ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር (ዲ/ዮርዳኖስ አበበ)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


በዚህ ቻናል ዲ/ዮርዳኖስ የሚያስተምራቸው ወቅታዊ እና የነገረ ቅዱሳን (ዝክረ ቅዱሳን ትምህርቶችን ከእርሱ በመቀበል እናስተላልፋለን):: "ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri






✝✝✝ እንኩዋን ለዳግሚያ ትንሳኤ በሰላም አደረሳችሁ ✝✝✝

=>ለስም አጠራሩ ጌትነት ይድረሰውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ትንሳኤው በሁዋላ ለደቀ መዛሙርቱ በጉባኤ 3 ጊዜ ተገልጦላቸዋል:-

1.በዕለተ ትንሳኤ ምሽት በፍርሃት ሳሉ
2.ያላመነ ቶማስን ለማሳመን በተነሳ በ8ኛው ቀን (ማለትም ዛሬ)
3.ከተነሳ ከ23 ቀናት በሁዋላ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻ ላይ ነው::

+ጌታ አርባውን ቀን ለአንዱም: ለሁለቱም በግል ይገለጥላቸው ነበር:: እመቤታችንን ግን ፈጽሞ አይለያትም ነበር::

+ጌታችን ከተነሳ በሁዋላ ለሳምንት ተለይቷቸው ስለ ነበር በቤተ ክርስቲያን ውዳሴ ማርያም እንጂ መልክዐ ኢየሱስ በማሕበር አይደገምም::

+በዚሕች ዕለት ደቀ መዛሙርቱ በጽርሐ ጽዮን ሳሉ ጌታችን "ሰላም ለእናንተ ይሁን" ብሏቸዋል:: ቶማስንም "ና ዳስሰኝ" ብሎታል:: ሐዋርያው እጁን ከተወጋ ጐኑ ላይ ቢያሳርፍ በመቃጠሉ "ጌታየ አምላኬም" ሲል ጮሆ ምስጢረ ተዋሕዶውን መስክሯል::

+ጌታም ቶማስን "እስመ ርኢከኒሁ አመንከኒ" (ማለትም ስላየኸኝ አመንከኝ)! "ብጹዐንሰ እለ እንዘ ኢይሬእዩኒ የአምኑኒ" (ሳያዩ የሚያምኑ ግን ብጹዐን (ማለትም ንዑዳን ክቡራን) ናቸው ብሎታል:: (ዮሐ. 20:24)

=>ከጌታችን ከትንሳኤው: ከቅዱሱም ሐዋርያ በረከት አይለየን::

=>+"+ ደጆች ተዘግተው ሳሉ ኢየሱስ መጣ:: በመካከላቸውም ቆሞ 'ሰላም ለእናንተ ይሁን' አላቸው:: ከዚያም በሁዋላ ቶማስን 'ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ:: እጅህንም አምጣና በጐኔ አግባው:: ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን' አለው:: ቶማስም 'ጌታዬ አምላኬም' ብሎ መለሰለት:: ኢየሱስም 'ስላየኸኝ አምነሃል:: ሳያዩ የሚያምኑ ብጹዓን ናቸው' አለው:: +"+ (ዮሐ. 20:26-29)

   >
✝️✝️✝️Resurrection Week - Pascha Week✝️✝️✝️

+*"❇️Antipascha – Dagem Tensa’e❇️ "*+

=>Glory be to the invocation of His name, the Holy Savior Jesus Christ, after His Holy Resurrection appeared to the disciples in a group setting trice.

1. During the night of the Day of Resurrection while they were frightened
2. To make doubting Thomas believe on the 8th day after His Resurrection (which is today)
3.  And at the shore of the sea of Tiberias 23 days after His Resurrection.

✝️The Lord used to appear only to one or to two of His disciples during the forty days [before His ascent]. Nevertheless, He never left our Lady.

✝️Because our Lord was not with the disciples for a week after He rose, in the Church the doxology dedicated to Jesus is not recited in a congregation but the Theotokion is prayed.

✝️On this day, while the disciples were at the Upper Room/Tsereha Tsion, our Lord said, “Peace be unto you”. He also said to Thomas “Come and touch Me”. And when the Apostle placed his hand on the Lord’s pierced side, because he was burned, Thomas cried out, “My Lord and my God” and attested the mystery of Tewahedo (the mystery of the Hypostatic Union).

✝️And the Lord said to Thomas “be not faithless, but believing!”, “blessed are they that have not seen, and yet have believed.” (John 20:24-29)

=>May our Lord not separate us from the blessings of His Resurrection and the Holy Apostle.

+"+And after eight days again his disciples were within, and Thomas with them: then came Jesus, the doors being shut, and stood in the midst, and said, Peace be unto you. Then saith he to Thomas, Reach hither thy finger, and behold my hands; and reach hither thy hand, and thrust it into my side: and be not faithless, but believing. And Thomas answered and said unto him, My Lord and my God. Jesus saith unto him, Thomas, because thou hast seen me, thou hast believed: blessed are they that have not seen, and yet have believed.+"+
(John 20:26-29)


💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠   
/(ማቴ ፫:፫/)

✝እንኳን አደረሰን!

🛑 ዝክረ ቅዱሳንን ላልደረሳቸው  እናድርስ እናስፋ ስለ ሀገራችን እንጸልይ ንስሐ እንግባ!!🛑

✝ 5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

፩👉ሃይማኖት
፪👉ጾም
፫👉ጸሎት
፬👉ስግደት
፭👉ምጽዋት
፮👉ፍቅር
፯👉ትህትና
፰👉ትዕግስት
፱👉የዋህነት

✝ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )   ንስሐ ግቡ።✝

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn




#Feasts of #Miyazia_19

✞✞✞On this day we commemorate the martyrdom of Saint Simeon the Armenian✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞St. Simeon the Martyr (the Armenian)✞✞✞
=>Though St. Simeon was an Armenian he received martyrdom in the land of Persia (the now Iran). Many martyrs were glorified (as pure offerings to the Lord) in Persia from the 1st century to the rise of Muslims in the 7th century.

✞Many of the martyrs were natives (citizens of Persia) but some were foreigners that came to the country and were martyred.  Persians used to worship the Sun greatly and tortured Christians to worship and bow down to this creature.

✞As St. Simeon was appointed a Bishop of one of the provinces of Persia, he partook of the afflictions as well. In those days, Christianity was not a festivity as it is today hence, St. Simeon (the shepherd) and around 150 of his spiritual children (his flock) endured much for the sake of the love of Christ.

✞And because they were found steadfast in their faith all 151 were sentenced to death and were martyred.

✞✞✞May the God of the martyrs.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 19th of Miyazia
1. St. Simeon the Martyr (Armenian)
2. The 150 Martyrs (The followers of Simeon)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Gabriel the Archangel
2. St. Isidorus (Isidore) the Martyr
3. Abune Abiye Egzi the Righteous
4. Abune Sene Iyesus
5. Abune Yoseph Brihane Alem (Light of the world)

✞✞✞ “For God is not unrighteous to forget your work and labour of love, which ye have shewed toward his name, in that ye have ministered to the saints, and do minister. And we desire that every one of you do shew the same diligence to the full assurance of hope unto the end: That ye be not slothful, but followers of them who through faith and patience inherit the promises.”✞✞✞
Heb. 6:10-13

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)

https://t.me/zikirekdusn




✞✞✞ እንኩዋን ለቅዱስ "ስምዖን ዘአርማንያ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+*" ቅዱስ ስምዖን ሰማዕት "*+

=>ቅዱስ ስምዖን የአርማንያ ሰው ቢሆንም ሰማዕትነትን
የተቀበለው በሃገረ ፋርስ (በአሁኗ ኢራን አካባቢ) ነው::
ፋርስ ከ1ኛው መቶ ክ/ዘ እስከ ተንባላት (መሐመዳውያን)
መነሳት (7ኛው መቶ ክ/ዘ) ድረስ ባለው ጊዜ ብዙ
ሰማዕታት ለክብር በቅተውባታል::

+ብዙዎቹ የዚያው (የፋርስ) ዜጐች ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ
የተሰዉት ከሌላ ሃገር መጥተው ነው:: ፋርሳውያን
አብዝተው ፀሐይን ያመልኩ ነበርና ክርስቲያኖቹን
የሚያሰቃዩት ይህቺውን ፍጡር እያመለኩ እንዲንበረከኩ
ነበር::

+ቅዱስ ስምዖንም ከፋርስ ግዛቶች በአንዱ ኤዺስ
ቆዾስነትን (እረኝነትን) ተሹሞ ነበርና የመከራው ተሳታፊ
ሆኗል:: በጊዜው ክርስትና እንደ ዛሬው "ሠርግና ምላሽ"
አልነበረምና ቅዱስ ስምዖን (እረኛው) እና 150 የሚያህሉ
ልጆቹ (መንጋው) ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብዙ ሆነዋል::

+በእምነታቸው ጸንተው በመገኘታቸውም እንዲገደሉ
ተወስኖባቸው 151ዱም ተሰውተዋል::

=>አምላከ ሰማዕታት በጽናታቸው አጽንቶ ከበረከታቸው
ይክፈለን::

=>ሚያዝያ 19 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ስምዖን ሰማዕት (አርማንያዊ)
2."150" ቅዱሳን ሰማዕታት (የስምዖን ማሕበር)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ኤስድሮስ ሰማዕት
3.አቡነ ዓቢየ እግዚእ ጻድቅ
4.አቡነ ስነ ኢየሱስ
5.አቡነ ዮሴፍ ብርሃነ ዓለም

=>+"+ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ
አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ:
ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ
አይደለምና:: በእምነትና በትእግስትም የተስፋውን ቃል
የሚወርሱትን እንድትመስሉ እንጂ ዳተኞች እንዳትሆኑ
ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን ትጋት እስከ
መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::+"+ (ዕብ. 6:10-13)

>

https://t.me/zikirekdusn


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሚያዝያ ቡሩክ፤ አመ ፲ወ፰፦

✝ተዝካረ ትንሣዔሁ ለመድኀኒነ ክርስቶስ
✝ተዝካረ ርደተ መንፈስ ቅዱስ (ጰራቅሊጦስ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን ፦

✿ቡላ ሰማዕት (ገብሩ ለእግዚአብሔር)
✿አንስት ንጹሐት ዘኢየሩሳሌም (ዘሰበካ ትንሣዔሁ ለመድኀኒነ)
✿አውሳብዮስ ሰማዕት (ገብሩ ለቅዱስ ሱስንዮስ)
✿ጴጥሮስ ሰማዕት ኃያል (እኁሁ ለአባ ብሶይ)
✿ሰማዕታት እለ ተቀትሉ በሃገረ ተርሴስ

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://t.me/zikirekdusn


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish




✝✞✝ እንኩዋን ለእናቶቻችን "ቅዱሳት አንስት" ዓመታዊ የመታሠቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+

+*" ቅዱሳት አንስት "*+

=>ከትንሳኤ ሳምንት ይህች ዕለት "ቅዱሳት አንስት" (የተቀደሱ ሴቶች) ተብላ ትጠራለች::

+በወቅቱ በኢየሩሳሌምና ዙሪያዋ ከተከተሉት ሴቶች ጌታችን 36ቱን መርጧል:: እነዚህ እናቶች ከዋለበት ውለው : ካደረበት አድረው : የቃሉን ትምሕርት ሰምተዋል:: የእጁንም ተአምራት አይተዋል:: ፈጽመውም አገልግለውታል::

+መጽሐፍ "አንስተ ገሊላ ኩሎን::
አዋልዲሃ ለጽዮን::
አስቆቀዋሁ ለመድኅን::
ከመ ዖፈ መንጢጥ እንዘ ይሤጽራ ገጾን::" ይላልና በዕለተ ዐርብ ፊታቸወውን እየነጩ : ደረታቸውን እየደቁ : እንባቸውም እንደ ጐርፍ እየፈሰሰ አብረውት ውለዋል::

+ጌታም ፍጹም ፍቅራቸውን ተመልክቷልና ከሁሉ አስቀድሞ ትንሳኤውን ለእነሱ ገለጠላቸው:: እነርሱም ትንሳኤውን በመፋጠን አብሥረዋል:: "ሰበካ ትንሳኤ፡ አዋልዲሃ ለጽዮን" እንዳለ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ፡፡ በዚህም ምክንያት ይህች ዕለት "ቅዱሳት አንስት" ተብላ ትከበራለች::

=>አምላካችን በፍቅርና በቅድስና ጌጥ ካጌጡ እናቶቻችን በረከትን ያድለን::

=>+"+ መልአኩም መልሶ ሴቶቹን አላቸው:- 'እናንተስ አትፍሩ:: የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና:: እንደተናገረ ተነስቷልና በዚሕ የለም:: የተኛበትን ሥፍራ ኑና እዩ:: ፈጥናችሁም ሒዱና ከሙታን ተነሣ: እነሆም ወደ ገሊላ ይቀድማቹሃል:: በዚያም ታዩታላችሁ ብላችሁ ለደቀ መዛሙርቱ ንገሯቸው' . . . እነሆም ኢየሱስ አገኛቸውና ደስ ይበላችሁ አላቸው:: እነርሱም ቀርበው እግሩን ይዘው ሰገዱለት:: +"+ (ማቴ. 28:5-10)

   >
✝️✝️✝️Resurrection Week - Pascha Week✝️✝️✝️

+*"❇️Resurrection Saturday – Day of Holy Women❇️ "*+

=>From Resurrection Week, this day, Saturday, is named Holy Women.

✝️Our Lord, during the time He ministered, chose 36 women from Jerusalem and the surroundings. And these mothers heard His teachings staying where He did. They saw the miracles made by His hands and served Him completely.
  
✝️As text states,
“All women of Galilee
And the daughters of Zion
Cried for the Savior
Like a swallow bird that grazes its face” they, on Great Friday, scratching their face, beating their chest and their tears falling like a flood spent the day with Him.

✝️And our Lord as He has seen their perfect love, revealed His resurrection before anyone to them. And they announced His resurrection hurriedly as Saint Yared had said, “The daughters of Zion, preached the resurrection.” And for this reason, this day, Resurrection Saturday, is commemorated as Holy Women.

=>May our God grant us from the blessings of our Mothers who are adorned with love and holiness.

+"+And the angel answered and said unto the women, Fear not ye: for I know that ye seek Jesus, which was crucified. He is not here: for he is risen, as he said. Come, see the place where the Lord lay. And go quickly, and tell his disciples that he is risen from the dead; and, behold, he goeth before you into Galilee; there shall ye see him . . . behold, Jesus met them, saying, All hail. And they came and held him by the feet, and worshipped him.+"+
(Matt. 28:5-10)



https://t.me/zikirekdusn


💠"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"💠   
/(ማቴ ፫:፫/)

✝እንኳን አደረሰን!

🛑 ዝክረ ቅዱሳንን ላልደረሳቸው  እናድርስ እናስፋ ስለ ሀገራችን እንጸልይ ንስሐ እንግባ!!🛑

✝ 5 ነገሮችን በደንብ ያዙ።
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

    3,🛑ጥረት

    4 🛑ጥንቃቄ

     5🛑ጽናት
=>እነዚህን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።

❇️9ኙ የቅድስና መንገዶች❇️

፩👉ሃይማኖት
፪👉ጾም
፫👉ጸሎት
፬👉ስግደት
፭👉ምጽዋት
፮👉ፍቅር
፯👉ትህትና
፰👉ትዕግስት
፱👉የዋህነት

✝ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል።
        (ቅዱስ መቃርስ )   ንስሐ ግቡ።✝

ዝክረቅዱሳን (ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት)

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
🛑በዩቲብለመከታተል👉https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

🛑በቴሌግራም👉
https://t.me/zikirekdusn




✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ✞✞✞

✞ አቡነ አቢብ (አባ ቡላ) ✞

✝ ልዩ ስሟ አምዓዳ በምትባል ሀገር በሉፊ አውራጃ በሮም አገር አንድ ጽኑ ክርስቲያን ነበር፡፡

✝ ይህ ክርስቲያን ስሙ አብርሃም ይሰኛል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከአንዱ አገር ወደ ሌላ አገር ሲሰደድ የኖረ እግዚአብሔርን የሚፈራ ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ ለነዳይና ለምስኪን ባልቴቶች እናት አባት ለሞቱባቸዉ ልጆች ምጽዋትን የሚሰጥ ነበር፡፡

✝ እንዲሁም እንደርሱ ደግ የሆነች ስሟ ሐሪክ የምትባል ደግ ሚስት ነበረችው የስሟ ትርጉምም  በክርስቶስ የታመነች ማለት ነው፡፡ 

✝ እነዚህ ሁለት ደግ ክርስቲያኖች ታዲያ ልጅ አልነበራቸውም ነገር ግን
ልጅ ባይኖራቸውም እለት እለት እግዚአብሔርን ከማመስገን በቀር አማረው አያውቁም ነገር ግን ለቤተ እግዚአብሔር  አገልጋይ የሚሆን አንድ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ በአንቃዕድዎ ወደ እግዚአብሔር ይለምኑ ነበር፡፡

✝ አንድ ቀን መልዐከ እግዚአብሔር ለዚህ   ደግ ሰው ተገልፆ ይኽ ፍሬ የአንተ ነው እርሱም ወደ እኔ የሚቀርብ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ፈቃዱንም የሚፈፅም ያማረ መባዕ ነው ብሎ እጅግ መልካም ፍሬን በእጁ ሰጠው፡፡

✝ ይኽ ደግ ሰው አብርሃምም ከእንቅልፉ ተነስቶ ይህንን  በህልሙ የሰማውንና የአየውን ነገር ኹሉ ለሚስቱ ሐሪክ ነገራት እርሷም ታላቅ ደስታ ተደሰተች ልዑል እግዚአብሔርን በአንድነት አመሰገኑ፡፡ሚስቱ ሐሪክም ፀነሰች፡፡

✝ ይኽቺ ሚስቱ ሐሪክ በፀነሰች ጊዜም በቤታቸው መካከል ሁለንተናው መልካምና ታላቅ ዛፍ በቀለ በቅጠሉ ላይ በዕብራይስጥ ቋንቋ የተጻፈ ጽሕፈትን አዩ ጽሕፈቱም በጽዮን አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ቅዱስ የእግዚአብሔር አገልጋይ ቡላ የሚል ነው፡፡

✝ ከዚህም በኀላ ሐሪክ መልከ መልካምና ከብርሃናት ይልቅ ፊቱ የሚያበራ ወንድ ልጅን ወለዱ፡፡እናቱና አባቱ ይህንን በአዩ ጊዜ ታላቅ ደስታ ተደስተው ለነዳያን ምጽዋትን ለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን በወርቅና በብር ያጌጡ የነዋየ ቅድሳት አልባሳትን ሰጡ ስሙንም ቡላ ብለው ሰየሙት፡፡ትርጓሜውም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው፡፡

✝ እናትና አባቱም በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት አሥር አመት በሆነው ጊዜም በመጀመሪያ አባቱ አብርሃም አረፈ ከትንሽ ቀናት በኀላ እናቱ ሐሪክ አረፈች፡፡

✝ በዚያን ዘመን ታዲያ ንጉሡ ቤተ ክርስቲያንን እንዲዘጉ እና ቤተ ጣዖት እንዲከፍቱ ክርስቲያን ሁላቸው የምስጋና ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን (ሎቱ ስብሐት) እንዲክዱ የሚል ወደዚያች አገር ደረሰ፡፡

✝ ይህ የተባረከ ብላቴና ቡላም ይህንን በሰማ ደጋጎች ክርስቲያንም ሲሰቃዩ ባየ ጊዜ ስለ ክርስቶስ በሰማዕትነት ይሞት ዘንድ ጨክኖ ሕዝብን ሰማዕትነት ለመቀበል በወዲህም በወዲያም ያሉትን ሕዝቡን እየገፋ ሄዶ ንጉሥ አቅሮጵስ ካለበት ቀርቦ ያፈርክና የተዋረድክ የረከስክ የጽድቅ ሁሉ ጠላት የዲያቢሎስ መልእክተኛ አንተና ንጉስክ የተነቀፋችሁ የምታመልኳቸው ጣዖታትም የተዋረዱና በምድር የረከሱ ናቸው አለው፡፡

✝ ንጉሡም ሰምቶ ይህንን ወጣቱ ቡላን አስረው ከፊቱ ያቆሙት ዘንድ አዝዞ ተመልከቱ የእሊክ ክርስቲያን ልቦናቸው የጸና ነው ትንሽ ብላቴና ሆኖ ሳለ ምንም አልፈራም ይልቁኑም እንድቀጣው ይቃወመኛል እንጂ አለ፡፡

✝ ይህንንም ብሎ በሚቆራርጥ ብረት ሠንሰለት አሰሩት ጀርባውን በአለንጋ እንዲገርፉት ሰውነቱም እየለያዩ እየቆራረጡ የውስጥ አንጀቱን በተቆለፈ ብረትና በስለታማ መጋዝ እጆቹንና እግሮቹን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡

✝ በእንዲህ ባለ መከራ ቢያሰቃዩትም ተመልሶ በእግሩ ይቆማል እንጂ አልሞተም ንጉሡ እሊህ ክርስቲያን መተታቸውን ተመልከቱ አለ፡፡

✝ እንዲሁም አባ ቡላ በአሥራ አምስት አመቱ ከሌላ ንጉሥ ጋር እንደ ቀድሞ ለረከሱ ጣዖቶች አልሰግድም በማለቱ ብዙ ስቃይ አሰቃየው በመጨረሻም አንገቱን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ብጹዕ ጻድቅ ቡላም ራሱን ከመቁረጣቸው አስቀድሞ ከመዝሙረ ዳዊት ሳምኬት ዐማፅያንን ጠልቼ ሕግህን ተከተልኩ ረዳቴና መጠጊያዬ አንተ ነህ በቃልህም አመንኩ የአምላኬን ትዕዛዝ እፈፅም ዘንድ  ዐማፅያን ከእኔ ራቁ በሕይወት እኖር ዘንድ እንደ ቃልህ ተቀበለኝ ተስፋዬንም አታስቀርብኝ ርዳኝ አድነኝ ሁል ጊዜ ሕግህን እናገራለሁ ከትእዛዝህ የሚርቁ ሁሉ ምኞታቸው አመፃ ነውና አዋረድኻቸው እሊኽ በምድር ያሉ ኃጥአን ከዳተኞች ናቸው፡፡ ስለዚህም አምልኮተ ሕግህን ወደድኹ፡፡ከሕግህ የተነሣ ፈርቻለሁና በአንተ መታመንን ከሰውነቴ ጋራ አስማማ፡፡ የሚለውን ጸሎት ጸለየ፡፡

✝ የእግዚአብሔር አገልጋይ ቡላም በዚህች ቀን በሚያዝያ 18 አንገቱን ተቆረጠ በዚህን ጊዜ መልአከ እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ወርዶ ራሱን ወስዶ ከሥጋው ቢያገናኘው እንደነበረ ሆኖ ተነሣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም አይዞህ አትፍራ እመን ጽና እግዚአብሔር ይረዳሃል ፡፡በሃገሪቱ ዳረቻ ወደ አለዉ ገዳም ሂድ እኔ የምሰጥህ በእጄ ያለች ልብስህ ሁል ጊዜ ይህች ናት ጌታችን ከወዳጆቹ ቅዱሳን መነኮሳት ጋራ ተሳታፊ እንድትሆን አዝዞኻል ብሎ የብርሃን መስቀል ምልክት ያላት አስኬማንም ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ተሰወረ፡፡

✝ ጻድቁ አባታችን አቡነ አቢብ(ቡላ) ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ መፍቅሬ ሰብእ (ሰውን ወዳጅ) አምላካቸውን አርአያ ያደረጉ ለሰው ያላቸውን ፍቅር አድንቆ ከማዕድ በኀላ ስብሐት ተብሎ የተረፈውን በእንተ አቡነ አቢብ ብሎ ሦስት ጊዜ የተመገበውን ሰው ሁሉ እስከ አሥር ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡

✝ የንዑድ ክቡር ጻድቁ አባታችን አቡነ አቢብ (ቡላ) ጸሎታቸዉና በረከታቸው ከእኛ ጋር ይኹን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ✞

(በዮሐንስ ዘሐረር - ዝክረ ቅዱሳን)

ምንጭ፡ ገድለ አቡነ አቢብ

https://t.me/zikirekdusn




#Feasts of #Miyazia_18

✞✞✞On this day we commemorate the departure of the Righteous Martyr Abba Peter✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Righteous Martyr Abba Peter✞✞✞

=>Martyrdom is the highest price a Christian pays for his/her faith. A person can subdue his body in the service of God or give away his wealth and property. However, the greatest gift is offering oneself. 

✞Giving oneself is possible in matrimony or asceticism. Nonetheless, its peak is martyrdom. As Saint Ephraim the Syrian said, “…the martyrs rejected the desire of this world, and poured out their blood for God, and have endured bitter death[s] for the sake of the kingdom of heaven”, martyrdom means enduring unpleasant death for the love of God. [Theotokion of Thursday]

✞Did not our Redeemer, Christ, while being the Lord of heaven and earth endure the humiliation of the Cross and die for us! Many religions in the world speak about killing directly or indirectly. But Christianity does not have a rule that puts forward or indicates killing [others as an option].

✞That is because He Himself told us, “Love your enemies, bless them that curse you, do good to them that hate you, and pray for them which despitefully use you, and persecute you” (Matthew 5:44). But if we do not nourish ourselves with faith and virtues daily, Christianity is not a belief where one becomes perfect in a day hence there might come failures in trials.

✞Particularly, we the Christian youths of today should give due attention, since the chronicles of the youth martyrs of the past are articulated to us in order that we steadfast. 

[Let’s see the account of Abba Peter in short for today.]

✞Abba Peter was one of the fruits of the Era of Persecution. In those days of tribulation (the 3rd century), because Egypt and Syria were in much adversity, many saints were martyred.  Particularly in Egypt, many pure fathers and holy mothers, enduring the afflictions, were glorified [in martyrdom].

✞And one of them was Abba Peter who learned the tang of Christianity while he was a child from his caretaker (his aunt).  He had a brother and a friend that he loved dearly. And his name was called Abba Bishoy. Both after being raised ethically, despised the world, entered the desert and lived for many years devoted to prayer and fasting. 

✞And during the Era of Persecution, they were accused and imprisoned for just worshipping Christ. They were lashed and were beaten. They have also endured in patience excruciating pains.  In the end, Abba Peter was martyred on this day and was glorified. And his friend and brother Abba Bishoy honorably shrouded and buried him. 

✞✞✞May the God of the martyrs let us partake from their diligent strife, their much longsuffering, and their perfect blessing.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 18th of Miyazia
1. St. Eusebius (St. Arsenius) the Martyr (Slave of St. Sousnyous)
2. St. Peter the Martyr
3. Martyrs of Tarsus

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. Philip the Apostle
2. Abune Ewostatewos/Eustathius/Eustathios, preacher of faith
3. Abune Anorios/ Honorius of Debre Tsegaga
4. Mar James of Egypt

✞✞✞ “I am more; in labours more abundant, in stripes above measure, in prisons more frequent, in deaths oft . . . In weariness and painfulness, in watchings often, in hunger and thirst, in fastings often, in cold and nakedness. Beside those things that are without, that which cometh upon me daily, the care of all the churches.”✞✞✞
2 Cor. 11:23-28

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)

https://t.me/zikirekdusn




✞✝✞ ሚያዝያ 18 ✞✝✞

✞✝✞ እንኩዋን ለጻድቅና ሰማዕት "አባ ዼጥሮስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✝✞

*+" ጻድቅና ሰማዕት አባ ዼጥሮስ "+*

=>ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል
የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው
ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል::
ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት
ነው::

+ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል::
የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ
ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ
መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ
እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::

+እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ
ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ
ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ
ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን
የሚመለከት ሕግ የለውም::

+እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን
መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: (ማቴ.
5:44) ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና
በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም
የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ
ይመጣል::

+በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል
ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን
እንድንጸና ነውና::

❖ቅዱስ አባ ጴጥሮስም ከዘመነ ሰማዕታት ፍሬዎች አንዱ
ነው፡፡ በዚያ የመከራ ዘመን (3ኛው መቶ ክ/ዘ) ግብፅና
ሶርያ በብዙ መከራ ውስጥ ሳሉ በርካታ ቅዱሳን
ተሰውተዋል፡፡ በተለይ በግብፅ ደግሞ ብዙ ንጹሐን አበውና
ቅዱሳት አንስት መከራውን ታግሠው ለክብር በቅተዋል፡፡

❖ከእነዚሁ አንዱ የሆነው አባ ጴጥሮስ ገና ከልጅነቱ
ጣዕመ ክርስትናን የተማረው ከአሳዳጊው (ከአክስቱ)
ነበር፡፡ በፍፁም ልቡ የሚወደው ወንድም እና ባልንጀራም
ነበረው፡፡ ስሙ ደግሞ አባ ብሶይ ይሰኛል፡፡ ሁለቱም በበጎ
ምግባር ተኮትኩተው ፡ ዓለምንም ንቀው በርሃ ገብተው ፡
በጾም በጸሎት ተወስነው ብዙጊዜ ኑረዋል፡፡

❖በመከራው ዘመን ደግሞ ክርስቶስን ስላመለኩ ብቻ
ተከሰው ታስረዋል፡፡ ተገርፈው ተደብድበዋል፡፡ ጭንቅ
ስቃይንም በትእግስት አሳልፈዋል፡፡ በፍጻሜውም አባ
ጴጥሮስ በዚህች ቀን ተሰውቶ ለክብር አክሊል በቅቷል፡፡
ወዳጁና ወንድሙ ቅዱስ ብሶይም በክብር ገንዞ
ቀብሮታል፡፡

=>አምላከ ሰማዕታት ከጸናች ገድላቸው ፡ ከበዛች
ትእግስታቸው ፡ ከፍጹም በረከታቸው ያሳትፈን፡፡

=>ሚያዝያ 18 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ አውሳብዮስ ሰማዕት
2.አባ ዼጥሮስ ሰማዕት
3.ሰማዕታተ ጠርሴስ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ
2.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ሰባኬ ሃይማኖት (ረባን)
3.አቡነ አኖሬዎስ ዘደብረ ጽጋጋ
4.ማር ያዕቆብ ግብፃዊ

=>+"+ በድካም: አብዝቼ በመገረፍ: አብዝቼ በመታሠር:
አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት:
ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት: በራብና በጥም: ብዙ
ጊዜም በመጦም: በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . .
የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ
የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው:: +"+ (2ቆሮ
11:23)

>

https://t.me/zikirekdusn

19 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.