ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ኢትኮፍ ያስገነባውን የቡና ማዕከል አስመረቀ

ኢትኮፍ ያስገነባውን ባለ አምስት ወለል የቡና ማዕከል በትናንት  እለት የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የመንግስት አካላትና እንግዶች በተገኙበት የምርቃት ስነስርእት ተካሂዷል::

ይህ የቡና ማዕከል በውስጡ የመዝናኛ ማዕከልን የያዘ ሲሆን የቡና ቅምሻ ስርዓትን፣ የባህላዊ ቡና አቅርቦትን፣ ሰርቶ ማሳያ፣ የቡና ትርኢት፣ የአርት ጋለሪና ቢዝነስ ሴንተርን ማካተቱም ተገልጿል::

ኢትኮፍ ለመጠጣት የተዘጋጁ የቡና ምርቶችን በራሱ ፋብሪካ ውስጥ እያመረተ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን እነዚህን ምርቶችንም ሃገር ውስጥ ለሚገኘው የውጪ ማህበረሰብ፣ ለኤምባሲዎች፣ ለዲፕሎማቶች፣ ለተለያዩ አየር መንገዶች፣ ደረጃቸውን ለጠበቁ ባለ ኮከብ ሆቴሎች ያቀርባል፡፡

በተጨማሪም ከሃገር ውጪም ኤክስፖርት የሚያደርግ ሲሆን ለተለያዩ የግል ተቋማት፣ ለመንግስት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች፣ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች እስከ ቡና ማፍያ ማሽን እንደሚያቀርብ ተነግሯል፡፡

ኢትኮፍ ቡናን ከተለመደው በጥሬና ቆልቶ ወደውጪ በመላክ በርካሽ የሚሸጥበትን ልማድ በመቀየር አዲስ አሰራርን ይዞ የመጣና ለሃገራችን በተለይም ለከተማችን ቱሪዝም ዕድገት የበኩሉን ድርሻ የሚያበረክት ነው ተብሏል::


በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል


በሱዳን ነጭ ናይል ግዛት የኮሌራ ተጠቂዎች ቁጥር ከ400 በላይ መድረሱን ተከትሎ ትምህርት ቤቶች ተዘጉ

ከፍተኛ የሆነውን የኮሌራ ወረርሽኝ ለመግታት በኮስቲና ዋይት ናይል ግዛት ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸው የተገለፀ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ400 በላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች እና 13 ሰዎች መሞታቸውን የክልሉ ባለስልጣናት ሪፖርት አድርገዋል። የኮሌራ በሽታ መስፋፋት በደቡባዊ ሱዳን በምትገኘው የነጭ ናይል ግዛት ነዋሪዎች ላይ ስጋት ደቅኗል። አክቲቪስቶች ሰዎች በበሽተኞች የተጨናነቀውን ኮስቲ ሆስፒታልን እንዲደግፉ አስቸኳይ ጥሪ አቅርበዋል።

የዋይት ናይል ግዛት የትምህርት ሚኒስቴር ተጠባባቂ ሚኒስትር አል-ታይብ አሊ ኢሳ በሰጡት መግለጫ “በኮስቲ የሚገኙትን ሁሉንም ትምህርት ቤቶች እና መዋለ ህፃናት ለአንድ ሳምንት ለመዝጋት ተወስኗል” ብለዋል። ውሳኔው ባለፉት ሰአታት ውስጥ “አጣዳፊ ተቅማጥ” መከሰቱን ተከትሎ የነጭ ናይል ጤ ሚኒስቴር ግምገማ የህብረተሰቡን እና የተማሪዎችን ደህንነት ስጋት ላይ ይጥላል የሚል ነው ሲሉ ተደምጠዋል።የትምህርት ሚኒስቴር በኮስቲ እና በሌሎች የክልሉ አካባቢዎች ያለውን ሁኔታ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት ትምህርት ቤቶችን መዘጋት ወይም  መከፈትን ለመወሰን ይሰራል ተብሏል።

የነጭ ናይል ግዛት የጤና ሚኒስትር አል ዘይን አደም ሳድ የኮሌራ ተጠቂዎች ቁጥር ከ400 በላይ መድረሱንና 13 ሰዎች መሞታቸውን ገልጸዋል። ሚኒስቴሩ ከአርብ ጀምሮ በአስተማማኝ የአፍ ክትባት ህክምና ለመስጠት እና የኮሌራ ምላሽ ዘመቻዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉንም ቅድመ ጥንቃቄዎች መደረጋቸውን ተናግረዋል። ሚበኮሌራ ምክንያት በኮስቲ ሆስፒታል በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች መሞታቸውን የሚያሳየው ሪፖርትን ያስተባበሉ ሲሆን የሟቾች ቁጥርም 13 ብቻ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በሱዳን ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች እስከ 80 በመቶ የሚደርሱ የጤና ተቋማት አገልግሎት መስጠት ያቆሙ ሲሆን 45 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ደህንነቱ በተጠበቀ አካባቢ ውስጥ ሆነውም አገልግሎት መስጠት ሳይችሉ ቀርተዋል። ከፍተኛ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጦት ፣የጦርነት ሰለባዎች እና መከላከል የሚቻሉ በሽታዎች ስርጭት እየተባባሰ ባለበት በተዳከመ ስርዓት ውስጥ የኮሌራ ስርጭት ለጤና ቀውሱ ተጨማሪ ፈተና መሆኑን ኮሚቴው አፅንዖት ሰጥቷል።ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በተለይም የዓለም ጤና ድርጅት፣ ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን እና ቀይ መስቀል በአስቸኳይ ጣልቃ በመግባት ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እና ወደ ሌሎች ክልሎች እንዳይዛመት ለመከላከል የጤና ሚኒስቴር እና የህብረተሰቡን ጥረት እንዲደግፉ ጠይቀዋል።

በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል




የሆንግ ኮንግ ዋና ተቃዋሚ ፓርቲ ራሱን ሊያከስም ማቀዱን አስታወቀ

የፓርቲው ሊቀመንበር ሎ ኪንሃይ በሰጡት መግለጫ የሆንግ ኮንግ ዲሞክራቲክ ፓርቲ መሪዎች በአንድ ወቅት የከተማዋ ትልቁ ተቃዋሚ የነበረውን ቡድን ይበተን ወይስ ይቆይ በሚለው ጉዳይ ላይ ድምፅ ለመስጠት እንደሚሰበሰቡ ገልፆል።

2019 የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞና ቻይና በከተማው ውስጥ ያለውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር የወሰደችውን እርምጃ ተከትሎ ከተመሰረተ 31 ዓመታት ያስቆጠረው ፓርቲው አሁን ላይ በህይወት ለመቆየት እየታገለ ነው። የቤጂንግ እና የሆንግ ኮንግ መንግስት ግን እንዲህ አይነት እርምጃዎች ለብሄራዊ ደህንነት አስፈላጊ ናቸው ሲሉ ይከራከራሉ።

በ2021 በሆንግ ኮንግ ውስጥ ለኮሚኒስት አገዛዝ ታማኝ የሆኑ ሰዎች እንደ ህግ አውጭ ወይም የአከባቢ ምክር ቤት አባል ሆነው ሊያገለግሉ እንደሚችሉ የሚያረጋግጥ “የአርበኞች ህግ” እየተባለ የሚጠራ ህግ ወጥቷል። ይህ ህግ ደግሞ አንድ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በምርጫ እንዳይሳተፍ በትክክል ይከለክላል።

ሊቀመንበሩ ከፓርቲው ስብሰባ በኋላ ማምሻውን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሚስተር ሎ የፓርቲው አመራሮች “በወቅቱ የፖለቲካ ሁኔታ” ላይ ተመስርተው ፓርቲውን ለማክሰም ወይም ለማቆየት እንዲወስኑ ጥሪ አቅርበዋል። "በሆንግ ኮንግ ዲሞክራሲን ማዳበር ሁሌም አስቸጋሪ ነው፣በተለይም ባለፉት ጥቂት አመታት በጣም ከባድ ሆኗል"ሲሉ ሚስተር ሎ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። የፓርቲው አመራሮች ውሳኔ የተደረገው በፖለቲካ ጫና ስለመሆኑ ሲጠየቁ ግን አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በአሁኑ ሰዓት ፓርቲውን የመዝጋት ሂደት የሚከታተል የስራ ቡድን ተቋቁሟል። በመጪው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ከሚሳተፉት አባላቱ ቢያንስ 75 በመቶ የሚሆኑት እርምጃው ከመጠናቀቁ በፊት ማጽደቅ አለባቸውም ተብሏል።

በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል


ከመንግስት ጋር እርቅ ፈጽመዉ የተመለሱ የቀድሞ የተገንጣዩ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ ኃላፊነት ተሰጣቸዉ

የመንግሥትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ኅብረተሰቡ ለተቀላቀሉ የቀድሞ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ኃላፊነት ተሰጥቷል።

በዚህም መሠረት፡-

1. አቶ ያደሳ ነጋሣ - በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የደኅንነት አማካሪ፣

2. አቶ ኦሮሚያ ረቡማ ተሰማ - የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ምክትል ኃላፊ፣

3. አቶ ቶሌራ ረጋሣ - የኦሮሚያ አስተዳደር እና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

#ዳጉ_ጆርናል


የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ድልድል ይፋ ሆኗል ፦

ፒኤስቪ ከ አርሰናል
ሪያል ማድሪድ ከ አትሌቲኮ ማድሪድ
ቤንፊካ ከ ባርሴሎና
ባየር ሙኒክ ከ ባየር ሊቨርኩሰን
ፌይኖርድ ከ ኢንተር
ክለብ ብሩጅ ከ አስቶን ቪላ
ዶርቱመንድ ከ ሊል
ፒኤስጂ ከ ሊቨርፑል

- በቀጥታ 8ቱን የተቀላቀሉ ክለቦች የመጀመሪያውን ዙር ከሜዳቸው ውጪ የመልሱን በሜዳቸው የሚያደርጉ ይሆናል።

ሩብ ፍፃሜ ፦

የፒኤስቪ እና አርሰናል ከ ሪያል ማድሪድ እና አትሌቲኮ

የፒኤስጂ እና ሊቨርፑል ከ ክለብ ብሩጅ እና አስቶን ቪላ

የቤንፊካ እና ባርሴሎና ከ ዶርቱመንድ እና ሊል

የባየርን እና የባየር ሊቨርኩሰን ከ ፌይኖርድ እና ኢንተር የሚገጥሙ ይሆናል።

#UCLDRAW
#ዳጉ_ጆርናል


በአዲስ አበባ ከተማ አምስት ሊትር ዘይት ከ1400 እስከ 1600 ብር እየተሸጠ ይገኛል

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ በከፍተኛ መጠን እየጨመረ እንደሚገኝ ብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ባደረገው የገበያ ቅኝት ለማወቅ ችሏል።

በተደገው የገበያ ቅኝት ከዚህ ቀደም 1200 እስከ 1300 ብር ይሸጥ የነበረው አምስት ሊትር የምግብ ዘይት አሁን ላይ ከ200 መቶ እስከ 300 ብር ጭማሪ አሳይቷል።

እንዲሁም መሰረታዊ የምግብ ፍጆታ የሚባሉት ምስር ከ200 ወደ 270 ፣ እንቁላል ከ11 ብር ወደ 18 ብር ጭማሪ የታየበት ሲሆን ሌሎች ምርቶች ላይ በአንድ ሳምንት ውስጥ የተጋነነ የዋጋ ጭማሬ መኖሩን በቅኝታችን አረጋግጠናል።

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል


የሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የገጠመው ችግር  ለመቅረፍ የገቢ ማሰባሰብ ስራ ሊጀመር ነው

👉 አካባቢው በረሃማ በመሆኑ ለከፍተኛ ድርቅ የሚጋለጥ ነው

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በማዕከላዊ ጎንደር ሃገር ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት ለሚገኘው  የሙት አንሣ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንደነት ገዳም የገቢ ማሰባሰቢ መርሃ ግብር ሊከናወን ነው።ለገዳሙ  እስካሁን 11 ሚሊዮን  ብር  የገንዘብ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን ለእንቅስቃሴ አስቸጋሪ የነበረውን ቦታ የማስተካከል  እንዲሁም ሌሎች ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ እና ወደ ገዳሙ የሚደርስ 8 ኪ.ሜ የጠጠር  መንገድ ተከናውኗል ። 

እነዚህ አብያተ-ክርስቲያናት እና ገዳማት መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን እየሰጡ  እያገለገሉ እንዲቀጥሉ ገቢ የማሰባሰብ መርሃ የሚከናወን መሆኑ ተነግሯል በራሳቸው አቅም ገቢ የሚያስገኙ  ስራዎችን ማከናወን እንዲሁም ምዕመኑ በሚሰጠው መባ እና አስራት በኩራት ይጠቀሳሉ። ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በአሁኑ ወቅት የገጠመው ችግር  ለመቅረፍ የገቢ ማሰባሰብ ስራ አስፈላጊ ነው ተብሏል።

በማዕከላዊ ጎንደር ሐገረ ስብከት በምስራቅ በለሳ ወረዳ ቤተክህነት የሚገኘው ይህ ገዳም፣ ከዘጠና በላይ መነኮሳትና በመቶ የሚቆጠሩ ፀበልተኞች የሚገኙበት እጅግ ድንቅ ተዓምር ያለበት ታሪካዊ የአንድነት ገዳም  ነው ። ይሁን እና  መነኮሳቱ በአሁኑ ወቅት ትልቅ ችግር ውስጥ  ይገኛሉ። አካባቢው በርሃማ በመሆኑ በበጋ ወቅት ለከፍተኛ ድርቅ ይጋለጣል። በዚህም ምክንያት ምንም ዓይነት አዝዕርት አይበቅልበትም ይህን ተከትሎ ቀደም ሲል ድጋፍ ያደርጉ የነበሩት የአካባቢው ነዋሪዎች ሳይቀር ለገዳሙ ምንም አይነት ድጋፍ ለማድረግ ተቸግረዋል መባሉ ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን  ሰምቷል።

ገዳማዊያኑ የሚቀምሱት እህል፣ የሚለብሱት ልብስ በመጠኑ የተሟላላቸው ቢሆንም ከጾም፣ ጸሎት መልስ ስጋቸውን የሚያሳርፉበት  ቤት የላቸውም። በአንድ  ጎጆ  ውስጥ ለሶስት ለአራት የሚያድሩበት ሁኔታ መኖሩ ተነግሯል ።በዚህ ገዳም የሚገኙ ገዳማዊያን  ከጸሃይ፣ ከብርድ፣ከዝናብ የሚከላከል መጠለያ አጥተው በከፍተኛ ችግር እየተፈተኑ የሚገኙ በመሆኑ፣ ገዳማዊያኑን ከነዚህ ችግሮች እንዲወጡና በቀጣይም ገዳሙ ራሱን እንዲችል ለማድረግ፣ በጠቅላይ ቤተክህነት እውቅና እና በሐገረ ስብከቱ ፍቃድ ገዳሙ ብቻ የሚጠቀመው በገዳሙ ስም የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች ይፋ ተደርገዋል ። በሕዝበ ክርስቲያኑ በሚደረገው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ሲሆን፣ ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተ-ክህነት፣በሐገረ ስብከትና በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት በመሰራት ላይ ይገኛል።

እነዚህን የታቀዱ ለገዳሙ አስፈላጊ እና መሰረታዊ የሆኑትን የልማት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ ለማሰባሰብ የሚረዱ የተለያዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መንገዶችን ለመጠቀም ጥረት  እየተደረገ እንደሚገኝ  ተገልጿል ።

በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል




በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እና በዓመት ከ5 ሺ በላይ ህጻናት አገልግሎት ይሰጣል የተባለው የነርቭ እና ህብለሰረሰር ቀዶ ህክምና ማዕከል ተመረቀ

በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የገነባነውን እና ለኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የህጻናት የነርቭ እና ህብለሰረሰር ቀዶ ህክምና የልህቀት ማዕከል አስመርቀናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስታውቀዋል።

ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎች የተሟሉለት ይህ የልህቀት ማዕከል በዓመት ከአምስት ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ህጻናት አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ለህጻናት ትልቅ አስተዋፅዖ ያለው እንዲሁም አዲስ አበባ ህጻናትን ለማሳደግ ምርጥ አፍሪካዊት ከተማ ለማድረግ የጀመርነውን ስራ የሚደግፍ ነው ብለዋል።

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የተገልጋዮች ፍላጎት ለማስተናገድና በጤናው ዘርፍ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ትኩረት ሰጥተን በመስራት ላይ የምንገኝ ሲሆን፣ በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ለገነባነው ለዚህ የልህቀት ማዕከል የሪች አናዘር ፋውንዴሽን ላደረገልን አስተዋፅዖ በነዋሪዎቻችን እና በራሴ ስም ላመሰግን እወዳለሁ ሲሉ ከንቲባዋ ገልፀዋል።

#ዳጉ_ጆርናል


የኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኤሌክትሮኒክ ፓስፖርት ስራ ጀመረ

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አዲስ ዘርጋሁት ባለው የኢ-ፓስፖርት ሲስተም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሚስጥራዊ ህትመትና ቴክኖሎጂ ልምድ አለው ከተባለው የጃፓኑ ቶፓን ሴኩሪቲ ኢትዮጵያ አ.ማ አማካይነት ዘመኑ በደረሰበት የሚስጥራዊ ህትመት የታተመ አዲስ ፖስፖርት በዛሬው እለት በሳይንስ ሙዚየም ይፋ አድርጓል።

አዲሱ ኢ-ፓስፖርት የባዮሜትሪክ ቴክኖሎጂን፣ የላቀ ምስጥርን እና መከላከያ ቁሳቁሶችን በማዋሃድ አለም አቀፍ ደረጃዎችን ማክበርን እና ደህንነትን በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል ተብሏል። የኢሜግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ከፓስፖርቱ ጎን ለጎን የአፕሊኬሽን ሂደቶችን ለማቀላጠፍ እና ለኢትዮጵያውያን ዜጎች አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ዘመናዊ የፓስፖርት አሰጣጥ ስርዓቶችን መዘርጋቱን ብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል።

የኢሚግሬሽን እና የዜግነት አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት  እንደገለፁት የኢ-ፓስፖርቱ መግቢያ ለኢትዮጵያ የስደተኞች አገልግሎት ለውጥ የሚያመጣ እንዲሁም በተሻሻለ ደህንነት፣በፍጥነት ሂደት እና በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው እና የድንበር ቁጥጥርን በማጠናከር የኢትዮጵያውያንን የጉዞ ልምድ በእጅጉ ያሳድገዋል ብለዋል።

አዲሱ የ ኢ ፓስፖርት ከቀድሞ ክፍያ ምንም የተጨመረም የተቀነሰም የዋጋ ሁኔታ የሌለው መሆኑን ተገልፆ እንዲሁም ከዚ ቀደመ ፓስፖርት ለማተም ወደ ውጪ የሚላከውን ወጪ በመቀነስ በሀገር ውስጥ የማተም ስራ መሰራቱ  የተገለፀ ሲሆን   ፓስፖርቱ የግለሰቡን መረጃና የጣት ዐሻራ የያዘ የኤሌክትሮኒክስ ቺፕስ አለው ተብሏል።በኢትዮጵያ ውስጥ የሚመረት ይህ ፓስፖርት፤ የቪዛ ገጾቹ የኢትዮጵያን መልክ የያዙ መሆናቸው ተገልፆል።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኢ-ፓስፖርት መጀመሩ ዘመናዊነትን እና ቅልጥፍናን የሚያራምዱ ስትራቴጂካዊ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን ወደ ፊት ለማራመድ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል። እንዲሁም ፕሮጀክቱ የቴክኖሎጂ እና የባለሙያዎች አንድነት እንዴት በህዝብ አገልግሎቶች ላይ ደህንነትን እና ቅልጥፍናን እንደሚያሳድግ እና የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።

በሰመኃር አለባቸው
#ዳጉ_ጆርናል




በእስራኤል በሽብር ጥቃት የተነሳ ሶስት አውቶቡሶች በፈንጂ መመታታቸውን ፖሊስ አስታወቀ

የእስራኤል ፖሊስ “የሽብር ጥቃት” ነው ሲል በጠረጠረው ክስተት በዋና ከተማዋ በቴል አቪቭ ደቡባዊ ክፍል ላይ ሶስት ባዶ አውቶቡሶች ፈንድተዋል። ሐሙስ ምሽት ላይ ጥቃቱ የደረሰው በባት ያም አካባቢ ውስጥ በመኪና ማቆሚያዎች ውስጥ ነው። ጉዳት በሰዎች ላይ አለመድረሱ ሪፖርት ተደርጓል። በሌሎች ሁለት አውቶቡሶች ላይ ያሉ መሳሪያዎች ሊፈነዱ አልቻሉም ሲል ፖሊስ ተናግሯል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ስለ ጥቃቱ በሰጡት መግለጫ የእስራኤል ጦር “በአሸባሪነት ማዕከላት ላይ የተጠናከረ ዘመቻ” እንዲወስድ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።በማህበራዊ ድረ-ገጾች ላይ የተቀረጹ ምስሎች እንዳመላከቱት በመኪና ማቆሚያ ቦታ ላይ ቢያንስ አንድ አውቶብስ በእሳት ሲቃጠል፣ ትልቅ ጭስ ወደ ላይ ሲወጣ ያሳያል። የፖሊስ ቃል አቀባይ አሪዬ ዶሮን እንዳሉት የፖሊስ መኮንኖች በቴል አቪቭ ተጨማሪ ቦምቦችን ለማግኘት አሁንም እየሞከሩ ይገኛል።

ዶሮን አክለው ከፍንዳታው በኋላ ለቻናል 12 እንደተናገሩት "የእኛ ሃይሎች አሁንም አካባቢውን እየፈተሹ ነው" ህዝቡ " የተተው ቦርሳ ወይም እቃ" ሲመለከት በንቃት መከታተል አለበት ብለዋል። የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሀን እንደዘገቡት ካልፈነዳው መሳሪያ 5 ኪሎ ግራም የሚመዝን ቦምብ እና በቅርቡ በዌስት ባንክ የእስራኤል ወታደራዊ የፀረ ሽብር ዘመቻን በመጥቀስ ለፈፀመችው ጥቃት በቀል አለ የሚል መልዕክት ተላልፏል።

የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በዌስት ባንክ የፍልስጤም ታጣቂ ቡድኖች ላይ በተለይም በሰሜን ቱልካም እና ጄኒን ዙሪያ በማተኮር ለወራት ጥቃት ሲፈፅም ቆይቷል። የእስራኤል ጦር ወረራውን አጠናክሮ በቀጠለበት ወቅት በመቶዎች የሚቆጠሩ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል። የፍንዳታ መሳሪያዎች ፍተሻዎች እንዲከናወኑ የትራንስፖርት ሚኒስትር ሚሪ ሬጄቭ በመላው ሀገሪቱ ሁሉንም አውቶቡሶች፣ባቡሮች እና የቀላል ባቡሮች ለአፍታ ስራ አቁመዋል ማለታቸውን ዳጉ ጆርናል ከእስራኤል መገናኛ ብዙሃን ዘገባ ተመልክቷል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል

13 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.