ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56

https://t.me/AiqemAdsMasterBot
👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ዩክሬን በሩሲያ ከተሸነፈች አውሮጳ ውስጥ ደህንነት አይኖርም ስትል ፖላንድ አስታወቀች

የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ቱስክ አውሮጳ “የጦርነት ዘመን” ውስጥ መግባቷን እና ዩክሬን በሩሲያ ከተሸነፈ ማንም አውሮጳ ውስጥ ደህንነት ሊሰማው አይችልም ሲሉ ግልጽ የሆነ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። "ማንንም ማስፈራራት አልፈልግም፤ ነገር ግን ጦርነት ከአሁን በኋላ ያለፈ ጽንሰ-ሀሳብ አይደለም" ሲሉ ለአውሮፓ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። "እውነት ነው ጦርነቱ የተጀመረው ከሁለት አመት በፊት ነበር" ብለዋል።

የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህንን አስተያየት የሰጡት አዲስ የሩስያ ሚሳኤሎች በዩክሬን ላይ ማነጣጠራቸው ተከትሎ ነው። ፖላንድ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ኔቶ አውሮፕላኖች የአየር ክልሏን ለመጠበቅ ተጭበርብረው እንደነበር ተናግራለች። ሩሲያ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ በዩክሬን ላይ የምታደርገውን ድብደባ አጠናክራለች። የዩክሬን አየር ሃይል 58 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን እና 26 ሚሳኤሎችን መምታቱን የገለፀ ሲሆን የዩክሬን ጠቅላይ ሚኒስትር ዴኒስ ሽሚሃል በሀገሪቱ በምዕራብ፣ በመሃል እና በምስራቅ በስድስት ክልሎች የኢነርጂ መሠረተ ልማት ተጎድቷል ብለዋል።

የቀድሞ የአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሚስተር ቱስክ የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በሞስኮ ክሮከስ ማዘጋጃ ቤት ላይ ለደረሰው ጥቃት ምንም አይነት ማስረጃ ሳይኖር ዩክሬንን ወቅሰዋል። እናም ዩክሬን ውስጥ እየጨመረ የሚሄደውን የሩሲያ ጥቃቶች ከዚህ መነሻ ነው ብለዋል ። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ሩሲያ በሃይፐርሶኒክ ሚሳኤሎች ኪየቭን ለመጀመሪያ ጊዜ በቀን ብርሀን ማጥቃትዋን ጠቁመዋል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል


የኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ምርት የጥራት መጓደል ችግር ያለበት በመሆኑ በተቀባይ ሀገራት ዘንድ ቅሬታ እንደሚቀርብበት ተነገረ

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአመት ከ7 መቶ ሺህ ኩንታል በላይ የቅመማ ቅመም ምርት እያመረተች ትገኛለች ቢባልም  በምርቱ ዙሪያ የጥራት መጓደል ችግር እንደሚስተዋል የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።

በባለስልጣኑ የቅመማ ቅመም ዴስክ ኃላፊ አቶ ሞገስ አሸናፊ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት፣በቅመማ ቅመም ዘርፍ ከአመራረት ጀምሮ ኤክስፖርት እስኪደረግ ባለው ሂደት ውስጥ የጥራት ጉድለቶች ይስተዋላሉ።ኢትዮጵያ ለውጪ ገበያ የምታቀርባቸው የተለያዮ የቅመማ ቅመም ምርቶች ቢኖሩም በዘርፉ በሚስተዋለው የጥራት ችግር  ከአንድ በመቶ በታች የሆነውን  የቅመማ ቅመም ምርቷን ብቻ ለውጪ ገበያ ታቀርባለች  ሲሉ ተናግረዋል።

በዚህም ችግር የተነሳ የኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ምርት ተቀባይ ሀገራት ቅሬታ እንደሚያቀርቡ የገለፁት ኃላፊው የጥራት መጓደል ችግሩ ሆን ተብሎ እና እውቀት ከማጣት የተነሳ ይከናወናል ብለዋል።ይህ ሁኔታ በተለይም በእርድ፣ዝንጅብል፣በርበሬ እንዲሁም በጥቁር አዝሙድ የቅመማ ቅመም ዓይነቶች ላይ በስፋት እንደሚስተዋል ተጠቅሷል።የቅመማ ቅመም ምርት የጥራት ደረጃውን እና የተፈጥሮ ቀለሙን በጠበቀ መልኩ መዘጋጀት ቢኖርበትም ምርቱን ከባእድ ነገሮች ጋር የመቀላቀል  ድርጊቶች እንደሚፈጸሙ ተጠቅሷል።

ከዚህም ውጪ ጥንቃቄ በጎደለው ዝግጅትና ክምችት  ለውጪ ገበያ በሚቀርበው የቅመማ ቅመም ምርት ላይ  ይዘቱን የሚቀይሩ የሻጋታ ምልክቶች  እንደሚስተዋሉ ተገልጿል።ከዚህ ቀደም በቅመማ ቅመም ዘርፏ ላይ የአመራረት ፓኬጅ ባለመኖሩ እና ህግ ሳይበጅለት በመቆየቱ  የጥራት መጓደል ችግር  እንዲኖር  እና ምርቱ ለውጪ ገበያ በሚቀርብበት ወቅት ቅሬታዎች እንዲቀርቡ ምክኒያት ሆኗል ተብሏል፡፡

እነዚህ ሁሉ ችግሮች ተዳምረው ኢትዮጵያ ከዘርፉ በሚገባት ልክ ተጠቃሚ እንዳትሆን አድርጓታል ያሉት አቶ ሞገስ የኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ምርት በአለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማድረግ የቅመማ ቅመም ምርት  ጥራት ቁጥጥርና ግብይት መመሪያ መዘጋጀቱን ገልፀዋል።ይህ መመሪያ የቅመማ ቅመም ላኪዎች፣አቀናባሪዎች እንዲሁም ቸርቻሪዎች የብቃት ማረጋገጫ ኖሯቸው ስራቸውን እንዲያከናዉኑ ያስገድዳል ተብሏል፡፡

በቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል


በሚዛን አማን ከተማ ያለ ወጪ ማዘዣ በቼክ ለባንክ ክፍያ እንዲፈፀም በማድረግ ወንጀል የተከሰሱ የስራ ሃላፊዎችና ሠራተኞች በእስራት ተቀጡ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በቤንች ሸኮ ዞን የወጪ ማዘዣ ሳይዘጋጅ በቼክ ጉርድ እና ለባንክ ክፍያ እንዲፈፀም በማድረግ ሙስና ወንጀል የተከሰሱ የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና ኢኮኖሚ  ልማት ጽህፈት ቤት የቀድሞ ሃላፊዎችና ሠራተኞች በእስራት እንዲቀጡ ተወስኗል ።
  
ተከሳሾች 1ኛ አልማዝ ጥሩነህ 2ተኛ ጌታቸው ጎበዜ 3ተኛ መሐመድ ሙል እና 4ተኛ ማስረሻ ጥላሁን የተባሉ ግለሰቦች  የሙስና ወንጀል መፈፀማቸው ተጠቁሟል ። በዚህም 1ኛ ተከሳሽ  መንግስታዊ  ሰነዶችን ወደ ሀሰት በመለወጥ  ጠቅላላ ድምር 473 ሺህ  82 ብር ለባንክ ክፍያ እንዲፈፀም በሚቀርበው በራሪ ቼክ ላይ የተፃፈን ብር ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅም ማዋልና  መንግስታዊ ስራን በማይመች አኳኋን መምራት የሙስና ወንጀል መፈፀም በጠቅላላ ድምር 45 ሺህ 500 ብር ለግል ጥቅም በማዋል ሁለት ክስ ቀርቦበታል ።

ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያሉ ተከሳሾች ደግሞ መንግስታዊ ስራን በማይመች አኳኋን መምራት የሙስና ወንጀል በመፈፀም ክስ ቀርቦባቸዋል ። ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ጥቅም ለራሳቸው ለማገኘት ወይም ሌላ ሰውን ለማስገኘት በማሰብ ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር የመንግስትን ሀብት  እንዲያስተዳድሩ እና እንዲፈርሙ የተሰጣቸውን ሃላፊነት ወደጎን በመተው ምንም የወጪ ማዘዥያ ሳይዘጋጅ በቼክ ጉርድ እና ለባንክ ክፍያ እንዲፈፀም ማድረግ በሚሉት ወንጀሎች ክስ ቀርቦባቸዋል ።

በዚህም መሠረት የቤንች ሸኮ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተከሳሾች ላይ የቀረበውን ክስ ሲያከራክር ቆይቶ መጋቢት 17 ቀን  2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት በአራቱም ተከሳሾች ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ አስተላልፏል ስለሆነም 1ኛ ተከሳሽ አልማዝ ጥሩነህ በ5 ዓመት ጽኑ እስራት እና 3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ፣ 2ተኛ ጌታቸው ጎበዜ በ4 ዓመት ፅኑ እስራት እና 2 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል ። 3ተኛ መሐመድ ሙል እና 4ተኛ ማስረሻ ጥላሁን በበኩላቸው እያንዳንዳቸው በ3 ዓመት ከ7 ወር ጽኑ እስራት እና 1 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል ።

እንዲሁም አራቱም ተከሳሾች መንግስት ላይ ጉዳት ያደረሱትን 443 ሺህ 82 ብር በጋራ ለመንግስት ገቢ እንዲያደርጉ ትዕዛዝ ተሰጥቷል ። በተጨማሪ አንደኛ ተከሳሽ አልማዝ ጥሩነህ መንግስት ላይ ለብቻው ያደረሰውን ጉዳት 57 ሺህ 276 ብር ለመንግስት ገቢ እንዲያደርግ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከዞኑ ኮሚኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያመላክታል ።


#ዳጉ_ጆርናል


በብሪታኒያ ጦር ዉስጥ ወታደሮች ጺማቸዉን እንዳያሳድጉ የተጣለዉ እገዳ ተነሳ

ወታደር እና የጦር መኮንኖች በብሪቲሽ ጦር ውስጥ እያገለገሉ ጺማቸውን እንዲያሳድጉ ከዛሬ ጀምሮ ፍቃድ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ይህዉ ፈቃድ ሲሰጥ ግን ወታደሮች ጺማቸዉ ንፁህ ፣ በትክክል ቅርጽ የወጣለትና እና በመደበኛነት ቁጥጥር የሚደረግባቸው መሆን አለባቸው።ፖሊሲው ወዲያውኑ ተግባራዊ የሚሆነው ሰራዊቱ ጺማቸዉን እንዲያሳድግ ከጦር ኃይሎች የመጨረሻው ዉሳኔ መተላለፉን ተከትሎ ነዉ፡፡አዲሱ መመሪያ በሰራዊቱ የፊት ፀጉር ፖሊሲ ዙሪያ ለዓመታት ሲደረግ የቆየ ውይይት ተከትሎ ነው።ለውጡ ለወራት የፈጀውን የሰራዊቱ ፖሊሲ በፖሊሲዉ  ላይ የተደረገውን ግምገማ ተከትሎ ነው ሲሉ የሰራዊቱ ቃል አቀባይ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የሰራዊቱ አመራር ፖሊሲውን ለመቀየር ከመወሰኑ በፊት ሊኖሩ የሚችሉ ለዉጦችን ሲገመግም ቆይቷል፡፡"ህዝባችንን ሰምተን እርምጃ ወስደናል" ሲሉ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል ።ሰራዊቱ እንዳስታወቀው ወታደሮቹ ጺማቸዉ ንፁህ ከመሆን ባለፈ መላጨት የሚጠበቅባቸው ልዩ አጋጣሚዎች ሊኖሩ ይችላሉ፣ እናም መኮንኖች እና ወታደሮች "ሁኔታዎች በሚወስኑበት ጊዜ እንዲላጩ ይታዘዛሉ ብሏል።የሰራዊቱ መሪዎች አዲሱ ፖሊሲ አዳዲስ ምልምሎችን ለመሳብ ይረዳል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ ተብሎ ይታሰባል።

እንደ ዴንማርክ፣ ጀርመን እና ቤልጂየም ያሉ በርካታ የውጭ ጦር ኃይሎች ወታደሮቻቸዉ ጺማቸውን እንዲያሳድጉ ከፈቀዱ ሀገራት ተርታ ይመደባሉ፡፡እንደ ሲክ ፣ ራስተፋሪያን እና የሌላ እምነት ተከታይ ያሉ የአንዳንድ እምነት ወታደሮች የአሠራር ውጤታቸውን ፣ ጤናቸውን እና ደህንነታቸውን አደጋ ላይ እስካላደረጉ ድረስ ፂማቸውን እንዲያሳድጉ ተፈቅዶላቸዋል።

ዘ ታይምስ እንደዘገበው አዲሱ ፖሊሲ በዋራንት ኦፊሰር ክፍል 1 ፖል ካርኒ፣ ለወታደሮቹ የአራት ደቂቃ የቪዲዮ መልእክት በማስተላለፍ መፈቀዱን ይፋ አድርጓል፡፡"የእንግሊዝ ንጉስ፣ ፖለቲከኞች እና አጋሮቻችንን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እዚህ ውጤቱ ላይ ለመድረስ ከተጠበቀው በላይ የተራዘመ ጊዜ ወስዷል" ተብሏል።የአጠቃላይ ሰራተኛው ዋና አዛዥ እንዳሉት የመኮንኖች እና ወታደሮቻችን ፂም እንዲያሳድጉ በመፍቀድ ፖሊሲው እንዲቀየር ተወስኗል ብለዋል፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር ግራንት ሻፕስ ባለፈው አመት ከጋዜጣው ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በሠራዊቱ ውስጥ ጺምን ማሳደግ መከልከል "አስቂኝ ነው" በማለት ተቋሙ "ዘመናዊ" አሰራር እንዲኖረዉ ጠይቀዋል።"ሰዎችን ወደ ወታደሩ ለመቀላቀል እየተቸገርን ፂምህን ብታሳድግ ከእኛ ጋር መቀጠል አትችልም እያልን ነበረ ሲሉ ተናግረዋል።ከ2019 ጀምሮ የሮያል አየር ሃይል ሰራተኞቹ የፊት ፀጉር እንዲያሳድጉ የፈቀደ ሲሆን የሮያል የባህር ኃይል ጺም ማሳደግን ከፈቀደ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




ኬኤፍሲ ናይጄሪያ በአካል ጉዳት ደንበኛው ላይ በሌጎስ አውሮፕላን ማረፊያ ለተፈጠረው የማግለል ተግባር ይቅርታ ጠየቀ

ግዙፉ የፈጣን ምግቦች አቅራቢ ኬኤፍሲ ናይጄሪያ በአካል ጉዳተኛ ደንበኛ ላይ ተፈጽሟል በተባለው መድልዎ የሀገሪቱ የአየር ማረፊያ ባለስልጣን አንዱን ጣቢያ ከዘጋ በኋላ ይቅርታ ጠይቋል።

የቀድሞው የናይጄሪያ ግዛት ገዥ የግቤንጋ ዳኒኤል ልጅ አዴቦላ ዳንኤል በኤክስ ላይ ባስተላለፈው መልዕክት በሌጎስ አየር ማረፊያ በሚገኘው የኬኤፍሲ ቅርንጫፍ በዊልቼር ምክንያት እንድወጣ ተደርጌያለሁ ሲል ያጋራው መልዕክት በናይጄሪያውያን ዘንድ ሰፊ ቁጣ ቀስቅሷል። በተጨማሪም የፌደራል አውሮፕላን ማረፊያ ባለስልጣን የኬኤፍሲ ቅርንጫፍ ቢሮውን በመዝጋት ምርመራ እንዲካሄድ አድርጓል።

ዳንኤል ባጋራው መልዕክት የተፈፀመብኝ ክስተት “ከዚህ በፊት ካጋጠሙኝ በሙሉ የከፋ ውርደት” ነበር ሲል ገልጿል። "ዛሬ ልክ እንደ ጠባቂ ውሻ ወደ ቤት እንዳይገባ እንደተከለከ ለ፤ ከሰው ያነሰሁ ብሎም ብቸኝነት ተሰምቶኛል" ሲል በፁሁፉ እጋርቷል። በናይጄሪያ በጣም እንቅስቃሴ በሚበዛበት የሙርታላ መሀመድ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የኬኤፍሲ ስራ አስኪያጅ የሆነች ግለሰብ አገልግሎት እንዲሰጠኝ ባለቤቴ እና ሁለት ወንድሞቼ ደጋግመው ቢለምኗትም አገልግሎቱን ከልክለውኛል ሲል ክስ አቅርቧል።

ስራ አስኪያጇ ምክንያት ለመስማት ፈቃደኛ አልሆነችም። በኬኤፍሲ የኤርፖርቱ ሙርታላ ሙሀመድ ቅርንጫፍ ዊልቸር የሚጠቀሙ ሁሉም አይነት ተሽከርካሪ ወንበሮች አይፈቀዱም በማለት ወዲያውኑ ልንሄድ እንደሚገባን በመግለጭ በውሳኔዋ ፀንታለች ብሏል። በኤክስ ላይ ኬኤፍሲ ናይጄሪያ በለጠፈው መልዕክት ቅሬታ አቅራቢውን ዳንኤልን ይቅርታ በመጠየቅ ችግሩን ለመቅረፍ ሰራተኞቹን በማካተት እና ርህራሄ ባለው የደንበኞች አገልግሎት ላይ ማሰልጠን ጨምሮ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አስታውቋል።

አክሎ መግለጫው "በእኛ እንግዳ ላይ በደረሰበት ብስጭት እና ጭንቀት በጥልቅ ተጸጽተናል እና ለተጎዱት በመሉ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን" ብሏል፡፡

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




በሐረር ከተማ በተማሪዋ ላይ ድብደባ የፈጸመችዉ መምህር በቁጥጥር ስር ዋለች

በሐረር ከተማ በተማሪዋ ላይ ድብደባ የፈጸመች መምህር በቁጥጥር ስር መዋሏን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ሰምቷል።

በሐረር ከተማ ሞዴል ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት ዉስጥ ተማሪ የሆነችዉ እሊሊ ናስር  በአካሏ ላይ ዩደረሰባትን ጉዳት የተመለከቱ ወላጆቿ ለፖሊስ ጥቆማ ማድረሳቸዉን በሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን የሴቶችና ህፃናት ምርመራ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ህይወት ጌታነህ ነግረዉናል። ይህንን ተከትሎ ፖሊስ ተከሳሽን በቁጥጥር ስር አዉሎ የመምህሯን ቃል ተቀብሏል።

መምህሯ ፤ ተማሪ እሊሊ ናስር በተደጋጋሚ አሳይታለች ባሉት የባህሪ ችግር ምክኒያት ለመቅጣት ሲሉ ድርጊቱን መፈጸማቸውን ለፖሊስ በሰጡት ቃል መናገራቸዉን ኢንስፔክተር ህይወት ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። 

መምህሯ ክስተቱ ስህተት መሆኑን አምነዉ ፖሊስም በዋስ እንደለቀቃቸዉ አክለዋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል


በእነ ክስርስቲያን ታደለ ፣ ዘመነ ካሴ ፣ እስክንድር ነጋ እና ሌሎች 52 ግለሰቦች ላይ የሽብርተኝነት ወንጀል ክስ ተመሰረተ

ዓቃቤ ሕግ ያለመከሰስ መብታቸው በተነሳባቸው የሕዝብ ተመራጮች ክርስቲያን ታደለ፣ ዮሐንስ ቧያለው እና ካሳ ተሻገር ላይ የሽብር ወንጀል ክስ መመስረቱን ዳጉ ጆርናል ሰምቷል። በክስ መዝገቡ ከተካተቱት 52 ተከሳሾች መካከል፣ እስክንድር ነጋ፣ ጫኔ ከበደና ዘመነ ካሴ ይገኙበታል።

ዓቃቤ ሕግ በክሱ፣ ተከሳሾቹ የፖለቲካ ርዕዮታቸውን በኃይል ለማስፈጸም በማሰብ፣ በኅቡዕ የተቋቋመውን የአማራ ፋኖ አንድነት ምክር ቤትን ዓላማዎች ለማስፈጸምና የአማራ ሕዝብ ርሥቶች ናቸው የሚሏቸውን አካባቢዎች በወታደራዊ ኃይል ለማስመለስ የተደራጁ ነበሩ ብሏል።

ዓቃቤ ሕግ፣ ተከሳሾቹ ከ1 ሺህ 100 በላይ ለሚኾኑ የጸጥታ አባላትና ሲቪሎች ሞትና 5 ሺህ 689 በላይ ታራሚዎችን በማስመለጥ ወንጀልም ተጠያቂ አድርጓቸዋል።

#ዳጉ_ጆርናል


የማሊያው ቁጥር በክብር ተቀመጠ!

በድንገት ህይወቱ ያለፈው ወጣቱ አማካይ የእግር ኳስ ተጨዋች አለልኝ አዘነ የሚለብሰው የማሊያ ቁጥር በክብር እንዲቀመጥ መወሰኑን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

የጣና ሞገዶቹ ተጫዋቾች በኮከብ ተጫዋቻቸው ህልፈተ ህይወት የተሰማቸዉን ሀዘን በትዉልድ ስፍራው በመገኘት እንደተሰናበቱ ለማወቅ ተችሏል።

አለልኝ አዘነ በባህር ዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ይለብሰዉ የነበረው የማልያ ቁጥር 23 ከዚህ በኋላ ማንም የክለቡ ተጫዋች የማይለብው ሆኖ በክብር እንዲቀመጥ የባህርዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ወስኗል።

#ዳጉ_ጆርናል


የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው ሲሉ አቶ ጌታቸው ረዳ ተናገሩ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ፣ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት በድጋሚ የሚያገረሽበት ዕድል ዝግ ነው በማለት ትናንት ከቻይናው ሲጂቲኤን ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል።

ያለፈው ጦርነት የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት አልነበረም ያሉት ጌታቸው ፣ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደርና የትግራይ ሕዝብ ድጋሚ ጦርነት እንዳያገረሽ የተቻላቸውን ጥረት ኹሉ እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።

ጌታቸው ይህን ያሉት ፣ በአላማጣ አቅራቢያ በትግራይ ኃይሎች እና ባካባቢው ሚሊሻዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ በተደረገ ማግስት ነው መባሉን ዳጉ ጆርናል ከዋዜማ ዘገባ ተመልክቷል።

አቶ ጌታቸዉ ይህንን ይበሉ እንጂ አብን፣ ሕወሃት ለአዲስ ዙር ጦርነት ቅስቀሳ እያደረገ ነው ሲል ትናንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ከሷል። ፓርቲው፣ በግጭት ማቆም ስምምነቱ መሠረት የሕወሃት ተዋጊዎች ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ሳይፈቱና መከላከያ ሠራዊት በትግራይ ክልል ጸጥታ ለማስከበር ሳይሠማራ ሕወሃት ለሌላ ዙር ጦርነት ፕሮፓጋንዳ በመለፈፍ ተጠምዷል ብሏል።

የፌደራሉና የአማራ ክልል መንግሥታት የሕወሃትን የጠባጫሪነት ቅስቀሳ በትኩረት እንዲከታተሉና በአማራ ክልል የሚካሄደው ግጭት "በንግግር" እና "ድርድር" እንዲፈታም አብን ጠይቋል። የአማራ ሕዝብ ሕወሃት ሊያደርስበት የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል በአንድነት እንዲቆም የጠየቀው ፓርቲው፣ የትግራይ ሕዝብም ራሱን ከሕወሃት ቀንበር እንዲያላቅቅ ጥሪ አድርጓል።

#ዳጉ_ጆርናል


‹‹ አብን ትናንት ምሽት ያወጣዉ መግለጫ የግለሰቦች እንጂ የፓርቲዉ አቋም አይደለም ›› - ከፍተኛ አመራር እና የምክር ቤት አባል

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ረቡዕ ምሽት ያወጣው መግለጫ እንደማይወክላቸዉ  የምክርቤት  አባላቱና ስማቸዉ እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ አንድ ከፍተኛ የቀድሞ አመራር ለአሻም ነግረዋታል፡፡

የቀድሞው ከፍተኛ አመራር ይህን ያሉበትን ሲያሥረዱ ‹‹ ከ9 ስራ አስፈጻሚ አባላት 6ቱ በሌሉበትና የምክርቤት አባላት የሆኑ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን ጭምር ሰብስቦ ባላወያየበት በጣት በሚቆጠሩ ግለሰቦች ፍላጎትና ሀሳብ ተጠናቅሮ በፓርቲዉ ስም የተሰጠ መግለጫ  ነዉ ›› ሲሉ ነቅፈውታል፡፡

እኚሁ አመራር አስከትለዉም ‹‹ ፓርቲዉ ለእውነት የቆመ ቢሆን  የስራ አስፈጻሚ፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላቱን ጠርቶ በማወያየት ማህበራዊ መሠረቴ ነው፤ እቆምልታለሁ ለሚለዉ ህዝብ፣ ለታሰሩና ለጠፉ አባላቶቹ መግለጫ ያወጣ ነበር ሲሉ ፓርቲያቸዉን ›› ተችተዋል፡፡

ይሁን እንጂ በእነዚህ ግለሰቦች በፓርቲዉ ስም የወጣዉ ዳግም ግጭት ቀስቃሽ  መግለጫ ጨምሮ  በትግራይና አማራ ክልልና የፌደራሉ መንግስት  በኩል ጉዳዩን  በእርጋታ በመመልከት  ህዝቡን  ከሰብዓዊና ቁሳዊ ዉድመቶች መታደግ ተገቢ ነዉ ሲሉ  የግል አቋማቸዉን አንጸባርቀዋል፡፡

በተመሳሳይ  ፓርቲዉን ወክለዉ የ2013 ምርጫ በተወዳደሩበት ስፍራ አሸንፈው የፌደራል የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባል የሆኑት አበባዉ ደሳለዉ በበኩላቸው መግለጫዉ የስራ አስፈጻሚ አባላት ከግማሽ በላይ ያልተሟሉበትና ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ተሰብስበዉ ያልተወያዩበት በመሆኑ መግለጫዉ የፓርቲዉ ነዉ ለማለት እንቸገራለን ሲሉ ለአሻም ነግረዋታል፡፡

አሻም በጉዳዩ ላይ የፓርቲዉን ሊቀመበር በለጠ ሞላን(ዶ/ር) ጨምሮ ቀሪ የስራ አስፈጻሚ አባላቱን ለማነጋገር ብትሞክርም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው በዘገባው ሊካተቱ አልቻሉም፡፡

Via አሻም
#ዳጉ_ጆርናል




በመላው የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡ ተገለፀ

ዛሬ ከቀኑ 9 ሠዓት 46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል።

ሲስተም ላይ በገጠመ ችግር ኃይል የተቋረጠ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን÷ ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው ተብሏል።

የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ  መሆኑም ተመላክቷል፡፡

እስከዛ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ  ተቋሙ ጠይቋል፡፡

#ዳጉ_ጆርናል


በአምቦ ወረዳ የ90 ዓመት አዛውንት አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ወረዳ ኢላሙ ጎሮሙጢ የተባለ አካባቢ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በእስራት መቀጣጡት የምዕራብ  ሸዋ ዞን  ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታውቋል ፡፡ 

የምዕራብ ሸዋ ዞን የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የላከእ መረጃ እንደሚያመላክተው ተከሳሽ ለቴራ ቀና የተባለው ግለሰብ  መጋቢት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 7 ሰዓት ላይ የ90 ዓመት ኣዛውንት  በመኖሪያ ቤታቸው  ተኝተው  ባሉበት  ቤታቸውን ሰብሮ በመግባት አስገድዶ የመድፈር ወንጀል እንደፈጸመ በማስረጃ ተረጋግጧል፡፡

ተከሳሽ  በእድሜ  የደከሙ ራሳቸውን መከላከል  የማይችሉ  አዛውንትን  በጉልበት  አስገድዶ  መድፈሩ ፖሊስ በህክምና ማስረጃ ያረጋገጠ እና የምርመራ መዝገቡን አጠናክሮ ለ ዓቃቢህግ መላኩን ብስራት ተመልክቷል ፡፡

በዚኅም  ዓቃቢ ህግ  ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልከቶ  በወንጀለኛ  መቅጫ ህግ መሰረት ክስ መስርቷል፡፡  ክሱን ሲመለከት የነበረው የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት  መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም  በዋለው ችሎት ተከሳሽ ለቴራ  ቀና በስምንት  ዓመት እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ  የተላለፈበት መሆኑን  የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት  ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት  ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የላከው መረጃ  ያመላክታል ፡፡

በኤደን ሽመልስ
#ዳጉ_ጆርናል


ህጋዊ የስፖርት ውርርድ ድርጅቶች ስራቸው በመቋረጡ የተነሳ ለሰራተኞቻቸው ደሞዝ መክፈል ሊያቆሙ መሆኑን አስታወቁ

የቫሞስ እና የሀበሻ የስፖርት ውርርድ ድርጅቶች እንዳስታወቁት ከታህሳስ ወር ጀምሮ በአዲስ አበባ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ግብረ ሐይል በማቋቋም እንዲዘጋ መደረጉን ተናግረዋል፡፡የቫሞስ ኢንተርቴይመንት ስራ አስኪያጅ አቶ የኔብልህ ባንታየው እና የሀበሻ ስፖርት ውርርድ ስራ አስኪያጅ አቶ መርሻ ቡዛየሁ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ከ5 ዓመት በፊት በብሄራዊ ሎተሪ ፍቃድ የተሰጠው ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሁለቱ ተቋማት በሀገር ውስጥ 156 እና 166 ቅርንጫፎች እንዳሏቸው እና ከ1ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎችም የስራ እድል የፈጠረ ዘርፍ መሆኑን ተናግረዋል ፡፡የሀበሻ ስፖርት ውርርድ ስራ አስኪያጅ አቶ መርሻ ቡዛየው ከታህሳስ ወር ጀምሮ ድርጅቶቹ መዘጋታቸውን እና ያለምንም ስራ ለሰራተኞቻቸው እንዲሁም ለቤት ኪራይ እየከፈሉ እንደቆዩም ገልፀዋል፡፡

የስፖርት ውርርድ ተቋማቱ በብሄራዊ ሎተሪ መመሪያ መሰረት ከ21 ዓመት በታች እና ተማሪዎች እንዳይገቡ የሚለውን መመሪያ መፈፀማቸውን እና ለዚህም ብለው ከ340 በላይ የጥበቃ ሰራተኞች ቀጥረው እንዳይገቡ ይከለክሉ እንደነበርም ተናግረዋል፡፡

የቫሞስ ኢንተርቴይመንት ስራ አስኪያጅ አቶ የኔብልህ ባንታየሁ አክለውም በስፖርት ውድድር ዘርፍ ውስጥ 8 መቶ ድርጅቶች ህጋዊ መሆናቸው ተነግሮናል፤ ሌሎቹ 3ሺ የሚሆኑት ግን በህገወጥ ስራ የተሰማሩ መሆናቸው ከተለየ የህጋዊነት አግባብ ያለን ድርጅቶች ወደ ስራችን እንድንመለስ መልስ ይሰጠን ሲሉ ጠይቀዋል፡

መልስ በመጠበቅ አራት ወራት እንደቆዩ ለሰራተኞቻቸው ሲከፍሉት የነበረውን ወርሀዊ ደሞዝ ከዚህ በላይ መክፈል የማይችሉበት ከባድ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን አቶ የኔብልህ ባንታየሁ እና አቶ መርሻ ብዙአየሁ ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።በቅሬታ አቅራቢዎቹ ዘንድ ህጋዊ የስፖርት ቤቶች ይከፈትልን የሚሉ አቤታታዎች ቢኖሩም ዘርፉ መዝጋቱ የሚደግፉና ቁጥጥሩ የላላ በመሆኑ ታዳጊዎች ላልተገባ ሱሱ ተዳርገዋል ሲሉ የሚደመጡም አሉ።

በምህረት ታደሰ
#ዳጉ_ጆርናል


ከእህቱ ሞት ጋር በተያያዘ በመንፈስ ተወግታ ነው በሚል ወሬ ተነሳስቶ የግድያ ወንጀል የፈፀመዉ ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ

በኢሊባቡር ዞን በያዮ ወረዳ አጨቦ ቀበሌ ልዩ ቦታው ብርቂቱ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ከእህቱ ሞት ጋር በተያያዘ በመንፈስ ተወግታ ነው በሚል ወሬ ተነሳስቶ አንድ ግለሰብን የገደለ ተከሳሽ በእስራት ተቀጥቷል ።

የ29 ዓመት እድሜ ያለው ምትኩ በቀለ የተባለ ግለሰብ ኑሮው ከቤተሰቦቹ ጋር አድርጎ ነበር ። ታላቅ እህቱ በተደጋጋሚ በመታመሟ የተነሳ የአዕምሮ መታወክ ይገጥማታል ። ሆኖም ከገጠማት የአዕምሮ መታወክ በህክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ በመስከረም ወር 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ትለያለች ።

ሞቷ በቤተሰቦቿ ላይ ከፍተኛ ሀዘን ያስከተለ ከመኖኑ ባሻገር ከአማሟቷ ጋር በተያያዘ የሚወራው ወሬ መላ ቤተሰቡን ያስከፋ ሲሆን በተለይም ደግሞ ምትኩን አስደንግጧል ። ወሬውም ሟች ህይወቷ ያለፈው በአካባቢው በምትገኝ ጫልቱ ተረፈ በተባለች ግለሰብ መንፈስ ተወግታ ነው ይባላል ።

ይህ ወሬ በመጨረሻም የምትኩን ልብ ለበቀል ያነሳሳል ። ጫልቱ በበኩሏ የሚወራው ችላ በማለት የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴዋን ትቀጥላለች ። በዚህም ጥቅምት 27 ቀን 2016 ዓ.ም  ዓመታዊውን የመድኃኒዓለም ክብረ በዓል አክብራ ስትመለስ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ ምትኩ በቀለ በመንገድ ጠብቆ በገጀራ ጭንቅላቷ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የኢሉባቡር ዞን ፖሊስ ኮሚኒኬሽን ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ገልጿል ።

በወቅቱ ተጎጅዋን በመረባረብ ወደ መቱ ካርል ሪፈራል ሆስፒታል ተወስዳ እርዳታ ቢደረግላትም ህይወቷ መትረፍ ሳይችል ይቀራል ። ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ የምርመራ መዝገቡን አጣርቶ ለዓቃቤ ህግ ይልካል ።

ዓቃቤ ህግ በደረሰው ማስረጃ ተመስርቶ በኢሊባቡር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ክስ ይመሰርታል ። ፍርድ  ቤቱ ዓቃቤ ህግ የመሠረተውን ክስ ሲመለከት ቆይቶ ተከሳሽ ምትኩ በቀለን ጥፋተኛ በማለት በ11 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል ።

በአበረ ስሜነህ
#ዳጉ_ጆርናል




የቻይናው ግዙፍ የስማርትፎን ኩባንያ ዢኦሚ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለገበያ ማቅረብ ሊጀምር ነው

የቻይናው የስማርት ስልክ አምራች ዢኦሚ የመጀመሪያውን የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ (ኢቪ) ለገበያ ለማቅረብ የተዘጋጀ ሲሆን ሀሙስ እለት ትእዛዝ መቀበል ጀምሯል። ዋና ስራ አስፈፃሚው ሌይ ጁን በዚህ ሳምንት እንደተናገሩት ስፒድ አልትራ 7 (SU7) ከ500,000 ዩዋን ወይም በ69 ሺ186 የአሜሪካን ዶላር ዋጋ እንደሚሸጥ ተናግረዋል። እርምጃው የቴክኖሎጂ ግዙፉ እንደ ቴስላ እና ቢዋይዲ ካሉ ተቀናቃኞቹ ጋር ያለውን ፉክክር ያጠናክራል።

የዢኦሚ ወደ ኤሌክትሪክ መኪና ገበያ መግባቱ በአለም አቀፍ ደረጃ የሽያጭ እድገት በመቀነሱ የዋጋ ጦርነትን አስነስቷል። ኩባንያው የ SU7 የጋራ ኦፕሬቲንግ ሲስተም ከስልኮች፣ ላፕቶፖች እና ሌሎች ምርቶቹ ተጠቃሚ ከሆነ ነባር ደንበኞችን ይስባልኛል ሲል ተስፋ አድርጓል።

ዢኦሚ በዓለም አቀፍ ደረጃ በሶስተኛ ስፍራ ላይ የተቀመጠ የስማርት ስልኮች አቅራቢ ሲሆን 12 በመቶው የገበያ ድርሻ እንዳለው ካውንተር ፖይንት የተባለው የምርምር ድርጅት ገልጿል። ዢኦሚ ካለፈው አመት ጀምሮ ፍተሻ ሲያደርግበት የነበረው SU7 ከፖርሽ ታይካን እና ፓናሜራ የስፖርት መኪና ሞዴሎች ጋር ንፅፅር ተደርጎበታል። በዓመት እስከ 200 ሺ የሚደርሱ ተሽከርካሪዎችን ማምረት በሚችል በቤጂንግ በሚገኝ ፋብሪካ በመንግስት ባለቤትነት በተያዘው የመኪና አምራች ዩኒት ይሠራል።

እስከዚህ ድረስ መድረስ በራሱ ትልቅ ስኬት ቢሆንም የመጨረሻው ስኬት ዢኦሚ የሸማቾች ገበያ ላይ ተፈላጊነቱን ማሳየት ነው ሲሉ ኩባንያው አስታውቋል። የኤሌክትሪክ መኪና ለመሥራት የሚፈልጉ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚያጋጥሟቸውን ፈተናዎች ለማመልከት የአይፎን አምራች አፕል ባለፈው ወር ተሽከርካሪዎችን የመሥራት ዕቅዱን መሰረዙ ይታወሳል።


ዢኦሚ በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ በተሽከርካሪ ንግዱ 10 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት አደርጋለሁ ብሏል። በቢሊየነሩ ኤሎን ማስክ የሚመራው ቴስላ በቅርብ ወራት ውስጥ በቻይና ያለውን ድርሻ በሀገር ውስጥ ተቀናቃኝ በሆነው ቢዋይዲ ተነጥቋል።የዋጋ ቅናሽ በማድረጉ ቴስላ ፉክክሩን መቋቋም አልቻለም።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.