፈተንን እናም የ 15 ቀን እረፍት ተሰጥን።
..... ከድሬን በስልክ ስለማገኘው ትምህርት መዘጋቱ አላሳሰበኝም ማታ ማታም ከመተኛታችን በፊት የፍቅር ቃላትን ተለዋውጠን እንተኛለን።


እንደተለመደው ሽንት ቤት ቁጭ ብዬ እያወራሁት እንዳለ አባዬ ውሀ በውዱእ በማንቆርቆርያ ላስቲክ ይዞ ወረፋ ሲጠብቅ በቀዳዳ ተመለከትኩት።
......የሰማኝ ስለመሰለኝ በድንጋጤ ስልኩን ጣልኩት። ስልኩም እንደተላከ ሰው ላጥ ብሎ የሽንት ቤቱ ቀዳዳ ውስጥ ገባ......

Part 9⃣

ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........

🔻ክፍል ዘጠኝ ከ6️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

7.8k 0 32 10 78

💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ ሰባት 7⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን




እኔም እግሩ ስር ተደፍቼ እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ ሁለተኛ አይለመደኝም የፈለከውን ቅጣኝ ወላጅ አታስመጣኝ ብዬ ለመንኩት በስተመጨረሻም 15 ግርፍት ተፈርዶብኝ ቂጤ እስኪላጥ ጠረፔዛ ላይ አስተኝተው ገረፉኝ።

እውነት ለመናገር አባቴን ከማመጣው አይደለም ቂጤ እስኪላጥ አካሌ እስኪሰባበር ቢገርፉኝ እመርጣለው። ምክንያቱም አባቴ ሱናደድ ሰይጣን ነው አንቆም ሊገለኝ ይችላል። ግርፋቱ እና ፍርሀቱ ተጨማምሮ እያንቀጠቀጠኝ ወደ ክፍል ገባሁ። ናትኔኤል የሆነች ልጅ ጠየቀችኝ ብሎ ለአባቱ ደብዳቤውን አሳይቶት አባቱ ደሞ ትምህርት ቤት መቶ ከሶኝ ነው ለዚህ የተዳረኩት። ከዛን ቀን ጀምሮ እኔና እየሩስ ደብዳቤ መፃፉን እርም ብለን ተውን።


እየሩስ ለከድር ያለኝን ስሜት ከነገርኳት ቀን ጀምሮ ካልነገርሽው እያለች ትጨቀጭቀኛለች። ለሱ ደብዳቤ ብትፅፊለት እኮ የሚመታሽ የለም እያለች የናቲን ጉዳይ እያስታወሰች ታስቀኛለች። በዚህ በኩል እስዋ በዛ በኩል ደሞ ይክላስ ተማሪዎች አላስቀምጥ አሉኝ እናም ደብዳቤ ፅፌ ልሰጠው ወሰንኩ።

ከድር ተክለ ሰውነቱ ረጅም እና ወፈር ያለ ነው ቡኒ አይን እና አመዳማ ወርቃማ የሚመስል ፀጉር አለው።እኔ ደሞ የሱ ተቃራኒ አጭር ቀጭን ነኝ። አብረን ስንሆን ላየን ሰው አባት እና ልጅ ነው የምንመስለው።

ሰኞ ረፋድ አካባቢ ደብዳቢውን ፃፍነው። ተፃፈ በ 20/06/2006 መልሱ ለ ጁመአ 24/06/2006 ብለን ቋጨነው። እናም ከክላስ ስንወጣ ልሰጠው ተስማማን


ከዛም ከመድረሳ ስወጣ እንደተለመደው ሰላምታ ተለዋውጠን ብቻ ደብዳቤውን ሳልሰጠው አለፍኩ። ልቤ በጣም ፈራ። እየሩስም ተናደደችብኝ እናም ነገ እኔ እሰጠዋለው ብላ በንዴት ቀማችኝ። አይነጋ የለ ነጋ ስንማር ውለን አስተማሪ አዳርቀን ..ወደ መድረሳ ስሄድ አገኘነው እና እዩ እሰጠዋለው ብላ እንዳልደነፍች ስታየው ተንቀጠቀጠች።ኧረ እራስሽ ስጭው ብላ ደብዳቤውን ሰጠችኝ። እኔም ሳልሰጠው አለፍኩ።
...... እዩ ተናዳለች ምክንያቱም ደብዳቤው ላይ ተፃፈ በ 20/06/2006 የሚለው ፅሁፍ ቀኑ በጨመረ ቁጥር ልንሰጠው ፈርተን እንዳቆየነው ይናገርብናል ብላ ተጨንቃለች።በስተመጨረሻም እሮብ በ 22/06/2006 አመተምህረት ደብዳቤውን ሰጠሁት። ከሰጠሁት በኋላ አይኑን ማየት ሞት መስሎ ታየኝ ፈራሁት። አላፈቅርሽም ተይኝ ቢለኝስ ምንድነው የማደርገው??? እያልኩ እራሴን በሀሳብ ወጠርኩ።

በሀሳብ ብዛት ሳልተኛ ስላደርኩ እራሴን በጣም አመመኝ በዚህም ምክንያት ሀሙስ ትምህርት ቤት ከመሄድ ቀረሁ። ጁመአም እራስ ምታቱ ቢሻለኝም አልተሻለኝም በሚል ስበብ በድጋሚ ቀረሁ።

ትምህርት ቤት ቀርቼ የማላውቀው ልጅ ዛሬ አመመኝ ብዬ ስቀር አባቴ በጣም ተጨንቆ ሀኪም ቤት መሄድ አለብሽ ብሎ ቢጋተተኝም ደህና ነኝ እረፍት ላድርግ ብዬ ነው ብዬ አረጋጋሁት። ደስ እንዲለውና ደህንነቴ እንዲታየው ብዬ ከተኛሁበት ተነስቼ ቤቱን አፀዳድቼ ቆንጆ ምስር ወጥ ሰርቼ ቤቱን ፏ ሽክ አደረኩት ።

ጁመአ ማምሻ አካባቢ እየሩስ ቤታችን መጣች እኔም ለምን እንደቀረሁ ጠየቀችኝ
.....እኔም አባቴ ስለነበር ትንሽ አሞኝ እንደሆነ ነገርኳት። ሻይ አፍልቼላት ከጠጣች በኋላ ልሸኝሽ ብያያት ተያይዘን ከቤት ወጣን እናም የቀረሁት ከድርን ላለማየት ብዬ እንደሆነ ነገርኳት።
....እስዋም የስንቱን ወንድ ፊት እንዳልፈተንን ዛሬ ምን ነክቶሽ ነው እንዲህ የምትሆኚው ??ብላ አደፍፈረችኝ እናም ነገ ቅዳሜ የማጠናከሪያ ትምህርቱን እንዳልቀር አስጠንቅቃኝ ሄደች።

ቃልዋን ተቀብዬ ቅዳሜ ጥዋት ቦርሳዬን ይዤ ለሜካፕ ክላስ ዩኒፎርም ስለማይለበስ ሽቅርቅር ብዬ ወደ ትምህርት ቤት ሄድኩ። ከድርን የማገኝባት ያቺ ፖል ብቻዋን ተገትራለች።የናፍቆት አይኔ እየተንከራተተ ትምህርት ቤቴ ገባሁ።
ተምረን ከጨረስን በኋላም ከእየሩስ ጋር ተያይዘን ወጣን። ከድር በተለምዶው ቦታው ቆሞዋል። ላናግረው ፈራሁ።
......አሰላሙ አለይኩም ሳልለው ዝም ብዬ ላልፍ ወሰንኩ እናም እየፈጠንኩ ስራመድ እዩ እንዳልሄድ እላዬ ላይ እንደ መዥገር ተጣብቃብኝ መልሱን ሳንሰማ ዛሬ አንሄድም ብላ ትመልሰኛለች።አሁንም አመለጥኳት ብዬ ስጓዝ ከየት መጣች ሳልል ገፍትራ ወደነበርኩበት ትመልሰኛለች።

ሳልፈልግ በግዴ እየተንቀጠቀጥኩ ወደ ከድር አመራሁ እናም መልሱን ለመስማት እንደወታደር ፊት ለፊቱ ተገትሬ ቆምኩ
.......ከድርም

Part
8️⃣

ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል

🔻ክፍል ስምንት ከ6️⃣0️⃣ 👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍😀 ማድረግ አይርሱ

     የፍቅር ቴሌግራም  ቻናል
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!

8k 0 35 1 64

💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ ስድስት 6⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን



ስገባም አልጋው ላይ እግሩን ወደ መሬት አንጠልጥሎ ተቀምጧል። ወይ የሰው መመሳሰል! አባዬ አልነበረም ግን በጣም ይመስላል።ቀድሞውኑ አይኔ ዋሽቶኝ ነው እንጂ አባቴ እንደዚህ አይነት ቅሌት እንደማይሰራ እና እንደዚህ አይነት ነውር እንደማያደርግ አውቃለው።


ቢሆንም አባዬ ስላልሆነ ንዴቴ አልቀነሰም ሊበርድልኝ አልቻለም ምክንያቱም ሰውዬው ወደ ሴተኛ አዳሪዋ ቤት የገባው ትልቅ ሰዉ ነዉ ። ቅሌታም ነህ ትልቅ ሰዉ አሰዳቢ እያልኩ ዘለፋዬን ቀጠልኩ
.......ሴተኛ አዳሪዋም ዞር በይ ገበያ አትዝጊብኝ ብላ እንደቆሻሻ አሽቀንጥራ ከቤትዋ አስወጣችኝ።

ቆሻሻውስ አንቺ ነሽ መገፍተር የሚገባሽ አንቺ ነሽ እያልኩ በልቤ የንዴት ስሜቴ ጥርሴን እያፈጫጨው ወደ ቤቴ ገባሁ።


ለከድር መናገር ያልቻልኩትንም ጭምር ንዴቴን አባብሶት እራስ ምታት እንደ መጋኛ አመመኝ።ቤትም እንደገባሁ ጥቅልል ብዬ ተኛሁ። በማግስቱም እንደተለመደው ቦርሳዬን እና ምሳዬን ይዤ ወደ ትምህርት ቤት አመራሁ። መንገዱን እየተጓዝኩ የማስበው ስለ ከድር ነው። ስሜቴን ያወቀብኝ እየመሰለኝ በራሴ አፈርኩ። እሱን ማናገሩም ሞት መሰለኝ። ከዛን ቀን ጀምሮ ብዙ ጊዜ አሰላሙ አለይኩም ሲለኝ ባልሰማ አልፈው ጀምሬያለሁ
አስተማሪዎቼ ሁሉም ማለት ይቻላል በጣም ይወዱኛል። በተለይ ደግሞ ጥያቄ ለመጠየቅ እና የማስበውን ለመናገር ስለማልፈራ ያበረታቱኛል። ሀሳባቸውንም ቢሆን ለመቃረን ቅድሚያ የምነሳው እኔ ነኝ በዚህም ምክንያት ነው ለኔ ያላቸው ፍቅር ልዩ የሆነው.


ሰባተኛ ክፍል አጋማሽ ደረስን። የፋይናል(የመጀመርያ መንፈቅ አመት ማጠቃለያ ) ፈተናችንን ከተፈተንን በኋላ የ 15 ቀን እረፍት ተሰጠን። 15 ቀኑ 15 አመት ሆነብኝ ጊዜው አልቆ ትምህርት እስክንጀምር ጓጓሁ። የከድር ናፍቆት አላስቀምጥ አለኝ።መድረሳ ስሄድም ቆሜ ብጠብቀውም ላገኘው አልቻልኩም።አንዳንዴም እያለቀስኩ አላህዬ አንድ ጊዜ አይኑን ብታሳየኝ ምናለ እያልኩ አነባለሁ።

የእረፍት ጊዜያችን አብቅቶ የትምህርት ገበታችንን ጀመርን።እየሩስ ናፍቀሽኛል ብላ ተጠመጠመችብኝ።እኔም ናፍቀሽኛል ብዬ አንገትዋ ስር ተወሽቄ አለቀስኩ። ግን ያለቀስኩት በ ከድር ናፍቆት እንጂ በእሷ አልነበረም። ባለፉት 15 ቀን ውስጥ የተፈጠረውን አንድ አዳዲስ ነገር ማውራት ጀመርን።

ለእየሩስም ከድርን አፍቅሬዋለሁ ብየ ነገርኳት። በዚህ መሀል ይክፍላችን ልጅ የሆነው ሮቤል ንግግሬን ሰምቶ በፌዝ ዘቢባ ፍቅር ያዛት እያለ አወራ። ሙሉ የክላሱ ተማሪዎችም ማፍቀሬን እና ማንን እንዳፈቀርኩ አወቁ።


ከድር መኖሪያ ቤቱ ከትምህርት ቤታችን አጠገብ ስለሆነ ማንነቱን ለማወቅ አልተቸገሩም። እኔና እዩ ወንዶችን የፍቅር ጥያቄ መጠየቃችንን አላቆምንም
የ ስድስተኛ ክፍል ተማሪ የሆነውን ናትናኤልን ለመጠየቅ ወሰንን እና ይሄንን ድርጊት እኔ እንዳደርገው ወስነን ደብዳቤውን ሰጠሁት።

በማግስቱም ጠዋት የመጀመርያ ክፍለጊዜ ላይ እየተማርን እንዳለ የክፍል ሀላፊዬ የክፍልን በር አንኳኳ እናም ስሜን ጠርቶ ቢሮ እንደምፈለግ ነገረኝ።
....... እኔም ምክንያቱን ባላቅም ወደ መምህራን ቢሮ አመራሁ። ሁሉም ክፍለጊዜ የሌለው አስተማሪ ተደርድሮ ቁመዋል። በተጨማሪም ናትናኤል እና አባቱም አሉ። ጉዳዩ ግራ ገባኝ የጠረጠርኩት ነገር አልነበረም።


ዳይሬክተራችን ነገ ወላጅ ይዘሽ እንድትመጪ አሁን ቦርሳሽን ይዘሽ ወደ ቤትሽ ሂጂ አለኝ። ምክንያቱ ሊገባኝ አልቻለም።
....... እንዴ ለምን?? ምን አጠፍሁ ቲቸር??? እባክህ እያልኩ ለመንኩት
.......ዳይሬክተሩም እንዳንቺ አይነት ባለጌ ተማሪ አንፈልግም ብሎ እየገፈታተረ ከቢሮ አስወጣኝ....


Part 7⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል


🔻ክፍል ሰባት ከ 6️⃣0️⃣ 👍በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌  የፍቅር ቴሌግራም  
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


💧〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰🧬
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አምስት 😀

✍️ ፀሀፊ ☞ #ዘቢባ_ሱልጣን



ሰባተኛ ሰፈርን ከሰባተኛ ክፍል ጋር ተቀላቀልን። ሰባተኛ ሰፈር መጠጥ ቤት እና ቡናቤት ይበዛል። ሴተኛ አዳሪዎችም ቤት ተከራይተው ወንድን በሚወሰውስ አለባበስ ወንዶችን ሲቀበሉ ማየት የተለመደ ነው። እዛ አካባቢ ከሚኖሩት ነዋሪዎች 50 % ማለት ይቻላል ሴተኛ አዳሪዎች ናቸው። ወላሂ እዛ አካባቢ ተወልዶ ያደገ ልጅ ሰው ሚሆንም አይመስለኝም። ሴተኛ አዳሪዎቹ ቤት ገብተው ከሴተኛ አዳሪዎቹ ጋር የሚተኙት ሰዎችን መመልከት ያሳፍራል። አብዛኛዎቹ በኛ እድሜ ላይ ያሉ ማለትም ከ 16_25 እድሜ ክልል ላይ የሚገኙ ወጣቶች ናቸው። የተቀሩት ደሞ ጎዳና ተዳዳሪዎች ናቸው።

ሰባተኛ ክፍል ስንገባ እድገት ተሰምቶኛል ደስተኛም ነኝ። ሁሉም ተማሪ የየራሱ ለውጥ አሳይቶአል ወንዶቹ ድምፃቸው እየጎረነነ ሴቶቹም ጡታቸው እያጎጠጎጠ መጥቷል። በትምህርት ቤታችን ህግ መሰረት ሰባተኛ ክፍልን 3 ትምህርት ቀይ(flat) የገባበት ማለትም ከ50 በታች ያመጣ ተማሪ ወደ ስምንተኛ ክፍል ማለፍ አይችልም ስለሆነም በዚህ ምክንያት እና በአንዳንድ ትምህርቶች ለውጥ ማለትም ኬሚስትሪ ሶሻል እና ባዮሎጂ የተባሉ ትምህርቶች በ እንግሊዘኛ መማር በመጀመሩ ምክንያት ሁሉም ተማሪ ስጋት ላይ ነው።

እኔ ግን እያሰጋኝ ያለው ትምህርቱ ሳይሆን ከከድር ጋር የያዘኝ ፍቅር መናገር አለመቻሌ ነው። ከ እየሩስ ጋር ወንዶችን መፈታተኑን ቀጥለንበታል።ከክፍላችን ወንዶች አንድም የቀረን የለም ሁሉንም ጠይቀናል።
ከመድረሳ ስወጣ እንደተለመደው ከድርን አገኘዋለው። ይሄን ያክል ጊዜ ስንገናኝ አሰላሙ አለይኩም ከመባባል ውጪ ሌላ ንግግርም ሆነ ቀረቤታ አልነበረንም።


አንድ ቀን ግን ስሜቴን ለከድር መናገር እንዳለብኝ ወሰንኩ እናም ለ እየሩስ ሀሳቤን ሳልነግራት ከትምህርት ቤት ስወጣ እዛቹ ፖል ተደግፎ አገኘሁት። እናም ወደርሱ አመራሁና አሰላሙ አለይኩም አልኩት
........እሱም በሚያምረው ፈገግታው ድምፁን አለሳልሶ ወአለይኩም ሰላም ወራህመቱላህ አለኝ።
.......ከዛም ለሆነ ጉዳይ ፈልጌህ ነበር ይመችሀል አሁን ብናወራ??? አልኩት።
......እሱም አይ አሁን መድረሳ ይረፍድብኛል ከመድረሳ በኋላ አለኝ።
......እኔ ደሞ ከመድረሳ በኋላ ስለሚመሽብኝ በቃ ነገ
9፡30 እዚሁ ቦታ ላይ እንገናኝ ብዬው ቀጠሮ ይዘን ተለያየን።


አይነጋ የለ ነጋ የቀጠሯችን ሰአት ደረሰ። የማጠናከሪያ ትምህርቴን ትቼ ከድርን ለማግኘት ሄድኩ።ቦታውም አገኘሁት። እንደተለመደው ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ እዛችው ፓል አጠገብ ድንጋይ ላይ ቁጭ ብለን ለምን ነበር የፈለግሽኝ ብሎ በጥያቄ ጀመረኝ።

ጥያቄውን ለመመለስ ተቸገርኩ በቃ ስለማፈቅርህ ያላንተ መኖር ስላልቻልኩ ይሄንን ልነግርህ ነው የመጣሁት ብዬ የሆዴን ለማውጣት ታገልኩ ግን አልቻልኩም።ከጥቂት ዝምታ በኋላ ምን ሆነሻል ንገሪኛ??? ብሎ ጥያቄውን ደገመው።
.....እኔም ወድያው ሀሳቤን ቀይሬ ስለ ኑሮህ ማወቅ ፈልጌ ነው.. ማለት ከማን ጋር ነው የምትኖረው?? ብዬ አስቀየስኩት
......እሱም እናቱ አረብ ሀገር እንደሆነች እና የሚኖረው ከ አባቱ ጋር እንደሆነ ነገረኝ።
......ንግግሩን ከጨረሰም በኋላ በቃ ለዚህ ነው የፈለግሽኝ? ብሎ ሌላ ጥያቄ አስከተለብኝ።
......እኔም ምን ያለበት ምን አይችልም እንደሚባለው ታዳ ሌላ ምን ይኖራል ??ብዬ ተኮሳተርኩበት። እናም ቀጥታ ወደ መድረሳ አመራሁ።


ከመድረሳ ቆይታዬም በኋላ ስወጣ እየሩስ የመድረሳችን በር ጋር ቆማ አገኘኋት። ግልምጫዋ ይገፍተራል። ከክፍል የወጣሁት ሳልነግራት ስለሆነ ተጨንቃለች። ጥያቄ ሳታነሳብኝ በፊት አስቀድሜ እኔ ስለደበረኝ አንቺንም እንዳትማሪ እንዳላደርግሽ ብዬ እኮነው ትቼሽ የወጣሁት እዩ አትቆጪ ብዬ አስቀድሜያት ሳኩ። ሳቄ ያስቃታል ጭንቀት ውስጥ እንኳን ብትሆን ፈገግታዬን ስታይ ትስቃለች። እነዛን ጥናኒጥ የአይጥ ጥርስ የሚመስሉት ጥርሶችዋን ከፈታ አሰጣችልኝ እናም ተቃቅፈን ጉዞአችንን ቀጠልን።



ለከድር ያለኝ ስሜት መናገር ባለመቻሌ አዝኛለው ደካማ እንደሆንኩ ተሰምቶኛል። ከመድረሳም ከወጣሁ በኋላ እዩን ሸኝቼ ስመለስ መሽቶብኝ መግሪብ አካባቢ ወደ ሰፈር ስገባ አቋራጭ መንገድ ለመጠቀም ብዬ በሴተኛ አዳሪዎቹ ቤት በኩል ሳልፍ አንድ ሰውዬ ተመለከትኩ። አባዬ ሴተኛ አዳሪ ቤት ሲገባ አየሁት። እግሬ ተንቀጠቀጠ ድንጋጤዬ ሰውነቴን ወረረው እንባዬ መዝነብ ጀመረ።አባዬ ብዬ ለመጥራት አፌ ተለጎመ። በደመነፍስ ወደ ቤቱ አመራሁ ሴተኛ አዳሪዋም በሩን ዘጋችው።

እየተንደረደርኩ ሄጄ የተዘጋዉን በር እየደበደብኩ አንቺ ውሻ ክፈቺው አባቴን አታሳስችው ክፈችው እያልኩ በሩን በእጄ እየወገርኩ።
......ልጅትዋም ከፈተችው።ገፍትሬያት አባቴን ለማናገር ወደ ውስጥ ዘልቄ ገባሁ......



🔻ክፍል ስድስት ከ6️⃣0️⃣ በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍💝 ማድረግ አይርሱ።
🔺🔺🔺🔺🔺😀😀😀😀😀

      ‌‌‌‌‌‌  የፍቅር ቴሌግራም  
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰
 
የታሪኩ ርዕስ
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
   
   #ክፍል ☞ አራት 4

ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን




ከትምህርት ቤት እና ከመድረሳ ስወጣ እየጠበቀ ሰላምታ መስጠት ጀምሯል ለዛም ነው መሰለኝ አይኔ ያረፈበት።

እየሩስም መውጫ እና መግቢያችን ላይ ስንፋጠጥ እያሾፈችብኝ ማላገጥ ጀምራለች።እዩ ንግግርዋ ይማርከኛል እንኳን ወንድን ሴትን ያሳስታል።በተለይ ሙድ ስትይዝ እ አይደለም እንዴ ¡አሀ ነው¡ ተይ ባክሽ¡ ኡኡቴ እያለች ግንባርዋን ሸብሽባ ቅንድብዋን ላይ ታች ምታጫውተው ነገር ይበልጥ እወድላታለው።

በዚህ አመት ሁለት አዳዲስ ነገር ተፈጥሯል እዩ ሀይድ ማየት ጀምራለች ሌላው ደግሞ ኩረጃን ተምረናል። እንዳውም ኩረጃን እየተማመንን ማጥናቱን ዘንግተነዋል። የ እዩ ሀይድ መምጫ ሰአት ሲደርስ የምትሆነው ነገር በጣም ያስቀኛል። ሞዴሱን ከፓንትዋ ጋር አገናኝታ ከለበሰች በኋላ ሞዴሱ ሾልኮ ሚወድቅባት እየመሰላት ከፓንቱ ላይ ሌላ ሁለተኛ ፓንት ትደርብበታለች በመቀጠልም ታይት ታጠልቃለች።በ ታይቱ ላይ ሌላ ቁምጣ ትደርብበታለች።ይሄ ነገርዋ በጣም ያስቀኛል።

ሰው ሁሉ ሀይድ ላይ መሆንዋን የሚያውቅባት ይመስላታል። የደራረበችው ፓንት እና ታይት ሰውነት(ዳሌ ) ይሰጣታል ይሄ ነገር ደሞ ይበልጥ ያስቀኛል። ሀይድዋ ሲመጣ የምትለብሰው ዩኒፎርም እራሱ ይለያል። የሌላ ጊዜው ዩኒፎርም ጉርድዋ ከጉልበትዋ ልክ የሆነ ሽንሽን አጭር ቀሚስ ነው ሀይድ ላይ ስትሆን ግን እስከ ቁርጭምጭሚትዋ ድረስ የሚደርስ ሽንሽን ጉርድ ነው ምትለብሰው።በዚህ ሁኔታዋ ስለምስቅባት የኔ ሳቅ ይበልጥ ያበሽቃታል።


በዚህ አመት የትምህርት ውጤቴ እያሽቆለቆለ ስለመጣ አባቴ ከትምህርት ሰአት ውጪ የጥናት (ማጠናከሪዬ) ትምህርት እንድማር አመቻቸ። አዲስ አበባ ላይ ብዙዎቹ ትምህርት ቤት የትምህርት ሰአት ለቅድመ መደበኛ(ለ kg ) ትምህርት
ከ 2፡30 እስከ 9፡00 ሰአት ሲሆን.. የመጀመርያ ደረጃ (primery school) ከ 2፡30 እስከ 9፡30 ነው።
የ ሁለተኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት(secondery and priparatory school) ከ 2፡00 እስከ 9፡00 ሰአት ነው።

ስለሆነም የማጠናከርያ ትምህርቴን የምማረው ከ መደበኛው ሰአት በኋላ ማለትም ከ 9፡30 በኋላ ከ 10፡00 ሰአት እስከ 11፡00 ሰአት ነው። ይሁን እንጂ ማጠናከሪያ ትምህርቱ ለኔ ለውጥ የለውም ምክንያቱም አባቴ ብሩን በየወሩ ይክፈል እንጂ እኔና እየሩስ ሰአቱን የምናሳልፈው እንደለመድነው ለወንዶቹ ደብዳቤ እየፃፍን ቀጣይ የምናጠምደውን ወንድ እያቀድን እንዲሁም የማጠናከሪያ ሰአታችንን አከባቢያችንን እየዞርን እየተሽከረከርን ነው ምናሳልፈው።


ልክ 9፡30 እንደተለቀቅን ማጠናከሪያውን ሳንገባ ከትምህርት ቤት ወጥተን አዲስ ወደተገነባው እና በውበቱ ስለሚወራለት ልደታ ኮንዶሚኒየም ሄደን ሰአታችን እስኪደርስ በመናፈሻው ተናፍሰን በዛውም በመውጫችን ከድርን አይተን እንሄዳለን። ለከድር ያለኝ ስሜት ከእለት ወደየለት እየጨመረ መጥቷል። ይናፍቀኛል። አቋሙ ተክለ ሰውነቱ አይኑ የፀጉሩ እስታይል ድምፁ ባጠቃላይ ሁሉ ነገሩ ይማርከኛል። ካላየሁት ይጨንቀኛል።

እሱም ይሄንን ተረድቶ ነው መሰለኝ ከትምህርት ቤት ስወጣ አልያም ከመድረሳ ስወጣ ከቤታቸው ፊት ለፊት አስባልቱ ዳር ድቅን ብሎ ቁሟል፡ የቆመው በ ገመድ የተተበተበው ፖል ተደግፎ አይኑን አንዴ ወደላይ አንዴ ወደታች አንዴም ደሞ ወደጎን እያየ ይጠብቀኛል። ንግግሩ ቀልቤን ገዝቶታል።ባጭሩ ምን አለፋችሁ በሙሉ አፌ እመሰክራለሁ አፍቅሬዋለሁ ።አይኑን ሳላይ ማደር እያቃተኝ መጥቷል። እሱን ለማየት ስል የመድረሳ ትምህርቴን ማቀላጠፍ ጀምሬያለሁ። በስህተት እንኳን ታምሜም ቢሆን ከመሄድ አልቆጠብም። ሀይድ ላይም ብሆን ቁርአን ባልቀራም መድረሳ ሄጄ እቀመጣለው።



የአመቱ ማጠቃለያ ፈተና ወሰድን። ሰኔ ሰላሳም ደረሰ። ሰኔ ሰላሳ ካርድ የምንቀበልበት ነዉ የስድስተኛ ክፍል ውጤቴ አመርቂ አልነበረም ከነበረው ቀንሷል። ከ 45 ተማሪ በ 80 ነጥብ 15ተኛን ደረጃ ይዤ አጠናቅቄያለሁ። በዚህም ዉጤቴ አባቴ ደስተኛ አልነበረም።

በዚህም የተነሳ ሰፈሩ አስተዋፅኦ አድርጎባት ነው ጥሩ ነገር እየተማረች አይደለም በማለት ሰፈር እንድንቀይር አደረገ። በዚህም ምክንያት ሰባተኛ ወደተባለው መርካቶ አቅራቢያ ወዳለው ሰፈር ቤት ተከራየን።

  ክፍል አምስት ከ60👍 በኋላ ይቀጥላል...  ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like👍 ማድረግ አይርሱ

      ‌‌‌‌የፍቅር ቴሌግራም ቻናል 
          ይ 🀄️ላ🀄️ሉን!


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
      #ክፍል ☞ ሶስት 3


✍ ፀሀፊ ☞ #ዘቢባ_ሱልጣን




      
     ምነው ይሄ ቀን ባልተፈጠረ ወይም ጥዋት ሳልነሳ በዛው ሞቼ በነበረ ብዬ ተመኘሁ .አይኔ ማመን አልቻለም ... ሳይንስ አስተማሪያችን ስታስተምረን እንስቅባት የነበረው በሀፍረትም አንገታችንን እንደፋ የነበረው የሴት ልጅ ፀጋ የሆነው የወር አበባዬ(ሀይዴ) መምጣት በሌለበት ቦታ መጣ።

ፈተናዉን ሰርቼ ጨርሼ ልሰጥ ስነሳ ወንበሩ በደም ተጨማልቆ ልብሴ በደም ተዘፍዝፎ አገኘሁት።መልሼ ቁጭ አልኩ።የምትፈትነዉ መምህርም ልትኮርጂ ነበር የተነሳሽው ከክፍል ውጪ ለ ዳይሬክተሩ ነው ማስረክብሽ እያለች ደነፋችብኝ
......እኔ ግን አልወጣም አልኳት። አልወጣም ስላት ንዴትዋ ተባብሶ ነይ ውጪ እያለች ትጎትተኝ ጀመር።

እኔም እንባዬ ከአይኖቼ እየዘነበ ኩብልል ኩብልል ብሎ ከጉንጬ እየተንሸራተተ አገጬን ረግጦ ደረቴን እያራሰ አልወጣም ብዬ ወንበሩን በሁለት እጄ ጠፍሬ ያዝኩት። አልወጣም ያልኩት በደም የተነከረው ልብሴን ነውሬን እንዳያዩብኝ ብዬ እንጂ ንቄያት አልነበረም። ጉልበትዋ ከጉልበቴ ስላልተመጣጠነ አሽቀንጥራ አስወጣችኝ።

በአግራሞት ሲመለከቱኝ የነበሩት የኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ደሙን ባዩ ጊዜ የድንጋጤ ድምፅ ሁሉም አሰሙ ።የሂወቴ ፍፃሜ እንደሆነ ተሰማኝ አላህ የረገመኝም እንደሆንኩም ተሰማኝ።አለቀስኩ።

...ፈታኝዋም መምህር ለምን አልነሳም እንዳልኩ ሲገባት መልሳ ታባብለኝ ጀመር። ሴት ተማሪዎቹም አይዞሽ ሁላችንም እኮ ሊመጣብን የሚችል ነገር ነው ነገ እኛም እንዳንቺ መሆናችን አይቀርም ለትንሽ ጊዜ ነው አሉኝ። ሳይንስ አስተማሪዬ ተጠራች እና ትንሽ ምክር እንድትሰጠኝ አደረጉ። በነገሩ በጣም ደንግጫለሁ ሰዎቹ የሚያወሩትም ነገር አይሰማኝም።ብቻ እያለቀስኩ እንዳለ አስተማሪዬ መጣችና አስተምሬሽ የለ? እንዲህ እንዳትሆኚ እንዳትደነግጪ እኮነው ያስተማርኩሽ አንቺ የተመረጥሽ ሴት ነሽ አንቺ ካሁን በኋላ አድገሻል ልቦና ገዝተሻል ማለት ነው ፡ ይሄ ማለት ለወላጆችሽ የደረሰች ሴት ልጅ አላቸው ማለት ነው ልደነግጪ አይገባም እያለች አባበለችኝ።

ነገሩን መቀበል ያቃተኝ ገና የ 12 አመት ልጅ ስለነበርኩ እና በ 5 አመት የምትበልጠኝ ታላቅ እህቴ ይሄንን ነገር(ሀይድ) አለማየትዋም ጭምር ነበር። ብቻ እንደምንም ተረጋጋሁ


አመቱ አለቀ አሪፍ ውጤት አምጥቼ ከ 59 ተማሪ 10ኛ ወጥቼ ወደ 6ተኛ ክፍል ተዘዋወርኩ። 10 ደረጃን ይዤ ስላችሁ ንቃችሁ ወይም ስቃችሁብኝ ሊሆን ይችላል ግን በዛ ትምህርት ቤት 10ኛ መውጣት በጣም ትልቅ ውጤት ነው። 10 ደረጃን ይዤ ብወጣም አማካኝ ውጤቴ 91.6 ነበር። እዛ ትምህርት ቤት የተማረ ተማሪ መጨረሻኛ እንኳን ቢወጣ ከሌላ ትምህርት ቤት 1ኛ ከወጣው ተማሪ ጋር ቢወዳደር ያሸንፍል። የማርክ ልዩነት ሆኖ እንጂ መጨረሻኛ የሚያሶጣው እውቀቱ አይደለም። አንድም ተማሪ ሳያውቅ አይሄድም። 6ተኛ ክፍልን አሀዱ ብለን ጀመርን።ቁርአን መቅራትም ጀመርኩ።እኔና እየሩስ የለየልን እብዶች ሆነናል። ቀልባችን ያረፈበት ወይም ደሞ ቀልቡ እኛ ላይ ያረፈ ወንድ ስናገኝ አስቀድመን እኛ የፍቅር ደብዳቤ ከሽነን እንፅፋለን፡፡
ብዙ ጊዜ የምንፅፈዉ ደብዳቤም ----------ካየሁህ ቀን ጀምሮ ላንተ ያለኝ ስሜት ከእለት ወደየእለት እየጨመረ መጥቶዋል። ከልቤ አፍቅሬሀለው ያላንተ ወንድ አይታየኝም ፡ ስተኛም ስነሳም የማልመው ስምህን የምጠራዉ አንተን ነው አንተ ማለት ለኔ ከፈጣሪ የተሰጠህ ልዩ ስጦታ ነህ ፡ አንተ ማለት ለኔ እስትንፋሴ ተስፋዬ የመኖሬ ትርጉም ነህ። እባክህ እሺ ብለህ የፍቅር ጥያቄዬን ተቀብለህ ነብሴን አስደስታት ልቤን ከጭንቀት ገላግላት እኔ ያላንተ ሁሉም ነገር አስጠልቶኛል።ከፈጣሪ የተሰጠኝን ነገን የማይብህ ልዩ ስጦታዬ ነህ ከእናትም ከአባቴም አስበልጬ አፈቅርሀለው.......
ብለን እየፃፍን እንሰጣቸዋለን

.......ጥያቄያችን ተቀብለው እሺታን ሊያሰሙን ሲመጡ ከመናገራቸው በፊት አስቀድመን ውሸት መሆኑን እና ለጨዋታ መሆኑን እንነግራቸዋለን።በዚህ መልኩ በወንዶች ስሜት እየተጫወትን እንዝናናለን።

እኔም ግን አንደኛ ክፍል ስማር የማውቀው ከድር ላይ አይኔ አርፏል። ከድር ሰቃይ ተማሪ ሲሆን ቤቱ አሁን ከምማርበት ትምህርት ቤት አጠገብ ነው።የሚማረው እዛው የተዋወቅንበት ትምህርት ቤት ካራማራ ነው።

ሰሞኑ ከድር አዲስ ባህሪ አምጥቷል ያለወትሮው ከትምህርት ቤት እና ከመድረሳ ስወጣ እየጠበቀ ሰላምታ መስጠት ጀምሯል ለዛም ነው መሰለኝ አይኔ ያረፈበት።

Part 4⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል
ቤተሰብ react
ቀንሷል ታሪኩን ደስ ካላላቹ comment ላይ አሳውቁን
ከ60👍 በኋላ ይለቀቃል ቶሎ ቶሎ ተጫኑት እንዲለቀቅ አንብባቹ ከጨረሳቹ በኋላ👍


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ ታሪክ〰〰〰💧
 
የታሪኩ ርዕስ
💁‍♂ #SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ ሁለት 2⃣

✍ ፀሀፊ ☞
#ዘቢባ_ሱልጣን


አንደኛ ክፍልን ካራማራ የተባለች እዛው ሰፈራችን ልደታ አካባቢ ያለች ትምህርት ቤት ገባሁ።
ከማይረሱ የትምህርት ቤት ትዝታዎቼ መካከል ዋነኛው ነው። የፍቅርን ትርጉም ሰው ማለት ምን እንደሆነ የተማርኩት እዛ ነው። ደሀ ሆነን እንደ ድህነታችን ሳይቸግረን ልብሳችን ቆሽሾ እንደቆሸሸ ሳይሰማን እከሌ ከኔ ይበልጣል እከሌ ከኔ ያንሳል ሳንል እንደ አህያ መሬት ላይ እየተንከባለልን እንደ ዶሮ መሬት እየጫርን አፈር እያቦካን ጭቃ እየጋገርን ውሀን ሻይ እያልን ቆሻሻ እየበላን አፈር እየላስን አልፈናል።

1 ብር ለወር ወጪያችን እየተጠቀምን በአምስት ሳንቲም እንደልብ አውላን 10 ሳንቲም እስከ ጓደኞቻችን ፈታ ታደርገናለች። በ አምስት ሳንቲም በረዶ(ጀላቲ) ገዝተናል ፤ በአምስት ሳንቲም አንድ እፍኝ ጋባ ገዝተን ተመግበናል፤ በአምስት ሳንቲም አንድ ፍሬ አካት ገዝተን ስንግጥ ውለናል፤በአምስት ሳንቲም 2 ናና ከረሜላ ገዝተን ከ ጓደኛችን ጋር ተካፍለን በልተናል። ሳንቲምም ከሌለን ሻጮቹን በአሳዛኝ የልጅነት ፊታችን እባክህ አንድ ፍሬ ስጠኝ እያልን እየለመንን ተመግበናል። በየመንደሩም ዞረን ካዝሚር እና አቦካዶ ያለበት ቤት አንኳክተን ለምነል በልተናል። ኩረጃ ምን እንደሆነ ሳናውቅ ትምርትን አጣጥመን በራሳችን ሰርተን አልፈናል።

እርስ በርሳችንም ፍቅር አለን ለብቻ መብላት እና መጠጣት አናውቅም ።አስተማሪዎቹም ፉንጋ እንሁን መልከ መልካም ሳያማርጡ ግንባር ግንባራችንን ጉንጭ ጉንጫችንን ይስሙናል። ሁሉም አስተማሪ ልጆቼ እንጂ ተማሪዎቼ አይሉንም ።እንዲህ እንዲህ እያልን አመቱ አለቀና ከ 50 ተማሪ አስራ አንደኛ በ 70 ነጥብ አምጥቼ ወደ ሁለተኛ ክፍል ተዘዋወርኩ።


ሁለተኛ ክፍል የገባሁት የግል ትምህርት ቤት ነው።አባቴ ለትምህርት ያለው ፍቅር እጅግ በጣም ልዩ ነው። እሱ እናት እና አባቱ ስላላስተማሩት እኛን እንደሱ እንዳንሆን ይጥራል ለትምህርትም ያለውን ሁሉ ያወጣል።ለዛም ነው ያለ አቅሙ የባለስልጣን ልጆች የሚማሩበትን የሀብታም ልጆች የሚቀማጠሉበትን ትምህርት ቤት ከለት ጉርስ ወጪው ቀንሶ ያስተማረኝ።ሰፈርም ቀይረናል ወደ ተወዳጁ ሰፈር አብነት ገብተናል። መቼስ የዱንያ ነገር የኪራይ ቤት ኑሮ ነውና በቤት ኪራይ ምክንያት
እንከራተታለን።የተወለድኩት ኮልፌ ያደኩት ልደታ አሁን ያለሁት አብነት የነገውን ደሞ አላህ ያውቃል።

አዲሱ ትምህርት ቤቴ ያሉት ተማሪዎች አለባበሳቸው እና ፀባያቸው እንዲሁም ንግግራቸው ሁሉ ነገራቸው ይለያል። የቄስ ትምህርት ቤት ተምሮ ያደገን ልጅ ወደግል ትምህርት ቤት ማምራት ይከብዳል ብቻ የአላህ ውሳኔ ሆኖ ገብቻለው።

ከሀብታም ልጆች ጋር ለመልመድ እጅግ በጣም ብቸገርም ጋደኞች ለማፍራት ብቸገርም ቀስ በቀስ እየለመድኩት መጥቻለው።የምማረው የፕሮቴስታንት ትምህርት ቤት እንደመሆኑ መጠን ሙስሊም ተማሪ እኔ ብቻ ነኝ ።ለዚህም ነበር ጓደኛ ለማፍራት ብዙ የተቸገርኩት።እያደር እያደር ከክፍላችን ተማሪዎች መካከል አንድዋ የሆነችው እየሩስን ተዋወኩ።


እዩ በጣም ልዩ የሆነች ልጅ ናት ከነ ማንነቴ ተቀብላኛለች። ሌሎች ተማሪዎች በሙስሊምነቴ ብዙም ባይቀርቡኝም እዩ ግን ልትርቀኝ አልቻለችም። አንድ ሁለት እያልን አመታት አለፈ 5ተኛ ክፍል ደረስኩ። ሁሉም የክፍላችን ልጆች እንደ ብርቅዬ ነው የሚያዩኝ። ዘቢ እንጂ ዘቢባ ብሎ ሚጠራኝ የለም።ወንድ ሴት ብሎ ልዩነት የለም ወንዱ ከሴት ጋር ተቃቅፎ ይጫወታል ግን ፆታዊ ልዩነት የለም ፍቅርም የለም።ቢሆንም ልዩነታችን የሰፋ ነው።

እኔ እዛ ትምህርት ቤት ከገባሁ ጀምሮ ዩኒፎርም የተገዛልኝ አንድ ጊዜ ነው እነሱ ሰኞ ማክሰኞ እና እሮብ ሀሙስ እና ጁመአ የሚለብሱት ዩኒፎርም የተለያየ ነው። እኔ ጫማ የማደርገው ከአመት አመት አንድ ሸራ እያጠብኩ ነው።ጫማውም እየጠበበኝ በመምጣቱ ምክንያት የእግሬ ጥፍሮች እና ጣቶች ታጥፈው አጎርብበዋል።እናቱ ቀርታበት ተደፍቶ እንደሚያለቅስ ህፃን እጥፍጥፍ ብለዋል። ጫማው እራሱ እንዲ እየዘለልኩበት እየተራገጥኩበት ሲያሻኝ ሱዚ ሲያሻኝ ደሞ እግር ኳስ ከወንዶች ጋር እየተራገጥኩበት አለመቀደዱ ይገርመኛል። አንዳንዴም ምነው በተቀደደ እና በስበቡ አዲስ በተገዛልኝ ብዬ ዱአ አደርጋለው።
ኑሮ ከባድ ነው አባቴን ግዛልኝ ከነሱ እኩል አድርገኝ ማለት አልችልም ብልም አይደረግልኝም።

በእርግጥ አሁን ላይ ጥሩ ስራ አለው ቸግሮት አያውቅም።እኔን
የሚቸግረኝ የሱ ድጋፍ በማጣቴ እንጂ በእርሱ ብር ማጣት ምክንያት አይደለም።አባቴ እንድማር እንጂ የነሱ አለባበስ እና ኑሮ እንድለምድ አይፈልግም እኔ ግን ሰፊውን ጊዜዬ ማሳልፈው ከነሱጋር ስለሆነ ሳልፈልግ ለምጄዋለው። ጫማቸው እና የፀጉር ጌጣቸው ያምረኛል ይማርከኛል ያስቀናኛል። እንዲህ እንዲህ እያለ የአምስተኛ ክፍል የመጀመርያ መንፈቅ አመት ማጠቃለያ ፈተና ምንፈተንበት ጊዜ ደረሰ።


የመጀመርያው ቀን እለተ ሰኞ አማርኛ እና እንግሊዝኛ ተፈትነን አለፍን ሁለተኛው ቀን እለተ እሮብ ሂሳብ እና ስነዜጋ እየተፈተንን እንዳለ ፈተናዬን ሰጥቼ ልወጣ ስል አንዳች ነገር ተከሰተ። ምድር ተከፍላ ብትዉጠኝ ደስታዬ ነበር። ምነው ይሄ ቀን ባልተፈጠረ ወይም ጥዋት ሳልነሳ በዛው ሞቼ በነበረ ብዬ ተመኘሁ ..

Part 3⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል
ከ60👍 በኋላ ይለቀቃል ቶሎ ቶሎ ተጫኑት እንዲለቀቅ አንብባቹ ከጨረሳቹ በኋላ👍


💧〰〰〰አስተማሪ እዉነተኛ  ታሪክ〰〰〰🧬
 
የታሪኩ ርዕስ
👩‍🎓
#SCHOOL_LIFE(የት/ቤት ሒወት )
     
#ክፍል ☞ አንድ 1️⃣

#✍_ፀሀፊ_☞_#ዘቢባ_ሱልጣን


ሁሉም ሰው ከትልቅ እስከ ትንሹ የልጅነት ጊዜውን የማይናፍቅ የለም እኔም ምንም እንኳን የዚን ያክል የመቦረቂያ እና የመጫወቻ ጊዜ ባይኖረኝም ትንሽም ብትሆን ያሳለፍኳት ነገር ትናፍቀኛለች ከአይምሮዬም አይጠፋም። እኔ የዘጠናዎቹ ትውልድ ነኝ። የዘጠናዎቹ ትውልድ በ facebook ግሩፕ ላይ ካያቹ በጣም የሚወራለት የዋህ እና ምንም የማያውቅ ትውልድ ነው።ይህ ግሩፕ በface book ብቻ ሳይሆን በ telegram ብዙ ተከታዮችን ያፈራ ነው።

ሲቀለድም የዘጠናው ትውልድ ሲጣላ ሮጦ ወደ ቤቱ ገብቶ አንበሳ ጫማውን አስርጎ ነበር የሚወጣው ያሁኑ ትውልድ ግን ሮጦ ወደ ቤቱ ገብቶ ስለት ይዞ ይወጣል ይባላል። የገጠሩን ባላውቅም እዚህ አዲስ አበባ በኛ ጊዜ ትምህርት የሚጀመረው በ ቄስ ትምህርት ቤት ነው። ኬጂ አናውቅ ነርሰሪ አናውቅ ሙስሊሙም ክርስትያኑም የቄስ ትምህርት ቤት ይገባል።

እኔም በ 6 አመቴ የቄስ ትምህርት ቤት አሀዱ ብዬ ተመዘገብኩ።እኛን ያስተማሩን የኔታ ክብር ምስጋና ይገባቸውና አንድም እውቀት አልሰሰቱብንም።ስንረብሽ ስናጠፋ እመሬት ተደፉ እያሉ ሲያሻቸውም ብላክቦርዱን ሳሙ እያሉ ቂጣችንን እየገረፉን አንድም ነገር ሳይገባን እንዳናልፍ አድርገው አስተምረውናል።ሲያስነጥሱ የኔታን ይማርልን እያልን ክፍል ስንገባም በአንድ ሰፊ የተሰነጠቀ ጣውላ(መቃን) ላይ ከ10_15 ልጆች አብረን እየተቀመጥን ጠበበን ቆረቆረን ሳንል የኔታም ሲገቡ እንደምን አደራቹ
ወይም እንደምን ዋላቹ ሲሉን ሙስሊም ክርስትያኑ በአንድ ላይ ደህና እግዚአብሄር ይመስገን መምህር!!!! እያልን አሳልፈናል።

ወላሂ ያን ጊዜ በጣም ነው የሚናፍቀኝ ዘረኝነት የለ መናናቅ የለ መኖር ብቻ! ለነገሩ የሚፍጀው ያሁኑ ትውልድ ነው እንጂ በኛ ዘመን አንድ አንባሻ የክፍል ተማሪዎችን በሙሉ ያዳርስ ነበር።ብቻዬን ልብላ የለም።መቼም የማይረሳኝ ግን ያንዳችንን ምሳ
በ እረፍት ሰአት ያንዳችንን ደግሞ ምሳ ሰአት የምንበላው ነገር ነው። ኢሊፖፕ ከረሜላ ገዝተን እስከ ማስቲካው ድረስ አንዳችን ጠብተን ማስቲካውን ደግሞ ለሌላችንን የምንካፈለው ነገርም አይረሳም።

ለነገሩ ይሄን ባህሪ ያላበሰን ዘመናችን ብቻ ሳይሆን መዲናችን አዲስ አበባም ጭምር ነው። ብዙዎች አዲስ አበባ መወለድ በራሱ first degree ነው ይላሉ።እውነት ነው ብል ማጋነን አይሆንብኝም። አዲስ አበባ ጥብቅብቅ ጭንቅንቅ ያለች የተጣበበች ብትሆንም ህዝቦቿ በጭንቅንቁ ውስጥ ፍቅርን ለግሷቸዋል። ሀገሪቷ ሰፊ ከመሆንዋ የተነሳ ነዋሪዎችዋም ከጥግ እስከጥጉ የሚያውቋት አይመስለኝም። ቀና ቢሉ የሚታየው ሰማይ ሳይሆን ሰማይ ጠቀስ ህንፃ ነው።በፎቅ ተጥለቅልቃለች። ቂያማ ሲደርስ ፎቅ ይበዛል እርጉዝ ይበዛል ዚና ይስፍፍል የተባለው እውነት መሆኑም የሚረጋገጠው እዚቹ ከተማ ላይ ነው።

አዲስ አበባ የሁሉም ከተማ ዘር ከዘር የማይለይ ኦሮሞ ከጉራጌ አማራ ከትግራይ ሶማሌ ከኦሮሞ አማራን ከስልጤ ሀመርን ከጉራጌ ሀድያን ከኦሮሞ ወላይታን ከስልጤ አደባለቃ ድራ ሞሽራ የያዘች ብቸኛ ከተማ አዲስ አበባ ናት። ለስራ እና ለጉብኝት የሚመጡ ቻይኖች እና የተለያዩ ሀገር ዜጎች መመልከት የተለመደ ነው። ሰውም ሌላ ከተማ ስራ የለም የተባለ ይመስል የሚጎርፈው አዲስ አበባ ነው። የገጠር ልጅ አዲስ አበባ ሲመጣ የአሜሪካ ዲቪ እንደደረሰው የሚቆጥረው እና የሚደሰተውም ለዚህ ይመስለኛል። ለነገ መጨነቅ አያውቅም መልበስ መጠጣት መብላት የየለት ተግባራችን ነው። ዝንጥ ብላ ስትዝናና አይተህ ወደሀት ተከትለሀት ቤትዋ ብትገባ ግን የፈራረሰ ሊወድቅ አንድ ሀሙስ የቀረው ቤት ነው የሚሆነው።

አዲስ አበባ አንዱ ቤት አንዱ ላይ ተጭኖ ሌላኛው ደግሞ በአንዱ ቤት ተንጠልጥሎ ነው የሚሰራው።ጎረቤት ቡና ለመጥራት በር ከፍቶ መውጣት አይጠበቅበትም እዛችው የቤቱ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ እከሌ!! ብሎ ቢጣራ ድምፁ ከጎረቤቱ ጆሮ ውስጥ ገብቶ ድርግም ይላል።ግን እኔን የማይገባኝ ነገር ቻይና ፈረንጅ ነው እንዴ? ልጅነቴ ይሁን ጅልነቴ ባላውቅም ፈረንጅ አይመስሉኝም።መልሱን ለናንተ ትቼዋለው።

አዲስ አበባን ለመግለፅ ቃላት ያጥረኛል በተለይ ግን የአብነት እና የአፍሪካ ትልቁ የገበያ ማእከል የሆነው የመርካቶ ልጅ መሆን ግን ይበልጥ መታደል ነው። የአብነት ልጅ ሲናደድ በድንጋይ ይበረቅሳል የተክለሀይማኖት ልጅ ሲናደድ 2 ተቆራጭ ኬክ አዞ ይበላል የመርካቶ ልጅ ሲናደድ ጉሮሮ ይዘጋል የቦሌ ልጅ ሲናደድ ያለቅሳል ተብሎ ይተረታል። አዲስ አበባ ላይ ሙዝ አንድ በልቶ መድገም እና ካፌ ቁጭ ብለህ ለብቻህ ሁለት ኬክ አዘህ መብላት ነውር ነው። ተክለሀይማኖት መርካቶ እና አብነት እንዲሁም አቶቢስ ተራ የአራዶች ሰፈር ተብሎ ሲጠራ ቦሌ እና መሰሎቹ የሀብታም ልጆች ሰፈር ነው። በዚህ መልኩ ከአብነት ትንሽ ዝቅ ብሎ ልደታ ሚባለው ሰፈር አድጌ ከቄስ ትምህርት ቤት ወደ አንደኛ ክፍል ገባሁ.......


Part  2⃣
ይ.........ቀ.......
........ጥ.......ላ........ል ከ60👍 በኋላ ይለቀቃል ቶሎ ቶሎ ተጫኑት እንዲለቀቅ አንብባቹ ከጨረሳቹ በኋላ
👍


በቅርቡ በአንድ ምርጥ ታሪክ እንገናኛለን ።🔤

ታሪኩ እውነተኛ ታሪክ ነው ስለዚህ አስተውላቹ አንብቡ እንዲሁም ሼር እና like ያበረታታናል።
🥰

ከ60 👍 በኋላ ይለቀቃል አዲሱ ታሪክ


​​#ሞርያ
:
#ክፍል_ስድስት  (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
:  
#እውነተኛ_የፍቅር_ታሪክ

…አላስቀምጠን ስትል ነው የመጣነው በቃ አትጥፊ ብለውኝሄዱ ስሄዱ ተመስገን አልኩ ሁሎቹም እንደሷ መሰሉኝ በዚህ መሃል በሁለተኛው ቀን ሚኪ ደወለ ገና ሄሎ ከማለቴ አንቺ  ምን ሁነሽ ነው የጠፋሽ ብሎ ጮኸብኝ እኔም ትንሽ ስራ ይዤ ነው ብዬ ቀበጣርኩበት እንዴት አድርጌ እውነቱን እንደ ምነግረው ግራ ገብቶኛል ይሄን ነገር ደግሞ ከሰው ከሚሰማ
ከእኔ ቢሰማ ይሻለዋል ለአቡሽ ያለውን ነገርኩት እሱም እንደኔ እኔው መናገር እንዳለብኝ ነገረኝ እንደ ምንም ብዬ ልነግረው ወስኜ እንገናኝ አልኩት በሰአቱ በጣም ጨንቆኛል ግን እሱ ከእኔ እስኪ ሰማው ነው ከዛን በኋላ ግድ የለኝም ሚኪ ጋር እንደ ተገናኘን ልነግረው ብዬ አቅሙን አጣሁ
በጣም ከበደኝ የሆነ የደበቅሽኝ ነገር አለ ልበል ቅድም  ጀምረሽ እኮ ሁኔታሽ እንደው ብሎ ሳቀበኝ ሚኪ ምን መሰለህ አንድ ትልቅ በደል ሰርቼብሃለው ብዬ ለመናገር እንኳ ከብዶኝ አንገቴን ደፋሁ እህ አፎሚያ ምን ሁነሻል ምን ያስቀየምሽኝ ነገር አለና ነው እንደዚህ ምትይኝ አለ እኔም እንደ ምንም ብዬ ከመጀመርያ እስከ መጨረሻ ነገርኩት ግን ሚገርመው ምንም አልደነቀውም ምንም አይነት ብስጭት አላየሁበትም ስለ ነገርሽኝ ከምንም በላይ ደስ ብሎኛል አለ እህ አልገባኝ  አልኩት ሁሉንም ነገር እህትሽ ሜሊ ነግራኛለች አንቺም ደግሞ ያደረግሽው ነገር ጸጽቶሽ ይቅርታ መጠየቅሽ ታላቅነትሽ ነው አለኝ ተነስቼ ነበር ያቀፍኩት በጣም ደስ አለኝ ቅልል አለኝ ይቅርታ ጠይቆ ምህረት እንደ ማግኘት ሚያስደስት ነገር ምን  አለ አልኩ በልቤ ደስታዬ ወደር አጣ በዚ መሃል ግን አንድ ያልጠበኩት ነገር መጣ ልክ ከሚኪ ጋር ተለያይተን ወደ ቤት እየተመለስኩ እያለ ከታች አቡሽ በኃላው ሻንጣ ነገር ይዞ ከእህቱ ጋር ወደ መሰመሩ እየወጡ ነው ደነገጥኩ ሰላም ብያቸው ወዴት ነው አልኩ አቡሽ ወደ ነበርኩበት ልመለስ ነዋ አለኝ ፈገግ እያለ የእውነት ለመናገር ልቤ ተነጥሎኝ የሄደ ያህል ተሰማኝ ደነገጥኩ አሁን ላይ አቡሽ ጋር ያለኝ ቅርበት ከምንም በላይ ነው አይኑን እንኳ ሳላይ ማደር አልችልም እንባዬ ቀደመኝ አንቺ ምን ሆንሽ ብሎ እንባዬን ጠረገለኝ እህቱ ይሄውልሽ አሁን እንደ ዱሮው አይቆይም እኔን ለማድረስ ነው ሚሄድ አለችኝ ብቻ ያለችኝን በቅጡ አልሰማኋትም ተሰናብተውኝ ሄዱ ሰፈር ውስጥ ብቻዬን የቀረው ያህል ተሰማኝ ጓደኞቼ ጋር ተለያይቼ አቡሽም ተለይቶኝ በጣም ተሰማኝ በአንድ በኩል ከጓደኞቼ መለየቴን ሳስብ ደስታን
  ይሰጠኛል ምክንቱም ዛሬ ከአስመሳይ ህይወት ወጥቻለሁ ሰላም ያለው እንቅልፍ እተኛለሁ እናታልል እናጭበርብር ሙድ እንያዝ ቺት እናድርግ ሚለኝ ሰው የለም አቡሽ ጋር ሁሌም እንደዋወላለን ቻት ላይ ገብቼ እሱ ከሌለ መልህክት አስቀምጬ እወጣለሁ እንደ በፊቱ
ማንም ጋር ስቀልድ ግዜዬን አላጠፋም እህቴ ከሚኪ ጋር ጓደኝነታቸውን ቀጠሉ በዚህ እንዳለሁ አንድ ቀን ድንገት እሁድ ጥዋት ላይ ከእቅልፌ ስነቃ ስገላበጥ ወደ አንድ ሰው የተጠጋው መሰለኝ ከሰመመን ውስጥ እንደ ምንም ተገላብጬም ቢሆን በእጆቼ ዳሰስኩ ደነገጥኩ ለገፋው ብል አልገፋኝ አለ ቀስ ብዬ ቀና አልኩ አንድ ሰው ተሸፋፍኖ ተኝቷል ከድነጋጤ የተነሳ መተፈስ ራሱ ተሳነኝ የሌሊት ልብሴን እንደ ለበስኩ ነው ምን
እንደ ተፈጠረ አላውቅም ቀስ ብዬ ከአልጋው ልወርድ ስል ወደኔ ተጠጋ በቃ ልጮህ ትንሽ ሲቀረኝ እጆቹን ጫፋቸውን ወጣ አደረገ አቡሽ ነው በቃ የዛን ቀን ደስታዬ ልዩ ነበር እኔም የራሴን አዳም አገኘሁ ሁሌም የራሳችን ባልሆነ ነገር ላይ
እንታገላለን ግድ የኛ ካልሆነ ብለን ከፈጣሪ ጋር እንጣላለን በየቀኑ ብዙ ሰው ጋር እንገናኛለን በየቀኑ ብዙ ነገር እናያለን እንሰማለን ማስመሰል እና ሰውን ማታለል በጣም ቀላል ነገር  ነው ግን ከህሊና ቅጣት ማንም አይድንም ሁሌም ፈጣሪ ለኛ ያለውን በዚገይም አያስቀርብንም።

       
🔤💞ተፈፀመ💞🔤

በታሪኩ እንደተማራቹ ተስፋ አደርጋለው እውነተኛ ታሪክ እንደመሆኑ መጠን። በሌላ ታሪክ እስከምንገናኝ ሰላም ያገናኘን🥰

እወዳችዋለው
😍😍🥰

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.